FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
Channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 469 subscribers, ranking 6 068 in the News & Media category and 768 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 469 subscribers.
According to the latest data from 12 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 70 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 11.40%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.29% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 4 840 views. Within the first day, a publication typically gains 3 520 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 36.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 13 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 12 July | +12 | |||
| 11 July | +8 | |||
| 10 July | +10 | |||
| 09 July | +10 | |||
| 08 July | +9 | |||
| 07 July | +14 | |||
| 06 July | +12 | |||
| 05 July | +19 | |||
| 04 July | +18 | |||
| 03 July | +19 | |||
| 02 July | +21 | |||
| 01 July | +6 |
| 2 | No text... | 2 111 |
| 3 | የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አስከብሮ ለማስቀጠል ሀገራዊ ኢኮኖሚን እና ወታደራዊ አቅምን ማጠናከር ያስፈልጋል፦
አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ አቶ ጌታቸው ኃይለማሪያም ኢንዱስትሪው ከተቋሙ በተሰጠው የተልዕኮ አቅጣጫ መሰረት የሰራዊታችንን የማድረግ አቅም ለማጠናከር ወታደራዊ ትጥቆችን በማምረት በማደሥና በማዘመን ሀገር የሚያኮራ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የአለም የፍትህ ሚዛን በጉልበተኞች እጅ በወደቀበት ሰዓት ወታደራዊ አቅምን ማሳደግ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አሥፈፃሚው ለዚህ ይረዳ ዘንድ ኢንዱስትሪው ዘመኑን የሚመጥኑ የተለያዩ ወታደራዊ ትጥቆችን እየመረተ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በበጀት ዓመቱ ለሰው ሀይል የአቅም ግንባታ ስራ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱ አሁን ለተገኘው ሁሉን አቀፍ ውጤት አሥተዋፅኦው ከፍ እንዲል ያሥቻለ መሆኑ እና ከነባር የማምረቻ ፋሲሊቲዎች በተጨማሪ አዳዲስ የወታደራዊ ትጥቆች ማምረቻ ግንባታዎች በትኩረት የተሰሩበት ዓመት እንደነበር በሪፖርቱ ተመላክቷል።
ይህ ሥኬትም ዘመኑን የዋጁ የጦር መሳሪያዎችን እንድናመርት ከማድረጉ ባሻገር ጦርነትን በሩቁ ለማስቀረትና ጠላቶቻችን ቆም ብለው እንዲያሰቡ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል።
የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ውጤታማነትና ጥንካሬ የሚለካው ከመንግሰት በሚያገኘው በጀት ብቻ ሳይሆን የራሱን የገቢ አማራጮች በማፈላለግ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረትም ነው። በዚህም ከአፍሪካ ሀገሮች ጋር ውል በመፈፀም ወታደራዊ ትጥቆቻቸውን በመጠገንና አምርቶ በመሸጥ ገቢን ማሣደግ ተችሏል።
አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም ግሩፑ እያሥመዘገበ ላለው ውጤት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አብይ አህመድና የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ሚናቸው የጎላ እንደነበር አንስተዋል።
የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ግሩፕ ምክትል ስራ አስፈፃሚና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ብርጋዲየር ጀነራል ዮሃንስ ትኬሳ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ዋናውን ተልዕኮ ከመወጣት ባሻገር ለተለያዬ አገልግሎት የሚውሉ የኮሜርሻል ምርቶች ማለትም የህዝብ መጓጓዣ አውቶብሶችን ፣ የተለያዬ ሞዴል ያላቸው መኪናዎችን በማምረት ገቢውን እያሳደገ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
