Fresh መረጃ | FreshNews
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Fresh መረጃ | FreshNews
کانال Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 55 472 مشترک است و جایگاه 3 059 را در دسته آموزش و رتبه 593 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 55 472 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -816 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -67 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.94% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.16% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 185 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 753 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ።
ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇
@Freshes_newsbot
Fresh News,Fresh Updates.”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 03 سپتامبر | 0 | |||
| 02 سپتامبر | 0 | |||
| 01 سپتامبر | 0 |
| 2 | እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ
የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል።
የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል።
በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል ።
የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል።
ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 717 |
| 3 | ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከሳምንታት በኋላ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ!
ጠቅላዩ በማኅበራዊ ገፃቸው ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ ማከናወናቸውን ገልጸዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 024 |
| 4 | ሶማሊያ የሶማሊላንድን እውቅና የማግኘት እንቅስቃሴ ለማገድ ከአረብ ሀገራት ጋር ውይይት እያደረገች ነው
ሶማሊያ አረብ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖአቸውን በመጠቀም እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችው እውቅና ወደ ሰፊ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዳይቀየር እንዲያግዱ ጥሪ አቀረበች።
የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሊ ሞሃመድ ኦማር ከሳውዲው አል ሻርቅ አል አውሳት (-Sharq Al-Awsat) ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ሞቃዲሾ የሌሎች ሀገራትን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተለች መሆኗን ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ ሶማሊያ በእስራኤል ውሳኔ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለማስረዳት ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ጋር በቀጥታ ግንኙነት ማድረጓን ተናግረዋል።
እንደ አሊ ባልካድ ገለፃ፣ እስራኤል ባለፈው ታህሳስ ወር ሶማሊላንድን በይፋ በመቀበል የመጀመሪያዋ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገር ሆናለች።
ሁለቱ ሀገራት አምባሳደሮችን የተለዋወጡ ሲሆን፣ ሶማሊላንድ በኢየሩሳሌም ኤምባሲዋን በመክፈት ፕሬዚዳንቷም በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል።
ሚኒስትሩ የእስራኤል ውሳኔ እስካሁን ሰፊ ዓለም አቀፍ እውቅና ባያስከትልም፣ በሶማሊላንድ የሚደረጉ የውጭ ሀገራት ወታደራዊ ወይም የደህንነት እንቅስቃሴዎች ውጥረትን ሊጨምሩና የአፍሪካ ቀንድን ለማረጋጋት አደጋ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።
በመሆኑም የአረብ ሀገራት ከማውገዝ ባለፈ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በመጠቀም ተጨማሪ እውቅናዎችን እንዲያግዱ ጠይቀዋል።
ሶማሊላንድ እ.ኤ.አ. በ1991 ነፃነቷን ካወጀች ጀምሮ የራሷን መንግሥትና የደህንነት ኃይል አዋቅራ ብትቀሳቀስም፣ ሞቃዲሾ ሶማሊላንድን የግዛቷ አካል አድርጋ ነው የምትቆጥረው።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 991 |
| 5 | የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከስምምነት ሊደርስ ነው
እንደ አሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትራንስፖርቴሽን ዘገባ መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የሚደርሱ ቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት ለማጠናቀቅ መቃረቡን ምንጮች ገለጹ።
ይህ ውል አየር መንገዱ ከአረብ ኤምሬትስ እና ቀጣናው አየር መንገድ ኩባንያዎች ጋር ያለውን ውድድር ለማጠናከር እና አዲስ የአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ማዕከል ለመገንባት ለያዘው እቅድ ትልቅ ማበረታቻ ነው ተብሏል።
እንደ ዘገባው ከሆነ፣ ግዢው ሁለት የነባሩን '777F' ሞዴል እና የተቀሩትን ደግሞ አዲስ ምርት የሆኑትን '777-8F' የጭነት አውሮፕላኖች ያካተተ ነው።
ቦይንግ የ '777X' አውሮፕላን ማረጋገጫ በመዘገየቱ ምክንያት ነባሩን ሞዴል የማምረት ፈቃድ ለማራዘም ከአሜሪካ አቪዬሽን ባለስልጣን ጋር እየተነጋገረ ይገኛል።
