fa
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

رفتن به کانال در Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Fresh መረጃ | FreshNews

کانال Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 58 402 مشترک است و جایگاه 2 909 را در دسته آموزش و رتبه 540 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 58 402 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 17 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -2 195 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -83 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 4.40% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 575 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 719 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

58 402
مشترکین
-8324 ساعت
-4087 روز
-2 19530 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئن '26
ژوئن '26
+2
در 7 کانال‌ها
مه '260
در 8 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+3
در 8 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+1 303
در 14 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '260
در 4 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '260
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '250
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+1
در 6 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '250
در 4 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '250
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اوت '250
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '250
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '250
در 6 کانال‌ها
Get PRO
مه '250
در 2 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '250
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '250
در 10 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '250
در 18 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+44
در 10 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+1 502
در 16 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+4 897
در 9 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+10 897
در 6 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+13 478
در 5 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+17 234
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+9 021
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+20
در 7 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+351
در 14 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+847
در 16 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+558
در 33 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+1 785
در 15 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+3 011
در 18 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+3 094
در 23 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+730
در 120 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+13 017
در 37 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+26 548
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+2 062
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+2 838
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+554
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+672
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+1 658
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+3 193
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+1 734
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+895
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+1 925
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+642
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+99
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+547
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+1 026
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+1 241
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+1 528
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+2 018
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+329
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+370
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+390
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+639
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+596
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+736
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+1 209
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+1 351
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+1 280
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+1 459
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
18 ژوئن0
17 ژوئن0
16 ژوئن+1
15 ژوئن0
14 ژوئن0
13 ژوئن0
12 ژوئن0
11 ژوئن+1
10 ژوئن0
09 ژوئن0
08 ژوئن0
07 ژوئن0
06 ژوئن0
05 ژوئن0
04 ژوئن0
03 ژوئن0
02 ژوئن0
01 ژوئن0
پست‌های کانال
ቼክ ሪፐብሊክ 1-1 ደቡብ አፍሪካ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩ በተቆጠረ ፍጹም ቅጣት ምት ሁለቱም ሀገራት ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል። ቼኮች ገና በጨዋታው መጀመሪያ በ6ኛው ደቂቃ ላይ
ቼክ ሪፐብሊክ 1-1 ደቡብ አፍሪካ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩ በተቆጠረ ፍጹም ቅጣት ምት ሁለቱም ሀገራት ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል። ቼኮች ገና በጨዋታው መጀመሪያ በ6ኛው ደቂቃ ላይ በሳድሌክ አማካኝነት መሪነቱን በመያዝ ጨዋታውን በጥሩ መነሳሳት ቢጀምሩም፣ የደቡብ አፍሪካው የባፋና ባፋና ኮከብ ተጫዋች ሞኩዌና በ83ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን ፍጹም ቅጣት ምት በጥራት ወደ ጎል በመቀየር ሀገሩን ከሽንፈት ታድጓል። በመጨረሻዎቹ የባክኖ ሰዓት ደቂቃዎች ላይ ጨዋታው በከፍተኛ መነሳሳት እና ውጥረት የቀጠለ ቢሆንም፣ ተጨማሪ ጎል ሳይቆጠር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

2
ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል የሚሉ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መረጃዎች ናቸው ተባለ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪትም ሆነ ምዝገባ እስካሁን አልተጀመረም ሲል አስታውቋል።
ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል የሚሉ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ  መረጃዎች ናቸው ተባለ   የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪትም ሆነ ምዝገባ እስካሁን አልተጀመረም ሲል አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ፣ ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል በሚል ስም የሚሰራጩ ማስታወቂያዎች ሀሰተኛ መሆናቸውን ገልጾ ዜጎች እንዳይታለሉ አሳስቧል።   በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ ከጆርዳን፣ ከኳታር እና ከሊባኖስ ጋር ባላት የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት ብቻ ህጋዊ የሥራ ስምሪት እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።   መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር ስምምነት የፈጸመው ሚኒስቴሩ ወጣቶችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ተወዳዳሪ ማድረግና የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማመቻቸት መሆኑን ጠቅሷል።በተጨማሪም ወደ ካናዳ እንልክዎታለን በሚል ሰበብ ገንዘብ የሚጠይቁ አካላት አጭበርባሪዎች መሆናቸውን ጠቁሞ  ለማንኛውም ፕሮግራም ክፍያ እንደማይጠየቅ መግለፁን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል ።   በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል
846
3
አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ40 አገራት ለሰብዓዊ ዕርዳታና ለአደጋ ምላሽ የሚውል 1 ቢሊዮን ዶላር ለተመድ ሕጻናት ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ለመስጠት ወሠነች። ከገንዘብ ድጋፉ 800 ሚሊዮን ዶላሩ ለዓለም የምግብ ፕሮግራም የሚሠጥ ሲሆን፣ 218 ሚሊዮን ዶላር ደሞ ለዩኒሴፍ እንደሚሠጥ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ገልጧል። ገንዘቡ ለሁለቱ ድርጅቶች የተፈቀደው፣ የእርዳታ አሠጣጣቸው ሊለካ የሚችል ውጤት የሚያስመዘግብና ተጠያቂነትን የሚያሠፍን በመኾኑ እንደኾነ መስሪያ ቤቱ ጠቅሷል። ድርጅቶቹ፣ ገንዘቡን ለምግብ እርዳታ፣ ለአልሚ ምግብ አቅርቦት፣ ለጤና፣ ለሕጻናት እንክብካቤ፣ ለሎጅስቲክ እንዲሁም ለውሃና ንጽህና አጠባበቅ እንዲያውሉት ተፈቅዶላቸዋል። ከገንዘብ ድጋፉ ተጠቃሚ ከሚኾኑት አገራት መካከል ከኢትዮጵያ በተጨማሪ፣ በርማ እና ዩክሬን ይገኙበታል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
861
4
#TPLF አሜሪካ በህወሓት (TPLF) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የእገዳ ጣለች። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህ+1
#TPLF አሜሪካ በህወሓት (TPLF) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የእገዳ ጣለች። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቀዋል። ውሳኔው የተላለፈው በስደተኞችና ዜግነት አዋጅ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ እገዳው በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በሚያስተጓጉሉ " አክራሪ አቋም " ባላቸው አባላትና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ በህወሓት አመራሮችና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የሰሜን ኢትዮጵያን ሰላም ዳግም ስጋት ላይ መጣሉን ጠቅሷል። በተለይም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች (TSF) እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል የተከሰተው ቀጥተኛ ግጭት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የተገኘውን አንጻራዊ መረጋጋት የሚፈታተን መሆኑ አመልክቷል። አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይን ጨምሮ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መደገፏን እንደምትቀጥል የገለጸው መግለጫው፤ በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን በሚያናጉ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ያሉትን አማራጮች ሁሉ ጥቅም ላይ እንደምታውል አስታውቃለች። የቪዛ ማዕቀብ የተጣለባቸው የህወሓት (TPLF) አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ስም በይፋ አልተገለጸም። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
