en
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

Open in Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Fresh መረጃ | FreshNews

Channel Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 55 438 subscribers, ranking 3 059 in the Education category and 593 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 55 438 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -816 over the last 30 days and by -67 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 3.94%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.16% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 185 views. Within the first day, a publication typically gains 1 753 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

55 438
Subscribers
-6724 hours
-3367 days
-81630 days
Posts Archive
በአዲስ አበባ ታፍና የተወሰደችው ህፃን በሰላም ስትገኝ አጋችዋ በቁጥጥር ስር ዋለች! ከጥቂት ቀናት በፊት ከቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ታፍና ተወስዳ የነበረችው ህፃን (ናኒ / ፊዮና ሰለሞን) በሰላም ተገኝ
በአዲስ አበባ ታፍና የተወሰደችው ህፃን በሰላም ስትገኝ አጋችዋ በቁጥጥር ስር ዋለች! ከጥቂት ቀናት በፊት ከቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ታፍና ተወስዳ የነበረችው ህፃን (ናኒ / ፊዮና ሰለሞን) በሰላም ተገኝታ ከቤተሰቧ ጋር እንድትቀላቀል ተደርጓል። ህፃን ፊዮና ሰለሞን (ናኒ) በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ ከሚገኝ ጫካ ውስጥ በሰላም ልትገኝ ችላለች። ህፃኗን አግታ 3 ሚሊዮን ብር ጠይቃ የነበረችው የቤት ሰራተኛዋ ወጣት መቅደስ ሞገስ በህብረተሰቡ ጥቆማና በፖሊስ ክትትል ጎንደር ከተማ ላይ በቁጥጥር ስር ውላለች። ተጠርጣሪዋ ከያዘችው ገንዘብ ውስጥ ከ370 ሺህ ብር በላይ ተይዞባታል።  ፖሊስ ከተባባሪዋ (ግርማ ወንድአሁን) እና ከሌሎች እጃቸው ካለበት አካላት ጋር የተያያዘውን ክትትል አጠናክሮ ቀጥሏል ተብሏል። @Addis_News @Addis_News

"ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ፤ተመለሱ የሚለንም የለም!" - ኮሎኔል ነጋሽ‼️ የኤርትራ አመራሮች እጣ-ፈንታ፦** ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎች እና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እን
"ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ፤ተመለሱ የሚለንም የለም!"  - ኮሎኔል ነጋሽ‼️ የኤርትራ አመራሮች እጣ-ፈንታ፦** ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎች እና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚደመሰሱና ኤርትራም በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ሥር እንደምትገባ ኮሎኔል ነጋሽ አስጠንቅቀዋል። የኢትዮጵያ የማያዳግም እርምጃ፦** የኢትዮጵያ ቀዳሚ ፍላጎት ሰላም መሆኑ ቢገለጽም፤ ሀገርን የሚያፈርሱ እና የሚያበጣብጡ ኃይሎችን ግን ዝም ብሎ ከመመልከት አልፎ፣ባሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ ተገቢውን ዋጋ እንደሚያስከፍሏቸው ቁርጡን ተናግረዋል። የተቀየረው የጦርነት አውድ፦** እንደ ቀደመው ጊዜ "ተራራ የመያዝ፣ የመልቀቅ፣የማፈግፈግና የማጥቃት" ዘመን አብቅቷል። አሁን ያለው ውጊያ ከፍተኛ የሰው ኃይልን ማዕከል ያደረገ ሳይሆን፣በአንድ ቦታ ላይ ሆኖ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ አቅም ጦርነቱን ማጠናቀቅ ወደሚቻልበት ደረጃ መሸጋገሩን አብራርተዋል። የ1990ው ታሪክ አይደገምም፦** በ1990 ዓ.ም ኤርትራ ሙሉ በሙሉ ተከባ የነበረ ቢሆንም፤የኤርትራ አመራሮች ከሞት የዳኑት "በጥቂት የኛ አመራሮች" (ወደ ኋላ ተመለሱ ባሉ) ምክንያት እንደነበር ኮሎኔሉ አስታውሰዋል። አሁን ግን ያ ታሪክ እንደማይደገምና "ተመለሱ የሚሉንም የሉም" ሲሉ የማያዳግም መልዕክት አስተላልፈዋል። @Addis_News @Addis_News

