Fresh መረጃ | FreshNews
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Fresh መረጃ | FreshNews
کانال Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 58 443 مشترک است و جایگاه 2 909 را در دسته آموزش و رتبه 540 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 58 443 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 17 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -2 195 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -83 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 4.40% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.94% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 575 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 719 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ።
ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇
@Freshes_newsbot
Fresh News,Fresh Updates.”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 18 ژوئن | 0 | |||
| 17 ژوئن | 0 | |||
| 16 ژوئن | +1 | |||
| 15 ژوئن | 0 | |||
| 14 ژوئن | 0 | |||
| 13 ژوئن | 0 | |||
| 12 ژوئن | 0 | |||
| 11 ژوئن | +1 | |||
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | 0 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | بدون متن... | 437 |
| 3 | ድምፃችን ይሰማ ተፈታኞች
ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል የፋርማሲ ተማሪዎች ፈተናችን ተሰርቋል ፈተና ከመግባታችን በፊት ተሰራጭቷል ብለዋል።
እንዲህም ሲሉ ለየኔቲዩብ ቅሬታቸው አሰምተዋል።
እኛ የፋርማሲ ተማሪዎች ስንሆን ትላንት እለት ማለት ሰኔ 1ዐ የ2018 የመውጫ ፈተና ወስደናል ።
ቢሆንም ግን የዛሬው የፋርማሲ exit ፈተና ቀድሞ ተሰርቆ ለበርካታ ተማሪዎች እንደተሰራጨ እኛ ተማሪዎች መረጃው ደርሶናል።
ይህ በመሆኑ እኛ ተማሪዎች በእጅጉ አዘነናል።ምክንያቱ እኛ ተማሪዎች ለዚህ ፈተና ብዙ ልፋታ ና ድካም አይተን እዚህ ብንደረስም አንዳንድ አላፊናት በማይሰማቸው ሰዎች ምክንያት ፈተና ተሰርቆ ለተማሪዎች እንደተሰራጨ ሙሉ መረጃ አለን፡፡
ስለሆነም ጉዳዬ በእስቸኳይ ተይቶልን ተገቢ መልስ እንዲሰጠን EPA ለሚመለከታው አካል ድምፅችንን ተሰሙልን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን
@Addis_News
@Addis_News | 727 |
| 4 | የአሜሪካ እና የኢራን ፕሬዚዳንቶች የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራረሙ፤ ትራምፕ ግን ዳግም ጥቃት ሊጀምሩ እንደሚችሉ አስጠነቀቁ!
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም በፕሬዚዳንቶቻቸው መካከል የተፈረመውን የጊዜያዊ ስምምነት ይዘት ረቡዕ ዕለት ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን ኢራን የገባችውን ቃል የማታከብር ከሆነ ጥቃቶችን ዳግም ለመጀመር እና የኢራን ባለሥልጣናትን ለመግደል ዝተዋል።
በ #ፈረንሳይ ከሌሎች የዓለም መሪዎች ጋር በቡድን 7 ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ትራምፕ፣ ቀደም ሲል የኢራንን የባለስቲክ ሚሳይሎች ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ቁርጠኛ የነበሩ ቢሆንም፤ አሁን ላይ ግን #ቴህራን የባለስቲክ ሚሳይሎች እንዳይኖሯት ማድረግ «ኢ-ፍትሐዊ» ነው በማለት፣ በመጀመሪያ ደረጃ ላይ ኢራንን ለማጥቃት ካስቀመጧቸው ምክንያቶች መካከል ቢያንስ አንዱን አንስተዋል።
ትራምፕ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለ ኢራን ሲናገሩ «ስምምነቱን ከጣሱ ክፉኛ እንደበድባቸዋለን። ይህ እንዲሆን ግን አልፈልግም፤ ስምምነቱን እንዲያከብሩ ነው የምሻው» ብለዋል። የአሜሪካ እና የኢራን ተደራዳሪዎች በሚቀጥሉት 60 ቀናት ውስጥ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እየሠሩ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ ትራምፕ ኢራናውያንን «ብልህ ሕዝቦች» ሲሉ የጠሯቸው ሲሆን፤ ይህ ሂደት በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምን እንደሚያሰፍን እና የነዳጅ ዋጋን እንደሚቀንስ ተስፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ቀደም ሲልም ትራምፕ «ጉዳዩ ካልተመቸኝ ወይም መልካም ምግባር ካላሳዩ፣ በቀጥታ በአናታቸው ላይ ቦምብ ወደ መጣል እንመለሳለን» ሲሉ ተናግረው ነበር።
የኢራን መሪዎች ለቀረበባቸው አዲስ ዛቻ ምላሽ ያልሰጡ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ. በ1979 የኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ከተመሠረተች በኋላ በአሜሪካ እና በኢራን ፕሬዚዳንቶች በጋራ የተፈረመ የመጀመሪያው ነው ተብሎ የታመነበትን የስምምነት ፎቶግራፎች ይፋ አድርገዋል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 683 |