951
5
የ"ፊንቴክ" የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ የ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ በተፈጸመ መጠነ-ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ታዋቂ አርቲስቶች እና የቲክቶክ አንቂዎ
የ"ፊንቴክ" የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ የ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ በተፈጸመ መጠነ-ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ታዋቂ አርቲስቶች እና የቲክቶክ አንቂዎች በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ፊት ቀርበዋል። በእስር ላይ የሚገኘውን 5ኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማልን ጨምሮ፣ በዋስትና መብት በውጭ ሆነው ጉዳያቸውን የሚከታተሉት ቀሪዎቹ ተጠርጣሪዎች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው በጠበቆቻቸው አማካኝነት የክስ መቃወሚያ አቅርበዋል። የ1ኛ ተከሳሽ ጠበቆች የ5 ገፅ፣ እንዲሁም የሌሎቹ ተከሳሾች ጠበቆች እያንዳንዳቸው ባለ 6 ገፅ የክስ መቃወሚያ ለችሎቱ ያስገቡ ቢሆንም፤ የቀረበለትን ሰፊ የክስ መቃወሚያ በዛሬው ዕለት ተመልክቶ ምላሽ መስጠት እንደማይችል አቃቤ ህግ ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግን ጥያቄ በመቀበል፣ የቀረቡትን የክስ መቃወሚያዎች መርምሮ ምላሽ ለመስጠት ለሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ሸገር ኤፍ ኤም @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 246
6
በጋዛ ከእስራኤል ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ወዲህ ከ1ሺ በላይ ሰዎች መገደላቸዉ ተሰማ በዩናይትድ ስቴትስ አደራዳሪነት በሃማስ እና በእስራኤል መካከል በጥቅምት ወር በተደረገው “የተኩስ አ
በጋዛ ከእስራኤል ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ወዲህ ከ1ሺ በላይ ሰዎች መገደላቸዉ ተሰማ   በዩናይትድ ስቴትስ አደራዳሪነት በሃማስ እና በእስራኤል መካከል በጥቅምት ወር በተደረገው “የተኩስ አቁም” ስምምነት ከተደረሰ በኋላ በጋዛ ከ1,000 በላይ ሰዎች ሲገደሉ በአከባቢዉ ያለው ሰብአዊ ሁኔታ አሁንም አስከፊ ሆኖ ቀጥሏል።የፍልስጤም ጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው እስራኤል በጋዛ ላይ በፈጸመችዉ ጥቃት ከተኩስ አቁሙ ወዲህ 1,005 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል ።   “ጋዛ ሌላ አሳዛኝ ምዕራፍ ላይ ስትደርስ አዝነናል፤ እጅግ የከፋው ደግሞ ጦርነቱ መጠናቀቁ የተነገራቸው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም የሚወዷቸውን እየቀበሩ ነዉ” ሲሉ ለፍልስጤማውያን የህክምና እርዳታ የጋዛ ዳይሬክተር ፊክር ሻልቱት ተናግረዋል።የተኩስ አቁም” ትልቁን ጦርነት አቁሟል፣ ነገር ግን ሁለተኛውን እና ይበልጥ አሳሳቢ የሆነው  የእስራኤል ወታደሮች ከጋዛ የሚወጡበት እና ሃማስ ትጥቅ የሚፈቱበት የስምምነት ምዕራፍ ተግባራዊ ለማድረግ ስምምነት ላይ አልደረሱም ሲሉ አክለዋል።   ከጥቅምት ወር ጀምሮ እስራኤል በፍልስጤም ግዛት ላይ የምትገኝ ሲሆን 64 በመቶውን የጋዛ ሰርጥ ተቆጣጥራለች ፣ ይህም በስምምነቱ ከታቀደው 53 ከመቶ ብቻ ነዉ፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (ኦቻ) እንዳስታወቀው ባለፈው አርብ፣ በምስራቅ ጋዛ ከተማ በደርዘን የሚቆጠሩ ቤተሰቦች የእስራኤል ወታደሮች ቢጫ መስመር እየተባለ የሚጠራውን ወደ ምዕራብ መስፋፋቱን የሚጠቁሙ ቢጫ ሲሚንቶ ብሎኮች ካስቀመጡ በኋላ ለመሰደድ ተገደዋል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
1 194
7
በሳውላ ከተማ የ8ተኛ ክፍል ፈተና ለሰው ሊፈተኑ የገቡ መምህርና ተማሪ በፖሊስ ተያዙ በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መ+2
በሳውላ ከተማ የ8ተኛ ክፍል ፈተና ለሰው ሊፈተኑ የገቡ መምህርና ተማሪ በፖሊስ ተያዙ በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው። ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል። የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል። በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል። @Seledadotio @Seledadotio
1 425
8
የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 38.23 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈሪ መኮንን በ2018 በጀት አመት
የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 38.23 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈሪ መኮንን በ2018 በጀት አመት በአስራ አንድ ወራት 42.49 ቢሊዮን ብር ጥቅል ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 38.23 ቢሊዬን ብር ገቢ መሰበሰቡን አስታውቀዋል፡፡ የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ3.97 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 273
9
ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ አሽቆለቆለ። በአሜሪካና ኢራን መካከል ለወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆምና የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ያለመ ጊዜያዊ ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ቀንሷል።
ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ አሽቆለቆለ። በአሜሪካና ኢራን መካከል ለወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማስቆምና የሆርሙዝ ሰርጥን ለመክፈት ያለመ ጊዜያዊ ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ቀንሷል። እንደ ሮይተርስ ዘገባ የተፈረመው ስምምነት በአቅርቦት ላይ የነበረውን ስጋት በማቃለሉ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል 78.66 ዶላር ሆኗል። በተመሳሳይ ፣ የዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዲየት (WTI) ዋጋም ወርዶ በበርሜል $75.81 ሆኖ ተመዝግቧል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 442
10
بدون متن...
