en
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

Open in Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Fresh መረጃ | FreshNews

Channel Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 55 204 subscribers, ranking 3 077 in the Education category and 596 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 55 204 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -908 over the last 30 days and by -66 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 4.11%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.26% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 268 views. Within the first day, a publication typically gains 1 800 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

55 204
Subscribers
-6624 hours
-4607 days
-90830 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '260
in 2 channels
August '26
+304
in 8 channels
Get PRO
July '26
+1
in 9 channels
Get PRO
June '26
+2
in 8 channels
Get PRO
May '260
in 8 channels
Get PRO
April '26
+3
in 8 channels
Get PRO
March '26
+1 303
in 14 channels
Get PRO
February '260
in 4 channels
Get PRO
January '260
in 0 channels
Get PRO
December '250
in 2 channels
Get PRO
November '25
+1
in 6 channels
Get PRO
October '250
in 4 channels
Get PRO
September '250
in 3 channels
Get PRO
August '250
in 1 channels
Get PRO
July '250
in 2 channels
Get PRO
June '250
in 6 channels
Get PRO
May '250
in 2 channels
Get PRO
April '250
in 2 channels
Get PRO
March '250
in 10 channels
Get PRO
February '250
in 18 channels
Get PRO
January '25
+44
in 10 channels
Get PRO
December '24
+1 502
in 16 channels
Get PRO
November '24
+4 897
in 9 channels
Get PRO
October '24
+10 897
in 6 channels
Get PRO
September '24
+13 478
in 5 channels
Get PRO
August '24
+17 234
in 5 channels
Get PRO
July '24
+9 021
in 5 channels
Get PRO
June '24
+20
in 7 channels
Get PRO
May '24
+351
in 14 channels
Get PRO
April '24
+847
in 16 channels
Get PRO
March '24
+558
in 33 channels
Get PRO
February '24
+1 785
in 15 channels
Get PRO
January '24
+3 011
in 18 channels
Get PRO
December '23
+3 094
in 23 channels
Get PRO
November '23
+730
in 120 channels
Get PRO
October '23
+13 017
in 37 channels
Get PRO
September '23
+26 548
in 0 channels
Get PRO
August '23
+2 062
in 0 channels
Get PRO
July '23
+2 838
in 0 channels
Get PRO
June '23
+554
in 0 channels
Get PRO
May '23
+672
in 0 channels
Get PRO
April '23
+1 658
in 0 channels
Get PRO
March '23
+3 193
in 0 channels
Get PRO
February '23
+1 734
in 0 channels
Get PRO
January '23
+895
in 0 channels
Get PRO
December '22
+1 925
in 0 channels
Get PRO
November '22
+642
in 0 channels
Get PRO
October '22
+99
in 0 channels
Get PRO
September '22
+547
in 0 channels
Get PRO
August '22
+1 026
in 0 channels
Get PRO
July '22
+1 241
in 0 channels
Get PRO
June '22
+1 528
in 0 channels
Get PRO
May '22
+2 018
in 0 channels
Get PRO
April '22
+329
in 0 channels
Get PRO
March '22
+370
in 0 channels
Get PRO
February '22
+390
in 0 channels
