FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት
کانال FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 42 352 مشترک است و جایگاه 6 173 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 766 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 42 352 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 575 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -10 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.28% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 5 203 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 363 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 38 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“# ቁልፍ እሴቶች
1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣
2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣
3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣
4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 22 ژوئن | +4 | |||
| 21 ژوئن | +11 | |||
| 20 ژوئن | +10 | |||
| 19 ژوئن | +10 | |||
| 18 ژوئن | +24 | |||
| 17 ژوئن | +5 | |||
| 16 ژوئن | +20 | |||
| 15 ژوئن | +12 | |||
| 14 ژوئن | +8 | |||
| 13 ژوئن | +20 | |||
| 12 ژوئن | +11 | |||
| 11 ژوئن | +17 | |||
| 10 ژوئن | +12 | |||
| 09 ژوئن | +6 | |||
| 08 ژوئن | +13 | |||
| 07 ژوئن | +6 | |||
| 06 ژوئن | +13 | |||
| 05 ژوئن | +7 | |||
| 04 ژوئن | +4 | |||
| 03 ژوئن | +11 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | +8 |
| 2 | بدون متن... | 2 236 |
| 3 | የሰሜን ምዕራብ ኮር ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
ስልጠናው በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ፣ ፕሮፌሽናል ሰራዊት ግንባታና አስተሳሰብ እንዲሁም በሀገራዊ ታሪኮችና እሴቶች ላይ ያተኮረ ነው።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል በላይ አየለ ሠራዊታችን ከህዝባችን የጋራ ታሪክ የተቀዱ በትውልዱ የሚዳብሩ በሀገር መልካም ገፅታና እሴቶችን የሚጠብቅ ማንነቱ ኢትዮጵያን ውግንናውም ለሁሉም ኢትዮጵያ ህዝቦችና ህገ-መንግስቱ የሆነ ፕሮፌሽናል ሰራዊት ነው ብለዋል።
የአባቶቻችን ጀግንነት የአሁኑ ፕሮፌሽናል ሰራዊት አርበኞች መሰረት መሆኑንም ያስረዱት ብርጋዲየር ጄኔራል በላይ አየለ የኮሩ አመራሮችም የአባቶችን ጀግንነት፣ ጥበብና በየጊዜው እየበለፀጉ የመጡ ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም እውቀት ያላቸው በዲሲፒሊን፣ በህግና ስርዓት ተልዕኳቸውን የሚፈፅሙ አመራሮች መፈጠራቸውን ተናግረዋል።