1 388
11
ድምፃችን ይሰማ ተፈታኞች ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል የፋርማሲ ተማሪዎች ፈተናችን ተሰርቋል ፈተና ከመግባታችን በፊት ተሰራጭቷል ብለዋል። እንዲህም ሲሉ ለየኔቲዩብ ቅሬታቸው አሰምተዋል። እኛ የፋርማሲ ተ
ድምፃችን ይሰማ ተፈታኞች ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል የፋርማሲ ተማሪዎች ፈተናችን ተሰርቋል ፈተና ከመግባታችን በፊት ተሰራጭቷል ብለዋል። እንዲህም ሲሉ ለየኔቲዩብ ቅሬታቸው አሰምተዋል። እኛ የፋርማሲ ተማሪዎች ስንሆን ትላንት እለት ማለት ሰኔ 1ዐ የ2018 የመውጫ ፈተና ወስደናል ። ቢሆንም ግን የዛሬው የፋርማሲ exit ፈተና ቀድሞ ተሰርቆ ለበርካታ ተማሪዎች እንደተሰራጨ እኛ ተማሪዎች መረጃው ደርሶናል። ይህ በመሆኑ እኛ ተማሪዎች በእጅጉ አዘነናል።ምክንያቱ እኛ ተማሪዎች ለዚህ ፈተና ብዙ ልፋታ ና ድካም አይተን እዚህ ብንደረስም አንዳንድ አላፊናት በማይሰማቸው ሰዎች ምክንያት ፈተና ተሰርቆ ለተማሪዎች እንደተሰራጨ ሙሉ መረጃ አለን፡፡ ስለሆነም ጉዳዬ በእስቸኳይ ተይቶልን ተገቢ  መልስ እንዲሰጠን EPA ለሚመለከታው አካል ድምፅችንን ተሰሙልን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን @Addis_News @Addis_News
1 417
12
የአሜሪካ እና የኢራን ፕሬዚዳንቶች የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራረሙ፤ ትራምፕ ግን ዳግም ጥቃት ሊጀምሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ! አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም በፕሬዚዳንቶቻቸው መካከል የተፈረመውን የጊዜያዊ ስምምነት ይዘት ረቡዕ ዕለት ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን ኢራን የገባችውን ቃል የማታከብር ከሆነ ጥቃቶችን ዳግም ለመጀመር እና የኢራን ባለሥልጣናትን ለመግደል ዝተዋል። በ #ፈረንሳይ ከሌሎች የዓለም መሪዎች ጋር በቡድን 7 ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ትራምፕ፣ ቀደም ሲል የኢራንን የባለስቲክ ሚሳይሎች ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ቁርጠኛ የነበሩ ቢሆንም፤ አሁን ላይ ግን #ቴህራን የባለስቲክ ሚሳይሎች እንዳይኖሯት ማድረግ «ኢ-ፍትሐዊ» ነው በማለት፣ በመጀመሪያ ደረጃ ላይ ኢራንን ለማጥቃት ካስቀመጧቸው ምክንያቶች መካከል ቢያንስ አንዱን አንስተዋል።  ትራምፕ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ ኢራን ሲናገሩ «ስምምነቱን ከጣሱ ክፉኛ እንደበድባቸዋለን። ይህ እንዲሆን ግን አልፈልግም፤ ስምምነቱን እንዲያከብሩ ነው የምሻው» ብለዋል። የአሜሪካ እና የኢራን ተደራዳሪዎች በሚቀጥሉት 60 ቀናት ውስጥ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እየሠሩ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ ትራምፕ ኢራናውያንን «ብልህ ሕዝቦች» ሲሉ የጠሯቸው ሲሆን፤ ይህ ሂደት በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምን እንደሚያሰፍን እና የነዳጅ ዋጋን እንደሚቀንስ ተስፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። ቀደም ሲልም ትራምፕ «ጉዳዩ ካልተመቸኝ ወይም መልካም ምግባር ካላሳዩ፣ በቀጥታ በአናታቸው ላይ ቦምብ ወደ መጣል እንመለሳለን» ሲሉ ተናግረው ነበር። የኢራን መሪዎች ለቀረበባቸው አዲስ ዛቻ ምላሽ ያልሰጡ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ. በ1979 የኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ከተመሠረተች በኋላ በአሜሪካ እና በኢራን ፕሬዚዳንቶች በጋራ የተፈረመ የመጀመሪያው ነው ተብሎ የታመነበትን የስምምነት ፎቶግራፎች ይፋ አድርገዋል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 326