Get PRO
January '22
+639
in 0 channels
Get PRO
December '21
+596
in 0 channels
Get PRO
November '21
+736
in 0 channels
Get PRO
October '21
+1 209
in 0 channels
Get PRO
September '21
+1 351
in 0 channels
Get PRO
August '21
+1 280
in 0 channels
Get PRO
July '21
+1 459
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September0
06 September0
05 September0
04 September0
03 September0
02 September0
01 September0
Channel Posts
ለአዲስ አመት ከ4 ሺህ በላይ የእርድ እንስሳትን እንደሚያቀርብ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታወቀ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የዘንድሮውን የአዲስ አመት በዓል አስመልክቶ በዛሬው እለት ለመገና
ለአዲስ አመት ከ4 ሺህ በላይ የእርድ እንስሳትን እንደሚያቀርብ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታወቀ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የዘንድሮውን የአዲስ አመት በዓል  አስመልክቶ በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥቷል። የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮሚሽነር አህመድ መሀመድ ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ተቋሙ በመጪው የአዲስ ዓመት በዓል 4 ሺህ 500 የቁም የእንስሳትን እርድ  ለማከናወን  ዝግጅት አጠናቋል። ከእነዚህም መካከል ከ3 ሺህ በላይ በሬዎች እና ከ1 ሺህ 500 በላይ በግና ፍየሎች እርድ እንደሚከናወን ተገልጿል።   የከተማዋ ነዋሪዎችም በግና ፍየልን በ300 ብር፣ እንዲሁም በሬዎችን ደግሞ በ2ሺ 100 ብር የቄራ የእርድ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የተጠቀሰው። ሕብረተሰቡ ጥራታቸውና ደህንነታቸው የተጠበቁ ሥጋዎችን  እንዲያገኝ ወደ ቄራዎች ድርጅት መምጣት እንደሚገባው ጥሪ ቀርቧል። በበዓሉ የአቅርቦት እጥረት እንዳይኖር እና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከል በአዲስ አበባ በሚገኙ የሸማቾች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች 1 ኪሎ የበሬ ሥጋ 1 ሺህ 200 ብር ሆኖ ለሽያጭ እንደሚቀርብ ተቋሙ ገልጿል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

2
የዶናልድ ትራምፕ አዲስ የፀጉር ቀለም በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆነ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በኒው ጄርሲ አውሮፕላን ማረፊያ ከፕሬዝዳንታዊው አውሮፕላን ኤር ፎርስ ዋን ሲወር
የዶናልድ ትራምፕ አዲስ የፀጉር ቀለም በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆነ ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በኒው ጄርሲ አውሮፕላን ማረፊያ ከፕሬዝዳንታዊው አውሮፕላን ኤር ፎርስ ዋን ሲወርዱ የታዩበት አዲስ ገጽታ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ​በፎቶዎቹ ላይ የፕሬዝዳንቱ ፀጉር ከተለመደው ቢጫ ቀለም ይልቅ ወደ ቡናማነት ያደላ ጠቆር ያለ ሆኖ በመታየቱ በርካታ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ልዩ ልዩ ግምቶችንና ቀልዶችን ሲሰነዝሩ ውለዋል። አንዳንዶች "ትራምፕ አሁን ጠይም ሆነዋል" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ ከታዋቂው ተዋናይ ብራድ ፒት ጋር አወዳድረውታል። ​ትራምፕ የዊግ ጥያቄን ቀደም ብለው አስተባብለው የነበረ ቢሆንም፣ የፀጉራቸው ቀለምና ቅርጽ በአጭር ጊዜ ውስጥ መለዋወጥ የህዝቡን ትኩረት መሳቡ አልቀረም። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ፀጉራቸው ቀለል ያለና ወፍራም ሆኖ መታየቱ ይታወሳል። @Addis_News @Addis_News
953
3
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ:: በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል።
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ:: በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል። በጥናቱ መሰረት ከ15 እስከ 24 በሚሆን የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ወጣቶች የሱስ ተጠቂ መሆናቸዉ ተረጋግጧል ሲሉ በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር አስካለማሪያም ቢክስ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ። እንደ ዶክተር አስካለማሪያም ገለፃ በወጣቶች ዘንድ የአልኮል ተጠቃሚነት ሱስ ከፍተኛዉን ድርሻ ይይዛል ። ሲጓራ እና ጫትን ጨምሮ ለማስታገሻነት በጥንቃቄ የሚወሰዱ መድኃኒቶችን ወጣቶች ለሱስ እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል ። ወጣቶች ራሳቸዉን ከሱስ ለመጠበቅ እርስ በእርስ መረዳዳት ፣ጊዜያቸዉን ትርጉም ባላቸዉ ነገሮች ላይ ማሳለፍ ፣ስፖርት መስራት እና በሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ መሳተፍ እንዳለባቸዉ ተነግሯል።የሱስ ተጠቂነት የሚያስከትለው ጫና ቀላል አለመሆኑን የሚያስረዱት ስፔሻሊስቷ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ለራሳቸዉ ቅድሚያ በመስጠት ህክምና ማድረግ እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል ። ሱስ በአካል እንዲሁም በአእምሮ ላይ የሚያሳድረዉን ተፅዕኖ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተገንዝቦ ከመፈረጅ ይልቅ በዙሪያው ያሉ የሱስ ተጠቂዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል ። በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል
1 131
4
ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በ
ከማረሚያ ቤት ከተፈታ በሦስተኛ ቀኑ የአምቡላንስ ተሽከርካሪ ቁልፍ የሰረቀው ግለሰብ በጽኑ እሥራት ተቀጣ። ከዚህ ቀደም በተጣለበት የፍርድ ውሳኔ መሠረት በማረሚያ ቤት ቆይታ የእስር ጊዜውን አጠናቆ በወጣ በሦስተኛው ቀን በድጋሚ በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው አቶ ያሬድ ገብረሚካኤል የተባለው ግለሰብ መሆኑ የአክሱም ከተማ ፖሊስ  አስታውቋል። የማዕከላዊ ዞን ዓቃቤ ሕግ ቢሮ እንዳስታወቀው ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ያለችን እህቱን ለመጠየቅ የመጓጓዣ ገንዘብ እንደሌለው በመግለጽ በዓድዋ ከተማ ቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንስ ተሳፍሮ በመጓዝ ላይ በነበረበት ወቅት ነው። ግለሰቡ በተሳፈረበት አምቡላንስ ውስጥ ተቀምጦ የነበረውን የተሽከርካሪውን ቁልፍ ሰርቆ ከተሰወረ በኋላ በጸጥታ አካላት በተደረገ ክትትል በአክሱም ከተማ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።የአክሱም ከተማ ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዉን እጅ ከፍንጅ ይዞ በቁጥጥር ስር በማዋሉ አስፈላጊውን ማጣራት በማጠናቀቅ መዝገቡን ለዓቃቤ ሕግ አቅርቧል። ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤትም ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቀረበበትን የሰነድ እና የሰው ማስረጃ መርምሮ ግለሰቡ በተከሰሰበት የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ6 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እሥራት እንዲቀጣ ወስኖበታል። @Seledadotio @Seledadotio
1 395
5
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሰሰሰበ ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀሌ፣ አክሱም፣ አ
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አሰሰሰበ ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀሌ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግቢ ውስጥ የሚገኙ የጦር ቄስፎች እና ታጣቂዎች በአስቸኳይ እንዲነሱና ግቢዎቹ ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲደረጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ። ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለዩኒቨርሲቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች በላኩት ደብዳቤ፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ ኃይሎችና የትጥቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው የተማሪዎችን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር-ማስተማር ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ አክሎም፣ የዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢዎች ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው በበቂ ሁኔታ ካልተረጋገጠ ሚኒስቴሩ ወደ ተቋማቱ ተማሪዎችን እንደማይመድብ አስታውቋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 524