የዲጂታል ዘመን ብቸኝነት፡ የእድሜ መጨመር እና የጓደኝነት ክበብ መጥበብ ምስጢር ​በወጣትነት እና በልጅነት ጊዜ ጓደኝነት በጣም ቀላል እና ተፈጥሯዊ ነገር ነበር። በትምህርት ቤት፣ በዩኒቨርሲቲ ወይም በስራ ቦታ በየቀኑ እንገናኛለን፤ ከስራ በኋላም ሆነ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ያለ ምንም ቅድመ ዝግጅት አብረን እናዝናና ነበር። በወቅቱ ጓደኝነትን ለማስቀጠል ልዩ እቅድ ወይም ቀጠሮ ማመቻቸት አያስፈልግም ነበር፤ ይልቁንም በቃ አብሮነት በተፈጥሮአዊ መንገድ የሚቀጥል የህይወት አካል ነበር። ነገር ግን ወደ አዋቂነት እድሜ ስንሸጋገር ነገሮች ሁሉ ስር ነቀል ለውጥ ያሳያሉ። የስራ ኃላፊነት፣ የቦታ መለዋወጥ፣ የፍቅር ህይወት እና የቤተሰብ ምስረታ ሰዎችን ወደ ተለያዩ የህይወት አቅጣጫዎች ይመራቸዋል። ቀደም ሲል የነበሩት ድንገተኛ ስብሰባዎች በጽኑ የታቀዱ ቀጠሮዎች ይሆናሉ፤ አብሮ የማሳለፍ ልምዶችም በቀላሉ "ምን አዲስ ነገር አለ?" በሚል አጭር የደህንነት ጥያቄ ይተካሉ። ​በአዋቂነት እድሜ ውስጥ የጓደኝነት ክበብ እየጠበበ መሄዱ የሰዎች የግል ስሜት ብቻ ሳይሆን በሳይንሳዊ መረጃዎች የተረጋገጠ እውነት ነው። በሰሜን አሜሪካ የተደረገ ጥናት እንዳመለከተው በፈረንሳይያውያኑ 1990 ከነበሩት ሰዎች መካከል 33 በመቶ የሚሆኑት ቢያንስ አስር የቅርብ ጓደኞች እንዳሏቸው ገልጸው የነበረ ቢሆንም፣ በ2021 ግን ይህ ቁጥር ወደ 13 በመቶ ዝቅ ብሏል። በተጨማሪም ምንም አይነት የቅርብ ጓደኛ የሌላቸው ሰዎች መጠን ከ 3 በመቶ ወደ 12 በመቶ አድጓል። ተመራማሪዎች ለዚህ ለውጥ እንደ ምክንያቱ የሚያስቀምጡት የሰዎችን በቦታ የመንቀሳቀስ ፍላጎት መጨመር፣ የህይወት ጎዳናዎች መለያየት፣ ዘግይቶ ማግባት እና በቅርብ ጊዜ የተከሰተው የአለም አቀፍ ወረርሽኝ ያስከተለውን ማህበራዊ ርቀት ነው። ​ይህ የማህበራዊ ግንኙነት መሸርሸር በተለይ በወንዶች ላይ በጎላ ሁኔታ ይታያል። በ1990 ከተጠየቁት ወንዶች መካከል 55 በመቶ የሚሆኑት ቢያንስ ስድስት የቅርብ ጓደኞች እንደነበሯቸው የተናገሩ ሲሆን፣ በ2021 ግን ይህ አሃዝ ወደ 27 በመቶ ወርዷል። በተመሳሳይ መልኩ ምንም አይነት የቅርብ ጓደኛ የሌላቸው ወንዶች ቁጥር ከ3 በመቶ ወደ 15 በመቶ አድጓል። የዚህ ዋነኛ ምክንያት ወንዶች አብዛኛውን ጊዜ ጓደኝነታቸውን የሚገነቡት በአንድ ላይ በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ማለትም በስፖርት፣ በስራ ወይም በትርፍ ጊዜ መዝናኛዎች በመሆኑ ነው። እነዚህ አብሮ የመስራት እና የመጫወት ልማዶች በህይወት ለውጥ ምክንያት ሲቋረጡ፣ የወንዶቹ ግንኙነትም አብሮ የመደብዘዝ እድሉ ከፍተኛ ይሆናል። ​በአሁኑ ዘመን እንደ ዋትስአፕ  እና ኢንስታግራም ባሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት ከሰዎች ጋር መገናኘት ከምንጊዜውም በላይ ቀላል ሆኗል። የጓደኞቻችንን የጉዞ ፎቶዎች፣ የቅርብ ጊዜ የስራ ለውጦችን እና የህይወት ሁነቶችን በስልካችን ስክሪን ላይ በሰከንዶች ውስጥ ማየት እንችላለን። ይህም በአካል ሳንገናኝ ስለ አንድ ሰው ህይወት ብዙ እንድናውቅ የሚያስችል አዲስ አይነት "ዲጂታል ቅርበት" ፈጥሯል። ዲጂታል ግንኙነት በሩቅ ያሉ ወዳጆችን ለማስጠጋት