en
Feedback
FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Open in Telegram

# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

Channel FDRE Defense Force - የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (@fdredefenseforc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 42 495 subscribers, ranking 6 062 in the News & Media category and 802 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 42 495 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -337 over the last 30 days and by -29 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.98%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.88% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 668 views. Within the first day, a publication typically gains 3 349 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 36.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
# ቁልፍ እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

42 495
Subscribers
-2924 hours
-1067 days
-33730 days
Posts Archive
   በቃሉ የፀና፣ ለሀገር የቆመ ጀግና ሠራዊት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ሕዝቦች አብራክ የተገኘ፣ ከህዝብ ማህፀን ምድር የተወለደ፣ የሀገርን ክብር፣ ሉዓላዊነትና ነፃነት ከልቡ የሚያከብር ጀግና  ሠራዊት ነው። የአባቶቹን የጀግንነት ታሪክ በትከሻው ተሸክሞ፣ የትናንቱን ክብር ወደ ዛሬ እና የዛሬውን አደራ ወደ ነገ እያስተላለፈ የሚጓዝ አኩሪና ባለድል ሠራዊትም ነው። በየዘመናቱ ኢትዮጵያን በጽናት የጠበቀ፣ በፈተና ጊዜ ያልተናወጠ፣ በችግር ፊት ያልተሸማቀቀ፣ የተሰጠውን ተልዕኮና ግዳጅ በብቃት፣ በዲሲፕሊንና በጀግንነት የፈጸመ ነው ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጽናት ማለት አለመውደቅ ብቻ አይደለም፤ ቢወድቁም ተነስቶ መቀጠል ነው። ጽናት ማለት ቃል መግባት ብቻ አይደለም፤ ቃሉን በተግባር ማረጋገጥ ነው። ጽናት ማለት ስለሀገር ፍቅር መናገርም ብቻ አይደለም፤ ለሀገር በተግባር መቆም ነው። የሠራዊታችን ጽናት በዚህ እምነት ይገለጻል። በቃሉ ይታመናል፤ በግዳጁ ይፀናል፤ በአደራው ይታመናል። ለሀገር ሲል የሚከፍለው መስዋዕትነት፣ ለሕዝብ ሲል የሚያደርገው ተጋድሎ እና በፈተና ውስጥ የሚያሳየው ጽናት የሀገር አደራን በተግባር የሚያረጋግጥ ምስክር ነው። የጽናት ቀን የሠራዊታችንን የተጋድሎ ታሪክ የምናስታውስበት ብቻ አይደለም። ለሀገር ሲሉ ሕይወታቸውን ለሰጡ ጀግኖች ክብር የምንሰጥበት፣ የተረከብነውን የሀገር አደራ የምናስብበት፣ የዛሬውን ሠራዊት ብርታት እና የነገዋን ኢትዮጵያ የምናስብበት የኩራት፣ የማስታወሻ እና የአደራ ቀን ነው። ሠራዊታችን ለኢትዮጵያ ሲል በጽናት ታግሏል፤ ለሕዝቦቻችን ሰላምና ደህንነት ሲል የሕይወት መስዋዕትነት ከፍሏል። የወደቁት ጀግኖች በሰጡት ሕይወት፣ የቆሙት ጀግኖች በያዙት ቃል እና የሚመጣው ትውልድ በሚረከበው አደራ መካከል የማይቋረጥ የሀገር ታሪክ ተጽፏል። የሠራዊታችን ጽናት በጦር ሜዳ ብቻ የሚመዘን አይደለም። ሀገርን በሰላም ማስቀጠል፣ የሕዝብን ደህንነት መጠበቅ፣ ሉዓላዊነትን ማስከበር፣ ሀገራዊ እድገትና ልማት በሰላም እንዲቀጥል የሚያስፈልገውን ምቹ ሁኔታ ለማስጠበቅ በሚደረገው ተጋድሎም ይገለጻል። ዛሬ የጽናት ቀንን ስናከብር፣ የትናንቱን ጀግንነት ብቻ አንዘክርም። የነገዋን ኢትዮጵያ በጽናት፣ በአንድነት፣ በሰላምና በሀገር ፍቅር ለመገንባት ያለብንን የጋራ አደራ እናድሳለን። ምክንያቱም ሀገር በአንድ ትውልድ ብቻ አትገነባም፤ በትውልድ ትውልድ በሚተላለፍ አደራ ትጠነክራለች። የትናንቱ ጀግንነት የዛሬ ብርታታችን ነው፤ የዛሬው ጽናት የነገው ተስፋችን ነው፤ የነገው ተስፋ ደግሞ የኢትዮጵያ ዘላለማዊ ጉዞ ነው። ጀግናው ሠራዊታችን ቃሉን ያድሳል፤ ለቃሉ ይታመናል። በቃል ኪዳኑ ይፀናል፤ ሀገርንም አፅንቶ ወደ ከፍታዋ ያሻግራል። በይታያል ምህረት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

ማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ ለአቅመደካማ አረጋዊያን  የቁሣቁሥ ድጋፍ አደረገ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም የብርሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት መጭው 2019 ዓ/ም አዲሱን ዓመት ምክኒያት በማድረግ በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢ ጠህናን ወረዳ በቀበሌ ተወካይ ለተመረጡ 15 አካል ጉዳተኛና አረጋዊያን የቁሳቁሥ ድጋፍ ማድረጉን የማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ ምክትል አዛዥ ለሎጀስቲክስ ሐላፊ ኮለኔል ጌቱ ወርቁ ተናግረዋል። የተደረገላቸው ድጋፍ ብርድ ልብስ ፣ፊኖ ዱቄትና ሥኳር ሲሆን ጊዜያዊ ችግራቸውን እንደሚቀርፍላቸው ጠቅሰው ከራስ በፊት ለህዝብ የሚለውን የተቋማችንን እሴት በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። ድጋፍ ከተደረገላቸው መካከል ወይዘሪት ሽማጫሽ ውበቱና ወይዘሮ አትክልት ታደሠ ሠራዊቱ በዝናብና በብርድ ሣይታክት ሠላማቸውን ከመጠበቅ በተጨማሪ በየጊዜው ለተቸገሩ ወገኖች ለይቶ በመርዳቱ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ዘጋቢ አረቡ ሠይድ ፎቶግራፍ ጥላሁን ጌታነህ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

ክፍለጦሩ ለአቅማ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ዩኒፎርም ድጋፍ አደረገ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ዕዝ የዋልታ ክፍላጦር አዛዥ ኮሎኔል ጌታቸው ወደጄ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አባይ ጮማን ወረዳ ለሚገኙ አቅማ ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ዩኒፎርም አበርክተዋል። ድጋፉ በአካባቢው በኢኮኖሚ ደካማ ለሆኑ ቤተሰቦች የሚገኙ ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ የሚያጋጥማቸውን የቁሳቁስ እጥረት በማቃለል፣ በትምህርታቸው የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ለማበረታታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ተመሪዎች የሀገር የነገ ተስፋ መሠረት በመሆናቸው፣ የተቸገሩ ተማሪዎችን መደገፍ የተማሪዎቹን የትምህርት ጉዞ ከማሳለጥ ባለፈ በአካባቢው የትምህርት ተሳትፎን ለማሳደግ ወሳኝ ሚና አለው ስሉም አዛዡ ተናግረዋል። የአባይ ጮማን ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሶሪ ፋራዳ ሠራዊቱ ህይዎቱን መስዋዕት አድርጎ ሀገር ከመጠበቅ ባሸገር ለህዝቡ እና ለቀጣይ ትውልድ ተስፋ ስጭ ተግባር በመፈፀሙ ምስጋና አቅርበዋል። ዘጋቢ ሁሴን ጀማል ፎቶግራፍ ሃብታሙ ሁሴን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የኢትዮጵያ ባህር ሃይል የስፖርት ውድድር መክፈቻ በቢሾፍቱ፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ባህር ሃይል የአባላቱን አካላዊና አእምሯዊ ዝግጁነት ለማሳደግ እንዲሁም የወንድማማችነት መንፈስን ለማጠናከር ያለመ ዓመታዊ የስፖርት