6
ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ! ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት የተ
ህውሓት የአባሳንጆን የሸምግልና ጥረት ገለልተኝነት እና ተጨባጭ ይዘት ይጎለዋል ሲል ተቸ! ህውሃት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሉሴጉን አባሳንጆ በትግራይ ሰላም ለማውረድ የሚያደርጉትን ጥረት የተቸ ሲሆን፣ አሸማጋይነታቸው «ገለልተኝነት፣ ተጨባጭ ሀሳብ» እና ወደ ትርጉም ያለው ውይይት የሚያመራ ግልጽ መንገድ የጎደለው ነው ሲል ከሰሰ። ህውሃት ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ለሰላማዊ ውይይት ዝግጁ መሆኑን ገልጾ፣ የኦሉሴጉን አባሳንጆ የሰላም ጥረት ከፌደራል መንግሥት ተፅዕኖ ነፃ ስለመሆኑ ጥያቄ አንስቷል። ድርጅቱ ማንኛውም የሰላም ሂደት ወገንተኛ ባልሆነ እና በገለልተኛ አሸማጋይ ሊመራ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል። መግለጫው አባሳንጆ በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ባለሥልጣናት መካከል ውይይት ለማመቻቸት ቀደም ሲል ያደረጓቸውን ጥረቶች ተቃውሟል። ኦሉሴጉን አባሳንጆ ሰኔ 2018 ዓ.ም. በትግራይ ያደረጉትን ጉብኝት እና በአንድ ወይም በሁለት ሳምንታት ውስጥ ለመመለስ ገብተውት የነበረውን ቃል በማስታወስ፣ ሆኖም ከሁለት ወራት በኋላ መመለሳቸውን ጠቁሟል። Via AS @Addis_News @Addis_News
1 435
7
ሩሲያ እና አሜሪካ በዩክሬን ጦርነት እልባትና በሁለተናዊ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልእክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃ
ሩሲያ እና አሜሪካ በዩክሬን ጦርነት እልባትና በሁለተናዊ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልእክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር ጋር ውይይት አደረጉ። ከሦስት ሰዓታት በላይ የፈጀውና በሞስኮ የተካሄደው ይኸው ስብሰባ “ፍሬአማ፣ ገንቢ እና እጅግ ግልጽ” እንደነበር የክሬምሊን ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል ፕሬዝዳንት ፑቲን በሰላም ሂደቱ ውስጥ በአሜሪካን ልዑካን ላይ ከፍተኛ እምነት እንዳላቸው ገልጸው፤ ለፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔዎች ከአሜሪካ ጋር አብሮ ለመሥራት ሩሲያ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል አሜሪካውያኑ ልዑካን በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅተው መቅረባቸውንና ወደ መፍትሔ ሊወስዱ የሚችሉ ሃሳቦችን ማቅረባቸው የተገለጸ ሲሆን በኪዬ በሚያደርጓቸው ቀጣይ ግንኙነቶችም የፑቲንን ግምገማዎች እንደሚጠቀሙባቸው ታውቋል የዕለቱ ውይይት ከዩክሬን ቀውስ ባለፈ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ትብብር እና ሊሠሩ የሚችሉ ግዙፍ የጋራ ፕሮጀክቶችን መቃኘቱ ተገልጿል ልዑካኑ በሞስኮ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ ወደ ኪዬቭ በማቅናት ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ ጋር ዛሬ እሁድ ዕለት እንደሚገናኙ ተረጋግጧል ስለ ልዑካኑ ጉብኝት የተጠየቁት ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም የቀረበ ሀሳብ ይዘው ሄደዋል ማለታቸውን ቢቢሲ አስታውሷል የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መልዕክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር ከዚህ ቀደም ሩሲያን ብዙ ጊዜ ጎብኝተዋል በዩክሬን የሚያደርጉት ውይይት ግን የመጀመሪያው ይሆናል ዜሌንስኪ በልዑካኑ ጉብኝት ወቅት በዩክሬን አየር ክልል ደኅንነታቸው እንደሚጠበቅ ዋስትና ሰጥተው ሩሲያም በተመሳሳይ መንገድ ለልዑካኑ ደኅንነት ዋስትና እንድትሰጥ ጠይቀዋል @Yenetube
1 370
8
አዲዳስ ከእስራኤል ወታደር ጋር ባካሄደው የማስታወቂያ ዘመቻ ተቃውሞ ቀረበበት። የስፖርት ትጥቅ አምራቹ አዲዳስ ከቀድሞ የእስራኤል ወታደር ጋር ያካሄደውን የማስታወቂያ ዘመቻ ተከተሎ ከደንበኞች ለቀረበ
