en
Feedback
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Open in Telegram

# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 481 subscribers, ranking 6 053 in the News & Media category and 764 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 481 subscribers.

According to the latest data from 12 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 70 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 11.40%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.29% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 840 views. Within the first day, a publication typically gains 3 520 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 36.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 13 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

42 481
Subscribers
-324 hours
-227 days
+7030 days
Posts Archive
በኢትዮጵያ የቼክ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚሮስላቭ ኮሴክ የመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ ሙዚየምን ጎበኙ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የቼክ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚሮስላቭ ኮሴክ እና በቼክ ሪፐብሊክ ወታደራዊ ሙዚየም ዳይሬክተር አሌክስ ኪንዤክ የተመራ ቡድን የመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ ሙዚየምን ጎብኝቷል፡፡ በጉብኝቱ የወታደራዊ ሙዚየሙ ታሪክ፣ አሁናዊ ሁኔታ እና ወደፊት ሊሰራ ስለታሰበው ዘመናዊ ወታደራዊ ሙዚየም ሰፋ ያለ ገለጻ የተደረገ ሲሆን የቼክ ሪፐብሊክ መንግስት ከመከላከያ ወታደራዊ ሙዚየም ጋር በጋራ በሚሰራባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቷል፡፡ የመከላከያ ወታደራዊ ቅርስ ጥናትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ጥሩዬ አሰፌ ኢትዮጵያ እና ቼክ ሪፐብሊክ የረዥም አመት ወታደራዊ ግንኙነት ያላቸው ሃገራት መሆናቸውን ጠቁመው ከመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ ሙዚየም ጋር ያለው ግንኙነት ቆየት ያለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሙዚየሙ በሚጠናከርበት ሁኔታ እና ወደፊት በሚሰራው ዘመናዊ ወታደራዊ ሙዚየም ላይ የቼክ ሪፐብሊክ መንግስት አብሮ ለመስራት ቃል መግባቱን የተናገሩት ሜጀር ጄነራል ጥሩዬ አሰፌ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ወታደራዊ ሙዚየሙን በመጎብኘት የሀገሩን ታሪክ እንዲያውቅ እና ወደፊት ለሚሰራው ዘመናዊ ወታደራዊ ሙዚየም በገንዘብ፣ በሃሳብ እና በሙያዊ ድጋፍ የበኩሉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በኢትዮጵያ የቼክ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚሮስላቭ ኮሴክ እና የቼክ ሪፐብሊክ ወታደራዊ ሙዚየም ዳይሬክተር አሌክስ ኪንዤክ በበኩላቸው በጉብኝቱ በኢትዮጵያ ወታደራዊ ታሪክ መደነቃቸውን ገልጸው የቼክ ሪፐብሊክ መንግስት በቀጣይ ሙዚየሙን በመደገፉ ረገድ በጋራ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ ዘጋቢ ማርታ ግርማ ፎቶግራፍ አበረ አየነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የደቡብ ጎንደር ዞን ሕዝብ ለሠራዊታችን የእርድ በሬዎችን እና ፍየሎችን ድጋፍ አደረገ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ድጋፉን