cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

TIKVAH-MAGAZINE

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። #ኢትዮጵያ ያግኙን +251913134524

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
196 369
Suscriptores
-2824 horas
+867 días
+1 49230 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ለጅማ ዩኒቨርስቲ እና በከተማዋ ለሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 22 ሺ መፅሃፍት ተበረከተ ተስፋ ለጅማ እና ሪቦ ፋውንዴሽን የተሰኙ ማህበራት ከ ስልሳ ሚሊዮን (60,000,000) ብር በላይ የሚገመቱ 22,000 መፅሃፍቶችን በስጦታት ማበርከታቸውን የጅማ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል። ማህበራቱ ይህንን ያደረጉት ከተለያዩ አውሮፓ ከሚኖሩ የጅማ እና አካባቢዋ ተወላጆች እና የዲያስፖራ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ሲሆን የጅማ ዩንቨርስቲ ከፍተኛ ማናጅመንት አባላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ሌሎች በተገኙበት ርክክቡ ተደርጓል። @TikvahethMagazine
Mostrar todo...
9👏 2
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11:30 አከባቢ በደረሰው በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አሳውቋል። አደጋው የተከሰተው ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ ነው። በአደጋውም በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ 4 ሰዎች ህይወት አልፏል። በ 2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ተገልጿል። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ስለመሆኑም ተጠቁሟል። @TikvahethMagazine
Mostrar todo...
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን ሥራ የማስኬድ ኃላፊነት ተቀበለ። በገበታ ለሀገር የተገነቡ ሎጆችን ስራ የማስኬድ ተግባርን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስካይ ላይት ሆቴል ተቋሙ በኩል እንዲወጣ የስምምነት ፊርማ ሥነሥርዓት ተካሂዷል። ስምምነቱ በቅርቡ የተመረቁትን ሃላላ ኬላ ሎጅ፣ ጨበራ ጩርጩራ የዝሆን ዳና ሎጅ እና ወንጪ ኢኮ ሎጅ እንዲሁም በመጠናቀቅ ላይ ያለውን የጎርጎራ ፕሮጀክትንም ያካትታል። "ቀጣይ የስራ ማስኬድ እና ማስተዳደር ተግባሩ ለብሔራዊ ሰንደቅ ተሸካሚው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሃላፊነት መሰጠቱም የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ከማስቻሉም ባለፈ ለአለምአቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነት ትውውቅ ከፍ ያለ ዕድል ይፈጥራል።" ሲል የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስታውቋል።
Mostrar todo...
53🤔 19👏 11😡 6
#MOR ° ባለፉት ዘጠኛ ወራት 374.20 ቢሊዮን ብር ገቢ ተሰብስቧል። ° 23ሺ ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴ ክፍያ መፈጸም ችለዋል። የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት 9 ወራት 374.20 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን የሚኒስቴር መ/ቤቱ ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የ9 ወራት ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት ገልፀዋል። መስሪያ ቤቱ 391.34 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ሲሆን፤ የዕቅዱን 95.62 በመቶ ማሳካት እንደቻለ ገልጿል። ከነዚህ ውስጥ 23,071 ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ዘዴ ክፍያ መፈጸም መቻላቸውም ተገልጿል። የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በቅንጅት በመስራት ባለፉት 9 ወራት የቴሌ ብር ሥርዓትን ለቀረጥና ታክስ አሰባሰቡ በሥራ ላይ ማዋል በመቻሉ 7,130 ግብር ከፋዮች በቴሌ ብር በኩል ክፍያቸውን እንደፈፀሙ ተነግሯል። በተያየዘ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ዘዴን ለማሳለጥ የታቀፉ የንግድ ባንኮች ቁጥር 21 እንዲደርስ የተደረገ መሆኑን ሲጠቆም የተቀሩት ባንኮችንም ወደ ሥርዓቱ ለማስገባት ሥራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። @TikvahethMagazine
Mostrar todo...
👏 9😡 4🤔 2
እንኳን አደረሳችሁ! ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ! ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን! ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764 ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore 😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://t.me/bluebellgiftstore/627
Mostrar todo...