ቢረዳም፣ አብሮ የማሳለፍን ተፈጥሯዊ ህያውነት ግን በጭራሽ ሊተካው አይችልም። ​የጽሑፍ መልእክቶች እና የዲጂታል ግንኙነቶች ብዛት እውነተኛ የልብ ቅርበትን እንደማያረጋግጡ ጥናቶች ያሳያሉ። በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል 54 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከጓደኞቻቸው ጋር በጽሁፍ መለዋወጣቸውን ቢናገሩም፣ አሁንም አብዛኞቹ የጎላ የብቸኝነት ስሜት እና የቅርብ ጓደኛ ማጣት እንደሚሰማቸው ገልጸዋል። አጭር የጽሁፍ መልእክት የአንድን ሰው አዲስ የስራ ሁኔታ መረጃ ብቻ ሊሰጠን ይችላል፤ በአካል ተገናኝቶ ማመሸት ግን ያ ሰው በእውነት እንዴት እንደሆነ ለመረዳት ያስችላል። እውነተኛ እና ዘላቂ የሆኑ አዳዲስ ትዝታዎች የሚፈጠሩት በአካል በሚደረጉ ድንገተኛ ንግግሮች እንጂ በስልክ ስክሪን ልውውጥ አይደለም። ​የሰው ልጅ በአንድ ጊዜ ሊኖረው የሚችለውን የጓደኞች ብዛት በተመለከተ የእንግሊዙ አንትሮፖሎጂስት ሮቢን ደንባር  ሳይንሳዊ ማብራሪያ ይሰጠናል። የእሱ ሞዴል እንደሚያሳየው አንድ ሰው በአማካይ አምስት በጣም የቅርብ፣ 15 የቅርብ፣ 50 ጥሩ ወዳጆች እና እስከ 150 የሚደርሱ የተረጋጉ ማህበራዊ ግንኙነቶች ሊኖሩት ይችላል። ይህም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚኖሩን በመቶዎች የሚቆጠሩ ተከታዮች ወይም "ወዳጆች" ከእውነተኛ የቅርብ ጓደኞች ጋር አንድ እንዳልሆኑ ያረጋገጣል። የሰው ልጅ ጊዜ እና ትኩረት የተወሰነ በመሆኑ፣ ግንኙነቱ በጠበቀ ቁጥር የሚጠይቀው ጊዜ እና ትኩረትም ከፍተኛ ይሆናል። ​ስለሆነም የእድሜ መጨመርን ተከትሎ የጓደኝነት ክበብ መጥበብ የግድ እንደ አሉታዊ ነገር ወይም እንደ ችግር ሊታይ አይገባም። ህይወታችን ሲቀየር እና የኃላፊነት ዘመናችን ሲሰፋ የጓደኝነት መልክም አብሮ መለወጡ ተፈጥሮአዊ ነው። አንዳንዶች በህይወታችን ውስጥ ለአስርት ዓመታት አብረውን ይዘልቃሉ፤ ሌሎች ደግሞ በዓመት ጥቂት ጊዜያት ብቻ የምንገናኛቸው ሰዎች ይሆናሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ያለ ምንም ጠብ ወይም ቅሬታ በጊዜ ሂደት ከዕለት ተዕለት ህይወታችን በፀጥታ ይርቃሉ። ​አንድ የቅርብ የነበረ ግንኙነት በጊዜ ሂደት እየቀዘቀዘ መሄዱን ማወቅ የስሜት ህመም ሊኖረው እንደሚችል አጠራጣሪ አይደለም። ነገር ግን የግንኙነቱ መጥፋት ወይም መራራቅ ቀደም ሲል አብሮ የተሳለፈው መልካም ጊዜና ትዝታ ዋጋ አልባ ነበር ማለት አይደለም። እያንዳንዱ ሰው በህይወታችን ውስጥ የራሱ የሆነ የጊዜ ገደብ እና ሚና ይዞ ይመጣል። ​በመጨረሻም፣ የጓደኝነት እውነተኛ እሴት የሚለካው በሰዎች ብዛት ሳይሆን በግንኙነቱ ጥራት እና ጥልቀት ነው። እያንዳንዱ የቅርብ ጓደኛ ሁልጊዜ በስልክ ሊገኝ ወይም በየቀኑ መልእክት ሊጽፍልን አይገባም። ጠንካራ እና ደጋፊ የሆነ የማህበራዊ ህይወት ለመገንባት የግድ ትልቅ የጓደኛ ስብስብ አያስፈልገንም። ​በዚህ በዲጂታል ዘመን ትልቁ ፈተናችን የጓደኞቻችንን የህይወት አየር ሁኔታ በስልካችን ከመከታተል አልፈን፣ በህይወታቸው ውስጥ በአካል በመገኘት እውነተኛውን አብሮነት መለማመድ መቻላችን ነው። ምንጭ: ብሊክ ጋዜጣ @Freshmerejaet @Freshmerejaet