መሪነት የሰራዊቱን ሞራል፣ ስነ-ልቦና ዝግጁነትና ግዳጅን የመፈፀም አቅም የሚያደረጅ የብዙ መልካም ባህሪያት ድምር ውጤት መሆኑን የገለፀት የኮሩ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ ኮሎኔል መዝገቡ ዘሩ፣ ኮሩ ግዳጁን እየፈፀመ በመሰልጠን በቀጣይ የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ በብቃት መፈፀም የሚያስችል የተቀናጀ የዝግጁነት አቅም መገንባቱንም ኮሎኔል መዝገቡ ዘሩ አስረድተዋል።
ስልጠናው ጊዜውን የዋጀ አቅም እንደፈጠረላቸው እና የሀገራችን መልካም ገፅታ ለማጠልሸት የሚፍጨረጨሩ ባዕዳና ባንዳዎች ላይ እርምጃ በመውሰድ የሀገራችንን ሰላም፣ ልማትና ህልውና የመጠበቅ የሁልጊዜ ተልዕኮ ስራቸው ላይ እንደሚገኙ የክፍለ ጦርና የሬጅመንት አመራሮች ተናግረዋል። የዘገበው አይተነው ወንዴ ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 947 |
| 4 | بدون متن... | 2 515 |
| 5 | ለኮሩ የመገናኛ አባላት ሲሰጥ የቆየው ሙያዊ ስልጠና ተጠናቀቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
የምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር የመገናኛ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ የሰራዊት አባላት ለአንድ ወር የቆየውን ስልጠና አጠናቀው ተመርቀዋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኮሩ ጥገና ኃላፊ ኮሎኔል አበራ ጥሩ ከሬጅመንት እና ከክፍለ ጦር ለተወጣጡ ተመራቂዎች መገናኛ ለሰራዊት የውጊያ ስራ ስኬታማነትና ለዕዝ ሰንሰለቱ ቀልጣፋ መረጃ ልውውጥ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል።
ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀት በተግባር ላይ በማዋል የኮሩን ተልዕኮ በላቀ ደረጃ ስኬታማ እንዲያደርጉ አመላክተዋል።
የኮሩ መገናኛ ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል አብዱራሃማን ኡመር በበኩላቸው፤ አባላቱ በመገናኛ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ ደህንነቱ የተጠበቀ መረጃ ልውውጥ ፣ የራዲዮ እና የዲጂታል መገናኛ ዘዴዎችን ጥልቅ ስልጠና መውሰዳቸውን ገልጸዋል።
ሰልጣኞቹ የተሰጣቸውን ስልጠና በከፍተኛ ስነ-ምግባርና ትጋት ማጠናቀቃቸውንም አብራርተዋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓት ማጠቃለያ ላይ በስልጠናው ከፍተኛ ውጤት ያመጡና አርአያነት ያለው ስነ-ምግባር ላሳዩ አባላት የእውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።
ዘጋቢ ሀብታሙ አወቀ
ፎቶ ግራፍ አማኑኤል ግርማ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 2 551 |
| 6 | بدون متن... | 2 433 |
| 7 | የፅንፈኛው ቡድን ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱ ወጣቶችን በማስገደድ እያሰለፈ መሆኑ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
የፅንፈኛው ቡድን ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱ ወጣቶችን ጭምር በማስገደድ ለባንዳነት አላማው ማስፈፀሚያ በጦርነት እየማገደ መሆኑን በሰሜን ሸዋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የተሰማራው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር ገልጿል።
የክፍለ ጦሩ አዛዥ ኮሎኔል ማቲዎስ ማዴቦ የፅንፈኛው ቡድን ቦታ እየቀያየረ ህብረተሰቡን ሰላም መንሳትና መዝረፍን ዓላማው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
