en
Feedback
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Open in Telegram

# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 359 subscribers, ranking 6 173 in the News & Media category and 766 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 359 subscribers.

According to the latest data from 21 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 575 over the last 30 days and by -10 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.28%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 203 views. Within the first day, a publication typically gains 3 363 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 38.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 22 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

42 359
Subscribers
-1024 hours
-207 days
+57530 days
Posts Archive
የፅንፈኛው ቡድን ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱ ወጣቶችን በማስገደድ እያሰለፈ መሆኑ ተገለፀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የፅንፈኛው ቡድን ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱ ወጣቶችን ጭምር በማስገደድ ለባንዳነት አላማው ማስፈፀሚያ በጦርነት እየማገደ መሆኑን በሰሜን ሸዋ ዞን በተለያዩ  ወረዳዎች የተሰማራው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር ገልጿል። የክፍለ ጦሩ አዛዥ ኮሎኔል ማቲዎስ ማዴቦ የፅንፈኛው ቡድን ቦታ እየቀያየረ ህብረተሰቡን ሰላም መንሳትና መዝረፍን ዓላማው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የመንግስትን የሰላም አማራጭ በማይቀበሉ የፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ በመውሰድ ሙትና ቁስለኛ ማድረጉንና ከ50 በላይ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች መማረኩን የገለፁት አዛዡ የቀረበላቸውን የሰላም ዕድል በማይቀበሉ የፅንፈኛ አመራርና አባላት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ  እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል። ዕድሜያቸው ለውትድርና ያልደረሱና የተማረኩ የፅንፈኛው አባላት ተገደው መግባታቸውንና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሾልከው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዳይመለሱ ወደ ማያውቁበት አካባቢ ወስደው  ለጥፋት ዓላማ እንደሚጠቀሙባቸውም ተናግረዋል። ዘገባው: የአየር ወለድ ክፍለ ጦር የሠራዊት ሰነ-ልቦና ግንባታ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈፀም ቀጣይነት ያለው ስልጠና ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተልዕኮን በላቀ ብቃት ለመፈፀምና ተተኪ አመራሮችን ለማፍራት ቀጣይነት ያለው ስልጠና ወሳኝ መሆኑን የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሜጀር ጄኔራል ዋኘው ዓለሜ  ተናገሩ። በዕዙ አንድ ኮር ሲሰጥ የቆየው የመቶ አመራርና የሻምበል ምክትል አዛዦች የአቅም ማጎልበቻ ሰልጠና ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ስልታዊ አመራሮች ሠራዊቱን በሁለንተናዊ መስክ የማብቃት ኃላፊነታችሁን በመገንዘብ በየጊዜው አቅማችሁን ማጎልበት ይጠበቅባችኋል ብለዋል። አሁን ያለውን ሀገራዊና ወቅታዊ ሁኔታ በመረዳት የምንመራውን የጦር ክፍል አካላዊና ስነልቦናዊ ብቃቱ የዳበረ፤ በአስተሳሰብ የላቀ ሁለንተናዊ ብቃት ያለው ተዋጊ ኃይል የማዘጋጅት ኃላፊነት እንዳለባቸውም ሜጄር ጄኔራል ዋኘው ዓለሜ አስገንዝበዋል። ጄነራል መኮንኑ ስልታዊ አመራሩ በዓላማ ፅናትና በቁርጠኝነት የትኛውንም ፈታኝና አስቸጋሪ መሰናክሎችን በማለፍ በተሰጠው የግዳጅ ቀጠና  ጠላትን በመምታት፣ በመደምሰስና የጠላትን ሴራ ከስሩ በመንቀል አኩሪ ገድል ማሰመዝገብ እንደሚገባም ለተመራቂዎቹ አሳስበዋል። ዘጋቢ ይሁን አሻግሬ ፎቶግራፍ  እያሱ ጃርሶ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የማይዘነጋ ውለታ- ለታሪክ ተጋሪ ህዝብ የተበረከተ ስጦታ፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከነሀሴ 24 እስከ ነሃሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ከሌሊት እስከ ምሽት የተካሔደ ከባድ ፍልሚያ። የጭና እና የወቅን ተራሮች የቀዝቃዛ አየር ሞቃት ፍልሚያዎች።  የቦዛ፣ የደንበልግሳ ፣ አዲ ጋግራይ ተራሮችና የብና ሜዳ ግብግብ የምዕራብ ዕዝ ትንታጎችን አስፈሪ ቁመና  በግልፅ ያመላከተ ነበር።  ጭጋግ፣ ዶፍና አመዳይ፤ የሞት ሽረት ከባድ ፍልሚያ፤ ኢ-ተገማች የጦርነት ዙር የከሸፈበት የፀለመቱ ምሽትና ንጋት። እነዚያ በጨገገው ሰማይ ስር የሞት ጥላ  የተደቀነባቸው፤ የመውደቅና የመጣል፤ የመግደልና የመሞት፤ የመገፋት መልሶ ደግሞ የመግፋት ፤ አንዳች ድብልቅልቅና ትርምስ የተፈራረቀባቸው ቀናት በእርግጥም አስከፊ ነበሩ።   የደምና ውሃ፤  የአጥንት ክስካሽና የስትንፋስ ህቅታ ድብልቅልቅ። ሰው የተከፈለበት የከረረ የውጊያ ዙር ምሳሌ ፤ የጭና ውጊያ። ስለ ሀገር ህልውና የተከፈለ የጀግንነት ዋጋ። ደግሞም ማሸነፍ፤ ድርብ ድል እዚያው አለ።    ልክ እንደ ድሮው፤ ልክ እንደ ያኔው ሠራዊቱ ከዳባት፣ ከወቅንና አካባቢዋ ህዝብ ጋር ተጣምሮና ተናቦ ያስመዘገበው የጋራ ታሪክ። እስከ መጨረሻ ህቅታ "ወይ ፍንክች" በሚል ታላቅ የአሸናፊነት ወኔ በነፍስ- ወከፍና በጥምረት የተከወነ ታሪክ እጅን በአፍ ያስጫነ ተጋድሎ። መቼም የማይረሳ፤ ተራሮች አፍ አውጥተው የተረኩት፤ የውሃ አካላት ደም ለብሰው ያቀለሙት በደምና በአጥንት የተከተበ በደባርቅና ዳባት ከተሞች መሃል የተካሔደ፤ "የእቆርጣለሁ አትቆርጥም" ፍልሚያ። የምዕራብ ዕዝ ክፍለጦሮች የውጊያ አቅማቸውንና የምት ኃይላቸውን ያሳዩበት የጦርነት አውድ። ቢፃፍ የሚነበብ ቢነገር የሚደመጥ የዚያን ሰሞን ፈተና እና እፎይታ። ሰው ከሰው በቅጡ በማይተያይበት ጭጋጋማ የቀን ጨለማ የመንፈስ መስተጋብር ያለ በሚመስል መልኩ የታየ ድንቅ መናበብ። ህዝቡም ሠራዊቱም ወታደር የሆነበት ባለ ጋቢና ባለ ሬንጀር ወጥቶ አደርነት።  በወቅቱ  በሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት በሚመራው ምዕራብ ዕዝ ስር  የሚገኙት  24ኛ፣ 53ኛ፣ 31ኛ፣ 71ኛ እና  72ኛ ክፍለጦሮች፤ በስተመጨረሻም 54ኛ ክ/ጦር  ከህወሃት ዘጠኝ እግረኛና አንድ የኮማንዶ ክፍለጦሮች ጋር የሞት ሽረት ግብግብ አድርገዋል።  መልክኣ-ምድራዊና የጨገገው የክረምት ወሩ ፈተና ብዛት ካለው የህወሃት ኃይል ጋር ተደማምሮ የእነዚያን አራትና አምስት የፍልሚያ ቀንና ሌሊቶች አስቸጋሪነት አክፍተውታል።   ያ ጦርነት በህወሃት በኩል ሁለት አላማዎችን ለማሳካት ታልሞ የተደረገ ስለመሆኑም ይነገራል። በአንድ በኩል ወደ መሃል ሃገር ለመገስገስ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የምዕራቡን ኮሪደር ለማስከፈት የተካሔደ ኢ-ተገማች ውሳኔ ነበር። አልተሳካም። የዚያን ሰሞኑ ታሪክ ተጋሪ የሆነው እና "ጭና ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ" ያለው የያኔው የምዕራብ ዕዝ አካል 403ኛ መከታ ኮር አራተኛ አመት የምስረታ በዓሉን አክብሯል።  በዕለቱም "እናንተ የወቅን አካባቢ ነዋሪዎች የጭና ተራራ ውለተኞች እነሆ ክሊኒክ ብሏቸዋል። የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አዘዘው መኮንን በዕለቱ የክብር ዕንግዳ በኩል ከልብ በተቀዳ ፍቅር ቁልፍ አስረክበዋል። የኮሩን 4ኛ አመት የምስረታ በዓል አስመልክተው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ክቡር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባስተላለፉት የድምፅ መልዕክት የ403ኛ ኮር አባላት ያስመዘገቡት ድል ታሪክ ሲዘክረው የሚኖር  በአስቸጋሪ መልክዓ ምድር ውስጥ ድል በማድረግ ሀገር ማሻገር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ህያው