✨ ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነ
✨  ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነፍ እድሎች ⚡ ቀላል እና ፈጣን ተሳትፎ 🎊 በየቀኑ አዲስ ደስታ 🏆 አሸናፊ የመሆን እድል 📍ባሉበት ሁነው በ ስልክዎ የሚዝናኑበት ጨዋታ 🌟 ዕድል ለሚሞክሩት በሩን ትከፍታለች! 🌟 ድል ለሚደፍሩት ትመጣለች! 🔥 ዛሬ ይቀላቀሉ! 🔥 ይጫወቱ! 🔥 ይዝናኑ! 🔥 ዕድልዎን ይሞክሩ @BellaBingo1bot ለማንኛውም እገዛ --09 72 75 73 19 ይደውሉ 💙 Bella Bingo – የደስታ፣ የዕድል እና የአሸናፊዎች ምርጫ!

#MoE የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን ወስደው በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋምና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲያስገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ተማሪዎች ምርጫቸውን ትምህርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን ማስገባት ይችላሉ። የምርጫ ማስገቢያ ድረ-ገጹ፦ student.ethernet.edu.et ነው። - በሕክምና ምክንያት ልዩ ሁኔታ ያላቸው፣ - የአካል ጉዳተኛ የሆኑ፣ - ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች - ከ6 ወር በታች ሕፃን የሚያጠቡ እናቶች ተገቢውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስቴሩ ገልጿል።       -ETHIO-MEREJA-      T.me/ethio_mereja

በጃናሞራ ወረዳ በደረሰው ድርቅ ከ85 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፍተኛ ረሀብ መዳረጋቸው ተገለጸ! በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞንጃናሞራ ወረዳ የክረምቱ ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ካለመግባቱ ጋር ተያይዞ በተፈ
በጃናሞራ ወረዳ በደረሰው ድርቅ ከ85 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፍተኛ ረሀብ መዳረጋቸው ተገለጸ! በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞንጃናሞራ ወረዳ የክረምቱ ዝናብ ወቅቱን ጠብቆ ካለመግባቱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ድርቅ 85 ሺህ ሰዎች ለችግር መዳረጋቸው ተነገረ። በወረዳው 17 ቀበሌዎች ድርቅ የተከሰተባቸው ሲሆን፣ ከፍተኛ ድርቅ በተከሰተበት ዋስል ቀበሌ ኗሪ የሆኑት አርሶ አደር ኑሬ አረስ እርሶም ሰው የሚበላው በማጣቱ ለጭንቀት መዳረጉን ይናገራሉ። በዋስል ቀበሌ የግብርና ባለሙያ የሆኑት አቶ በላይ አስምሮ ድርቁ በፈጠረው ተፅዕኖ የተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎችን ማህበረሰቡ በማዋጣት በሃይማኖት ተቋማት እያገዘ ያለበት ሁኔታ አለ ሲሉ ተናግረዋል።"የዚያ አካባቢ አብዛኛው ማህበረሰብ ሙስሊም ነው፣ እና ጀምዕአ የሚሉት አለ የሚሰበሰቢበት አርብ አርብ  እና በዛ  ተሰብስበው ለተራቡ ሰዎች እያዋጡ ነው እየረዱ ያሉት። እዳታ የሚሰጣቸውም ስለሌለ፣ ፕላንፕሌትም  ፋፋ ምንም የሚመጣም ስለሌለ አዎ በዛ ያልተካተቱ ሰዎች ራሱ በርሀብ ሊሞቱ ስለሆነ  ከዛ ተመርጠዉ የእለት ምግብ  እንዲሰጣቸው የተደረገበት ሁኔታ አለ።"... https://p.dw.com/p/5KbDo @YeneTube @FikerAssefa

እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታ
እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው  የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል። የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል። በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ  የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል ። የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል። ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሳምንታት በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ! ጠቅላዩ በማኅበራዊ ገፃቸው ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሳምንታት በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ! ጠቅላዩ በማኅበራዊ ገፃቸው ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ ማከናወናቸውን ገልጸዋል። @Seledadotio @Seledadotio

ሶማሊያ የሶማሊላንድን እውቅና የማግኘት እንቅስቃሴ ለማገድ ከአረብ ሀገራት ጋር ውይይት እያደረገች ነው ሶማሊያ አረብ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖአቸውን በመጠቀም እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችው እውቅና ወደ ሰፊ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዳይቀየር እንዲያግዱ ጥሪ አቀረበች። የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ሞሃመድ ኦማር ከሳውዲው አል ሻርቅ አል አውሳት (-Sharq Al-Awsat) ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ሞቃዲሾ የሌሎች ሀገራትን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተለች መሆኗን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ ሶማሊያ በእስራኤል ውሳኔ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለማስረዳት ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ጋር በቀጥታ ግንኙነት ማድረጓን ተናግረዋል። እንደ አሊ ባልካድ ገለፃ፣ እስራኤል ባለፈው ታህሳስ ወር ሶማሊላንድን በይፋ በመቀበል የመጀመሪያዋ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገር ሆናለች። ሁለቱ ሀገራት አምባሳደሮችን የተለዋወጡ ሲሆን፣ ሶማሊላንድ በኢየሩሳሌም ኤምባሲዋን በመክፈት ፕሬዚዳንቷም በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ሚኒስትሩ የእስራኤል ውሳኔ እስካሁን ሰፊ ዓለም አቀፍ እውቅና ባያስከትልም፣ በሶማሊላንድ የሚደረጉ የውጭ ሀገራት ወታደራዊ ወይም የደህንነት እንቅስቃሴዎች ውጥረትን ሊጨምሩና የአፍሪካ ቀንድን ለማረጋጋት አደጋ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። በመሆኑም የአረብ ሀገራት ከማውገዝ ባለፈ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በመጠቀም ተጨማሪ እውቅናዎችን እንዲያግዱ ጠይቀዋል። ሶማሊላንድ እ.ኤ.አ. በ1991 ነፃነቷን ካወጀች ጀምሮ የራሷን መንግሥትና የደህንነት ኃይል አዋቅራ ብትቀሳቀስም፣ ሞቃዲሾ ሶማሊላንድን የግዛቷ አካል አድርጋ ነው የምትቆጥረው። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከስምምነት ሊደርስ ነው እንደ አሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትራንስፖርቴሽን ዘገባ መሰረት ​የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከስምምነት ሊደርስ ነው እንደ አሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትራንስፖርቴሽን ዘገባ መሰረት ​የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የሚደርሱ ቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት ለማጠናቀቅ መቃረቡን ምንጮች ገለጹ። ይህ ውል አየር መንገዱ ከአረብ ኤምሬትስ እና ቀጣናው አየር መንገድ ኩባንያዎች ጋር ያለውን ውድድር ለማጠናከር እና አዲስ የአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ማዕከል  ለመገንባት ለያዘው እቅድ ትልቅ ማበረታቻ ነው ተብሏል። ​እንደ ዘገባው ከሆነ፣ ግዢው ሁለት የነባሩን '777F' ሞዴል እና የተቀሩትን ደግሞ አዲስ ምርት የሆኑትን '777-8F' የጭነት አውሮፕላኖች ያካተተ ነው። ቦይንግ የ '777X' አውሮፕላን ማረጋገጫ በመዘገየቱ ምክንያት ነባሩን ሞዴል የማምረት ፈቃድ ለማራዘም ከአሜሪካ አቪዬሽን ባለስልጣን ጋር እየተነጋገረ ይገኛል። ​አየር መንገዱ እና ቦይንግ በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጡት ይፋዊ አስተያየት ባይኖርም፣ ውሉ አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የካርጎ ኤክስፖርት አገልግሎት ያለውን የበላይነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተገልጿል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚዎች ውስጥ 62 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸው ተነገረ። የ12 ክፍል ማለፊያ ነጥብ ካመጡት ውስጥ 7ቱ ሴት ታራሚዎች ይገኙበታልም ተብላል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃና በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል እና በዘዋይ ማረሚያ ማእከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱት ተፈታኞች 63 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 62 ማለፋቸውን ማረመያ ቤቱ አስታውቋል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ፣ በሴቶች ማረሚያ ማዕከላት በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እና ለፈተና የተቀመጡት 31 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፤ከነዚህም ውስጥ 7ቱ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡   በተመሳሳይ የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 23 የህግ ተማሪዎች  መካከል 22ቱን ማሳለፍ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በአጠቃላይ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚስች 62 ማለፋችው ተነግራል፡፡የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ካስፈተናቸው በሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መቶ በመቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ማስመዘገብ ተችሏል፡፡ የሕግ ታራሚ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ተከትሎ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ እንደተናገሩት ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የፈጠረው ምቹ የትምህርት ከባቢ እና የታሪሚዎች ጠንካራ ተነሳሽነት ለዚህ አስደናቂ 100 ከመቶ ውጤት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። በማዕከላቱ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም የህዝብ ት/ቤት ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ መምህራን የተመደቡለት መሆኑን የገለፁት አቶ ሳምሶን የህግ ታራሚ ተማሪዎችም በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁም አመላክተዋል፡፡ አቶ ሳምሶን አክለውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ታራሚዎች ተስፋና መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን ማረሚያ ቤት የህይወት ማብቂያ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው፤ ብለዋል። የህግ ታራሚ ተማሪዎች  ያመጡት ውጤት መታረምና መታነፃቸውን ማሳያ በመሆኑን ገልፀው መንግስት በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን መንገድ አሊያም የትምህርት ሚኒስቴር የሕግ ታራሚ መሆናቸውን በመረዳት ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡   @Freshmerejaet @Freshmerejaet

«የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» — ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በራሳቸው የሶሻል ሚዲያ መድረክ Truth Social ባሰፈሩት አነጋጋሪ መልእክት፣
«የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» — ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በራሳቸው የሶሻል ሚዲያ መድረክ Truth Social ባሰፈሩት አነጋጋሪ መልእክት፣ ስትራቴጂካዊውን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ  ስም ለመቀየር ሀሳብ አቅርበዋል። ትራምፕ ባሰፈሩት መልእክት «አሁን አካባቢውን በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ቁጥጥር ስር ስላደረግነው፣ የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» ሲሉ ጠይቀዋል አክለውም እንደ አሜሪካ ሀገር ሁሉ ቦታው «ከመቼውም ጊዜ በላይ ሳቢና ተፈላጊ  ይሆናል!» ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ይህ የትራምፕ አስተያየት የመጣው በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በሆርሙዝ የባህር መስመር እና በላራክ ደሴት አካባቢ ከፍተኛ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል ፍጥጫ እና ጥቃት በተካሄደበት ወቅት ነው። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ። ​ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁ
በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ። ​ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁኑ ሰዓት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል። ​ግለሰቡ በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት በመሞከራቸው፣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የአምስት ዓመት እስራት እና የ10 ሺህ ብር ቅጣት ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑ ይታወሳል። ​ከእሳቸው ጋር አብረው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸው እንደነበር አይዘነጋም። ተከሳሾቹ የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው ከተፈረደባቸው በኋላ፣ ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ በይፋ ከእስር ተለቀዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter

በባህርዳር ከተማ የቀን ሰራተኛው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆነ 👉 ሽልማቱ ከወሎ ወደ ባህር ዳር ደርሷል የባህር ዳር ነዋሪው ወጣት ኃይሌ እስከዚያው መኮንን በቆረጠው ቶምቦላ ሎተሪ በ4ኛ ዕጣ
+1
በባህርዳር ከተማ የቀን ሰራተኛው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆነ 👉 ሽልማቱ ከወሎ ወደ ባህር ዳር ደርሷል የባህር ዳር ነዋሪው ወጣት ኃይሌ እስከዚያው መኮንን በቆረጠው ቶምቦላ ሎተሪ በ4ኛ ዕጣ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆኗል፡፡ ወጣት ኃይሌ በቀን ስራ የተሰማራ ሲሆን አልፎ አልፎ ህይወቱን ለመቀየር ብዙ ሥራዎችን ይሞክር እንደነበር ገልጾ፤ ከነዚህም አንዱ እና ዋነኛው ሎተሪን መቁረጥ እንደነበር የገለጸ ሲሆን እድልና አጋጣሚ ገጥሞ እድለኛ አድርጎኛል በማለት ሽልማቱን ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በተረከበበት ወቅት በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኖ ገልጾልናል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio

የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት በርካታ ተዋጊዎችን በማንቀሳቀስ ላይ መኾኑን አስታወቀ። ወደ ብሉ ናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ የተንቀሳቀሱት ተዋጊዎች የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ለመውጋት ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር የወገኑ ኃይሎች እንደሆኑ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ጀምሮ በግዛቲቱ በርካታ አካባቢዎች በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክ ከተማ ከአንድ ሳምንት በፊት ከሱዳን ጦር ሠራዊት መንጠቁ ይታወሳል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet

በቻይና ጎዳናዎች ላይ ስራ የጀመረው የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የወደፊቱ የትራፊክ ቁጥጥር አዲሱ ምዕራፍ በምስራቅ ቻይና ዢጂያንግ ግዛት በምትገኘው ዮንግካንግ ከተማ፣ የትራፊክ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የማ
በቻይና ጎዳናዎች ላይ ስራ የጀመረው የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የወደፊቱ የትራፊክ ቁጥጥር አዲሱ ምዕራፍ በምስራቅ ቻይና ዢጂያንግ ግዛት በምትገኘው ዮንግካንግ ከተማ፣ የትራፊክ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የማስተካከል ስራ የሚያግዝ የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የመጀመሪያ የሙከራ ስራውን በይፋ ጀምሯል። ይህ የቴክኖሎጂ ድንቅ ውጤት የሆነው ሮቦት ለ30 ደቂቃ ብቻ በመብራት ከተሞላ በኋላ ለአራት ሰዓታት ያህል ያለምንም እረፍት በተከታታይ መስራት የሚችል ነው። የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው የመንገድ መገናኛዎች ላይ የሚከናወኑ መደበኛና ተደጋጋሚ ተግባራትን በብቃት ለማከናወን ተቀርጾ የተሰራ ነው። ሮቦቱ በተለይም አሽከርካሪዎችንና እግረኞችን በስርዓት የመምራት፣ የመንገድ ላይ ደህንነት ማሳሰቢያዎችን የመስጠትና በትራፊክ መጨናነቅ ወቅት የትራፊክ ፖሊሶችን ስራ በከፍተኛ ደረጃ የማቃለል ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል። ይህ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ውጤት የከተሞችን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አስተዳደር ወደ አዲስ የዘመናዊነት ደረጃ የሚያሸጋግር ድንቅ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል። @Addis_News @Addis_News