አዲዳስ ከእስራኤል ወታደር ጋር ባካሄደው የማስታወቂያ ዘመቻ ተቃውሞ ቀረበበት። የስፖርት ትጥቅ አምራቹ አዲዳስ ከቀድሞ የእስራኤል ወታደር ጋር ያካሄደውን የማስታወቂያ ዘመቻ ተከተሎ ከደንበኞች ለቀረበበት ተቃውሞ እና የሰፊ ማዕቀብ ጥሪዎች ተጋልጧል። ኩባንያው "ሲንግል ሹ ሰርቪስ" የተሰኘውን የነጠላ ጫማ አገልግሎቱን ለማስተዋወቅ በጋዛ ውጊያ ወቅት እግሩን ያጣውን የቀድሞ የእስራኤል ወታደር ሻሌቭ ቢቶንን ማሳተፉ ነው ተቃውሞውን ያስነሳው። የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎች ኩባንያው የእስራኤልን ጦር ይደግፋል ሲሉ የከሰሱ ሲሆን፣ ታዋቂውን ተዋናይ ጃቪየር ባርዴምን ጨምሮ በርካቶች በምርቱ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጥሪ አቅርበዋል።ተቃዋሚዎቹ በጋዛ በሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን እና ህፃናት ለከባድ አካል ጉዳት በተዳረጉበት አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ፣ ኩባንያው የቀድሞ የእስራኤል ወታደርን ለዘመቻው መምረጡ ተገቢ አይደለም ብለዋል። አዲዳስ በ23 የአውሮፓ ሀገራት ያስተዋወቀው ይህ አገልግሎት ለአካል ጉዳተኞች የሚሰጥ ቢሆንም፣ አብዛኛው ተቃውሞ ያተኮረው ኩባንያው በወሰደው ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ምርጫ ላይ መሆኑ ተገልጿል። ሰላማዊ ነጋሲ #ዳጉ_ጆርናል
1 217
9
የሱዳን ጦር በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን ተቆጣጠረ የሱዳን ጦር (SAF) እና አጋር ኃይሎች እሑድ ዕለት በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን
የሱዳን ጦር በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን ተቆጣጠረ   የሱዳን ጦር (SAF) እና አጋር ኃይሎች እሑድ ዕለት በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት የምትገኘውን ሐምራት አል ዊዝ ከተማን የተቆጣጠሩ ሲሆን፣ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎችን (RSF) ከአካባቢው በማስወጣት ወደ መዲናዋ ካርቱም የሚወስደውን ወሳኝ የአቅርቦት መስመር በእጃቸው አስገብተዋል።   ​ይህ የወታደራዊ ግስጋሴ የተካሄደው ሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ የተሰነዘረውን ፈጣን የማጥቃት እርምጃ ተከተሎ ሲሆን፣ በወቅቱ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች (RSF) ከሰፊ የግዛቱ ክፍሎች እንዲወጡ ተደርጓል።   ይህም ወሳኝ የሆነውን የወጪ ንግድ መስመር (Export Road) ቁጥጥር ለማስመለስ ያስቻለ ከመሆኑም በላይ፣ ከዳርፉር አዋሳኝ አካባቢዎች አቅራቢያ ወደሚገኙት ምዕራባዊ ምሽጎች ታጣቂዎቹ እንዲያፈገፍጉ አስገድዷቸዋል።   ​ሐምራት አል ዊዝን መቆጣጠር፤ ጦሩ በጀብራት አል ሼክ እና በባራ ወታደራዊ ከተሞች ዙሪያ ያለውን የመከላከል አቅም የሚያጠናክርለት ሲሆን፤ ሰሜን ኮርዶፋንን ከካርቱም ጋር የሚያገናኘውን ዋና መንገድ ለንግድ እና ለዜጎች እንቅስቃሴ ደኅንነቱ የተጠበቀ ያደርገዋል።   ​የወታደራዊ ምንጮች እንደገለጹት፤ ጦሩ በሰሜን ኮርዶፋን ከሚገኙት ትላልቅ ወረዳዎች አንዷ በሆነችው ሶዳሪ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በባራ እና በጀብራት አል ሼክ በኩል ከባድ ማጠናከሪያዎችን በማስገባት ወደ ምዕራብ ዳርፉር አቅጣጫ ለመግፋት እየሠራ ነው።   ​ይህ የምድር ማጥቃት በምዕራብ ሰሜን ኮርዶፋን በሚንቀሳቀሱ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች የጦር ተሽከርካሪዎች፣ የጦር ሠፈሮች እና ተንቀሳቃሽ ክፍሎች ላይ በየዕለቱ በሚደረጉ የድሮን ጥቃቶች የታጀበ መሆኑን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል።   @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 256
10
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚ
ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው የሙዚቃ አልበም ሊለቁ ነው! ላለፉት ሶስት አስርት አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ልደቱ፤ ሀሳብን በዜማ በሚል ለአዲስ አመት የሙዚቃ አልበም ሊያሰራጩ መሆኑን ገልጸዋል። ፖለቲከኛው አዲስ የከፈቱትን የዩቲዩብ ገጽ ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሳወቁት የሙዚቃ አልበሙን ያዘጋጁት አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም ነው። እንደሚታወሰው ቴዲ አፍሮ ኢቶሪካ አልበሙን ካሰራጨ በኋላ የፈጠረውን ተጽእኖ ተከትሎ አቶ ልደቱ በወቅቱ፣ "የመንፈስ ቅናት አደረብኝ" ሲሉ ገልጸው ነበር። @Seledadotio @Seledadotio
1 277
11
በመቀሌ እና ድሬዳዋ ከተሞች አበባ'ን የማምረት እንቅስቃሴ የተቀዛቀዘ እንደሆነ ተነገረ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የአበባ ምርት በስፋት እየተካሄደባቸው ያሉ ምቹ አካባቢዎች መኖራቸውን የተገለጸው