የመንግስትን የሰላም አማራጭ በማይቀበሉ የፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሙትና ቁስለኛ ማድረጉንና ከ50 በላይ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች መማረኩን የገለፁት አዛዡ የቀረበላቸውን የሰላም ዕድል በማይቀበሉ የፅንፈኛ አመራርና አባላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱና የተማረኩ የፅንፈኛው አባላት ተገደው መግባታቸውንና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሾልከው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዳይመለሱ ወደ ማያውቁበት አካባቢ ወስደው ለጥፋት ዓላማ እንደሚጠቀሙባቸውም ተናግረዋል። ዘገባው: የአየር ወለድ ክፍለ ጦር የሠራዊት ሰነ-ልቦና ግንባታ ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 317 |
| 8 | بدون متن... | 3 235 |
| 9 | ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈፀም ቀጣይነት ያለው ስልጠና ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈፀምና ተተኪ አመራሮችን ለማፍራት ቀጣይነት ያለው ስልጠና ወሳኝ መሆኑን
የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጀር ጄኔራል ዋኘው ዓለሜ ተናገሩ።
በዕዙ አንድ ኮር ሲሰጥ የቆየው የመቶ አመራርና የሻምበል ምክትል አዛዦች የአቅም ማጎልበቻ ሰልጠና ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ስልታዊ አመራሮች ሠራዊቱን በሁለንተናዊ መስክ የማብቃት ኃላፊነታችሁን በመገንዘብ በየጊዜው አቅማችሁን ማጎልበት ይጠበቅባችኋል ብለዋል።
አሁን ያለውን ሀገራዊና ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት የምንመራውን የጦር ክፍል አካላዊና ስነልቦናዊ ብቃቱ የዳበረ፤ በአስተሳሰብ የላቀ ሁለንተናዊ ብቃት ያለው ተዋጊ ኃይል የማዘጋጅት ኃላፊነት እንዳለባቸውም ሜጄር ጄኔራል ዋኘው ዓለሜ አስገንዝበዋል።
ጄነራል መኮንኑ ስልታዊ አመራሩ በዓላማ ፅናትና በቁርጠኝነት የትኛውንም ፈታኝና አስቸጋሪ መሰናክሎችን በማለፍ በተሰጠው የግዳጅ ቀጠና ጠላትን በመምታት፣ በመደምሰስና የጠላትን ሴራ ከስሩ በመንቀል አኩሪ ገድል ማሰመዝገብ እንደሚገባም ለተመራቂዎቹ አሳስበዋል።
ዘጋቢ ይሁን አሻግሬ
ፎቶግራፍ እያሱ ጃርሶ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 961 |
| 10 | بدون متن... | 3 636 |
| 11 | የማይዘነጋ ውለታ- ለታሪክ ተጋሪ ህዝብ የተበረከተ ስጦታ፦
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
ከነሀሴ 24 እስከ ነሃሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ከሌሊት እስከ ምሽት የተካሔደ ከባድ ፍልሚያ። የጭና እና የወቅን ተራሮች የቀዝቃዛ አየር ሞቃት ፍልሚያዎች። የቦዛ፣ የደንበልግሳ ፣ አዲ ጋግራይ ተራሮችና የብና ሜዳ ግብግብ የምዕራብ ዕዝ ትንታጎችን አስፈሪ ቁመና በግልፅ ያመላከተ ነበር።
ጭጋግ፣ ዶፍና አመዳይ፤ የሞት ሽረት ከባድ ፍልሚያ፤
ኢ-ተገማች የጦርነት ዙር የከሸፈበት የፀለመቱ ምሽትና ንጋት። እነዚያ በጨገገው ሰማይ ስር የሞት ጥላ የተደቀነባቸው፤ የመውደቅና የመጣል፤ የመግደልና የመሞት፤ የመገፋት መልሶ ደግሞ የመግፋት ፤ አንዳች ድብልቅልቅና ትርምስ የተፈራረቀባቸው ቀናት በእርግጥም አስከፊ ነበሩ።
የደምና ውሃ፤ የአጥንት ክስካሽና የስትንፋስ ህቅታ ድብልቅልቅ። ሰው የተከፈለበት የከረረ የውጊያ ዙር ምሳሌ ፤ የጭና ውጊያ። ስለ ሀገር ህልውና የተከፈለ የጀግንነት ዋጋ። ደግሞም ማሸነፍ፤ ድርብ ድል እዚያው አለ።