ውድድር ቢሾፍቱ በሚገኘው ማሰልጠኛ ማዕከል ማስጀመሩን አስታውቋል። በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ካፒቴን ተዘራ በቀለ ስፖርት ለባህር ሃይል አባላት የአካልና የአእምሮ ብቃትን ለመጠበቅ የመከላከያ ሰራዊቱ መሰረታዊ አካል መሆኑን ገልጸው፣ ሁሉም ተወዳዳሪዎች የስፖርታዊ ጨዋነትን መመሪያ በመከተል ውድድር ማድረግ እንደሚገባቸው ጠይቀዋል። ውድድሩ በሚቀጥሉት ቀናት በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ በማጠናቀቂያው ስነ-ስርዓት ላይ አሸናፊ ለሆኑ ቡድኖችና ተወዳዳሪዎች የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት እንደሚበረከት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዘጋቢ ዳንኤል ደስታ ፎቶግራፍ አዱኛ ዳቢ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የፅናት ቀን የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ለሀገር ሰላምና ልማት እያበረከቱ ያሉትን አስተዋጽኦ የሚያሳይ ነው።      ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጳጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም የፅናት ቀን የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ለሀገር ሰላም፣ ደህንነትና ልማት እያበረከቱ ያሉትን አስተዋጽኦ ለመላው ሕዝብ ለማስተዋወቅ የሚያስችል አጋጣሚ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ገለጹ። ምክትል ኮሚሽነሩ የፅናት ቀንን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ዝግጅቱ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አስተዳደር፣ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አስተዳደር እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በጋራ የሚያዘጋጁት መሆኑን ጠቁመዋል። ሀገራችን በጀመረችው የማንሰራራት ጉዞ የዕድገትና የልማት ግቦችን ለማሳካት ሰላምና ደህንነት መሠረታዊ ጉዳይ በመሆኑ፣ የፀጥታ ተቋማት የሚወጡት ሚና ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በጠንካራ ሕዝባዊ መሠረት ላይ ተገንብቶ ከዘመኑ ጋር የዘመነ አቅም በመገንባት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት፣ ብሄራዊ ጥቅምና አንድነት ለመጠበቅ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል። ሠራዊቱ የአየርና የየብስ ግዛትን በመጠበቅ፣ ሀገረ-መንግሥትንና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ከሚያጋጥሙ ስጋቶች በመከላከል እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች በመሳተፍ የሀገሪቱን ስም እያስጠበቀ መሆኑንም አክለዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በበኩሉ የሕግ የበላይነትንና ሰላምን በማስፈን፣ ዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል፣ ወሳኝ ተቋማትንና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመጠበቅ ለሀገራዊ ሰላምና ፀጥታ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነሩ ጠቅሰዋል። በዘመናዊው የፀጥታ ሥራ የመረጃ፣ የሳይበር ደህንነትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሚና እየጨመረ መምጣቱን ያመለከቱት ምክትል ኮሚሽነሩ፣ የሀገሪቱን ወሳኝ ዲጂታል መሠረተ ልማቶች ከሳይበር ጥቃቶች መጠበቅና የዲጂታል ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የዘመኑ የፀጥታ ሥራ ዋና አካላት መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስንና ሌሎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ከፀጥታ ሥራ ጋር በማስተሳሰር የሀገሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመፍታት፣ የፀጥታ ሥራን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገው ሥራ መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል። የፅናት ቀን በዚህ መልኩ የፀጥታ ተቋማት የሚያከናውኗቸውን ሥራዎችና የሚያስመዘግቧቸውን ውጤቶች ለሕዝብ ለማስተዋወቅ፣ የተቋማትን ቅንጅት ለማጠናከርና ለሀገራዊ ሰላምና ልማት የሚያበረክቱትን ድርሻ ለማጉላት ጠቃሚ መድረክ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ገልጸዋል። ዘጋቢ ብዙአየሁ ተሾመ ፎቶግራፍ አበረ አየነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የበዓል ወቅት የሳይበር ጥንቃቄ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም በበዓላት ወቅት የገንዘብ ዝውውር እና የሸመታ ፍላጎት ስለሚጨምር፣ የሳይበር ወንጀለኞች ይህንን አጋጣሚ ለጥቃት ይጠቀሙበታል። ሰዎች በደስታ እና በችኮላ ላይ ስለሚሆኑ፣ የሚላኩላቸውን የማታለያ መልእክቶች በጥልቀት ሳይመረምሩ የመቀበል እድላቸው ከፍተኛ ነው። አጭበርባሪዎች "ትልቅ ሽልማት አሸንፈዋል" በሚሉ መልእክቶች የግል እና የባንክ መረጃዎችን ለማግኘት ይሞክራሉ። እንዲሁም፣ የሐሰት ማስፈንጠሪያዎችን (Phishing Links) በመላክ የይለፍ ቃላትን እና የባንክ አካውንት መረጃዎችን ይሰርቃሉ። "ቅናሹ ሊያበቃ ነው፣ ይፍጠኑ..." በሚል የችኮላ ስሜት በመፍጠርም ገንዘብ እንዲላክላቸው ያደርጋሉ። ራሳችንን ለመጠበቅ፣ ያልተረጋገጡ የሽልማት እና የቅናሽ መልእክቶችን እንዲሁም አጠራጣሪ ሊንኮችን ፈጽሞ አለመጫን ያስፈልጋል። የክፍያ ጥያቄዎችን ትክክለኛነት በስልክ ወይም በይፋዊ መተግበሪያዎች ማረጋገጥ እና የባንክ መለያዎችን በሁለት ደረጃ ማረጋገጫ (Two-Factor Authentication) ማጠናከር አስፈላጊ ነው። የግል ሚስጥራዊ ቃላትን (PIN/Password) ለማንም አሳልፎ አለመስጠትም አስተማማኝ ጥንቃቄ ነው። የመከላከያ የሳይበር ማዕከል የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የማንሠራራት ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥ
+1
        የማንሠራራት ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የማንሠራራት ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥ
        የማንሠራራት ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

በ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ሲካሄድ የቆየው ስፖርታዊ ውድድር ተጠናቀቀ።         የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 01 ቀን 2018 ዓ.ም በ7ተኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ሻለቆች እና ስታፍ መምሪያዎች መካከል ሲካሄድ የቆየው የስፖርት ውድድር የክፍለ ጦሩ አመራሮችና ሲቪል አመራሮች በተገኙበት ፍፃሜውን አግኝቷል።         ውድድሩ በእግር ኳስ፣ በመረብ ኳስ፣ በተኩስ፣ በቴንስና በገመድ ጉተታ የተካሄደ ሲሆን አሸናፊ ቡድኖች ኮከብ ተጫዋች፣ ኮከብ ግብ አግቢ እና የ5ኪሎ ሜትር ሩጫ አሸናፊዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል። የ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ፎቶ ይሰማው በስፖርት የዳበረ ሠራዊት የድል ባለቤት መሆኑ የማይቀር መሆኑን ገልፀው ስፖርት በፍቅር በወዳጅነት እና በመተሳሰብ ከተካሄደ ይበልጥ የጋራ አንድነትን እንደሚፈጥር አሥረድተዋል። ዘገባው የክፍለ ጦሩ የሠራዊት ስነ ልቦና ግንባታ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