በመቀሌ እና ድሬዳዋ ከተሞች አበባ'ን የማምረት እንቅስቃሴ የተቀዛቀዘ እንደሆነ ተነገረ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የአበባ ምርት በስፋት እየተካሄደባቸው ያሉ ምቹ አካባቢዎች መኖራቸውን የተገለጸው ሲሆን በመቀሌ እና ድሬዳዋ ከተሞች ግን መቀዛቀዝ እንደታየባቸዉ ተገልጿል። ከኢትዮ ኤፌም ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አበባ ፥ ፍራፍሬ እና አትክልት አምራቾች ማህበር ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ቴዎድሮስ ዘዉዴ እንደሚሉት አዳዲስ የአበባ ምርት ኢንቨስትመንት ሀኔታዎች መኖራቸውን ይገልጻል። ባለሀብቶች በዘርፉ እንዲገቡ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነዉ ያሉት አቶ ቴዎድሮስ መቀሌ ላይ ብዙም እንቅስቃሴ እንደሌለ ገልፀዋል በተመሳሳይ መልኩ ድሬዳዋ ከተማ አበባን በተመለከተ የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ እንዳለ ተናግረዋል። በባቱ ፣ቢሾፍቱ ፥ሆለታ እና ሰበታ ሰፋፊ የአበባ እርሻ የሚካሄድባቸው መሆኑን ያነሱት የማህበሩ ዳይሬክተር በባህርዳር ዙሪያ አየር መንገዱን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንቅስቃሴዎች መኖራቸዉን እና ለዉጪ ገበያ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ ያሉ ኩባንያዎች መኖራቸዉን ጠቁመዋል። አሁን ላይ በጉራጌ ዞን አካባቢ አዳዲስ የኢንቨስትመንት መሬቶች መኖራቸዉን ተለይቶ ሂደቶች መጀመራቸውን አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል። በተጨማሪም በሀዋሳ ከ100 ሄክታር በላይ የአበባ እርሻ የሚገኝበት አካባቢ መሆኑ ተጠቅሷል። የማህበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ የአበባ ምርት ከሌሎች የሆልቲካልቸር ምርቶች በገዘፈ መልኩ እድገቱ መሻሻሎች እንደታየበት መሆኑን ጠቅሰዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሎጀስቲክ አቅሙን ከፍ ማድረጉን ተከትሎ ለምርቱ ተፎካካሪነት እድል ፈጥሯል ሲሉም ይገልፃሉ። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 398
12
የአሜሪካ ፍርድ ቤት ለኢትዮጵያ እና ለሌሎች ሀገራት የዲቪ-2026 አመልካቾች ተስፋ ሰጪ ውሳኔ አስተላለፈ የካሊፎርኒያ ክልላዊ ፍርድ ቤት ዳኛ ኤድዋርድ ዳቪላ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚስቴር በዲቪ አመልካቾች ላይ ተጥለው የነበሩ የቪዛ እገዳዎችን የሚያነሳ ውሳኔ ማስተላለፋቸውን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ የ48 ሀገራት አመልካቾች የቪዛ ሂደታቸውን እንዲቀጥሉ መንገድ መከፈቱ ተገለጸ። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚስቴር ቀደም ሲል ጥሎት የነበረውን እገዳ ያነሳ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣ አመልካቾች እስከ መስከረም 20 ቀን 2019 ዓ.ም በሚጠናቀቀው የዲቪ-2026 ፕሮግራም ገደብ ውስጥ ሰነዶቻቸውን ማቅረብ እና የተያዙላቸውን ቃለ-መጠይቆች መከታተል እንደሚችሉ አስታውቋል። ይህ የፍርድ ቤት ውሳኔ ለአፍሪካ ሀገራት ትልቅ እድል ይዞ የመጣ ሲሆን፣ ከ49 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ እና ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ 53 ሺህ 939 ሰዎች በDV-2026 ተመዝግበው ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል ግብፅ በ5,527 ከፍተኛውን ቁጥር ስትይዝ፣ አልጄሪያ በ5,457፣ ሱዳን በ5,226፣ ኬንያ በ3,949 እንዲሁም ኢትዮጵያ በ3,287 አመልካቾች ቀጣዩን ደረጃ በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ። ባለፉት አምስት ዓመታት ከ50 ሺህ በላይ ስደተኞችን ወደ አሜሪካ የላኩ እንደ ናይጄሪያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ያሉ ሀገራት በዚህ ፕሮግራም ውስጥ አልተካተቱም። በአለም አቀፍ ደረጃ ከ20.8 ሚሊዮን በላይ ብቁ ተወዳዳሪዎች መካከል 129,516 ሰዎች ለዲቪ-2026 የተመረጡ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በየዓመቱ እስከ 55 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የአሜሪካ ቋሚ መኖሪያ ቪዛ ይሰጣል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 591
13
26 ስልክና 34 ሺህ ብር የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️ በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች አደረጃጀት ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት 26 ስልክ እና 34,000 ብር የ
26 ስልክና 34 ሺህ ብር የሰረቀው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️ በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር  የወጣቶች አደረጃጀት ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመቀናጀት 26 ስልክ እና 34,000 ብር የሰረቀን ግለሠብ በቁጥጥር ስር አውለዋል። ‎ @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 786