ለሠራዊታችን ያበረከቱት እስቴ፣ አንዳቤት ፣ስማዳ ፣ሰዴሙጃ፣ ክምር ድንጋይ ፣ላይ ጋይንት ፣ዓርብ ገበያ  ፣አምባሳሜ ወረዳዎች እና የባህር ዳር ከተማ ዙሪያ ናቸው። ድጋፋን ከሰጡ ወረዳዎች መካከል የእስቴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ማንተፋርዶ ሞላ እንደተናገሩት ፣ ለህዝብ ሠላምና አንድነት ከፍተኛ መስዋዕትነትን እየከፈለ ሠላምና ልማትን እያረጋገጠ ለሚገኘው ሠራዊት የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ድጋፉን ከተረከቡት መካከል የምስራቅ ዕዝ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ልጅዓለም ምትኩ እና የክፍለ ጦር አመራሮች ፣የተደረገላቸው ድጋፍ የአንድነት ማሳያ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም ከህብረተሰቡ ከዞን፣ ከወረዳ፣ ከከተማ አስተዳደሮች እና ከፀጥታ አካላት ጋር ሠላምን ለማረጋገጥ ተቀናጅቶ መስራታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ዘጋቢ አማኑኤል ታደሰ ነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የወዳጅነት የእግር ኳስ ጨዋታ - በምዕራብ ዕዝ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም የምዕራብ ዕዝ አብዲሳ አጋ ክፍለ ጦር ከዋልታ ከአድዋ ክፍለ ጦር ጋር ያደረገው የወዳጅነት የእግር ኳስ ጨዋታ በአድዋ ክፍለ ጦር 2 ለ1 በሆነ ውጤት አሸናፊነት ቢጠናቀቅም ተመልካቹን ያዝናና እና ያሥደሰተ ሆኖ አልፏል። በጨዋታው ላይ የተገኙት የምዕራብ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለውጊያ ድጋፍ አገልግሎት ብርጋዲየር ጄኔራል ወርቅነህ ጉደታ እንደዚህ ዓይነት የወዳጅነት የስፖርት ውድድሮች በቀጣይም በሌሎች ክፍለ ጦሮችና አሃዶች መካከል በማካሄድ የሠራዊቱን አንድነት ማጠናከር፣ የአካል ብቃትን ማሳደግና ዕዙን በተለያዩ የስፖርት መድረኮች የሚወክሉ ብቁ ስፖርተኞችን ማፍራት እንዲቻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል። በወዳጅነት ጨዋታው ላይ የምዕራብ ዕዝ አመራሮች፣  የኮርና ክፍለ ጦር አዛዦች፣ የሠራዊቱ አባላት እንዲሁም የዳንሻ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።  ዘጋቢ ፍፁም ከተማ ፎቶግራፍ ቻላቸው አዱኛ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ሠራዊቱ ለአቅመ ደካማ አርሶ አደሮች ሰብል የማረም ድጋፍ አደረገ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም በሰሜን ምዕራብ ዕዝ አንድ ክፍለ ጦር በሰቲት ሁመራ  ቃብቲያ አካባቢ ለሚገኙ አቅመ ደካማ አርሶ አደሮች የሰብል አረም ድጋፍ አድርገዋል። የክፍለጦሩ አባላት ከግዳጃቸው ጎን ለጎን በአካባቢው ለሚገኙ 12 እማወራና አባ ወራዎች የሰብል አረም በማረም ድጋፍ ስለማድረጋቸው የክፍለ ጦሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ጀዋር ዴኮ ገልፀዋል። ሠራዊቱ በየትኛውም ግዳጅ ላይ ሆኖ ህብረተሰቡን የማገዝና የመደገፍ ባህል ያለው ነው ያሉት ኮሎኔል ጀዋር ዴኮ በግዳጅ ወቅት ከጎናችን ሆኖ ለሚደግፈን ህዝባችን የምናደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል። በስራው ለይ የተሳተፉ የሠራዊት አባላትም ከግዳጃችን ጎን ለጎን በልማታዊ ስራ ላይ በመሳተፋችን ደስታ ተሰምቶናል ቀጣይም በማንኛውም የድጋፍ ስራ ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን ብለዋል። የሰብል ማረም ድጋፍ ከተደረገላቸው እማወራዎች መካከል ወይዘሮ አልጋነሽ ግሸን ፣ ወይዘሮ ፅርይቲ አየለና ወይዘሮ ሰላም አያሌው ሠራዊታችን ለህዝቡ ያለውን ፍቅርና ክብር በተግባር ያሳየ ፤ፀሃይና ብርድ ሳይበግረው ግዳጅ የሚወጣ መከታችን በመሆኑ እናከብረዋለን ሁልጊዜም ከጉኑ ነን ሲሉ ተናግረዋል። ዘጋቢ ተፈሪ እንዳለ ፎቶግራፍ ሳምሶን ሚሊዮን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የዕዙ ኮር ያሠለጠናቸውን የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና ሙያተኞች አስመርቋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 06 ቀን 2018 ዓ.