ልክ እንደ ድሮው፤ ልክ እንደ ያኔው ሠራዊቱ ከዳባት፣ ከወቅንና አካባቢዋ ህዝብ ጋር ተጣምሮና ተናቦ ያስመዘገበው የጋራ ታሪክ። እስከ መጨረሻ ህቅታ "ወይ ፍንክች" በሚል ታላቅ የአሸናፊነት ወኔ በነፍስ- ወከፍና በጥምረት የተከወነ ታሪክ እጅን በአፍ ያስጫነ ተጋድሎ።
መቼም የማይረሳ፤ ተራሮች አፍ አውጥተው የተረኩት፤ የውሃ አካላት ደም ለብሰው ያቀለሙት በደምና በአጥንት የተከተበ በደባርቅና ዳባት ከተሞች መሃል የተካሔደ፤ "የእቆርጣለሁ አትቆርጥም" ፍልሚያ።
የምዕራብ ዕዝ ክፍለጦሮች የውጊያ አቅማቸውንና የምት ኃይላቸውን ያሳዩበት የጦርነት አውድ። ቢፃፍ የሚነበብ ቢነገር የሚደመጥ የዚያን ሰሞን ፈተና እና እፎይታ።
ሰው ከሰው በቅጡ በማይተያይበት ጭጋጋማ የቀን ጨለማ የመንፈስ መስተጋብር ያለ በሚመስል መልኩ የታየ ድንቅ መናበብ። ህዝቡም ሠራዊቱም ወታደር የሆነበት ባለ ጋቢና ባለ ሬንጀር ወጥቶ አደርነት።
በወቅቱ በሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት በሚመራው ምዕራብ ዕዝ ስር የሚገኙት 24ኛ፣ 53ኛ፣ 31ኛ፣ 71ኛ እና 72ኛ ክፍለጦሮች፤ በስተመጨረሻም 54ኛ ክ/ጦር ከህወሃት ዘጠኝ እግረኛና አንድ የኮማንዶ ክፍለጦሮች ጋር የሞት ሽረት ግብግብ አድርገዋል።
መልክኣ-ምድራዊና የጨገገው የክረምት ወሩ ፈተና ብዛት ካለው የህወሃት ኃይል ጋር ተደማምሮ የእነዚያን አራትና አምስት የፍልሚያ ቀንና ሌሊቶች አስቸጋሪነት አክፍተውታል።
ያ ጦርነት በህወሃት በኩል ሁለት አላማዎችን ለማሳካት ታልሞ የተደረገ ስለመሆኑም ይነገራል። በአንድ በኩል ወደ መሃል ሃገር ለመገስገስ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የምዕራቡን ኮሪደር ለማስከፈት የተካሔደ ኢ-ተገማች ውሳኔ ነበር። አልተሳካም።
የዚያን ሰሞኑ ታሪክ ተጋሪ የሆነው እና "ጭና ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ" ያለው የያኔው የምዕራብ ዕዝ አካል 403ኛ መከታ ኮር አራተኛ አመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል። በዕለቱም "እናንተ የወቅን አካባቢ ነዋሪዎች የጭና ተራራ ውለተኞች እነሆ ክሊኒክ ብሏቸዋል። የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አዘዘው መኮንን በዕለቱ የክብር ዕንግዳ በኩል ከልብ በተቀዳ ፍቅር ቁልፍ አስረክበዋል።
የኮሩን 4ኛ አመት የምስረታ በዓል አስመልክተው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት የድምፅ መልዕክት የ403ኛ ኮር አባላት ያስመዘገቡት ድል ታሪክ ሲዘክረው የሚኖር በአስቸጋሪ መልክዓ ምድር ውስጥ ድል በማድረግ ሀገር ማሻገር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ህያው የጀግንነት ታሪክ መሆኑን አውስተው የተመዘገበው ድል ጀግንነት እና ፅናትን አስተምሮ ያለፈ ደማቅ ታሪክ መሆኑን አንስተዋል።
በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የጠላትን የመስፋፋት ህልም ወደ ቅዠትነት ከቀየሩ አይበገሬ የኢትዮጵያ አናብስት መካከል 403ኛ መከታ ኮር አንዱ መሆኑንም አድነቀዋል።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኮሩ አመራር እና አባላት ከደመወዛችሁ በማዋጣት በአስቸጋሪው ወቅት ከጎናችሁ ለነበረው የሰሜን ጎንደር ህዝብ ገንብታችሁ ያስረከባችሁት ደረጃውን የጠበቀ የጤና ጣቢያ ህዝባዊ ባህሪያችሁን በተግባር ያስመሠከረ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው ሲሉ አመሠግነዋቸዋል።
እኔም ሰኔ ወር ላይ ሆኜ በወርሃ ሐምሌ 2013 ዓ.ም የተመዘገበን የድል ታሪክ መዘገቤ ምክንያቱ ይሔው ነው። ጉዳዩ ከህንፃ ግንባታ ይሻገራል።