14
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ለፈተ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች፣ ሰኞ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆኑ ተገልጿል። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
2 177
15
አሳዛኝ ዜና‼️ ከአድስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል! 18 የሚደርሱ ቆስለዋል። ሸኖ — በሸኖ ከ+2
አሳዛኝ ዜና‼️ ከአድስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አልፏል! 18 የሚደርሱ ቆስለዋል። ሸኖ — በሸኖ ከተማ አስተዳደር ኦንቱ ቀበሌ፣ «አዳ ሀሮ» ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ18 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው የትራፊክ ደህንነት ክፍሎች አስታወቁ። የሸኖ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አብዲሳ መርጋ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-A04933 አ.አ የሆነ ‘ባስ ኤፍኤም’ የህዝብ ማጓጓዣ ተሽከርካሪ ከሚፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከሩ ምክንያት ነው ብለዋል። በአደጋው ሕይወታቸው ካለፉት 6 ሰዎች መካከል 2 ወንዶች እና 4 ሴቶች እንደሚገኙበት ታውቋል። በተጨማሪም ጉዳት ከደረሰባቸው 18 ተጓዦች (12 ወንዶች እና 6 ሴቶች) ውስጥ 13ቱ ከባድ እና መካከለኛ አደጋ የገጠማቸው ሲሆን፣ አምስቱ ደግሞ ቀላል ጉዳት አስተናግደዋል። የሟቾች አስከሬን በህብረተሰቡና በትራፊክ ፖሊስ አባላት ትብብር ወደ ሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን፣ ተጎጂዎችም በዚሁ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ለተሻለ ህክምና ወደ ሌሎች ከፍተኛ ሆስፒታሎች የተላኩ ሲሆን፣ አነስተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ጉዟቸውን ወደ ደብረ ብርሃን እና አዲስ አበባ መቀጠላቸው ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio
2 457
16
ቢኒያም ሽብሬ ከማስተር ሀገረሰላም አርባ (ቦንጆ) ጋር በ Ethio Fight ይፋለማሉ! ከ16 ቀን በኋላ በጉጉት በሚጠበቀው የ Ethio Fight የትግል ውድድር ላይ፣ ቢኒያም ሽብሬ ከሌላኛው ጠንካ+1
ቢኒያም ሽብሬ ከማስተር ሀገረሰላም አርባ (ቦንጆ) ጋር በ Ethio Fight ይፋለማሉ! ከ16 ቀን በኋላ በጉጉት በሚጠበቀው የ Ethio Fight የትግል ውድድር ላይ፣ ቢኒያም ሽብሬ ከሌላኛው ጠንካራ ተፎካካሪ ማስተር ሀገረሰላም አርባ (በቅፅል ስሙ "ቦንጆ") ጋር እንደሚፋለም ታውቋል። ከአሜሪካ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ የገባው ቢኒያም ሽብሬ በአሁኑ ሰዓት ደማቅ አቀባበል እየተደረገለት የሚገኝ ሲሆን፣ የትውልድ አካባቢው የፈረንሳይ ሌጋሲዮን ወጣቶችም ለተፎካካሪው ልዩ የድጋፍ እና የአቀባበል ስነ-ስርዓት አዘጋጅተውለታል። ሁለቱ ጠንካራ ስፖርተኞች የሚያደርጉት ይህ ታላቅ ፍልሚያ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ግምትና ትኩረት አግኝቷል። ይህንን ታላቅ ውድድር ጉርሻ ፔጅ በስፋት ሽፋን መስጠት ይጀምራል። መልካም እድል ከወዲሁ ለሁሉም ተፋላሚዎች @Seledadotio @Seledadotio
2 352
17
216ኛው የለንደን ደርቢ አርሰናል ከ ቼልሲ ሁለቱ የባስክ ግዛት ተወላጆች እና አብሮ አደጎቹ ሚኬል አርቴታ እና ዣቢ አሎንስ በዓለም ትልቁ ሊግ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለት ትልልቅ ክለቦችን ይዘው
216ኛው የለንደን ደርቢ አርሰናል ከ ቼልሲ ሁለቱ የባስክ ግዛት ተወላጆች እና አብሮ አደጎቹ ሚኬል አርቴታ እና ዣቢ አሎንስ በዓለም ትልቁ ሊግ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁለት ትልልቅ ክለቦችን ይዘው ተፋጠዋል። እግር ኳስን በተወለዱበት አካባቢ በሚገኝው የአንቲጎኩ አካዳሚ የጀመሩት እና ለ6 ዓመት በዚሁ አካዳሚ አብረው የተጫውቱት አርቴታ እና አሎንሶ ለሪያል ሶሴዳድ ዋናው ቡድንም ተጫውተው አሳልፈዋል። በባየር ሊቨርኩሰን ድንቅ ጊዜ ካሳለፈ በኋላ በማድሪድ የተወሰን ጊዜ የቆየው ዣቢ አሎንሶ በቼልሲ ራሱን ለትልቁ ፈተና አዘጋጅቷል። በሊጉ የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎችን ያሸነፈው አሎንሶ፤ የመጀመሪያ ትልቁን ፈተና ዛሬ ይጋፈጣል። ምሽት 12፡30 በኤምሬትስ ከሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል። በተመሳሳይ አርሰናልም የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎችን ያሸነፈ ሲሆን በአሸናፊነቱ ለመቀጥል በለንደን ደርቢ ጠንካራ የፊት መስመር ካለው ቼልሲ ይገናኛል። በኤምሬስት የሚደረገው ጨዋታ 7 ግቦችን ያስቆጠረው የቼልሲ የፊት መስመር ምንም ግብ ካልተቆጠረበት የአርሰናል ተከላካይ የሚያደርጉት ትንቅንቅ በመሆኑ ጨዋታውን እንዲጠበቅ የሚያደርግው ሲሆን በሌላ በኩል ሁለቱ ስፔናዊያን ታክቲሺያን ጨዋታውን እንዴትባለ መልኩ ይወጡታል የሚለው የሚጠበቅ ነው። አርሰናል ከቼልሲ በተገናኝባቸው ያልፉት 9 ጨዋታዎች በአንዱም ያልተሸነፍ ሲሆን 6ቱን አሸንፏል። በጨዋታው በመድፈኞቹ በኩል ዩሪየን እና ዊሊያም ሳሊባ አሁንም ከጉዳቱ ያልተመለሱ ተጨዋቾች ሲሆኑ፤ ኤዝሪ ኮንሳ በመድፍኞቹ ማልያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቋሚነት ሊጀምር ይችላል ተብሏል። ሞይሰስ ካይሴዶ የመሰለፉ ነገር ያልተረጋገጥ ሲሆን ጆርዳን ሄንደርሰን እና ፓሊስትራ አሁንም በጉዳት ከስብስቡ ውጪ ናቸው። @Seledadotio @Seledadotio
2 054
18
ከወራት በፊት ህይወቱ ያለፈዉ ብሪታንያ ናይጄሪያዊ ኢጎ ቲኒ የሞቱ ምክኒያት ከብልት ማስተለቅ ህክምና በኋላ የገጠመዉ ተጓዳኝ የጤና ችግር ነዉ ተባለ የድምጻዊ ዴቪዶ የቅርብ ጓደኛ ነበር የተባለዉና በ
ከወራት በፊት ህይወቱ ያለፈዉ ብሪታንያ ናይጄሪያዊ ኢጎ ቲኒ የሞቱ ምክኒያት ከብልት ማስተለቅ ህክምና በኋላ የገጠመዉ ተጓዳኝ የጤና ችግር ነዉ ተባለ የድምጻዊ ዴቪዶ የቅርብ ጓደኛ ነበር የተባለዉና በናይጄሪያ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እዉቅና ያለዉ ኢጎ ቲኒ በመጋቢት ወር ነበር በ 43 አመቱ ህይወቱ ማለፉ የተሰማዉ። የጎልማሳዉ ታዋቂ ሰዉ ህልፈት እስካሁን ይፋ ሳይደረግ ቆይቶ የነበረ ቢሆንም ምክኒያቱ ከታወቀ በኋላ የአለም መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቧል። ግለሰቡ ህይወቱ ከማለፉ በፊት በታይላንድ ባንክሆክ የብልቅ ማስተለቅ ህክምና አድርጎ ነበር ተብሏል። ግለሰቡ ከህክምናዉ በኋላ የልብ ህመም አጋጥሞት ነበር ተብሏል። በተጨማሪም በህክምዉ ሀኪሞች ተጠቅመዉት የነበረዉ 40 ሚሊ ሊትር ሀይሉሮኒክ የተሰኘ አሲድ በሳንባዉ ላይ ተገኝቷል መባሉ ተሰምቷል። ግለሰቡ ህይወቱ ከማለፉ በፊት ማሳጅ በሚደረግበት ወቅት ሁለት ጊዜ ራሱን ስቶ ነበርም ተብሏል። ግለሰቡ ወዲያዉ ወደ ሆስፒታል ቢወሰድም ወደ ሳንባዉ የደም ዝዉዉር በመቋረጡ ህይወቱ አልፏል። @Addis_News @Addis_News
1 979
19
አዲስ አበባ‼️ "በአዲስ አበባ የክረምቱን ማብቃትና የጸደይ (ብራ) መግባት የሚያበስረው የጎቤ እና ሽኖዬ ፌስቲቫል በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው።" ወጣቶች ባህላዊ አልባሳት አጊጠው በየጎዳናው፣ በታ+2
አዲስ አበባ‼️ "በአዲስ አበባ የክረምቱን ማብቃትና የጸደይ (ብራ) መግባት የሚያበስረው የጎቤ እና ሽኖዬ ፌስቲቫል በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው።" ወጣቶች ባህላዊ አልባሳት አጊጠው በየጎዳናው፣ በታዋቂ ግለሰቦችና በመንግሥት ኃላፊዎች መኖሪያ ቤቶች በመዘዋወር መልካም ምኞት እየገለፁና ስጦታዎችን እየተቀበሉ ይገኛሉ። @Seledadotio @Seledadotio
1 987
20
አትሌት ገመቹ ጎዳና በ3ሺህ ሜትር መሰናክል የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ የ2026 ዳይመንድ ሊግ የዙር ውድድር ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል አ+2
አትሌት ገመቹ ጎዳና በ3ሺህ ሜትር መሰናክል የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ የ2026 ዳይመንድ ሊግ የዙር ውድድር ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል። በመጀመሪያው ቀን የዙሪክ ዳይመንድ ሊግ የፍፃሜ ውድድር በ5ሺህ ሜትር አሸናፊ የነበረችውን ኢትዮጵያዊቷን አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉን ጨምሮ፣ አምስት አፍሪካውያን አትሌቶች አትሌቶች አጠቃላይ አሸናፊዎች ነበሩ። በሁለተኛው ዕለት ደግሞ ገመቹ ጎዳና ከኢትዮጵያ ሁለተኛ ከአፍሪካ ስድስተኛው የዳይመንድ ሊጉ አሸናፊ ሆኗል። ገመቹ ሞሮኳዊውን የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ሱፊያን ኤል ባካሊ አስከትሎ ሲገባ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 8:08.67 ወስዶበታል። ሱፊያን ኤል ባካሊ 2ኛ፣ ኬንያዊው ሲሞን ኮዌች ደግሞ 3ኛ ሆነዋል። ሳሙኤል ፍሬው ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቋል። በወንዶች 5ሺህ ሜትር ቢኒያም መሀሪ 4ኛ፣ በሴቶች 800 ሜትር ሳይዳ ፀሀዬ 3ኛ እንዲሁም በ1500 ሜትር ብርቄ ኃየሎም 9ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁበት የምሽቱ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ውጤቶች ናቸው። #ዳጉ_ጆርናል
1 941