| 5 | በጂንካ ማረሚያ ተቋም 31 የህግ ታራሚዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈተኑ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኘው የጂንካ ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚ ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መስጠቱን አስታዉቋል፡፡ይህ እርምጃ ታራሚዎች በማረሚያ ተቋማት ውስጥ እያሉም ቢሆን የትምህርት እድላቸውን እንዳያጡ እና ለተሻለ የወደፊት ህይወት እንዲዘጋጁ የሚያግዝ ተግባር መሆኑ ተጠቁሟል።
የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ኔሬሬ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተማሪዎቹ ፈተናውን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ በትኩረትና በተረጋጋ መንፈስ እንዲሰሩ ምክር እና ማበረታቻ ተሰጥቷቸዋል።ለፈተናው ስኬታማነት አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ያስረዱት ምክትል ኮማንደሩ በዘንድሮው አመት በማረሚያ ተቋሙ የ6ኛ ክፍል ፈተና 31 ታራሚዎች መዉሰዳቸዉን ገልፀዋል።ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ሴቶች ናቸው።
የታራሚዎች ትምህርት እና የሙያ ስልጠና በዘመናዊ የማረሚያ ሥርዓት ውስጥ ዋነኛ አካል ተደርጎ ይወሰዳል። በተለይም ታራሚዎች ከቅጣታቸው በኋላ ወደ ማህበረሰቡ በተሻለ ሁኔታ እንዲመለሱ፣ እውቀትና ክህሎት አግኝተው ራሳቸውን በአዎንታዊ መንገድ እንዲያሻሽሉ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል።
በመባ ወርቅነህ
@Ethionews433 @Ethionews433 | 837 |
| 6 | ግብጽ በሱዳናዊያን ማዕድን አውጭዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈጸመች።
በግብፅ እና በሱዳን መካከል ለረጅም ዘመናት አወዛጋቢ ሆኖ በቆየው "የሀላይብ ትሪያንግል" (Halaib Triangle) ግዛት ውስጥ የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች በፈጸሙት ድንገተኛ የአየር ጥቃት ቢያንስ የሰባት ሱዳናዊያን ወርቅ አውጪዎች ሕይወት ማለፉ ተዘገበ።
ጥቃቱ የተፈጸመው በዚሁ አወዛጋቢ ቀጠና ውስጥ በሚገኘው "ጀበል አል ኡቃያት" በተሰኘው የወርቅ ማውጫ ስፍራ ላይ ነው። እንደ የአይን እማኞች እና የአካባቢው መረጃዎች ከሆነ፣ በጥቃቱ ወቅት የግብፅ የጦር ሄሊኮፕተሮች በስፋት የታዩ ሲሆን ከሰባቱ ሟቾች በተጨማሪ በአስር የሚቆጠሩ ዜጎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
በአሁኑ ሰዓት ሱዳን በከፋ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኝ ሲሆን፣ የግብፅ መንግስት ደግሞ የጄነራል አብዱልፈታህ አል-ቡርሃን የሚመራውን የሱዳን ጦር (SAF) በግልጽ በመደገፍ የቅርብ ወዳጅ ሆና እየሰራች ነው። ግብፅ ለሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ ድጋፍ በምትሰጥበት በዚህ ወቅት ግን በድንበር አካባቢ የሚገኙ
ሱዳናዊያንን ኢላማ ያደረገ ጥቃት መፈጸሟ በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ላይ ጥያቄን ጭሯል። የሱዳን ወታደራዊ መንግስት ዜጎቹ በግብፅ ጦር መገደላቸው እየታወቀ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ይፋዊ መግለጫ አለመስጠቱ እና ዝምታን ጉዳዩን አስገራሚ አድርጎታል። ይህ ዝምታ በሱዳን ህዝብ ዘንድ "መንግስት ለወታደራዊ ድጋፍ ሲል የዜጎቹን ደህንነት ችላ ብሏል" የሚል ቅሬታን እየቀሰቀሰ ይገኛል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 046 |
| 7 | የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው!
በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ "ድርድር ለማስጀመር" ሁሉ ማቀዳቸውን እየተናገሩ ናቸው።
በፈረንሳይ የቡድን 7 ጉባዔ ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ ጋር የተገናኙት ትራምፕ፤ የዓባይ ግድብ "ውዝግብንም በድጋሚ ይጀመራል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከሁለትዮሽ ውይይት በኋላ “ከግብጹ ፕሬዝዳንት፣ ከጓደኛዬ ጋር በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። እሳቸው በመላው ዓለም የተከበሩ ናቸው... ግንኙነታችንም በግል ደረጃ ለረጅም ጊዜ በጣም ጠንካራ ሆኖ ቆይቷል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከአልሲሲ ጋር ጥሩ ወዳጅነት እንዳላቸው የገለፁት ትራምፕ፣ "ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ነው የተገነባው" በማለት ገልጸዋል።
"ግዙፍ ግድብ" ሲሉ በጠሩት የህዳሴ ግድብ ላይ "መፍትሔ የሚያመጣ ውይይት እናስጀምራለን" ያሉት ፕሬዝዳንቱ “የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉም ገልጸዋል።
"በኢትዮጵያ የተገነባው ግድብ በግብፅ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ ነው" በማለትም የተለመደ ግጭት ቀስቃሽ ንግግር አድርገዋል።
ትራምፕ ለአል-ሲሲ ሲናገሩ "እውነቱን ማወቅ ከፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጣም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ነው የተያዛችሁት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አነሳስተዋቸዋል። #aljazeera
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 560 |
| 8 | ከእግር ኳስ በላይ...