ዕዙ በተለያዬ የሙያ ዘርፍ ያሠለጠናቸውን ሙያተኞች አሥመረቀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 01 ቀን 2018 ዓ.ም 10ኛ ዕዝ በሎጀስቲክስ፣ በሰው ሃብት አመራር፣ በፋይናንስ ስራ አመራር እና በበጀት ሙያ ሲሰለጥኑ የቆዩ ሙያተኞችን አሥመርቋል። በስልጠናው ማጠቃለያ የተገኙት የ10ኛ ዕዝ ሎጅስቲክ ኃላፊ ኮሎኔል አወል ሀሠን የሙያተኞችን አቅም በስልጠና ማሳደግ የውጊያ ድጋፍን የሚያሳልጥ ዋና መሣሪያ በመሆኑ በምታገኙት ክፍተት ሁሉ ራሳችሁን ማብቃት  ይገባል፤ በሰልጠና ያገኛችሁትን እውቀትም ወደ ተግባር በመቀየር የተሠጣችሁን ግዳጅ በብቃትና በሀላፊነት መወጣት አለባችሁ ብለዋል። የ10ኛ እዝ ፋይናንስ ስራ አመራር ኃላፊ ኮሎኔል ፍፁም ወልዴና የሠው ሃብት አመራር ኃላፊ ኮሎኔል አማረ ደምሴ በበኩላቸው ሰልጣኞች በነበራቸው ቆይታ በመከላከያ ሙያተኞችና በውስጥ አቅም የተከናወነው ስልጠና በንድፈ-ሓሳብና በተግባር የተደገፈ መሆኑን ገልፀው ሠልጣኞች በሚከውኑት የእለት ተእለት የድጋፍ አሠጣጥ ሥራዎቻቸው ላይ  ያሉባቸውን ክፍተቶች የሚፈታ ስልጠና መሆኑ ገልፀዋል። በስልጠናው የተሳተፉት ሠልጣኝ አባላትም በስልጠናው ካላቸው እውቀት ባሻገር  የተሻለ ግንዛቤ እንደፈጠሩ ገልፀው ያገኙትን እውቀት፣ ክህሎትና ተሞክሮ  ወደ ተግባር በመቀየርና በአሃዱዎቻቸው ተግባራዊ ማድረግ የሚጠበቅባቸው መሆኑን አንስተዋል። ዘገባው የ10ኛ እዝ የሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official

የአሽከርካሪዎችን ብቃት በማረጋገጥ የትራፊክ አደጋን ማሰወገድ እንደሚገባ ተገለፀ። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 01ቀን 2018 ዓ.ም የአሽከርካሪዎችን ብቃት በማረጋገጥና የተሽከርካሪ ደህንነት በመጠበቅ የትራፊክ አደጋን ማሰወገድ እንደሚገባ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ትራንስፖርት ኃላፊ ኮሎኔል ታደለ ገረመው ተናገሩ። የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ትራንስፖርት በትራፊክ አደጋ መንስኤዎችና በመፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ለዕዙ አመራሮች ሰጥቷል። አመራሩ የአሽከርካሪዎችንም ሆነ የተሽከርካሪዎችን ደህንነት የመከታተል፣የመቆጣጠርና ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን የመቆጣጠር ኃላፊነት አለበት ያሉት ኮሎኔል ታደለ ገረመው በቸለልተኝነት ጥፋት በሚፈፅሙት አሽከርካሪዎችም ተገቢውን የእርምት እርምጃ በመውሰድ ማስተማር ይገባልም ብለዋል። አሸከርካሪዎች ውድ የሆነውን የሰው ህይወትና ከፍተኛ ሃብት የወጣበት የተቋሙን ንብረት የሚያጓጉዙ በመሆናቸው የጥንቃቄ ደንቦችን ማሟላታቸውን ማረጋገጥ የሁሉም አመራር ኃላፊነት ስለመሆኑም ተናግረዋል። የዕዙ ትራንስፖርት ብቁ አሽከርካሪዎችን ለማፍራት ከመከላከያ ትራንስፖርትና ከአዋሽ የውጊያ ቴክኒክ ትምህርት ቤት የወታደራዊ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ጋር በመተባበር ስልጠና በመስጠት አደጋዎችን ለመቀነስ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል። ዘጋቢ አለምፀሃይ ተሾመ ፎቶግራፍ አበራሽ ተሰፋዬ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት https://dfmc.mod.gov.et/ https://youtube.com/@fdredefenseforce-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2 https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0 https://www.facebook.com/fdredefense.official