የሆንግ ኮንግ አክቲቪስት ጆሹዋ ዎንግ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ ጥፋተኛነቱን አመነ ታዋቂው የሆንግ ኮንግ የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች ጆሹዋ ዎንግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር አብሮ በመስራት እና ማዕቀብ እንዲጣል
የሆንግ ኮንግ አክቲቪስት ጆሹዋ ዎንግ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ ጥፋተኛነቱን አመነ ታዋቂው የሆንግ ኮንግ የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች ጆሹዋ ዎንግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር አብሮ በመስራት እና ማዕቀብ እንዲጣል በመጠየቅ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ የቀረበበትን ክስ ፍርድ ቤት ቀርቦ አምኗል። የ29 ዓመቱ አክቲቪስት እ.ኤ.አ በ2020 በቻይና እና በሆንግ ኮንግ ላይ ማዕቀብ ወይም ማገጃ እንዲጣስ የውጭ ሀገራትን ጠይቋል በሚል በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሷል።ወንጀሉ ከ3 እስከ 10 ዓመታት የሚደርስ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ድርጊቱ ከባድ አደጋ አደረሰ ተብሎ ከታመነ እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ሊደርስበት ይችላል። ዎንግ በአሁኑ ወቅት በመንግስት ላይ በማመፅ ወንጀል የተበየነበትን የአምስት ዓመት ገደማ ቅጣት በመፈጸም ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ከእስር ይፈታል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። ዓቃቤ ሕግ እንዳስታወቀው፣ ዎንግ ዓለም አቀፍ ማዕቀብ እንዲጣል ለመጠየቅ መጣጥፎችን የጻፈና የቀድሞዋ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ ከበርካታ የውጭ ሀገር ፖለቲከኞች ጋር ተገናኝቷል። ክሶቹ ሲነበቡለት በታላቅ ድምፅ ጥፋተኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣ የምዕራባውያን ዲፕሎማቶችም በችሎቱ ላይ ተገኝተዋል። የቅጣት ውሳኔው የሚሰጥበት ቀን በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል።   ሰላማዊ ነጋሲ @Ethionews433 @Ethionews433

የብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብራዚል ጉብኝታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ያደረጉትን ውይይት መ
+2
የብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብራዚል ጉብኝታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ያደረጉትን ውይይት መነሻ በማድረግ ቢሮው መከፈቱን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር መለስ ዓለም ገልጸዋል። ተቋሙ ቢሮውን በአዲስ አበባ መክፈቱ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማላቅ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተመላክቷል። ሀገራቱ የብሪክስ አባል እንደመሆናቸው ትብብራቸውን ወደ ተጨባጭ የንግድ ዕድሎች ለመቀየር እገዛ እንደሚያደርግም ነው የተገለጸው፡፡ በተጨማሪም የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያና በምስራቅ አፍሪካ ገበያ ያሉ የንግድ እድሎችን ለመመልከት የሚያስችል ነው፡፡ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የሚገኙ ባለሀብቶች በብራዚል ያለውን ዕድል ለመመልከት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