በእርግጥም የተገነባው ክሊኒክ አይደለም ታላቅ የተጋድሎ ሐውልት እንጂ። ሐውልቱም ገና ሳያክም የሚያድን፤ ሳይከትብ የሚፈውስ ግብረ ምጡቅ የፈውስ መንደር ነው። በክሊኒኩ አንደኛው ክፍል፤ ያን ጊዜ ዋጋ የከፈሉ የሠራዊት አባላት፣ የአካባቢው የመስተዳድር አካላትና የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚያሳዩ ፎቶዎች በመታሰቢያነት ተቀምጧል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የያኔው የዕዙ አዛዥና አሁን ላይ ደግሞ የመከላከያ መገናኛና ኢንፎርሜሽን ሲስተም ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት ወደኋላ መለስ ብለው ጊዜውን እያሰቡ ጎብኝተውታል።
በወቅቱ ውጊያውን በመምራት የታሪኩ አካል የነበሩት የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አማረ ባህታን ጨምሮ ያኔ የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦር አመራር የነበሩት ሁሉ በቦታው ታድመዋል። የእነሱ መገኘት ደግሞ ለህዝብ የተሰጠ ክብር ማሳያ ነው። ህዝቡም ባለታሪኮቹን ግራና ቀኝ በፈረስ አጅቦ በደስታ ተቀብሏቸዋል። ክብር ለሚገባው ክብር ይሁን!! መከላከያ ህዝብ ነው ከህዝብ አብራክ ወጥቶ ለህዝብና ለሀገር ሲል ህይወቱን ይሠጣል ለህዝብ ያገለግላል።
በሰለሞን ሁነኛው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 4 767 |
| 12 | بدون متن... | 4 105 |
| 13 | የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል - ዳግም ውልደት
ሀገራችን በቀይ ባሕር ቀጣና የነበራትን ጂኦ-ፖለቲካዊ እና የንግድ መስመር ደኅንነት ለማስጠበቅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል፣ በዘመኑ ከነበሩት የአፍሪካ የባሕር ኃይሎች እጅግ ዘመናዊ እና ተወዳዳሪ ተቋም ነበር።
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል በ1946 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በዘመናዊ መልክ ተመሠረተ። የዚህ ኃይል ምሥረታ የተፋጠነው ታዲያ የቀይ ባሕር ጠረፎችን (ምጽዋን እና አሰብን) መጠበቅ የግድ በመሆኑ ነው።
ባሕር ኃይላችን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን በማቋቋም ከእንግሊዝ ሮያል ኔቪ፣ ኖርዌይ እና አሜሪካ ጋር በመተባበር መኮንኖችን በከፍተኛ ዲሲፕሊን ያሠለጥን ነበር።
በደርግ ዘመን የባሕር ኃይሉ ይበልጥ እየተጠናከረ ሄደ። ባሕር ኃይላችን በወቅቱ ዘመናዊ የጥበቃ መርከቦች፣ ፈጣን አጥቂ ጀልባዎች፣ የባሕር ላይ ፈንጂ አምካኝ መርከቦች እና ከሶቭየት ኅብረት የተገኙ የሚሳኤል ተሸካሚ ጀልባዎች ባለቤትም ነበር።
ይሁን እንጂ በሰሜን የሀገራችን ክፍል ጦርነቱ እየተባባሰ በመምጣቱ፣ ሠራዊቱ መደበኛ ጥበቃውን ትቶ የሕይወት መሥዋዕትነት የጠየቁ ከባድ ውጊያዎችን በቀይ ባሕር ጠረፎች ላይ ለማድረግ ተገዷል።
የ1983ቱ የፖለቲካ ለውጥ እና የባሕር በር ማጣት በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ላይ ያደረሰው ጉዳት ከፊል ሳይሆን ሁለንተናዊ እና አውዳሚ ነበር። የባሕር ኃይል ያለ ባሕር በር ሊኖር ስለማይችል፣ ሠራዊቱ ታሪካዊ መሠረቱን አጣ።
በ1982 ዓ.ም ምጽዋ፣ እንዲሁም በ1983 ዓ.ም አሰብ በሻዕቢያ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ፣ የባሕር ኃይሉ የጦር መርከቦች ማቆሚያዎቹን፣ የጥገና ዶኮችን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ መልካም ስም የነበረውን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን አጣ።
በከፍተኛ ወጪ እና ጥረት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት (እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ሩሲያ) የሠለጠኑት የባሕር ኃይል አባላት ተበተኑ። ይህ ውድቀት እጅግ ውድ የሆነ የሀገር ሀብት ብክነትን ያስከተለ ከመሆኑም በላይ፣ በባሕር ኃይሉ አባላት እና በሕዝቡ ሥነ-ልቦና ላይ ጥልቅ የኀዘን እና የቁጭት ጠባሳ ጥሏል።
የባሕር በር ከተዘጋ በኋላ፣ ከጦርነቱ የተረፉት የጦር መርከቦች የገዛ ሀገራቸውን ውኃ ለቅቀው ወደ የመን፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ ወደቦች ለመሰደድ ተገደዱ።
በወቅቱ ሠራዊቱ በመበተኑ እና በጀቱም በመቋረጡ ምክንያት፣ መርከቦቹ የቆሙበትን ከፍተኛ የወደብ ኪራይ በውጭ ምንዛሪ መክፈል አልተቻለም።
በዚህም የተነሣ በአስተናጋጅ ሀገራቱ መርከቦቹ በዝገት እንዲበላሹ ተደርገው፣ በመጨረሻም በጨረታ ለብረታብረትነት እንዲሸጡ ሆነዋል።
የባሕር ኃይል ዳግም ምሥረታ እና የዲፕሎማሲ ጥረቶች
ምንም እንኳን ታሪካዊው ሠራዊት ቢፈርስም፣ የአካዳሚው ምሩቃን በሀገራችን የባሕር ትራንስፖርት ዘርፍ ትልቅ ዐሻራ ጥለው አልፈዋል።
በቅርብ ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ ይህን ታሪካዊ ስህተት ለማረም እና ጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖዋን ለመመለስ ወሳኝ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምራለች።
ሀገራችን በ2011 ዓ.ም የባሕር ኃይሏን በይፋ መልሳ አቋቁማለች። አዲሱ የባሕር ኃይል በተግባር ሉዓላዊነትን ለማስከበር የባሕር በር የግድ ይለዋል። ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርሕ ላይ በተመሠረተ ዲፕሎማሲ የባሕር በር ለማግኘት ሰፊ ጥረት እያደረገች ነው።
የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ታሪክ የውድቀት ብቻ ሳይሆን የትንሣኤም ታሪክ ነው። ይህ የሠራዊቱ ትንሣኤ ከወታደራዊ አደረጃጀትም በላይ በርካታ ታሪካዊ ትርጉሞችን የያዘ ነው፦
በተቋሙ መፍረስ ምክንያት በቀድሞ የባሕር ኃይል አባላትም ሆነ በኢትዮጵያውያን ሥነ-ልቦና ውስጥ ተፈጥሮ የነበረውን ጥልቅ ስብራት የሚጠግን እና የሀገርን የተገፈፈ ኩራት ዳግም የሚመልስ ነው።
በምጽዋ አካዳሚ ተቀርጾ የነበረውን ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን እና በቀይ ባሕር ቀጣና የነበረውን የደኅንነት ዘብነት ራዕይ በአዲስ ትውልድ ከዳር የሚያደርስ ነው።
የባሕር ኃይላችን ዳግም መቋቋም የኢትዮጵያን ስትራቴጂያዊ ሕልውና የሚያረጋግጥ እና የቀድሞውን የባሕር ላይ ገናናነታችንን በአዲስ ሞራል፣ በአዲስ አቅም እና ራዕይ ዳግም ሕያው ያደረገ ታሪካዊ ትንሣኤ ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 957 |
| 14 | بدون متن... | 3 525 |
| 15 | በ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የተሠራው የጠጠር መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፓዊ ወረዳ፣ በ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የተሠራ የጠጠር መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፎቶ ይሰማው በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ክፍለጦሩ "ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር" በሚለው መርህ መሰረት፣ የቀጠናውን ሰላም ከማስከበር ባለፈ ለልማትና ዘብ መቆሙን አረጋግጧል አጠናክሮም ይቀጥላል ብለዋል።