3
ልጆች 13 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን ባይጠቀሙ ሲል በፈረንሳይ የተሰራ ጥናት አመለከተ። በተለያየ የእድሜ ደረጃ ላይ ያሉ ህፃናት እና ታዳጊዎች ስማርት ስልኮችን በመጠቀም የተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን ሲጠቀሙ አለፍ ሊልም በነዚህ የትስስር ገጾች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ይስተዋላል። የስማርት ስልክ አጠቃቀም ጥንቃቄ የሚያስፈልገው እንደሆነ ቢነገርም ሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ ስማርት ስልኮች ላይ የሚገኙት የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህፃናትና ታዳጊዎችን ለሱስ ከመዳረግ ባለፈ በልጆች ላይ ስነልቦናዊ ጉዳት እያስከተለ ስለመሆኑ ይነገራል። ጉዳዩን አስመልክቶ በፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ሀሳብ አመንጪነት ታዳጊ ልጆችን ከአደጋ ለመጠበቅ ኒውሮሎጂስት እና የዘርፉ ባለሙያዎች የስልክ ስክሪን አጠቃቀም መመሪያዎችን ለመንግስት እንዲጠቁሙ  በማሰብ 3 ወራትን የፈጀ ጥናት ተሰርቷል። በጥናቱም ልጆች 13 አመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን እንዲጠቀሙ መፈቀድ እንደሌለበትና እንደ #ቲክቶክ፣ #ኢንስታግራም እና #ስናፕቻት የመሳሰሉ ማህበራዊ ሚዲያዎችን እስከ 18 አመት ድረስ መጠቀም እንደሌለባቸው ጥናቱ አመልክቷል። ጥናቱም ከ3 አመት በታች ያሉ ህጻናት የቴሌቪዥን ስክሪኖች ጨምሮ ለስልኮች ተጋላጭ መሆን እንደሌለባቸው የጠቆመ ሲሆን አንድ ህፃን 11 ዓመት ሳይሞላው ስልክ ሊኖረው እንደማይገባና ይህ ካልሆነ ህፃናት በልጅነታቸው ስሜታቸውን ከመግለፅ እና ነገሮችን ከመረዳት አኳያ ሊያዳብሯቸው የሚገባቸውን ችሎታዎች ሊጎዳ እንደሚችል ተገልጿል። የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በጥር ወር ህፃናትን ላይ ጉዳት እየዳረገ ስለሚገኘው የስማርት ስልክ እንዲሁም የስክሪን አጠቃቀም " እገዳዎች ወይም ገደቦች " ሊኖሩ ይችላሉ ማለታቸውም ነው የተነገረው። ይህ ጥናት በኢትዮጵያ ካለው የህፃናትና ታዳጊዎች ስማርት ስልክ አጠቀም አንፃር እንዴት ይታያል?
Mostrar todo...
👏 141 26🕊 11😨 7🤔 6😡 1
"የዓለም ባንክ የአፍሪካ ሀገራትን መዋቅራዊ ችግሮች ከመደገፍ ለሴሚናር ገንዘብ ማውጣት ይቀለዋል" የዩጋንዳው ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዩጋንዳው ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዓለም ባንክ ድሃ የአፍሪካ ሀገራት ለዕድገታቸው እንቅፋት የሆኑ የእርሻ፣ ትራንስፖርትና መሰል መዋቅራዊ ችግሮችን እንዲፈቱ ብድር ከመስጠት ይልቅ ለሚዘጋጁት ‘ሴሚናሮች’ ብድር ቅድሚያ ይሰጣል ሲሉ ወቀሳ ሰነዘሩ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት በኬኔያ በተካሄደው የአለም አቀፍ ልማት ማህበር የአፍሪካ ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ነው። " አለም ባንክ ሰዎች ተቀምጠው ለሚመገቡት ሴሚናሮች  ብድር ለመስጠት ፈጣን ናቸው። ነው ነገር ግን የመስኖ እና የመሠረተ ልማት ልማትን አይደግፉም " ሲሉ ወቅሰዋል። ፕሬዝዳንቱ አፍሪካ ዘላቂ ልማት (Sustainable underdevelopment) አያስፈልጋትም አፍሪካ የምትፈልገው ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ (Socio-Economic Transformation) ነው ያሉ ሲሆን ዘላቂ ልማትን የሚባለውን ፅንሰ ሀሳብ እድገት የሌለው ሲሉ ገልጸውታል። "አንድ ሴት በዚህ ዓመት ካረገዘች በሚቀጥሉት ሦስት እና አራት ዓመታት እርጉዝ አትሆንም፥ ይህ ፈጽሞ አይፈጠርም ተፈጥሯዊው እድገት ለወራት ታረግዛለች ልጁ ያድጋል፤ ይወለዳል፤ ይጎለምሳል። የሆነ ምዕራፍ ላይ እርግዝናው (Quantitative) ወደ ልጅነት ይቀየራል (Qualitative) እነዚህን ቃላት በዶክመንታችሁ አስተካክሏቸው።" ሲሉ ገልጸዋል። ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ አክለውም፥ አፍሪቃ የጥሬ ዕቃዎቿን ወደ ውጭ መላክ እንድታቆም የጠየቁ ሲሆን ጥሬ እቃ ላይ እሴት ሳይጨመር መላክ በአፍሪካዊያን ሀብት ሌሎችን ማበልጸግ እንደሆነ የቡና እና የማዕድን ሀብትን በምሳሌ አንስተው አስረድተዋል። "ኡጋንዳ ሀብታም ሀገር ብትሆንም አብዛኞቹ ዜጎቿ ለዕለት ጉርስ እንጂ ለኪስ የሚሆን ገንዘብ ከሚያገኙበትን ሥርዓት ( Money Economy) ውጪ ናቸው። ይህንን ለመቅረፍ ገንዘብ የሚሰጠኝ የለም ምክንያቱም ሁሉም ገንዘብ ለአቅም ማጎልበቻ (Capacity Building ) ነው። እኛ ግን በራሳችን ፈንድ እየሰራን ነው" ሲሉ ተናግረዋል። በአፍሪካ የግሉ ዘርፍ እየተደገፈ ባለመሆኑ እድገት እየተመዘገበ እንዳልሆነ የገለፁት ሙሴቬኒ የግሉ ዘርፍ እንዲበረታታ በቅድሚያ በአነስተኛ ዋጋ ማምረት መቻል ለዚህም ደግሞ  የመንገድ የኤሌክትሪክ ሀይል ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅሰው የዓለም ባንክ ለእነዚህ ነገሮች ፈንድ ያደረገበትን ኦዲት ያድርግ ሲሉ ጠቅሰዋል። (📹 28 MB)
Mostrar todo...
👏 224 23😨 4😡 4🕊 2
እንኳን አደረሳችሁ! ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ! ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን! ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764 ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore 😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://t.me/bluebellgiftstore/627
Mostrar todo...
4😡 1
ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ ነው ተባለ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከዚህ ቀደም ታጥቀው ይንቀሳቀሱ የነበሩና ሌሎች ወጣቶች በ2 ማኅበር ተደራጅተው በጀመሩት የዓሳ ማስገር ስራ ከህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ መሆኑ ተገለፀ። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሐይቅ ግድቡ ውሀ መያዝ ከጀመረ ወዲህ በተለይም ለዓሳ ምርት ምቹ መሆኑ ሲገር በ8 ወራት ውስጥ 1729 ቶን ዓሳ ምርት ከህዳሴ ግድብ መገኘቱን ዶይቼ ቨለ በዘገባው አመልክቷል። ወጣቶቹ የተደራጁበት ማህበርም 56 የሚደርሱ ወጣቶችን ያቀፈ ሲሆን በግደቡ ዳርቻ በሚሰሩት የዓሳ ማስገር ስራ በቀን ከ2 እስከ 3 ኩንታል ዓሳ እንደሚኝና በአካባቢው የዓሳ ማስገር ስራውን በማህበሰረብ አቀም ለማድረግና ለማሻሻል ዘመናዊ ጅልባዎች ያስፈልጋሉ ተብሏል።
Mostrar todo...
👏 272🤔 40 34🕊 12😡 6😢 1
#CholeraUpdate በኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የኮሌራ ታማሚዎች ቁጥር እንደተመዘገበ ተነገረ በአፍሪካ ባለፈው መጋቢት ወር በኮሌራ በሽታ ከተያዙ 14,441 አዲስ የኮሌራ ታማሚዎች መሃከል ከአህጉሪቱ ከፍተኛ ታማሚዎች የተመዘገቡባት ኢትዮጵያ መሆኗን የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመልክቷል። በተጠቀሰው ወር በኢትዮጵያ 4009 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው ተነግሯል። በኮሌራ ከተያዙት ሰዎች ውስጥም 24 ሰዎች መሞታቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ባለፉት 3 ወራት 9,429 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 111 ሰዎች መሞታቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል። በአፍሪካ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2023 እስከ ማርች 31 ቀን 2024 በጠቅላላው በ18 ሀገራት 271,119 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ሲያዙ በተጠቀሰው ጊዜ በኢትዮጵያ 39,892 ሰዎች በበሽታው ተይዘው 524 ሰዎች መሞታቸውም ነው የተገለፀው።
Mostrar todo...
😢 24 5🤔 1