የቮዚንሃ እናት እና የአሜሪካ መንግስት አስገራሚ ውሳኔ
በ2 ቀን ውስጥ ከ50 ሺህ Followers ወደ 12.1 ሚሊዮን Followers የገባው።
የአሜሪካ መንግስት የኬፕ ቨርዱን ኮከብ ግብ ጠባቂ ቮዚንሃን (Vozinha) እናት ወደ አሜሪካ ለማምጣት በይፋ ጥረት እያደረገ ይገኛል!
ቮዚንሃ በዓለም ዋንጫው ላይ ድንቅ ብቃቱን አሳይቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቪዛ እጥረት እና በከፍተኛ ክፍያ ምክንያት እናቱ ከጎኑ መሆን አለመቻሏ ይታወሳል። አሁን ግን ይህ ትልቅ ህልሙ እውን ሊሆን ተቃርቧል።
እግር ኳስ ከጨዋታ በላይ ነው። ስለ ቤተሰብ፣ ስለ መስዋዕትነት እና ስለ ፍቅር ጭምር ነው! ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ እናቱ በቅርቡ ከልጇ ጋር እንድትገናኝ ሲጫወት በስታዲየም ውስጥ ሆና እንድታየው የብዙዎች ምኞት ነው።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 467 |
| 9 | "አዲስ አበባ ጎርፍ ብትጠቃ አደጋው የደረሰበት ክፍለ ከተማ ይጠየቃል!"
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተያዘው ክረምት “በአዲስ አበባ ውስጥ ጎርፍ ቢያጋጥም ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ” ተናገሩ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተያዘው ክረምት “የጎርፍ አደጋዎች አጋጥመው፣ ሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ቢያደርሱ፣ ከማንም በላይ ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ” አስጠነቀቁ፡፡
ከንቲባዋ ይህንን ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተደዳደር የ90 ቀናት መሪ እቅድ የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡
“ሕዝብ ውስጥ ትውላላችሁ፣ ታድራላችሁ፤ ትሰራላችሁ” ያሉት አዳነች፣ “ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርባችሁ፣ ችግሩን ታውቃላችሁ፣ ዋና ማእከል ሁሉንም ችግር ማወቅ አይጠበቅበትም” ብለዋል፡፡
መንግስት አሁን ያለውን የከተማ እድሳት አካሂዶ “የክረምት ጎርፍ ሰው አጠቃ
የሚል..አይገባንም (ዲዘርቭ አናደርግም)” ሲሉ የተደመጡት ከንቲባዋ፣ መንገዶች ሲሰሩ የታለፉ ቦታዎች ካሉ በአፋጣኝ መጠገን እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
ክፍለ ከተሞች በበጎ ፍቃድ ስራዎች አዳዲስ የጎርፍ መውረጃ መተላላፊያዎችን መጠገን፣ አዲስ ካስፈለገም መገንባት የግድ መሆኑን አጽዕኖት ሰጥተው አስምረውበታል፡፡
በተጨማሪም በማብራሪያቸወው መንግስት የጀመራቸው ቤቶች ለመጨረስ ማቀዱን፣ የጭቃ ቤቶች ግንባታ መቆሙን፣ ጠጋግኖ ቁጥር ለማብዛት የሚደረገው አካሄድ እንደቀረም አስረድተዋል፡፡
ከዛ ይልቅ ክፍለ ከተሞች የተለያዩ በጎ ፍቃደኞች በማስተባባር የበጎ ፍቃድ ቤቶች እንዴት ሊሰሩ እንደሚችሉ ማሰብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 429 |
| 10 | የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ መከላከያ አታሼ በአውሶም ድጋፍ ዙሪያ ተወያዩ
የሶማሊያ ጦር አዛዥ እና የግብፅ የመከላከያ አታሼ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የደኅንነት ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር በሞቃዲሹ መምከራቸው ተገልጿል።
ይህ ውይይት ሶማሊያ የደኅንነት ሽግግሯን እያፋጠነችና በአል-ሸባብ ላይ የምታደርገውን ዘመቻ በቀጠለችበት በዚህ ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን ወታደራዊ ትስስር በግልጽ የሚያመላክት ነው።
እንደ ሒራን ኦንላይን ዘገባ፤ የሶማሊያ ሔራዊ ጦር አዛዥ ሜጀር ጀነራል ኢብራሂም መሐመድ ማሕሙድ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሶማሊያ የግብፅ መከላከያ አታሼ ከሆኑት ሜጀር ጀነራል አሕመድ ፋትሂ አብደልሰታር ጋር ተገናኝተው መክረዋል።