የጀግንነት ታሪክ መሆኑን አውስተው የተመዘገበው ድል ጀግንነት እና ፅናትን አስተምሮ ያለፈ ደማቅ ታሪክ መሆኑን አንስተዋል። በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የጠላትን የመስፋፋት ህልም ወደ ቅዠትነት ከቀየሩ አይበገሬ የኢትዮጵያ አናብስት መካከል 403ኛ መከታ ኮር አንዱ መሆኑንም አድነቀዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኮሩ አመራር እና አባላት ከደመወዛችሁ በማዋጣት በአስቸጋሪው ወቅት ከጎናችሁ ለነበረው የሰሜን ጎንደር ህዝብ ገንብታችሁ ያስረከባችሁት ደረጃውን የጠበቀ የጤና ጣቢያ ህዝባዊ ባህሪያችሁን በተግባር ያስመሠከረ አርዓያነት ያለው ተግባር ነው ሲሉ አመሠግነዋቸዋል። እኔም ሰኔ ወር ላይ ሆኜ በወርሃ ሐምሌ 2013 ዓ.ም የተመዘገበን የድል ታሪክ መዘገቤ ምክንያቱ ይሔው ነው። ጉዳዩ ከህንፃ ግንባታ ይሻገራል። በእርግጥም  የተገነባው  ክሊኒክ አይደለም ታላቅ የተጋድሎ ሐውልት እንጂ።  ሐውልቱም ገና ሳያክም የሚያድን፤ ሳይከትብ የሚፈውስ ግብረ ምጡቅ የፈውስ መንደር ነው። በክሊኒኩ አንደኛው ክፍል፤ ያን ጊዜ ዋጋ የከፈሉ የሠራዊት አባላት፣ የአካባቢው የመስተዳድር አካላትና የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚያሳዩ ፎቶዎች በመታሰቢያነት ተቀምጧል።   የዕለቱ የክብር እንግዳ የያኔው የዕዙ አዛዥና አሁን ላይ ደግሞ የመከላከያ መገናኛና ኢንፎርሜሽን ሲስተም ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጄኔራል መሰለ መሰረት ወደኋላ መለስ ብለው ጊዜውን እያሰቡ ጎብኝተውታል። በወቅቱ ውጊያውን በመምራት የታሪኩ አካል የነበሩት የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል አማረ ባህታን ጨምሮ ያኔ የዕዝ፣ የኮርና የክፍለ ጦር አመራር  የነበሩት ሁሉ በቦታው ታድመዋል። የእነሱ መገኘት ደግሞ ለህዝብ የተሰጠ ክብር ማሳያ ነው። ህዝቡም ባለታሪኮቹን ግራና ቀኝ በፈረስ አጅቦ በደስታ ተቀብሏቸዋል። ክብር ለሚገባው ክብር ይሁን!! መከላከያ ህዝብ ነው ከህዝብ አብራክ ወጥቶ ለህዝብና ለሀገር ሲል ህይወቱን ይሠጣል ለህዝብ ያገለግላል። በሰለሞን ሁነኛው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል - ዳግም ውልደት ሀገራችን በቀይ ባሕር ቀጣና የነበራትን ጂኦ-ፖለቲካዊ እና የንግድ መስመር ደኅንነት ለማስጠበቅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል፣ በዘመኑ ከነበሩት የአፍሪካ የባሕር ኃይሎች እጅግ ዘመናዊ እና ተወዳዳሪ ተቋም ነበር። የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል በ1946 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በዘመናዊ መልክ ተመሠረተ። የዚህ ኃይል ምሥረታ የተፋጠነው ታዲያ የቀይ ባሕር ጠረፎችን (ምጽዋን እና አሰብን) መጠበቅ የግድ በመሆኑ ነው። ባሕር ኃይላችን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን በማቋቋም ከእንግሊዝ ሮያል ኔቪ፣ ኖርዌይ እና አሜሪካ ጋር በመተባበር መኮንኖችን በከፍተኛ ዲሲፕሊን ያሠለጥን ነበር። በደርግ ዘመን የባሕር ኃይሉ ይበልጥ እየተጠናከረ ሄደ። ባሕር ኃይላችን በወቅቱ ዘመናዊ የጥበቃ መርከቦች፣ ፈጣን አጥቂ ጀልባዎች፣ የባሕር ላይ ፈንጂ አምካኝ መርከቦች እና ከሶቭየት ኅብረት የተገኙ የሚሳኤል ተሸካሚ ጀልባዎች ባለቤትም ነበር። ይሁን እንጂ በሰሜን የሀገራችን ክፍል ጦርነቱ እየተባባሰ በመምጣቱ፣ ሠራዊቱ መደበኛ ጥበቃውን ትቶ የሕይወት መሥዋዕትነት የጠየቁ ከባድ ውጊያዎችን በቀይ ባሕር ጠረፎች ላይ ለማድረግ ተገዷል። የ1983ቱ የፖለቲካ ለውጥ እና የባሕር በር ማጣት በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ላይ ያደረሰው ጉዳት ከፊል ሳይሆን ሁለንተናዊ እና አውዳሚ ነበር። የባሕር ኃይል ያለ ባሕር በር ሊኖር ስለማይችል፣ ሠራዊቱ ታሪካዊ መሠረቱን አጣ። በ1982 ዓ.ም ምጽዋ፣ እንዲሁም በ1983 ዓ.