13
በጂንካ ማረሚያ ተቋም 31 የህግ ታራሚዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈተኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኘው የጂንካ ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚ ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መስጠቱ+2
በጂንካ ማረሚያ ተቋም 31 የህግ ታራሚዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈተኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኘው የጂንካ ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚ ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መስጠቱን አስታዉቋል፡፡ይህ እርምጃ ታራሚዎች በማረሚያ ተቋማት ውስጥ እያሉም ቢሆን የትምህርት እድላቸውን እንዳያጡ እና ለተሻለ የወደፊት ህይወት እንዲዘጋጁ የሚያግዝ ተግባር መሆኑ ተጠቁሟል። የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ኔሬሬ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተማሪዎቹ  ፈተናውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ በትኩረትና በተረጋጋ መንፈስ እንዲሰሩ ምክር እና ማበረታቻ ተሰጥቷቸዋል።ለፈተናው ስኬታማነት አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች  መደረጋቸውን ያስረዱት ምክትል ኮማንደሩ በዘንድሮው አመት በማረሚያ ተቋሙ የ6ኛ ክፍል ፈተና 31 ታራሚዎች መዉሰዳቸዉን ገልፀዋል።ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ሴቶች ናቸው። የታራሚዎች ትምህርት እና የሙያ ስልጠና በዘመናዊ የማረሚያ ሥርዓት ውስጥ ዋነኛ አካል ተደርጎ ይወሰዳል። በተለይም ታራሚዎች ከቅጣታቸው በኋላ ወደ ማህበረሰቡ በተሻለ ሁኔታ እንዲመለሱ፣ እውቀትና ክህሎት አግኝተው ራሳቸውን በአዎንታዊ መንገድ እንዲያሻሽሉ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል። በመባ ወርቅነህ @Ethionews433 @Ethionews433
1 487
14
ግብጽ በሱዳናዊያን ማዕድን አውጭዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመች። በግብፅ እና በሱዳን መካከል ለረጅም ዘመናት አወዛጋቢ ሆኖ በቆየው "የሀላይብ ትሪያንግል" (Halaib Triangle) ግዛት ውስጥ የ
ግብጽ በሱዳናዊያን ማዕድን አውጭዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመች። በግብፅ እና በሱዳን መካከል ለረጅም ዘመናት አወዛጋቢ ሆኖ በቆየው "የሀላይብ ትሪያንግል" (Halaib Triangle) ግዛት ውስጥ የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች በፈጸሙት ድንገተኛ የአየር ጥቃት ቢያንስ የሰባት ሱዳናዊያን ወርቅ አውጪዎች ሕይወት ማለፉ ተዘገበ። ጥቃቱ የተፈጸመው በዚሁ አወዛጋቢ ቀጠና ውስጥ በሚገኘው "ጀበል አል ኡቃያት" በተሰኘው የወርቅ ማውጫ ስፍራ ላይ ነው። እንደ የአይን እማኞች እና የአካባቢው መረጃዎች ከሆነ፣ በጥቃቱ ወቅት የግብፅ የጦር ሄሊኮፕተሮች በስፋት የታዩ ሲሆን ከሰባቱ ሟቾች በተጨማሪ በአስር የሚቆጠሩ ዜጎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል። በአሁኑ ሰዓት ሱዳን በከፋ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኝ ሲሆን፣ የግብፅ መንግስት ደግሞ የጄነራል አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን የሚመራውን የሱዳን ጦር (SAF) በግልጽ በመደገፍ የቅርብ ወዳጅ ሆና እየሰራች ነው። ግብፅ ለሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ ድጋፍ በምትሰጥበት በዚህ ወቅት ግን በድንበር አካባቢ የሚገኙ ሱዳናዊያንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈጸሟ በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ጥያቄን ጭሯል። የሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዜጎቹ በግብፅ ጦር መገደላቸው እየታወቀ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ይፋዊ መግለጫ አለመስጠቱ እና ዝምታን ጉዳዩን አስገራሚ አድርጎታል። ይህ ዝምታ በሱዳን ህዝብ ዘንድ "መንግስት ለወታደራዊ ድጋፍ ሲል የዜጎቹን ደህንነት ችላ ብሏል" የሚል ቅሬታን እየቀሰቀሰ ይገኛል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 543
15
የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው! በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋ+1
የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው! በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል። በህዳሴ ግድብ ዙሪያ "ድርድር ለማስጀመር" ሁሉ ማቀዳቸውን እየተናገሩ ናቸው። በፈረንሳይ የቡድን 7 ጉባዔ ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ ጋር የተገናኙት ትራምፕ፤ የዓባይ ግድብ "ውዝግብንም በድጋሚ ይጀመራል" ሲሉ ተደምጠዋል። ከሁለትዮሽ ውይይት በኋላ “ከግብጹ ፕሬዝዳንት፣ ከጓደኛዬ ጋር በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። እሳቸው በመላው ዓለም የተከበሩ ናቸው... ግንኙነታችንም በግል ደረጃ ለረጅም ጊዜ በጣም ጠንካራ ሆኖ ቆይቷል" ሲሉ ተደምጠዋል። ከአልሲሲ ጋር ጥሩ ወዳጅነት እንዳላቸው የገለፁት ትራምፕ፣ "ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ነው የተገነባው" በማለት ገልጸዋል። "ግዙፍ ግድብ" ሲሉ በጠሩት የህዳሴ ግድብ ላይ "መፍትሔ የሚያመጣ ውይይት እናስጀምራለን" ያሉት ፕሬዝዳንቱ “የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉም ገልጸዋል። "በኢትዮጵያ የተገነባው ግድብ በግብፅ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ ነው" በማለትም የተለመደ ግጭት ቀስቃሽ ንግግር አድርገዋል። ትራምፕ ለአል-ሲሲ ሲናገሩ "እውነቱን ማወቅ ከፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጣም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ነው የተያዛችሁት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አነሳስተዋቸዋል።  #aljazeera @Seledadotio @Seledadotio
1 825
16
ከእግር ኳስ በላይ... የቮዚንሃ እናት እና የአሜሪካ መንግስት አስገራሚ ውሳኔ በ2 ቀን ውስጥ ከ50 ሺህ Followers ወደ 12.1 ሚሊዮን Followers የገባው። የአሜሪካ መንግስት የኬፕ ቨርዱ+1
ከእግር ኳስ በላይ... የቮዚንሃ እናት እና የአሜሪካ መንግስት አስገራሚ ውሳኔ በ2 ቀን ውስጥ ከ50 ሺህ Followers ወደ 12.1 ሚሊዮን Followers የገባው። የአሜሪካ መንግስት የኬፕ ቨርዱን ኮከብ ግብ ጠባቂ ቮዚንሃን (Vozinha) እናት ወደ አሜሪካ ለማምጣት በይፋ ጥረት እያደረገ ይገኛል! ቮዚንሃ በዓለም ዋንጫው ላይ ድንቅ ብቃቱን አሳይቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቪዛ እጥረት እና በከፍተኛ ክፍያ ምክንያት እናቱ ከጎኑ መሆን አለመቻሏ ይታወሳል። አሁን ግን ይህ ትልቅ ህልሙ እውን ሊሆን ተቃርቧል። እግር ኳስ ከጨዋታ በላይ ነው። ስለ ቤተሰብ፣ ስለ መስዋዕትነት እና ስለ ፍቅር ጭምር ነው! ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ እናቱ በቅርቡ ከልጇ ጋር እንድትገናኝ ሲጫወት በስታዲየም ውስጥ ሆና እንድታየው የብዙዎች ምኞት ነው። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 749