በውይይታቸውም ወታደራዊ ሥልጠናን፣ ለሶማሊያ ኃይሎች የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ እና በአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና መረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ማዕቀፍ ውስጥ የሚደረገውን ትብብር ጨምሮ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 537 |
| 11 | ትራምፕ በዩክሬን ሰላም እንዲወርድ ግፊት እንደሚያደርጉ ተናገሩ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ በተካሄደው የጂ7 መሪዎች ጉባኤ ላይ ከፕሬዘዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር “በጣም ጥሩ” ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሰላም ስምምነት ማድረግ እንዳለባትና እርሳቸውም ጦርነቱን ለማቆም የሚችሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
ትራምፕ በጦርነቱ በርካታ ወጣቶች እያለቁ መሆኑን በመጥቀስ “እኔ ስምንት ጦርነቶችን አስቆሜያለሁ ይህኛው ግን ለመፍታት በጣም ቀላሉ ይሆናል ብዬ ያሰብኩት ነበር” ብለዋል።
ይሁን እንጂ ስምንት ጦርነቶችን አስቆሜያለሁ ማለታቸው በሰፊው አከራካሪ ሆኗል።
ዘለንስኪ ከጂ7 መሪዎች፣ ከትራምፕ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ጋር ከተወያዩ በኋላ በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፥ ዋናው ትኩረት የዩክሬንን የአየር መከላከያ ማጠናከርና ዲፕሎማሲውን ማራመድ እንደሆነ ገልጸዋል።
ከጂ7 መሪዎች ጠቃሚ የሆኑ የቃል ኪዳን ድጋፎችን ተጨማሪ ሚሳኤሎች፣ የማምረቻ ፈቃድ እና የክረምት ድጋፍ ማግኘታቸውን የገለጹት ዘለንስኪ፥ አሜሪካ ለዚህ ሁሉ ዋስትና ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን አክለዉ ተናግረዋል ።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 549 |
| 12 | ወደ መቀሌ‼️
የአሜሪካ ኤምባሲ ልዑክ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ ሊያመራ መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በሚቀጥለው ሳምንት ወደ መቐለ ከተማ ያቀናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ያገኘውነው መረጃ ያመለክታል።
ስለ ጉብኝቱ ዋና ዓላማ፣ ስለ ልዑካን ቡድኑ አባላት ማንነት እስካሁን በይፋ የተገለጸ ነገር የለም። ይሁን እንጂ በመቐለ ከህወሓት አመራሮች ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ጉዞ በህወሓት እና በፌዴራል መንግሥቱ መካከል እየተካረረ የመጣውን ውጥረት ለማርገብ ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል።
@Addis_News
@Addis_News | 1 524 |
| 13 | ተመላሽ አጀንዳዎችን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሉበት ለክልሎች እናስረክባለን ሲል የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ለጉባኤው የማይበቁ እና በክልል ደረጃ የሚፈቱ አጀንዳዎችን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሉበት ለክልል አመራሮች ለማስረክብ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለጸ።
ይህ የተባለው በዛሬው ዕለት በስካይ ላይት ሆቴል የኢትዮጵያ ንግድ ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተወካዮች ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር ምክክሩ፣ ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የግሉ ዘርፍ ያለውን ሚና በተመለከተ በተወያየበት ወቅት ነው።
ኮሚሽኑ ከ126 ሺህ በላይ የወረዳ ተወካዮች ጋር መወያየቱን የገለጸ ሲሆን በዚህም የ1789 ጥቅቃን ቡድኖች አጀንዳዎች መሰብሰባቸውን አስታውሷል።