ም አሰብ በሻዕቢያ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ፣ የባሕር ኃይሉ የጦር መርከቦች ማቆሚያዎቹን፣ የጥገና ዶኮችን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ መልካም ስም የነበረውን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን አጣ። በከፍተኛ ወጪ እና ጥረት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት (እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ሩሲያ) የሠለጠኑት የባሕር ኃይል አባላት ተበተኑ። ይህ ውድቀት እጅግ ውድ የሆነ የሀገር ሀብት ብክነትን ያስከተለ ከመሆኑም በላይ፣ በባሕር ኃይሉ አባላት እና በሕዝቡ ሥነ-ልቦና ላይ ጥልቅ የኀዘን እና የቁጭት ጠባሳ ጥሏል። የባሕር በር ከተዘጋ በኋላ፣ ከጦርነቱ የተረፉት የጦር መርከቦች የገዛ ሀገራቸውን ውኃ ለቅቀው ወደ የመን፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ ወደቦች ለመሰደድ ተገደዱ። በወቅቱ ሠራዊቱ በመበተኑ እና በጀቱም በመቋረጡ ምክንያት፣ መርከቦቹ የቆሙበትን ከፍተኛ የወደብ ኪራይ በውጭ ምንዛሪ መክፈል አልተቻለም። በዚህም የተነሣ በአስተናጋጅ ሀገራቱ መርከቦቹ በዝገት እንዲበላሹ ተደርገው፣ በመጨረሻም በጨረታ ለብረታብረትነት እንዲሸጡ ሆነዋል። የባሕር ኃይል ዳግም ምሥረታ እና የዲፕሎማሲ ጥረቶች ምንም እንኳን ታሪካዊው ሠራዊት ቢፈርስም፣ የአካዳሚው ምሩቃን በሀገራችን የባሕር ትራንስፖርት ዘርፍ ትልቅ ዐሻራ ጥለው አልፈዋል። በቅርብ ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ ይህን ታሪካዊ ስህተት ለማረም እና ጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖዋን ለመመለስ ወሳኝ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምራለች። ሀገራችን በ2011 ዓ.ም የባሕር ኃይሏን በይፋ መልሳ አቋቁማለች። አዲሱ የባሕር ኃይል በተግባር ሉዓላዊነትን ለማስከበር የባሕር በር የግድ ይለዋል። ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርሕ ላይ በተመሠረተ ዲፕሎማሲ የባሕር በር ለማግኘት ሰፊ ጥረት እያደረገች ነው። የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ታሪክ የውድቀት ብቻ ሳይሆን የትንሣኤም ታሪክ ነው። ይህ የሠራዊቱ ትንሣኤ ከወታደራዊ አደረጃጀትም በላይ በርካታ ታሪካዊ ትርጉሞችን የያዘ ነው፦ በተቋሙ መፍረስ ምክንያት በቀድሞ የባሕር ኃይል አባላትም ሆነ በኢትዮጵያውያን ሥነ-ልቦና ውስጥ ተፈጥሮ የነበረውን ጥልቅ ስብራት የሚጠግን እና የሀገርን የተገፈፈ ኩራት ዳግም የሚመልስ ነው። በምጽዋ አካዳሚ ተቀርጾ የነበረውን ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን እና በቀይ ባሕር ቀጣና የነበረውን የደኅንነት ዘብነት ራዕይ በአዲስ ትውልድ ከዳር የሚያደርስ ነው። የባሕር ኃይላችን ዳግም መቋቋም የኢትዮጵያን ስትራቴጂያዊ ሕልውና የሚያረጋግጥ እና የቀድሞውን የባሕር ላይ ገናናነታችንን በአዲስ ሞራል፣ በአዲስ አቅም እና ራዕይ ዳግም ሕያው ያደረገ ታሪካዊ ትንሣኤ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

በ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የተሠራው የጠጠር መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፓዊ ወረዳ፣ በ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር የተሠራ የጠጠር መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። የክፍለጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፎቶ ይሰማው በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ክፍለጦሩ "ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር" በሚለው መርህ መሰረት፣ የቀጠናውን ሰላም ከማስከበር ባለፈ ለልማትና ዘብ መቆሙን አረጋግጧል አጠናክሮም ይቀጥላል ብለዋል። በዚህም መሰረት ከ2.5 ኪሎ ሜትር በላይ የሆነ የውስጥ ለውስጥ የጠጠር መንገድ በክፍለጦሩ ጥረት ተሠርቶ ለአገልግሎት መብቃቱ ለህብረተሰቡ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አዛዡ ተናግረዋል። የፓዊ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት፣ የከተማው ማዘጋጃ ቤት፣ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ትራንስፖርት፣ የገጠር መንገድ ጽህፈት ቤት እንዲሁም ባለሃብቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ለመንገድ ሥራው መሳካት ድጋፍ በማድረጋቸው ኮሎኔል ፎቶ ይሥማው አመሥግነዋል። የፓዊ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይርጋ አሰፋ በበኩላቸው፣ 7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለጦር በወረዳው የልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የህዝብ ልጅ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል። ክፍለጦሩ ከዚህ ቀደም በበጋ መስኖና በመኸር እርሻ ስራዎች ሲያደርገው የነበረውን የተቀናጀ ድጋፍ በማስታወስ፣ አሁን ደግሞ የህዝቡን አንገብጋቢ የመሰረተ ልማት ችግር በዘላቂነት መቅረፉ የሚያሥመሠግን ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል። በመርሃ ግብሩ የተገኙ የከተማው ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ መንገዱ በተለይም በክረምት ወራት ለነዋሪዎች እንቅስቃሴና ማህበራዊ መስተጋብር ከፍተኛ ችግር ሆኖ መቆየቱን አስታውሰው፣ አሁን ይህ ችግር በክፍለጦሩ መፍትሄ ማግኘቱ ለከተማዋ ዕድገት ትልቅ እፎይታ መፍጠሩን ከምሥጋና ጋር ተናግረዋል። ዘገባዉ የክፍለጦሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነዉ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የምስራቅ ዕዝ ኮር የቀጠናውን ሠላም በሚገባ እያረጋገጠ መሆኑን አሥታወቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የምስራቅ ዕዝ ኮር  አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ፈይሳ አየለ የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ባንዳዎች ሰላምና አንድነቷን ለማደፍረስ የሚቋምጡባትን ሃገር ከመጠበቅ በላይ ትልቅ ሃላፊነት የለም ሲሉ ተናገሩ። ለሃገራችን ሰላም እንቅፋት የሆኑ የውስጥና የውጭ ፀረ - ሰላም ሃይሎችን ህልም በማምከን ረገድ የኮሩ ሰራዊት የፈፀመውና እየፈፀመው ያለው አኩሪ ገድል ሃገርና ህዝቦቿ በትውልድ ቅብብሎሽ የሚዘክሩት አኩሪ ተግባር ነው ብለዋል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ ዞን አንጫር ወረዳ ሰቃ ቀበሌ የተሰማራው የአንድ ክፍለጦር ሰራዊት አሸባሪውን ሸኔ የደመሰሰ ሲሆን ፣ ክላሽ እና ሞተር ሳይክል ከጠላት መቀበል መቻሉን ጄነራል መኮንኑ ገልፀዋል። በቦርደር የተሰማራ ሠራዊት በትላንትናው ዕለት 02 የአልሸባብ ሰርጎ ገብ መያዙንም ተናግረዋል ። የኮሩ ሠራዊት በፈተናዎች ሁሉ ፀንቶ ጀግንነቱን አረጋግጦ የጠላትን አከርካሪ እየሰባበረ በድል አድራጊነት የሚጓዝ ክንደ ብርቱ ነው ሲሉ የኮሩ አዛዥ በምክንያትነት ገልፀዋል። ብርጋዲየር ጄኔራል ፈይሳ ህዝባችንን ሰላም በመንሳት ለሃገራችን ልማት እንቅፋት ሆነው በመሰለፍ ሰራዊቱን ዕረፍት ለማሳጣት የተጠመዱ የጥፋት ቡድኖች ላይ አሥፈላጊውን እርምጃ በመውሠድ እና አሸባሪው የአልሸባብ ቡድን በማንኛውም ጊዜና ወቅት ድንበር ተሻግሮ በምስራቅ ኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለውን ልማት እንዳያደናቅፍ በንቃት እንጠብቃለን ብለዋል። ዘጋቢ ሀብታሙ ገመቹ ፎቶግራፍ አብዶ አሊ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የፍትህ አመራሮች የኃይል ዝግጁነትን የማስጠበቅ ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለፀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን አስታውቋል። የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት አጠቃላይ አሠራሩን በተመለከተበት ማጠቃለያ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰው ሀብት አመራር ዋና መመሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀኔራል አጫሉ ሸለመ የፍትህ ስራ ቀጣይነት ያለው በመሆኑ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ መልኩ ሰራዊቱ በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ እንዲሆንና ወንጀልን ቀድሞ እንዲከላከል የፍትህ አመራርና ሙያተኞች ኃላፊነታችሁን በትጋት ልትወጡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። የዕዞች ኃይሎች እና የዋና መምሪያ የፍትህ አመራርና ሙያተኞች የኃይል ዝግጁነትን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለባችሁ ያሉት ሌተናል ጄኔራል አጫሉ ሸለመ የመከላከያ ፍትህ ዳይሬክቶሬቱን በስልጠናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ በመደገፍ ስኬታማ የስራ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ አስተዋጽኦ ያደረጉ ተቋማትንም አመስግነዋል። በተቋሙ የህግ የበላይነት እና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የማድረግ ዓላማን የያዘው የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት የዕዞች ኃይሎችና የዋና መምሪያ ፍትህ አመራሮችን አቅም በስልጠና በማዳበር በበጀት ዓመቱ ተገቢና በህግ ላይ የተመሰረተ ስኬታማ ስራ ለማከናወን መቻሉን የመከላከያ ፍትህ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ ተናግረዋል። በርካታ አባላትን በፍትህ ዘርፎች ላይ በከፍተኛ የትምህረት ተቋማት እያስተማረ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ  በሰራዊቱ የህግ ክፍተት እንዳይኖር በቃልና በሰነድ የተደገፈ የህግ ምክሮች ከመስጠት ባሻገር በፍትሀብሔር ጉዳዮች ላይ የተቋሙን ጥቅም የሚያስጠብቁ ስራዎች ተከናውኗል ብለዋል። የሰራዊቱ አመራር እና አባላት በህገ መንግሥቱ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በስኬት እንዲፈፅሙ ንቃተ ህሊናን በማሳደግ ወንጀሎችን በመከላከል ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት የፍትህ  ዳይሬክተሩ እስከ ታች ድረስ ያለውን አደረጃጀት ኃይል በመጠቀም ውጤታማ መሆን መቻሉንም አሥረድተዋል። በተለያዩ የፍትህና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና በመስጠትና የፍትሀብሔር ጉዳዮችን በማማከር ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሽልማት ተበርክቷል። ዘጋቢ ጀማነሽ ታደሰ ፎቶግራፍ ብርቱካን ረጋሳ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት እና የአመራርነት ሚና ለማሣደግ እየተሠራ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ሚኒስቴር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክትሬት ከዕዞች፣ ከሃይሎች እንዲሁም ከመከላከያ ልዩ ልዩ ክፍሎች ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል። ለሁለት ቀን በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የመከላከያ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጀረኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ እንደተናገሩት የሴቶች አደረጃጀት በሰራዊቱ የሚገኙ ብቁ ሴቶችን ወደ መሪነት ለማምጣት እና የሴቶችን እኩልነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ላይ ትልቅ እገዛ አለው፡፡ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አደረጃጀት አስተባባሪነት ከተከናወኑ ስራዎች ውስጥ ለጀግና ሰማዕታት ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት ገንብቶ ማስረከብ ፤ለሀገር ዋጋ የከፈሉ ጀግኖችን መጎብኘት፣ ለተለያዩ በጎ አድራጎት ማህበራት ድጋፍ ማድረግ እና ከተለያዩ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር በጋራ ተባብሮ መስራት ይጠቀሳሉ፡፡ አለምአቀፍ የሴቶች ቀን በአል ላይ የተቋማችን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ሴት የሰራዊት አባላትን በቀጣይነት እንዲደግፉ የተደረገው ጥረት በበጀት አመቱ ከተሰሩ በርካታ ስራዎች መሀከል ይገለፃል። በቀጣይም አቅም ሊፈጥሩ የሚችሉ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት ሴት የሰራዊት አባላት ጥንካሬያቸውን በማስቀጠል ከጀግንነት ተግባራቸው ጎን ለጎን በትምህርታቸው ብቁ ሆነው እንዲቀጥሉ ለማድረግ እንሰራለን ሲሉ ብርጋዲየር ጄኔራል ሁሉአገርሽ ድረስ ተናግረዋል። በእለቱ በስራ አፈጻጸማቸው ጥሩ ውጤት ያመጡና ሀገራቸውን ረጅም ግዜ ያገለገሉ ጀግና ከፍተኛ መኮንኖች የእውቅና ሰርተ-ፊኬትና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በመድረኩ ላይ ተካፋይ ከነበሩ አመራሮች መካከል ኮሎኔል ቸኮለች ወንዳቸው እና ሻምበል አብነት ታደሰ በሰጡት አስተያየት የውይይት መድረኩ በሴቶች አደረጃጀት ከፍተኛ ኃላፊነት ተሰጥቷቸው በስራ ላይ የሚገኙ አመራሮችን በአንድ መድረክ ከማገናኘቱ በላይ   የዕርስ በርስ የተሞክሮ ልውውጥ ያደረጉበት ለቀጣይ ስራቸው የተሻለ አቅም የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል። ዘጋቢ ፍቅሩ ከበደ ፎቶ ግራፍ ድምሩ ህሩይ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ጤና ይሥጥልን ጥቂት ሥለጤናዎ ያለ ምንም ምልክት የዓይን ብርሃንን የሚያሳጣው በሽታ - ግላኮማ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ያለምንም የህመም ስሜት ብርሃንን ቀስ በቀስ በመስረቅ “የእይታ ሌባ” በመባል የሚታወቀው የግላኮማ ወይም የዓይን ግፊት በሽታ፣ ወቅታዊ ክትትልና ምርመራ ካልተደረገለት ለዘላቂ ዓይነ-ስውርነት ዋነኛ መንስኤ እየሆነ ነው፡፡ በተለይም ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ምንም ዓይነት ምልክት ሳይጠብቁ በዓመት ከአንድ እስከ ሁለት ጊዜ መደበኛ የዓይን ግፊት ምርመራ ሊያደርጉ ይገባል። የዓይን ኳስ በተፈጥሮው በውስጡ በሚገኝ ፈሳሽ አማካኝነት ቅርጹን ጠብቆ ይቆያል። ነገር ግን የዚህ ፈሳሽ መውጫ ቀዳዳዎችና የተፈጥሮ ማፍሰሻ ቱቦዎች በተለያዩ ምክንያቶች ሲጠቡ ወይም ሲደፈኑ፣ ፈሳሹ ሳይወጣ ቀርቶ በዓይን ውስጥ ይከማቻል። ይህ ክስተት በዓይን ውስጥ ከፍተኛ ግፊት የሚፈጥር ሲሆን፣ ግፊቱም የዓይን ምስል ከጀርባ ወደ አእምሮ የሚወስደውን ‘ኦፕቲክ ነርቭ’ የተባለውን ስስ የነርቭ አካል በመጫን ቀስ በቀስ እንዲሞትና እይታ እንዲጠፋ ያደርጋል። የግላኮማ ዋነኛው አደገኛ ባህሪ መጀመሪያ አካባቢ ምንም ዓይነት የህመም ስሜት ወይም ግልጽ ምልክት የማያሳይ መሆኑ ነው። በሀገራችን በስፋት የሚታየው የግላኮማ ዓይነት (Open-angle glaucoma) እይታን ቀስ በቀስ የሚያጠፋ በመሆኑ፣ ብዙ ጊዜ ሕመምተኞች እይታቸው እስከሚጠፋ ድረስ ወደ ሕክምና ተቋማት አይሄዱም። ለዚህ በሽታ ይበልጥ ተጋላጭ የሚሆኑ ደግሞ፣ የቅርብ ወይም የሩቅ እይታ ችግር ኖሯቸው ለረጅም ጊዜ መነፅር የሚጠቀሙ፣ በቤተሰብ የቅርብ አባል ላይ የበሽታው ታሪክ ያላቸው እንዲሁም እንደ ስኳርና የደም ግፊት ያሉ ስር የሰደዱ ተጓዳኝ በሽታዎች ያሉባቸው ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም በዓይን ላይ ድንገተኛ አደጋ ከደረሰ እና ከሐኪም ትዕዛዝ ውጪ የሚወሰዱ የዓይን ህመም ማስታገሻ መድኃኒቶችን ለረጅም ጊዜ የሚጠቀሙ ግለሰቦች ለሕመሙ የመጋለጥ ዕድላቸው እጅግ ከፍተኛ ነው። የግላኮማ ሕክምና እንደ በሽታው ደረጃ የሚለያይ ቢሆንም፣ የሚሰጡት ሕክምናዎች በሙሉ በሽታው ባለበት ደረጃ ላይ እንዲቆምና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል የሚረዱ ብቻ ናቸው። በሽታውን ለመቆጣጠርም በዋናነት የዓይን ጠብታ መድኃኒቶች፣ የጨረር እና የቀዶ ጥገና ሕክምና ሥራ ላይ ይውላሉ። በሽታው ተከስቶ እይታ ላይ ዘላቂ ጉዳት ሳይደርስ በፊት ብቸኛውና አስተማማኙ አማራጭ መደበኛ የዓይን ምርመራ ማድረግ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የመከላከያ ሎጀስቲክስ ለሠራዊታችን የተሟላ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍ የማረጋገጥ ዝግጁነት፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ሀገር ካልፈረሰ ብለው ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ ያሉ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን ለመደምሰስ ዝግጁነቱን ላረጋገጠው ጀግናው ሠራዊታችን፣ የተሟላ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍ ለመስጠት መከላከያ ሎጀስቲክስ ዝግጁነቱን በተግባር አረጋግጧል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ በውስጥ አቅም ለ5ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን የከባድ ጭነት ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና የጥገና ሙያተኞችን በዛሬው ዕለት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት በመከላከያ ሎጀስቲክስ የትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዲየር ጄኔራል ፍቃዱ ታደሰ፤ ስልጠናው አደጋን በመቀነስ፣ የተቋምን ሀብት በአግባቡ በመያዝና አገልግሎት ላይ በማዋል፤ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍን ይበልጥ ለማሳለጥ ታስቦ ተተኪ ሙያተኞችን  ከሁሉም ኃይሎች፣ ዕዞች እና ክፍሎች በመመልመል ሙሉ በሙሉ በውስጥ አቅም የተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል። በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው የስራ መመሪያና መልዕክት ያስተላለፉት የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል፣ በመጀመሪያ ላስመራቂዎችና ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። "የሎጀስቲክስ ተልዕኳችንን የምንፈፅመው እናንተን ይዘን በመሆኑ፣ አሁን ባዳበራችሁት አቅም የውጊያ አገልግሎት ድጋፋችንን ይበልጥ ስለምናሳልጥ ደስታ ይሰማኛል" ያሉት የዋና መምሪያ ኃላፊው፤ የስልጠናው ዋና ዓላማም ሙያተኞች በነበራቸው ዕውቀት ላይ ተጨማሪ አቅም ፈጥረው በግዳጅ ላይ ለሚገኘው ሠራዊት የሚሰጠውን ድጋፍ በላቀ ብቃት ለማከናወን መሆኑን አስገንዝበዋል። "ሀገር ካልፈረሰ ብለው ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ተቀናጅተው ህዝባችንን የሚያሰቃዩ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን ለመደምሰስ ጀግናው ሠራዊታችን እየሰራ ይገኛል። ለዚህ ሠራዊት ሎጀስቲክስ ሌት ከቀን በመስራት የተሟላ የውጊያ አገልግሎት ድጋፍ እያረጋገጠ ነው!" ብለዋል ሌተናል ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል። የዋና መምሪያ ኃላፊው የሎጀስቲክስ ስራ በመናበብና በቅንጅት እንጂ በተናጠል የሚሰራ አይደለም፤ የዛሬ ተመራቂ አሽከርካሪዎችና የጥገና ሙያተኞች ቅንጅት ይህንኑ መርህ የሚያረጋግጥ በመሆኑ ሠራዊታችን ለታጠቃቸው ተሽከርካሪዎች እናንተ ሀኪሞቻቸው ናችሁ፤ አይናገሩም እንጂ ህክምና ይፈልጋሉ። በተማራችሁት መሰረት ተቀናጅታችሁ በማከምና በማቀብ ሁልጊዜ ለግዳጅ ዝግጁ አድርጓቸው ብለዋል። "በመፍጠር ማባዛት፣ በማቀብ ማሳለጥ" የሚሉትን የሎጀስቲክስ እሴቶቻችንን መተግበር አለባችሁ፤ አሁን የገነባነው ሙያተኛ ቀደም ሲል ሀገር አፍራሾች በሴራ እንዳዳከሙት ሳይሆን፣ በማንኛውም ጊዜና ቦታ ሠራዊቱን ማገልገል የሚችል ብቁ የሎጀስቲክስ ሙያተኛ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ አሁን ላይ ሠራዊታችን የታሪካዊ ጠላቶቻችን ተላላኪ የሆኑትን ሀገር አፍራሽ እና ፀረ-ሰላም ኃይሎችን አድኖ ለመደምሰስ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ የሆነበት ወቅት መሆኑን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ የመከላከያ ሎጀስቲክስም የዚህን ጀግና ሠራዊት ተልዕኮ ለማሳለጥና የድል ግስጋሴውን ለማፋጠን፣ ተተኪ ሙያተኞችን ያለማቋረጥ በማብቃት፣ ንብረትን በማቀብ እና ቀን ከሌት በመስራት አስተማማኝ ደጀንነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል እናንተም ይህንን የበለጠ ታሳልጣላችሁ ሲሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም በዕለቱ ስልጠናውን በብቃት ለሰጡ አሰልጣኞች እና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀትና ልዩ ሽልማት በማበርከት የምረቃ ስነ-ስርዓቱ ተጠናቋል። ዘገባው የዋና መምሪያው ፅህፈት ቤት ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official