በዚህም መሰረት ከ2.5 ኪሎ ሜትር በላይ የሆነ የውስጥ ለውስጥ የጠጠር መንገድ በክፍለጦሩ ጥረት ተሠርቶ ለአገልግሎት መብቃቱ ለህብረተሰቡ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አዛዡ ተናግረዋል።
የፓዊ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት፣ የከተማው ማዘጋጃ ቤት፣ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ትራንስፖርት፣ የገጠር መንገድ ጽህፈት ቤት እንዲሁም ባለሃብቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ለመንገድ ሥራው መሳካት ድጋፍ በማድረጋቸው ኮሎኔል ፎቶ ይሥማው አመሥግነዋል።
የፓዊ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይርጋ አሰፋ በበኩላቸው፣ 7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር በወረዳው የልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የህዝብ ልጅ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።
ክፍለጦሩ ከዚህ ቀደም በበጋ መስኖና በመኸር እርሻ ስራዎች ሲያደርገው የነበረውን የተቀናጀ ድጋፍ በማስታወስ፣ አሁን ደግሞ የህዝቡን አንገብጋቢ የመሰረተ ልማት ችግር በዘላቂነት መቅረፉ የሚያሥመሠግን ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ የተገኙ የከተማው ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ መንገዱ በተለይም በክረምት ወራት ለነዋሪዎች እንቅስቃሴና ማህበራዊ መስተጋብር ከፍተኛ ችግር ሆኖ መቆየቱን አስታውሰው፣ አሁን ይህ ችግር በክፍለጦሩ መፍትሄ ማግኘቱ ለከተማዋ ዕድገት ትልቅ እፎይታ መፍጠሩን ከምሥጋና ጋር ተናግረዋል። ዘገባዉ የክፍለጦሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነዉ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 561 |
| 16 | بدون متن... | 3 798 |
| 17 | የምስራቅ ዕዝ ኮር የቀጠናውን ሠላም በሚገባ እያረጋገጠ መሆኑን አሥታወቀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
የምስራቅ ዕዝ ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ፈይሳ አየለ የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምና አንድነቷን ለማደፍረስ የሚቋምጡባትን ሃገር ከመጠበቅ በላይ ትልቅ ሃላፊነት የለም ሲሉ ተናገሩ።
ለሃገራችን ሰላም እንቅፋት የሆኑ የውስጥና የውጭ ፀረ - ሰላም ሃይሎችን ህልም በማምከን ረገድ የኮሩ ሰራዊት የፈፀመውና እየፈፀመው ያለው አኩሪ ገድል ሃገርና ህዝቦቿ በትውልድ ቅብብሎሽ የሚዘክሩት አኩሪ ተግባር ነው ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ዞን አንጫር ወረዳ ሰቃ ቀበሌ የተሰማራው የአንድ ክፍለጦር ሰራዊት አሸባሪውን ሸኔ የደመሰሰ ሲሆን ፣ ክላሽ እና ሞተር ሳይክል ከጠላት መቀበል መቻሉን ጄነራል መኮንኑ ገልፀዋል። በቦርደር የተሰማራ ሠራዊት በትላንትናው ዕለት 02 የአልሸባብ ሰርጎ ገብ መያዙንም ተናግረዋል ።
የኮሩ ሠራዊት በፈተናዎች ሁሉ ፀንቶ ጀግንነቱን አረጋግጦ የጠላትን አከርካሪ እየሰባበረ በድል አድራጊነት የሚጓዝ ክንደ ብርቱ ነው ሲሉ የኮሩ አዛዥ በምክንያትነት ገልፀዋል።
ብርጋዲየር ጄኔራል ፈይሳ ህዝባችንን ሰላም በመንሳት ለሃገራችን ልማት እንቅፋት ሆነው በመሰለፍ ሰራዊቱን ዕረፍት ለማሳጣት የተጠመዱ የጥፋት ቡድኖች ላይ አሥፈላጊውን እርምጃ በመውሠድ እና አሸባሪው የአልሸባብ ቡድን በማንኛውም ጊዜና ወቅት ድንበር ተሻግሮ በምስራቅ ኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለውን ልማት እንዳያደናቅፍ በንቃት እንጠብቃለን ብለዋል።