አክሎም ከ1200 በላይ ወረዳዎች ላይ አጀንዳዎችን መሰብሰቡን አስታውሶ በአማራ ክልል ካሉት ከ400 በላይ ወረዳዎች ውስጥ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት በአራት ወረዳዎች ግን ውይይት አለመካሄዱን አልሸሸገም፡፡
በትግራይም በተመሳሳይ ከ22 ጊዜ በላይ ውይይቶች ከተካሄዱ በኋላ አመቺ ሁኔታ የለም በማለት በአዲስ አበባ ከክልሉ ተወካዮች ጋር ማካሄዱ ይታወሳል። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ምክክሩን ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በአአዲስ አበባ ከ4000 በላይ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ለማካሄድ ቀን መቁረጡ አይዘነጋም፡፡
የምክክሩ ሁኔታ በምን መልኩ እንደሚካሄድ ገለጻ የሰጡት የሀገራዊ ምክክርኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ(ዶ/ር) “ተሳታፊዎች አንድ ሳምንት ቀደም ብለው አዲስ አበባ ይገባሉ” ያሉ ሲሆን፣ ይህም ተሳታፊዎች በምክክሩ ሂደት ላይ እንዲተማመኑ እና እንዲግባቡ ያደርጋል ብለዋል።
በዚህም መሰረት ውይይቱ የሚካሄደው በቡድን በመሆን ሲሆን በመጀመሪያ ደረጃ 50 ሰዎችን የሚይዝ 80 ቡድኖች ይኖራሉ ተብሏል። በዚህ 80ዎቹ ቡድን ውስጥ ድሬድዋ አነስተኛ የተሳታፊ ቀጥር ያላት መሆኗ ተመላክቷል።
እነዚህ ቡድኖች ከተወያዩ በኋላ የተሳታፊዎች ቁጥር ወደ 250 በማደግ በ16 ቡድኖች ውስጥ የሚደረግ ውይይት እንደሚኖር ያሰረዱ ሲሆን ይህ ስብስብ ደግሞ “ስልታዊ ቡድኖች” ተብለው የሚጠሩ ናቸው። ኮሚሽነሩ አክለውም ስምንት ቡድኖች እና 500 ሰዎችን የሚይዘው ቡድን ደግሞ መሰረታዊ በሆኑ አጀንዳዎች ይወያያል ብለዋል።
ኮሚሽነር አምባዬ፣ ከመጀመሪያው አንስቶ ባሉት ቡድኖች እያንዳንዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ይኖሩታል ያሉ ሲሆን እያንዳንዱ ቡድን መግባባት ላይ እንዲደርስ እና በሰሜታዊ ንግግሮች እንዳይመሩ የባለሙያዎች ቡድን እንደሚኖር እንዲሁም ባለሙያዎቹም ሙያዊ ድጋፍ እንደሚቸሩ አስታውቀዋል፡፡
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 601 |
| 14 | በትግራይ ጭምብል ያጠለቁ ታጣቂዎች አሰቃቂ እርምጃ እየወሰዱ ነው!
ቢቢሲ ትግረኛ በትግራይ ክልል እየተፈጸመ ስላለው የግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ አስደንጋጭ የምርመራ ሪፖርት ይዦ ወጥቷል፡፡ በወርቅ ማውጫ ስፍራዎች እና በሌሎች ስፍራዎች እየተፈጸመ ያለውን አፈሳ በዝርዝር የሚዳስሰው ዘገባው፤ ከህውሃት ታጣቂዎች ባለፈ ጭምብል ያጠለቁ ታጣቂዎችም በንጹሃን ላይ እርምጃ እየወሰዱ እንደሚገኝ ጠቅሷል፡፡ እነዚህ ጭምብል ያጠለቁ ታጣቂዎች የሕውሓት ወታደሮች ስለመሆናቸው ግን አልታወቀም፡፡
ግንቦት 17/2018 ዓ.ም. በዓብይ ዓዲ ከተማ አቅራቢያ በሚገኙ ሁለት የወርቅ ማዕድን ማውጫዎች አባግባ እና ሩባኸዛ ከሚባሉ አካባቢዎች የትግራይ ኃይሎች አርሚ 60 አባላት እና ፊታቸውን የሸፈኑ ታጣቂዎች ከ700 ሰዎች በላይ ሰዎችን እንዳፈሱ ቢቢሲ ትግርኛ ከተጎጂዎች እና ከተጎጂ ቤተሰቦች መረጃ አግኝቷል።
የአራት ልጆች አባት የሆነው አቶ ሰለሞን ኃይለማርያም በዓብይ ዓዲ ከተማ ለሌሎች ሰዎች ድንጋይ እና አሸዋ በአህያ በመሸከም የቀን የጉልበት ሥራ ሠርቶ በሚያገኘው ገንዘብ ልጆቹን ያሳድግ ነበር። ነገር ግን እንደተለመደው ለሥራ ከወጣ በኋላ ከዛ በኋላ እሱ እና የአጎቱ ልጅ ወደ ቤት ሳይመለሱ መቅረታቸውን ቤተሰቡ ለቢቢሲ ገልጿል።
ባለቤቱ ወይዘሮ መድረኽ ኪዳነማርያም "ሰኞ ዕለት ወደ ሥራ እንደሄደ ጥዋት 3፡00 ሰዓት ላይ ነው ወሰዱት።. . . የምሠራበት ቦታ መንገድ ዳር ስለሆነ በግዳጅ ታፍሰው በመኪና ሲያልፉ አየሁኝ። 'እዚህ መኪና ላይ አለ' ሲሉኝ 500 ብር ተበድሬ ስጡልኝ ብየ ሰጥኋቸው" ብላለች።
ከዚያም በኋላ ባለቤቷ ከማይቅነጣል አልፎ ወደሚገኝ ወታደራዊ ማሠልጠኛ እንደተወሰደ መረጃ እንዳገኘችም ትገልፃለች። "በጣም ተጨንቀናል። ልጆቹ ናፍቀውታል። አባታችን እያሉ እያስቸገሩኝ ነው። ልጆቹን የሚረዳ አንድም የለም። ሰለሞንም ልጆቹን ትቶ እዚህ ውስጥ የመግባት ፍላጎት የለውም፤ በኃይል ነው የወሰዱት።"