በአጠቃላይ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ወታደራዊ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬን ገቢ በማስገኘት ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ደጋፊ መሆን እንደቻለም ብርጋዲየር ጄኔራል ዮሃንስ ትኬሳ ገልፀዋል።
በዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ውይይት ላይ የተሳተፉት አመራሮች በበኩላቸው በተገኘው ውጤት ደስ መሰኘታቸውን ገልፀው በቀጣይ የስራ ዘመን የግሩፑን ፍላጎት ለማርካትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ፈጠራና የቴክኖሎጅ ዝማኔ ላይ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ብለዋል። በመጨረሻም በ2019 በጀት ዓመት የሥራ እቅድ ላይ ወይይት ተደርጎ የአፈፃፀም አቅጣጫ ተቀምጧል።
ዘጋቢ ማሩ ግርማይ
ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 064 |
| 4 | የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 1 |
| 5 | No text... | 2 507 |
| 6 | ፅንፈኛው ካምፕ አድርጎት የነበረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
የፅንፈኛው ቡድን ማረፊያ ካምፕ አድርጎት የነበረውን የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሐይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ከጠላት በማፅዳት ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ሜጄር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ገልፀዋል።
አውሮፕላን ማረፊያው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድን (ዶክተር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
ከ30 ዓመታት በፊት ተቋርጦ የነበረው አውሮፕላን ማረፊያው በዘመናዊ መልክ ግንባታው ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም ባለፉት አራት ዓመታት በፀጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ ቆይቷል። ነገር ግን መከላከያ ሠራዊቱ የልማት አደናቃፊ የሆነውን ፅንፈኛ ቡድን በማፅዳት አካባቢውን ሠላም በማድረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ የአውሮፕላን ማረፊያ እውን እንዲሆን ሠራዊቱ ታላቅ መስዋዕትነት የከፈለበት ነው ያሉት የ6ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ቦታው ከዓመታት በፊት ጠላት ማረፊያ ካምፑ አድርጎት እንነደነበረና ቦታውን ሠራዊቱ ተዋግቶ ያፀዳበት ሁኔታ እንዳለ አሥረድተዋል።
6ኛ ዕዝ ተሠማርቶ በሚገኝበት ቀጠና ሁሉ የተላላኪዎችን የሽብር ተልዕኮ መና እያደረገ ሕብረተሰቡ በሠላም ወጥቶ እንዲገባ እየሠራ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ ልማት ጠል የሆነው ፅንፈኛው ቡድን መሠረተ ልማቶች እንዳይለሙ ሙኩራ ቢያደርግም የሕዝብ ልጅ የሆነው መከላከያ ግን ልማት እንዲቀጥል ማድረጉን ተናግረዋል።
ዕዙ በምሥራቅ ጎጃምና አካባቢው ከተሠማራ ወዲህ የጥፋት ቡድኑ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሆን የከፈተውን ውጊያ ማምከን የቻለ ሲሆን የጠላት ምኞትም ህልም ሆኖ መቅረቱን ገልፀዋል።
ሠራዊቱ ባይኖር ኖር ደብረ ማርቆስና አካባቢው የሠላምን አየር አይተነፍሱም ነበር ያሉት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ መከላከያ ባስገኘልን ሠላም ፊታችንን ወደ ልማት አዙረናል ብለዋል።
ሕብረተሰቡም ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የአየር ትራንስፖርት እውን ሆኖ በማየቱ ደስታውን የገለፀ ሲሆን ለዚህ ስኬትና ሠላም መረጋገጥ ትልቁን ድርሻ ለተወጣው መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
ዘጋቢ ውብሸት አንበሴ
ፎቶግራፍ ገነት አወቀ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 628 |
| 7 | No text... | 2 450 |
| 8 | የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ የውጊያ ድጋፍ ሙያ የሠለጠኑ ሙያተኞችን አሥመረቀ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ ሙያ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመርቋል፡፡
በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሜካናይዝድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ከፍያለው አምዴ የዕዙን ሠራዊት ለማዘመን ከተለመደው አሰራር ለመውጣት ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች መጠቀም እና ዕቅድ በመንደፍ ዝግጁነትን የማጠናከር ሥራ እየተሠራ ነው።
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክና ሥርዓተ መንግስት ያላት፣ ነፃነቷንና ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የኖረች ሀገር መሆኗን የጠቀሱት አዛዡ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያ በራሷ በተፈጥሮ ሀብቷ ሰርታ እዳትለወጥ ያለ እረፍት ቢሰሩም ሴራቸውን ለማክሸፍ ዝግጁነታችን ከምንጊዜም በላይ አጠናክረን እንቀጥላለንም ብለዋል፡፡
ጀግኖች አባቶቻችን በመሥዋዕትነት ያፀኗትን እና ከነ ሙሉ ክብሯ ያስረከቡንን ታላቅ ሀገር ለትውልድ ጠብቃችሁ በክብር ማሻገር ይጠበቅባችኋል ሲሉ ለተመራቂዎች አሥገንዝበዋል።
የማሰልጠኛ ማዕከሉ አዛዥ ኮሎኔል አየለ ወልደ ጊዮርጊስ በበኩላቸው ዕዙ እንደ ዕዝ ራሱን ካደራጀ ማግስት ጀምሮ ሀገርና ህዝብን በሚመጥን መልኩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ብቃት ሊፈፅም የሚችል የሀገር ኩራት የሆነ የሜካናይዝድ ድጋፍ ሰጪ ሙያተኛ እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 518 |
| 9 | No text... | 2 392 |
| 10 | No text... | 1 |
| 11 | ሠላም አስከባሪ ሻለቃው የደቡብ ሡዳን አስራ አምስተኛ አመት የነፃነት ቀንን አከበረ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
በዌስተርን ኢኳቶርያ ያምቢዮ ካምፕ በተከበረው የደቡብ ሱዳን አሥራ አምስተኛ ዓመት ክብረ በዓል አከባበር የተገኙት የካምፑ ፊልድ ኦፊሰር ቡዱን መሪ ሚስተር ጆዎፌሪ የደቡብ ሡዳን ሠላም ለማፅናት በቀጠናው የተሠማራው የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ ተልዕኮውን በአስተማማኝ እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል።
የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል እንዳለ እሸቱ ሠላም አስከባሪ ሠራዊት ከተልዕኮው ባሻገር ከአካባቢው የፀጥታ አካላት እና ከሕብረተሠቡ ጋር እጅ እና ጓንት ሆኖ በመስራት የቀጠናውን ሠላም ለማረጋገጥ የሚያኮራ ግዳጅ መፈፀሙን ተናግረዋል።
አሁን ላይ የ21ኛ ሞተራይዝድ ሠላም አስከባሪ ሠራዊት በሴክተር ሳውዝ ጁባ እና በዌስተርን ኢኳቶርያ ሰፊ ቀጠና ሸፍኖ ተዕኮውን እየተወጣ ይገኛል።
በደቡብ ሱዳን የነፃነት ቀን በዓል የተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን የደቡብ ሡዳን የባህል ቡድን የኪነ ጥበብ ስራዎችን አቅርቧል።
ዘጋቢ ፍፁም ተካ
ፎቶ ግራፍ ግርማቸው አብረሀ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 949 |
| 12 | የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 1 |
| 13 | No text... | 2 643 |
| 14 | በስልጠና የተገነባ ሠራዊት የድል ባለቤት መሆኑ አያጠያይቅም።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
የምዕራብ ዕዝ ህዳሴ ኮር ከማሰልጠኛ ተመድበው የመጡ መሰረታዊ ወታደሮችን ለሁለት ወራት ወታደራዊ ሥልጠና በመሥጠት አስመርቋል።
በስነ - ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የምዕራብ ዕዝ ህዳሴ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጀነራል ንጉሴ ለውጤ ፤ ሠራዊቱ የሸኔ ሽብር ቡድንን እና ፅንፈኛውን ቡድን ከቀጠናው በማፅዳት ለህዝባችን አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን በሚያደርገው ስኬታማ የግዳጅ አፈፃፀም የወታደራዊ ስልጠናዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል።
ኮሩ እየሰለጠኑ መዋጋት እየተዋጉ መሰልጠን የሚለውን መርህ በመከተል በተሰማራባቸው የግዳጅ ቀጠናዎች ባስመዘገባቸው አኩሪ ድሎች የፀረ-ሰላም ሀይሎችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማዳከም ሀገራዊ ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ኮሩ የተሰጠውን ተልዕኮ በድል በመፈፀም መስዋዕትነት ከፍሎ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በስኬት እንዲጠናቀቅ አሥተዋፅኦ ማበርከቱን የተናገሩት ጀኔራል መኮንኑ ሠራዊቱ እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት የመወጣት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት።