ዘጋቢ ሀብታሙ ገመቹ
ፎቶግራፍ አብዶ አሊ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 550 |
| 18 | بدون متن... | 3 601 |
| 19 | የፍትህ አመራሮች የኃይል ዝግጁነትን የማስጠበቅ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም
የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን አስታውቋል። የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት አጠቃላይ አሠራሩን በተመለከተበት ማጠቃለያ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰው ሀብት አመራር ዋና መመሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ የፍትህ ስራ ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ መልኩ ሰራዊቱ በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ እንዲሆንና ወንጀልን ቀድሞ እንዲከላከል የፍትህ አመራርና ሙያተኞች ኃላፊነታችሁን በትጋት ልትወጡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
የዕዞች ኃይሎች እና የዋና መምሪያ የፍትህ አመራርና ሙያተኞች የኃይል ዝግጁነትን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለባችሁ ያሉት ሌተናል ጄኔራል አጫሉ ሸለመ የመከላከያ ፍትህ ዳይሬክቶሬቱን በስልጠናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በመደገፍ ስኬታማ የስራ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ አስተዋጽኦ ያደረጉ ተቋማትንም አመስግነዋል።
በተቋሙ የህግ የበላይነት እና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የማድረግ ዓላማን የያዘው የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት የዕዞች ኃይሎችና የዋና መምሪያ ፍትህ አመራሮችን አቅም በስልጠና በማዳበር በበጀት ዓመቱ ተገቢና በህግ ላይ የተመሰረተ ስኬታማ ስራ ለማከናወን መቻሉን የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ ተናግረዋል።
በርካታ አባላትን በፍትህ ዘርፎች ላይ በከፍተኛ የትምህረት ተቋማት እያስተማረ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ በሰራዊቱ የህግ ክፍተት እንዳይኖር በቃልና በሰነድ የተደገፈ የህግ ምክሮች ከመስጠት ባሻገር በፍትሀብሔር ጉዳዮች ላይ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ ስራዎች ተከናውኗል ብለዋል።
የሰራዊቱ አመራር እና አባላት በህገ መንግሥቱ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በስኬት እንዲፈፅሙ ንቃተ ህሊናን በማሳደግ ወንጀሎችን በመከላከል ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት የፍትህ ዳይሬክተሩ እስከ ታች ድረስ ያለውን አደረጃጀት ኃይል በመጠቀም ውጤታማ መሆን መቻሉንም አሥረድተዋል።
በተለያዩ የፍትህና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና በመስጠትና የፍትሀብሔር ጉዳዮችን በማማከር ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሽልማት ተበርክቷል።
ዘጋቢ ጀማነሽ ታደሰ
ፎቶግራፍ ብርቱካን ረጋሳ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official | 3 680 |
| 20 | بدون متن... | 3 679 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