17
"አዲስ አበባ ጎርፍ ብትጠቃ አደጋው የደረሰበት ክፍለ ከተማ ይጠየቃል!"  ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተያዘው ክረምት “በአዲስ አበባ ውስጥ ጎርፍ ቢያጋጥም ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ” ተናገሩ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተያዘው ክረምት “የጎርፍ አደጋዎች አጋጥመው፣ ሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ቢያደርሱ፣ ከማንም በላይ ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ” አስጠነቀቁ፡፡ ከንቲባዋ ይህንን ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተደዳደር የ90 ቀናት መሪ እቅድ የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ “ሕዝብ ውስጥ ትውላላችሁ፣ ታድራላችሁ፤ ትሰራላችሁ” ያሉት አዳነች፣ “ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርባችሁ፣ ችግሩን ታውቃላችሁ፣ ዋና ማእከል ሁሉንም ችግር ማወቅ አይጠበቅበትም” ብለዋል፡፡ መንግስት አሁን ያለውን የከተማ እድሳት አካሂዶ “የክረምት ጎርፍ ሰው አጠቃ የሚል..አይገባንም (ዲዘርቭ አናደርግም)” ሲሉ የተደመጡት ከንቲባዋ፣ መንገዶች ሲሰሩ የታለፉ ቦታዎች ካሉ በአፋጣኝ መጠገን እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ክፍለ ከተሞች በበጎ ፍቃድ ስራዎች አዳዲስ የጎርፍ መውረጃ መተላላፊያዎችን መጠገን፣ አዲስ ካስፈለገም መገንባት የግድ መሆኑን አጽዕኖት ሰጥተው አስምረውበታል፡፡ በተጨማሪም በማብራሪያቸወው መንግስት የጀመራቸው ቤቶች ለመጨረስ ማቀዱን፣ የጭቃ ቤቶች ግንባታ መቆሙን፣ ጠጋግኖ ቁጥር ለማብዛት የሚደረገው አካሄድ እንደቀረም አስረድተዋል፡፡ ከዛ ይልቅ ክፍለ ከተሞች የተለያዩ በጎ ፍቃደኞች በማስተባባር የበጎ ፍቃድ ቤቶች እንዴት ሊሰሩ እንደሚችሉ ማሰብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 651
18
የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ መከላከያ አታሼ በአውሶም ድጋፍ ዙሪያ ተወያዩ የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ የመከላከያ አታሼ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የደኅንነት ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር
የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ መከላከያ አታሼ በአውሶም ድጋፍ ዙሪያ ተወያዩ የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ የመከላከያ አታሼ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የደኅንነት ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር በሞቃዲሹ መምከራቸው ተገልጿል። ይህ ውይይት ሶማሊያ የደኅንነት ሽግግሯን እያፋጠነችና በአል-ሸባብ ላይ የምታደርገውን ዘመቻ በቀጠለችበት በዚህ ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን ወታደራዊ ትስስር በግልጽ የሚያመላክት ነው። እንደ ሒራን ኦንላይን ዘገባ፤ የሶማሊያ ሔራዊ ጦር አዛዥ ሜጀር ጀነራል ኢብራሂም መሐመድ ማሕሙድ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሶማሊያ የግብፅ መከላከያ አታሼ ከሆኑት ሜጀር ጀነራል አሕመድ ፋትሂ አብደልሰታር ጋር ተገናኝተው መክረዋል። በውይይታቸውም ወታደራዊ ሥልጠናን፣ ለሶማሊያ ኃይሎች የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እና በአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና መረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ማዕቀፍ ውስጥ የሚደረገውን ትብብር ጨምሮ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 707
19
ትራምፕ በዩክሬን ሰላም እንዲወርድ ግፊት እንደሚያደርጉ ተናገሩ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ በተካሄደው የጂ7 መሪዎች ጉባኤ ላይ ከፕሬዘዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር “በጣም ጥሩ”
ትራምፕ በዩክሬን ሰላም እንዲወርድ ግፊት እንደሚያደርጉ ተናገሩ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ በተካሄደው የጂ7 መሪዎች ጉባኤ ላይ ከፕሬዘዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር “በጣም ጥሩ” ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት ማድረግ እንዳለባትና እርሳቸውም ጦርነቱን ለማቆም የሚችሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ትራምፕ በጦርነቱ በርካታ ወጣቶች እያለቁ መሆኑን በመጥቀስ “እኔ ስምንት ጦርነቶችን አስቆሜያለሁ ይህኛው ግን ለመፍታት በጣም ቀላሉ ይሆናል ብዬ ያሰብኩት ነበር” ብለዋል። ይሁን እንጂ ስምንት ጦርነቶችን አስቆሜያለሁ ማለታቸው በሰፊው አከራካሪ ሆኗል። ዘለንስኪ ከጂ7 መሪዎች፣ ከትራምፕ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ጋር ከተወያዩ በኋላ በኤክስ  ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፥ ዋናው ትኩረት የዩክሬንን የአየር መከላከያ ማጠናከርና ዲፕሎማሲውን ማራመድ እንደሆነ ገልጸዋል። ከጂ7 መሪዎች ጠቃሚ የሆኑ የቃል ኪዳን ድጋፎችን ተጨማሪ ሚሳኤሎች፣ የማምረቻ ፈቃድ እና የክረምት ድጋፍ ማግኘታቸውን የገለጹት ዘለንስኪ፥ አሜሪካ ለዚህ ሁሉ ዋስትና ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን አክለዉ ተናግረዋል ። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 743
20
ወደ መቀሌ‼️ የአሜሪካ ኤምባሲ ልዑክ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ ሊያመራ መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ
ወደ መቀሌ‼️ የአሜሪካ ኤምባሲ ልዑክ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ ሊያመራ መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል። በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ ከተማ ያቀናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ያገኘውነው መረጃ ያመለክታል። ስለ ጉብኝቱ ዋና ዓላማ፣ ስለ ልዑካን ቡድኑ አባላት ማንነት እስካሁን በይፋ የተገለጸ ነገር የለም። ይሁን እንጂ በመቐለ ከህወሓት አመራሮች ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ጉዞ በህወሓት እና በፌዴራል መንግሥቱ መካከል እየተካረረ የመጣውን ውጥረት ለማርገብ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል። @Addis_News @Addis_News
1 703