ዘካርያስ* ከወርቅ ማውጫ አካባቢ "ፊታቸውን በሸፈኑ ታጣቂዎች" በኃይል ከታፈሱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች መካከል አንዱ ነው።
በአፈሳው ወቅት ድብደባ፣ ማንገላታት እና ተኩስ ጭምር እንደነበር የሚናገረው ዘካሪያስ ከጣንቋ አበርገለ፣ ቀይሕ ተኽሊ እና ዓብይ ዓዲ ወረዳዎች የመጡ 500 ሰዎች ወደ ዓብይ ዓዲ ከተማ ማዘጋጃ ቤት፤ ከቆላ ተምቤን የመጡ 200 ሰዎች ደግሞ በዓብይ ዓዲ ከተማ ነዳጅ ማደያ አቅራቢያ ወደሚገኘው ግንባታው ወዳላለቀ ሕንፃ በታጣቂዎቹ መወሰዳቸውን ይናገራል።
ቢቢሲ ትግርኛ ያነጋገራቸው ሌሎች ሰዎች ከታፈሱ በኋላ ለከተማው ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት እንዲሁም ለዓብይ ዓዲ ከተማ እና ወረዳ አስተዳደር እንዳስረከቧቸው ይናገራሉ።
በዓብይ ዓዲ ከተማ ማዘጋጃቤት አዳራሽ የከተማዋ ከንቲባ እና ምክትሉ እንዲሁም የፀጥታ ኃላፊዎች በመምጣት 'ትዋጋላችሁ' እንዳሏቸው ጨምረው አስረድተዋል።
ከማዕድን ቁፋሮ የተያዙት ወጣቶች " 'ወድ ትግል ነው የምትሄዱት' አሉን። ልብስ ሳንለብስ ራቁታችን ነን ያለነው፣ እቃችን እና ሞባይላችን ሳንይዝ ከሥራ ላይ ነው ያፈሳችሁን፤ ልብሳችንን እንኳን እንልበስ አልናቸው። እነሱ ግን 'አያገባንም አትሄዱም አሉን" ብለዋል።
ዘካሪያስ በተለያየ ጊዜ በትግራይ ውስጥ በተካሄደ ጦርነት የቤተሰቡ አባላቱ መሰዋታቸውን ገልጾ ከተጣራ በኋላ መለቀቁን ተናግሯል።
ከዚያም በኋላ አውቶቡስ፣ ኦራል እና አይሱዙ መኪኖች አምጥተው ጭነው ወደ ሌላ ቦታ እንደወሰዷቸው ቢቢሲ ያነጋገራቸው ተጎጂዎች ይናገራሉ።
የአርሚ 60 የትግራይ ኃይሎች ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ዘልዑል ማቲዮስ ለቢቢሲ በሰጡት ምላሽ የሚመሩት ቡድን በአባግባ አካባቢ ተሰማርቶ "እርምጃ" እንደወሰደ ገልጸዋል።
"በአካባቢው ሰፊ የማዕድን ወረራ አለ። እዚያ የነበሩትን ወጣቶች 'ኦፕሬሽን' በማካሄድ በትነናቸዋል። . . . በሩባኸዛ እና በአባግባ የነበረ ወጣት ለሌላ የፀጥታ ሁኔታ በጣም አስቸጋሪ ስለነበር እርምጃ ወስደናል" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ወጣቶቹ ማይቅነጣል እና ዕዳጋ ዓርቢ መካከል ወደሚገኘው ወታደራዊ ማሠልጠኛ እንደተወሰዱ ቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ኮሎኔሉ "... የማውቀው ነገር የለም" ሲሉ መልሰዋል። | 1 484 |
| 15 | የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ ከአሜሪካ ጋር የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ እስራኤል ጦሯን ከሊባኖስ ማስወጣት እንደሚኖርባት ዳግም አሳሰቡ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ልታደናቅፍ ትችላለች የሚል ስጋት እየጨመረ በመጣበት ወቅት ነው። ዶናልድ ትራምፕ ሳይቀሩ፣ የጦርነት አጋራቸው የሆነችውን እስራኤልን “ኃላፊነት የጎደለው እርምጃ እየወሰደች ነው” በማለት ተችተዋታል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ በሰጡት መግለጫ፣ “የእስራኤል ጦር በዚህ ጦርነት ወቅት ከተቆጣጠራቸው ግዛቶች ሳይወጣ፣ ጦርነቱ ሙሉ በሙሉ አብቅቷል ሊባል አይችልም” ብለዋል። የሂዝቦላህ የሚዲያ ግንኙነት ኃላፊም እንደገለጹት፣ ኢራን ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው ቀጣይ የውይይት ምዕራፍ ላይ የእስራኤል ጦር ከሊባኖስ እንዲወጣ ጥያቄ እንደምታቀርብ ለቡድኑ ማረጋገጫ ሰጥታለች።
እነዚህ አስተያየቶች የተሰሙት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ ኤቪያን በተካሄደው የቡድን 7 መሪዎች ጉባኤ ላይ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን በጠንካራ ቃላት በወቀሱበት ወቅት ነው። ትራምፕ ኔታንያሁ “በሊባኖስ ረገድ የበለጠ ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ መንቀሳቀስ አለባቸው” ያሉ ሲሆን፣ በቅርቡ እስራኤል በቤሩት ላይ የፈጸመችውን የቦምብ ጥቃት “አረመኔያዊ” ሲሉ ጠርተውታል።
ትራምፕ አክለውም፣ “እስራኤል ከሂዝቦላህ ጋር ለረዥም ጊዜ ስትዋጋ ቆይታለች፣ በዚህም ምክንያት በጣም ብዙ ሰዎች እየተገደሉ ነው” ብለዋል። “አንድን የምትፈልጉትን ሰው ለማደን ስትሉ የመኖሪያ ህንፃን ማፍረስ የለባችሁም፤ ምክንያቱም በእነዚያ ህንፃዎች ውስጥ ብዙ ሰዎች አሉ። ሁሉም ደግሞ የሂዝቦላህ አባላት አይደሉም፣ ይህንን በእርግጠኝነት ልነግራችሁ እችላለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።
የሶሪያ መንግስት ከሂዝቦላህ ጋር “በመገናኘት” ረገድ የተሻለ ስራ ሊሰራ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ደማስቆ በሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ከሂዝቦላህ ጋር የተዋጉ የቀድሞ አማፂያን የሚመሩት ቢሆንም፣ አሁን ያለው መንግስት ግን መረጋጋትን ይፈልጋል።
ትራምፕ ከኔታንያሁ ጋር “ለማመን የሚያስቸግር የግል ግንኙነት” እንዳላቸው ቢገልጹም፣ አሁን ያለውን ውጊያ ግን ከኢራን ጋር ከተደረገው ስምምነት አንፃር ሲመዘን “እንደ ጥቃቅን ነገር” ነው የቆጠሩት። የትራምፕ አስተያየት እንደሚያሳየው እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነትን ለመቀበል ፍቃደኛ አለመሆኗ እና ከኢራን ጋር ለተደራደሩት የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እየደገነችው ያለው አደጋ ትዕግስታቸውን እየተፈታተነው ይመስላል።
“ያለ አሜሪካ፣ ያለ እኔ፣ እስራኤል አትኖርም ነበር፤ ምክንያቱም እኔ ያደረግኩትን ለማድረግ የተዘጋጀ ሌላ ፕሬዝዳንት የለም” ብለዋል። የእስራኤል እርምጃ በሰላም እቅዱ ላይ የደገነው ስጋት የአውሮፓ መሪዎችን ስለ ስምምነቱ ዘላቂነት ያላቸውን ስጋትት አጠናክሮታል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 523 |
| 16 | ሕወሃት፣ ፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ አዲስ ጥቃት ሊከፍት ተዘጋጅቷል በማለት ከሠሠ።
መንግሥት የድሮን ጥቃቶችን በመፈጸም፣ ጦር ሠራዊቱን በማነቃነቅና በትግራይ ላይ እቀባ በማድረግ ሁለተኛ ዙር ጦርነት ሊያካሂድ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል ያለው ሕወሃት፣ የፌደራል መንግስትቱ ባለስልጣናት የትግራይ ኃይሎችን በጦርነት ሰባኪነት የሚከሱት የጦርነት ዝግጅታቸውን አቅጣጫ ለማስቀየር ነው በማለት ተችቷል።
በትግራይ ስላለው ሁኔታ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት የኢትዮጵያን ሕዝብና ዓለማቀፉን ማኅበረሰብ እያሳሳቱ ይገኛሉ በማለት ጭምር ሕወሃት ወቅሷል።
ሕወሃት፣ ባለፉት ሦስት ወራት ለጦርነቱ ተፈናቃዮች ይቀርብ የነበረው የሰብዓዊ እርዳታ መቋረጡንም ገልጧል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 498 |
| 17 | ታሪክ መስራት የማይሰለቸው ምትሀተኛ
ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ያደረገውን ታሪካዊ 200ኛ ጨዋታውን፣ ለሀገሩ 118ኛ እንዲሁም በዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ 16ኛ ጎሉን በማስቆጠር በድምቀት አክብሮታል።
ሮድሪጎ ዴ ፖል ያቀበለውን ኳስ ሜሲ እንደተለመደው በቅልጥፍና ተቆጣጠረው፤ ከዚያም ወደ ግብ ክልል እየገሰገሰ ሄደ።
ከግቡ 25 ያርድ ያህል ርቀት ላይ ሲደርስም፣ ማንም ያልጠበቀውን አስደናቂና ኃይለኛ ምት ወደ ግብ መታው።
የአልጄሪያው ግብ ጠባቂ ሉካ ዚዳን ኳሷን በሁለት እጆቹ ለመመለስ ቢሞክርም፣ የኳሷን የኃይል ግስጋሴ ግን ሊያስቆመው አልቻለም።
የዓለም ሻምፒዮኖቹ አርጀንቲናውያን መሪነቱን ጨበጡ፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ደግሞ ሜሲ ብቻ ነበር።
ሜሲ ጎሉን ያከበረበት መንገድ ልክ በሕይወቱ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ጎል እንዳስቆጠረ ሰው ነው በለቅሶ፤ ባለው ልዩ ብቃት ደግሞ ፈጽሞ የሚያረጅ አይመስልም።
ሜሲ ንጋት ላይ አርጀንቲና ከአለጄርያ ባደረጉት ጨዋታ ሶስት ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ መስራት ችሏል።
በዚህም በዓለም ዋንጫ ታሪክ በዕድሜ ትልቁ (39) ሀትሪክ የሰራ ተጫዋች ሆኗል።