የደቡብ ኮሪያ ጠንቋዮች AI ገቢያችንን ክፋኛ ቀንሶብናል ብለው አማረሩ በቴክኖሎጂ ምጥቀት ቀዳሚ ከሆኑት የዓለማችን አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ደቡብ ኮሪያ፣ የቅርብ ጊዜው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዕድገት የዘመናት ታሪክ ባለው የባህላዊ ዕድል ትንበያ (ጥንቆላ) ኢንደስትሪ ላይ ከፍተኛ አደጋ እየደቀነ መሆኑ ተሰማ። በአገሪቱ የሚገኙ ታዋቂ ዕድል ተንባዮችና ጠንቋዮች ወደ እነርሱ ይመጡ የነበሩ ደንበኞቻቸው ፊታቸውን ወደ AI ቴክኖሎጂ በማዞራቸው ምክንያት ሥራቸው ክፉኛ እንደ ተቀዛቀዘባቸው በምሬት በመግለጽ ላይ ናቸው። በዋና ከተማዋ ሴኡል ዳርቻ በሚገኘውና በባህላዊ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) መንደርነቱ በሚታወቀው ‘ሚያ መንደር’ ውስጥ አሁን ላይ የደንበኞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል። ቀደም ባሉ ዓመታት የደቡብ ኮሪያ ነዋሪዎች ስለ ጤናቸው፣ ትዳር፣ ፍቅር፣ ገንዘብ እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸው ለመጠየቅ ወደዚህ መንደር በብዛት ይጎርፉ ነበር። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ አብዛኞቹ ዜጎች በአካል ወደ መንደሩ ከመሄድ ይልቅ በኢንተርኔት አማካኝነት እንደ ChatGPT እና Gemini ያሉ የ-AI መተግበሪያዎችን በመጠቀም ዕድላቸውን መተንበይ መምረጣቸው ተገልጿል። በዚሁ መንደር ውስጥ ከቀሩት ጥቂት ዕድል ተንባዮች መካከል አንዷ የሆኑት የ86 ዓመቷ አዛውንት ሶንግ ኦ-ሱን ሁኔታውን ሲያስረዱ፣ እሳቸው አሁንም ከዘመናዊው የኢንተርኔት ዓለም ርቀው እንደሚኖሩና ዕድልን ለመተንበይ “አራቱ የዕጣ ፈንታ ምሰሶዎች” (Saju) የሚባለውን የኮሪያ ጥንታዊ ኮከብ ቆጠራ ዘዴ በብሬይል መጽሐፍ እያነበቡ እንደሚጠነቁሉ ገልጸዋል። አዛውንቷ ባለፉት 40 ዓመታት ያካበቱት ይህ የሰዎች ስነ-ልቦና የመረዳትና የማማከር ልምድ AI በቀላሉ ሊተካው የማይችለው የላቀ ሰብአዊ ችሎታ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። “በሕይወት የመኖር ተስፋ ቆርጠው ለመሞት እንኳ ወደ እኔ የመጡ ሰዎችን አሳምኜና አጽናንቼ ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉ አድርጌያለሁ” ሲሉም የሥራቸውን ማኅበራዊ ፋይዳ ያስረዳሉ። ይሁን እንጂ የኢኮኖሚው እውነታ ሌላ ሆኗል። ቀደም ሲል በአካባቢው ከ 70 እስከ 80 የሚደርሱ ጠንቋዮች በሥራ ላይ የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ቁጥራቸው ከ20 በታች ዝቅ ብሏል። እንደ ‘ኢንኖፎሬስት’ (Innoforest) የተባለው የደቡብ ኮሪያ የጀማሪ ኩባንያዎች ትንተና ድርጅት መረጃ መሠረት፣ በአገሪቱ ያለው የዕድል ትንበያ ገበያ እጅግ ግዙፍና በ 2024 ብቻ በግምት 986 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የደረሰ ቢሆንም፣ አብዛኛው የገበያ ድርሻ ግን ወደ ዘመናዊ መተግበሪያዎች እየተዛወረ ነው። ለዚህ ሽግግር ዋነኛው ምክንያት የዋጋና የቅልጥፍና ጉዳይ መሆኑ ይነገራል። የ-AI መተግበሪያዎች አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በነጻ ወይም በጣም በዝቅተኛ ክፍያ በሰከንዶች ውስጥ የሚሰጡ ሲሆን፣ በአንጻሩ እንደ ወይዘሮ ሶንግ ያሉ ባህላዊ ባለሙያዎች ለአንድ የዕድል ትንበያ ክፍለ-ጊዜ እስከ 35 ዶላር ገደማ ያስከፍላሉ። ይህ የዋጋ ልዩነትና የቴክኖሎጂው ተደራሽነት፣ ወጣቱ የኮሪያ ትውልድ ከባህላዊው መንደር ይልቅ ስማርት ፎኑን እንዲመርጥ ማድረጉን የዘርፉ ታዛቢዎች ገልጸዋል። 45% - 55% የሚጠጉ ደቡብ ኮርያውያን በህይወት ዘመናቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ የህይወት እጣ ፋንታቸው እንዲተነበይላቸው በመፈለግ ወደ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) ቤት ያመራሉ። Via መዝናኛ ሚዲያ ዳጉ_ጆርናል @Freshmerejaet @Freshmerejaet

✨ ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነ
✨  ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨ 🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው! 🎁 አስደሳች ቦነሶች 💰 የማሸነፍ እድሎች ⚡ ቀላል እና ፈጣን ተሳትፎ 🎊 በየቀኑ አዲስ ደስታ 🏆 አሸናፊ የመሆን እድል 📍ባሉበት ሁነው በ ስልክዎ የሚዝናኑበት ጨዋታ 🌟 ዕድል ለሚሞክሩት በሩን ትከፍታለች! 🌟 ድል ለሚደፍሩት ትመጣለች! 🔥 ዛሬ ይቀላቀሉ! 🔥 ይጫወቱ! 🔥 ይዝናኑ! 🔥 ዕድልዎን ይሞክሩ @BellaBingo1bot ለማንኛውም እገዛ --09 72 75 73 19 ይደውሉ 💙 Bella Bingo – የደስታ፣ የዕድል እና የአሸናፊዎች ምርጫ!