ም በህክምና ሙያተኞች የምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የኮሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አብርሃም ሞሲሳ ሠልጣኞች ክቡር የሆነውን የህክምና ሙያ በሚገባ ሰልጥናችሁ ለምርቃት በመብቃታችሁ ልትደሰቱ ይገባል ብለዋል። የስልጠናውን ሪፖርት ያቀረቡት የኮሩ ህክምና ቡድን ሀላፊ ሌተናል ኮሎኔል የማነ አባዲ ተመራቂ የሰራዊቱ አባላት በመጀመሪያ ደረጃ ህክምና ብቁ የሚያደርጋቸውን የትምህርትና የተግባር ስልጠና መውሰዳቸውን ገልፀዋል። ተመራቂ የሰራዊቱ አባላት በበኩላቸው በወሰዱት ስልጠና ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው በቀሰሙት ዕውቀትና ልምድ በመጠቀም ተቋማቸውንና ሀገራቸውን በሚገባ ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዘገባው የኮሩ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

በጅማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የእግር ኳስ ውድድር በማዕከላዊ ዕዝ አሸናፊነት ተጠናቀቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የጅማ ከተማ ስፖርት ፅህፈት ቤት ያዘጋጀውና በአስር የግልና የመንግስት ተቋማትን በማሳተፍ ሲካሄድ የቆየው የጤና ስፖርት የእግርኳስ ውድድር በማዕከላዊ ዕዝ ጤና ስፖርት ቡድን አሸናፊነት ተጠናቋል ። ውድድሩ በሁለት ምድቦች ተከፍሎ ለወራት የተካሄደ ሲሆን ሠራዊቱን የወከለው የዕዙ ጤና ስፖርት ቡድን በየዙሩ ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ አቻ ተለያይቶ ቀሪ ጨዋታዎችን በሰፊ የጎል ልዩነት እያሸነፈ የመጣ ሲሆን የፍፃሜ ጨዋታውን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የዋንጫና ሰርተ-ፊኬት ሽልማቱን ያበረከቱት የጅማ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ኢንጅነር መሃመድ ሳኒ የህዝብ መከታና የሀገር ወዳድነት ምሳሌ የሆነው ሠራዊታችንን የወከለው የዕዙ ስፖርት በድን በፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነትና ዲሲፕሊን ከውድድሩ ጅማሮ እስከ ፍፃሜው ድረስ ላሳየው አርዓያነት የላቀ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል። የማዕከላዊ ዕዝ ስፖርት ከፍል ሃላፊ ሻለቃ ኤልያስ ታፈሰ ውድድሩን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ይህን መሰል ስፖርታዊ መድረክ ፈጥሮ ውድድሩ እንዲካሄድ ላደረገው የከተማው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምስጋና አቅርበው በውጤቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል። የፍፃሜ ጨዋታውን ከቀዩ ፊትነስ ስፖርት ቡድን ጋር ያደረገው የዕዙ ጤና ስፖርት ቡድን መደበኛ የጨዋታ ጊዜውን አንድ አቻ አጠናቆ በመለያ ምት 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎ የውድድሩን ዋንጫ ወስዷል። ዘጋቢ ዮሴፍ ጉርቢያው ፎቶግራፍ ሚኪያስ እስክንድር የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አስከብሮ ለማስቀጠል ሀገራዊ ኢኮኖሚን እና ወታደራዊ አቅምን ማጠናከር ያስፈልጋል፦     አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ አቶ ጌታቸው ኃይለማሪያም ኢንዱስትሪው ከተቋሙ በተሰጠው የተልዕኮ አቅጣጫ መሰረት የሰራዊታችንን የማድረግ አቅም ለማጠናከር ወታደራዊ ትጥቆችን በማምረት በማደሥና በማዘመን ሀገር የሚያኮራ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የአለም የፍትህ ሚዛን በጉልበተኞች እጅ በወደቀበት ሰዓት ወታደራዊ አቅምን ማሳደግ የህልውና ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አሥፈፃሚው ለዚህ ይረዳ ዘንድ ኢንዱስትሪው