የዓለም ዋንጫ ብዙ ግብ በማስቆጠርም (16) ከጀርመናዊዉ ሚሎስላቭ ክሎስ ሪከርድ ተጋርቷል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 738 |
| 18 | ከአብይ ጎን እቆማለሁ-ጄኔራሉ‼️
የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ልጅ የሆኑት እና የዩጋንዳ ጦር ዋና አዛዥ የሆኑት ጄኔራል ሙኡዚ በቲውተር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል።
'በትግራይ ሌላ ጦርነት እንዳይነሳ እለምናለሁ፣በጣም እወዳቸዋለሁ ግን ጦርነት ሰልችቶናል ብሏል።
ጦርነት ከተነሳ ግን ወንድሜን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድን እደግፋለሁ"ብሏል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 764 |
| 19 | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የባንኮች ፍላጎት ከአቅርቦቱ በሁለት እጥፍ በላይ በልጧል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የመደበ ቢሆንም፣ በባንኮች በኩል የቀረበው ፍላጎት ግን ከአቅርቦቱ በላይ በእጅጉ ጨምሮ ታይቷል። በጨረታው ላይ የተሳተፉት የፋይናንስ ተቋማት ለመግዛት የጠየቁት አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ማዕከላዊ ባንኩ ካቀረበው በሁለት እጥፍ በላይ በመብለጥ 236.30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሷል።
በተካሄደው በዚህ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ ዋጋው 158 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህ ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ላይ 16 የሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች የተሳተፉ ቢሆንም፣ ካለው የተገደበ አቅርቦት እና ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ የምንዛሬ ድልድሉን ማግኘት የቻሉት ግማሾቹ ወይም 8ቱ ባንኮች ብቻ መሆናቸውን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 721 |
| 20 | የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
ከጠዋቱ 2:00-9:30
ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ አካባቢ፣ አርበኞች ት/ቤት፣ ዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ እና አካባቢው ፣
ፊሊጶስ ቤ/ክ፣ እስላም መቃብር፣ ሎሚ ሜዳ ፣ ጠሮ መስጊድ፣ጠሮ ሥላሴ፣ አወልያ፣ ካኦጄጄ፣ አበነሃብተማርያም፣ አስኮ ጨረታ እና አካባቢው፣
ኮተቤ አንቆርጫ አካባቢ፣ ጨለቆ፣ አቡ ሱቅ፣ ውሃ ታንከር፣ ጫካ ፕሮጀክት እና አካባቢው፣
ከጠዋቱ 3:00-8:00
ቦሌ ግሪክ ት/ቤት አካባቢ፣ ኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ፓላስ አካባቢ፣ፒኮክ ፓርክ እና አካባቢው ፣
ሴቶች አደባባይ፣ ካሳንቺስ መብራት ኃይል፣ ሂልተን ሆል ጀርባ፣ ኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል፣ ሐናን ዳቦ፣ ኢሊሌ ሆቴል፣ እናት ባንክ እና አካባቢው፣
ከጠዋቱ 4:00-12:30
አትላስ ሆቴል፣ ሻላ መናፈሻ፣ ኤስኦኤስ፣ ደሳለኝ ሆተል ጀርባ፣ ደሳለኝ ሆቴል፣ ፕሬዚደንሺያል ሆቴል፣ ወደ ሩዋንዳ ኦቨርፓስ እና አካባቢው፣
ከጠዋቱ 4:40- ምሽቱ 11:00
ቡራዩ ድሬ ከአስፋልት በላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ቶልቻ እና አካባቢው፣
ከጠዋቱ 5:00-10:30
ዓለም ገና፣ ኢንዱስትሪ መንደር፣ ፉሪ ሬዲዮ ጣቢያ፣ ፉሪ፣ ሃጂ ሪልስቴት አካባቢ፣ ወርዶፋ ሎጅ፣ ዳርፉር ሰፈር፣ ጀሞ 2 እና አካባቢው፣
ከጠዋቱ 2:00-10:00
አቃቂ ዓለም ባንክ፣አርሴማ ጸበል እና አካባቢው
ከጠዋቱ 2:30-8:30
ጋምቤላ ፋኚዶ፣ ኡኩና ቀበሌ፣ መንደር 14 እና አካባቢው፣
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 945 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