ተመራቂዎችም በወሰዱት ወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ በተከተለ ስልጠና መሰረት ከመሰረታዊ ውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ካገኙት እውቀት ላይ ተጨማሪ አቅም በመፍጠር ተልዕኳቸውን በጀግንነት በመፈፀም ተቋሙን እና የኢትዮጵያን ህዝብ የሚያኮራ ስራ የማከናወን ሃላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል ።
የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሩ ዘመቻ ሃላፊ ሌተናል ኮሎነል ወንደወሰን ብርሃኑ ሰልጣኞች በቆይታቸው ኮሩ ባዘጋጀው የስልጠና መርሃ ግብር መሰረት የሚሰጣቸውን ግዳጅ በድል መወጣት የሚያስችል የወታደራዊ አቅም ማጎልበቻ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልፀዋል። የዘገበው ጋብዘው ዳና ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 955 |
| 15 | No text... | 2 588 |
| 16 | በአሸባሪው ሸኔ ላይ ያነጣጠረ እርምጃ መውሰዳቸውን ክፍሎች አሥታወቁ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
የ6ኛ ዕዝ አንድ ኮር ተሰማርቶ በሚገኝበት ምዕራብ ሸዋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እና በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ የሚገኘው የንስር ክፍለ ጦር በአሸባሪው ሸኔ ላይ የተጠናከረ እርምጃ መውሰዳቸውን አሥታውቀዋል።
የ6ኛ ዕዝ ኮር ሠራዊት ማንኛውንም አስቸጋሪ ሁኔታ በመቋቋም በሽብር ቡድኑ ላይ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ ሸኔን የመደምሰስ የመማረክ እና ትጥቅና መሣሪያን በቁጥጥር ሥር ማዋል እየተቻለ ሥለመሆኑ የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል ሃብታሙ ምህረቴ ገልፀዋል።
የሽብር ቡድኑ ይጠቀምባቸው የነበሩ ስናይፐር ፣ ክላሽ፣ ቦንብ፣ የተለያዩ ዓይነት ተተኳሾች ተይዘዋል።
በተመሳሳይ በመተከል ዞን ድባጤ ወረዳ ቆርካ ቀበሌ የሚገኘው የንስር ክፍለ ጦር ሬጅመንት፣ አሸባሪው ሸኔ ለጥፋት ኃይሉ ሲጠቀምበት የቆየውን በርካታ መሣሪያ መያዙን በምዕራብ ዕዝ የንስር ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ባምላኩ ሰንደቁ ገልፀዋል።
የክፍለጦሩ አዛዥ አሸባሪው ሸኔ ለጥፋት ሲጠቀምበት የቆየውን 27 መሣሪያ በአሰሳና ፍተሻ ከነታጣቂዎች መያዙን ጠቅሰው፣ የክፍለጦሩ ሠራዊት ስልታዊ ጥበብን በመጠቀም መረጃ ሰጪ የሸኔ ተላላኪ ሴሎችን በመያዝ መሣሪያዎች የተደበቁባቸውን ስፍራዎች በመለየት ግዳጁን በብቃት እየፈጸመ መሆኑን ተናግረዋል። ዘገባው የክፍሎች ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 054 |
| 17 | No text... | 3 152 |
| 18 | No text... | 1 |
| 19 | ግዳጅን በብቃት ለመፈፀም በወታደራዊ ስልጠና አቅምን መገንባት እንደሚገባ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም
ግዳጅን በአስተማማኝ ብቃት ለመፈፀም በወታደራዊ ስልጠና አቅምን መገንባት እንደሚገባ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።
በመቅደላ ክፍለጦር የስልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሀኑ በቀለ አገራችን በሉዓላዊነታቸው የማይደራደሩ የእልፍ ጀግኖች መኖሪያና መፍለቂያ መሆኗን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ወራሪውን ኃይል በማይደፈር ክንዳቸው አርበድብደው ባንዳን አባረው ቅኝ ያልተገዛች ሀገር አውርሰውናል ያሉት አዛዡ የዚህ ዘመን ትውልድ የሆነው እኛም የተረከብናትን ሀገር ነፃነቷን ሳናስደፍር ለትውልድ ከነሙሉ ክብሯ እናስረክባለን ሲሉ ተናግረዋል።
በየጊዜው የሀገርን ልማትና ብልፅግና ለማደናቀፍ የሚሞክሩ ሳይመቻቸው ሲቀር ደሞ በዘርና በሃይማኖት የሃሰት ትርክት እየነዙ የገራችን ሰላም የሚነሱ ባንዳዎች ህልማቸው ቅዠት እንዲሆን ማድረግ ብቻም ሳይሆን የኢትዮጵያ ስጋት እንዳይሆኑ አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም አዛዡ አንስተዋል።
በስልጠና የተገኘውን አቅም ማጎልበት፤ ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር የሆነውን እሴት በመላበስ የህዝባችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የበለጠ ዝግጁ መሆን እንደሚገባም ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ አሳስበዋል።
ዘጋቢ ሮቤል ስዩም
ፎቶግራፍ እንዳልካቸው ሀጂ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 093 |
| 20 | No text... | 2 958 |