ዘመኑን የሚመጥኑ የተለያዩ ወታደራዊ ትጥቆችን እየመረተ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በበጀት ዓመቱ ለሰው ሀይል የአቅም ግንባታ ስራ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱ አሁን ለተገኘው ሁሉን አቀፍ ውጤት አሥተዋፅኦው ከፍ እንዲል ያሥቻለ መሆኑ እና ከነባር የማምረቻ ፋሲሊቲዎች በተጨማሪ አዳዲስ የወታደራዊ ትጥቆች ማምረቻ ግንባታዎች በትኩረት የተሰሩበት ዓመት እንደነበር በሪፖርቱ ተመላክቷል። ይህ ሥኬትም ዘመኑን የዋጁ የጦር መሳሪያዎችን እንድናመርት ከማድረጉ ባሻገር  ጦርነትን በሩቁ ለማስቀረትና ጠላቶቻችን ቆም ብለው እንዲያሰቡ የሚያደርግ መሆኑን አንስተዋል። የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ግሩፕ ውጤታማነትና ጥንካሬ የሚለካው ከመንግሰት በሚያገኘው በጀት ብቻ ሳይሆን የራሱን የገቢ አማራጮች በማፈላለግ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረትም ነው። በዚህም ከአፍሪካ ሀገሮች ጋር ውል በመፈፀም ወታደራዊ ትጥቆቻቸውን በመጠገንና አምርቶ በመሸጥ ገቢን ማሣደግ ተችሏል። አቶ ጌታቸው ኃይለ ማሪያም ግሩፑ እያሥመዘገበ ላለው ውጤት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አብይ አህመድና የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ሚናቸው የጎላ እንደነበር አንስተዋል። የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ግሩፕ ምክትል ስራ አስፈፃሚና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ብርጋዲየር ጀነራል ዮሃንስ ትኬሳ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ዋናውን ተልዕኮ ከመወጣት ባሻገር ለተለያዬ አገልግሎት የሚውሉ የኮሜርሻል ምርቶች ማለትም የህዝብ መጓጓዣ አውቶብሶችን ፣ የተለያዬ ሞዴል ያላቸው መኪናዎችን በማምረት ገቢውን እያሳደገ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ ኢንዱስትሪ ግሩፑ ወታደራዊ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬን ገቢ በማስገኘት ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ደጋፊ መሆን እንደቻለም ብርጋዲየር ጄኔራል ዮሃንስ ትኬሳ ገልፀዋል።  በዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ውይይት ላይ የተሳተፉት አመራሮች በበኩላቸው በተገኘው ውጤት ደስ መሰኘታቸውን ገልፀው በቀጣይ የስራ ዘመን የግሩፑን ፍላጎት ለማርካትና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ፈጠራና የቴክኖሎጅ ዝማኔ ላይ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ብለዋል። በመጨረሻም በ2019 በጀት ዓመት የሥራ እቅድ ላይ ወይይት ተደርጎ የአፈፃፀም አቅጣጫ ተቀምጧል። ዘጋቢ ማሩ ግርማይ ፎቶግራፍ ፉራ አብደላ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

ፅንፈኛው ካምፕ አድርጎት የነበረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የፅንፈኛው ቡድን ማረፊያ ካምፕ አድርጎት የነበረውን የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለ ሐይማኖት አውሮፕላን ማረፊያን ከጠላት በማፅዳት ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ሜጄር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ገልፀዋል። አውሮፕላን ማረፊያው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድን (ዶክተር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል። ከ30 ዓመታት በፊት ተቋርጦ የነበረው አውሮፕላን ማረፊያው በዘመናዊ መልክ ግንባታው ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም ባለፉት አራት ዓመታት በፀጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ ቆይቷል። ነገር ግን መከላከያ ሠራዊቱ የልማት አደናቃፊ የሆነውን ፅንፈኛ ቡድን በማፅዳት አካባቢውን ሠላም በማድረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ይህ የአውሮፕላን ማረፊያ እውን እንዲሆን ሠራዊቱ ታላቅ መስዋዕትነት የከፈለበት ነው ያሉት የ6ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ብርሃኑ ጥላሁን ቦታው ከዓመታት በፊት ጠላት ማረፊያ ካምፑ አድርጎት እንነደነበረና ቦታውን ሠራዊቱ ተዋግቶ ያፀዳበት ሁኔታ እንዳለ አሥረድተዋል። 6ኛ ዕዝ ተሠማርቶ በሚገኝበት ቀጠና ሁሉ የተላላኪዎችን የሽብር ተልዕኮ መና እያደረገ ሕብረተሰቡ በሠላም ወጥቶ እንዲገባ እየሠራ እንደሚገኝ የገለፁት አዛዡ ልማት ጠል የሆነው ፅንፈኛው ቡድን መሠረተ ልማቶች እንዳይለሙ ሙኩራ ቢያደርግም የሕዝብ ልጅ የሆነው መከላከያ ግን ልማት እንዲቀጥል ማድረጉን ተናግረዋል። ዕዙ በምሥራቅ ጎጃምና አካባቢው ከተሠማራ ወዲህ የጥፋት ቡድኑ ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሆን የከፈተውን ውጊያ ማምከን የቻለ ሲሆን የጠላት ምኞትም ህልም ሆኖ መቅረቱን ገልፀዋል። ሠራዊቱ ባይኖር ኖር ደብረ ማርቆስና አካባቢው የሠላምን አየር አይተነፍሱም ነበር ያሉት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ መከላከያ ባስገኘልን ሠላም ፊታችንን ወደ ልማት አዙረናል ብለዋል። ሕብረተሰቡም ለዓመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የአየር ትራንስፖርት እውን ሆኖ በማየቱ ደስታውን የገለፀ ሲሆን ለዚህ ስኬትና ሠላም መረጋገጥ ትልቁን ድርሻ ለተወጣው መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ዘጋቢ ውብሸት አንበሴ ፎቶግራፍ ገነት አወቀ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ የውጊያ ድጋፍ ሙያ የሠለጠኑ ሙያተኞችን አሥመረቀ፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 05 ቀን 2018 ዓ.ም የሜካናይዝድ ዕዝ በተለያዬ ሙያ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት  አስመርቋል፡፡ በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሜካናይዝድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ከፍያለው አምዴ የዕዙን ሠራዊት ለማዘመን ከተለመደው አሰራር ለመውጣት ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች መጠቀም እና ዕቅድ በመንደፍ ዝግጁነትን የማጠናከር ሥራ እየተሠራ ነው። ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ታሪክና ሥርዓተ መንግስት ያላት፣ ነፃነቷንና ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ የኖረች ሀገር መሆኗን የጠቀሱት አዛዡ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያ በራሷ በተፈጥሮ ሀብቷ ሰርታ እዳትለወጥ ያለ እረፍት ቢሰሩም ሴራቸውን ለማክሸፍ ዝግጁነታችን  ከምንጊዜም በላይ አጠናክረን እንቀጥላለንም ብለዋል፡፡ ጀግኖች አባቶቻችን በመሥዋዕትነት ያፀኗትን እና ከነ ሙሉ ክብሯ ያስረከቡንን ታላቅ ሀገር ለትውልድ ጠብቃችሁ በክብር ማሻገር ይጠበቅባችኋል ሲሉ ለተመራቂዎች አሥገንዝበዋል። የማሰልጠኛ ማዕከሉ አዛዥ ኮሎኔል አየለ ወልደ ጊዮርጊስ በበኩላቸው ዕዙ እንደ ዕዝ ራሱን ካደራጀ ማግስት ጀምሮ ሀገርና ህዝብን በሚመጥን መልኩ የሚሰጠውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ብቃት ሊፈፅም  የሚችል የሀገር ኩራት የሆነ የሜካናይዝድ ድጋፍ ሰጪ ሙያተኛ እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል። ዘገባው የዕዙ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ https://dfmc.mod.gov.et/ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት  ቴሌግራም  https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official