አየር መንገዱ እና ቦይንግ በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጡት ይፋዊ አስተያየት ባይኖርም፣ ውሉ አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የካርጎ ኤክስፖርት አገልግሎት ያለውን የበላይነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 007 |
| 6 | የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚዎች ውስጥ 62 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸው ተነገረ።
የ12 ክፍል ማለፊያ ነጥብ ካመጡት ውስጥ 7ቱ ሴት ታራሚዎች ይገኙበታልም ተብላል፡፡
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃና በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል እና በዘዋይ ማረሚያ ማእከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱት ተፈታኞች 63 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 62 ማለፋቸውን ማረመያ ቤቱ አስታውቋል፡፡
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ፣ በሴቶች ማረሚያ ማዕከላት በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እና ለፈተና የተቀመጡት 31 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፤ከነዚህም ውስጥ 7ቱ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡
በተመሳሳይ የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 23 የህግ ተማሪዎች መካከል 22ቱን ማሳለፍ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በአጠቃላይ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚስች 62 ማለፋችው ተነግራል፡፡የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ካስፈተናቸው በሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መቶ በመቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ማስመዘገብ ተችሏል፡፡
የሕግ ታራሚ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ተከትሎ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ እንደተናገሩት ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የፈጠረው ምቹ የትምህርት ከባቢ እና የታሪሚዎች ጠንካራ ተነሳሽነት ለዚህ አስደናቂ 100 ከመቶ ውጤት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
በማዕከላቱ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም የህዝብ ት/ቤት ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ መምህራን የተመደቡለት መሆኑን የገለፁት አቶ ሳምሶን የህግ ታራሚ ተማሪዎችም በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁም አመላክተዋል፡፡
አቶ ሳምሶን አክለውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ታራሚዎች ተስፋና መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን ማረሚያ ቤት የህይወት ማብቂያ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው፤ ብለዋል።
የህግ ታራሚ ተማሪዎች ያመጡት ውጤት መታረምና መታነፃቸውን ማሳያ በመሆኑን ገልፀው መንግስት በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን መንገድ አሊያም የትምህርት ሚኒስቴር የሕግ ታራሚ መሆናቸውን በመረዳት ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን
እንዲያመቻችላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 150 |
| 7 | «የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» — ፕሬዝዳንት ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በራሳቸው የሶሻል ሚዲያ መድረክ Truth Social ባሰፈሩት አነጋጋሪ መልእክት፣ ስትራቴጂካዊውን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ስም ለመቀየር ሀሳብ አቅርበዋል።
ትራምፕ ባሰፈሩት መልእክት «አሁን አካባቢውን በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ቁጥጥር ስር ስላደረግነው፣ የሆርሙዝን ስም ወደ "ትራምፕ ስትሬት" ብንቀይረውሳ?» ሲሉ ጠይቀዋል
አክለውም እንደ አሜሪካ ሀገር ሁሉ ቦታው «ከመቼውም ጊዜ በላይ ሳቢና ተፈላጊ ይሆናል!» ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ይህ የትራምፕ አስተያየት የመጣው በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በሆርሙዝ የባህር መስመር እና በላራክ ደሴት አካባቢ ከፍተኛ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል ፍጥጫ እና ጥቃት በተካሄደበት ወቅት ነው።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 193 |
| 8 | በሀሰተኛ ሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የነበሩት ቀሲስ በላይ መኮንን ከእስር መፈታታቸው ተገለጸ።
ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ ጠዋት ከእስር ተፈተው በአሁኑ ሰዓት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።
ግለሰቡ በሐሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማውጣት በመሞከራቸው፣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የአምስት ዓመት እስራት እና የ10 ሺህ ብር ቅጣት ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑ ይታወሳል።
ከእሳቸው ጋር አብረው ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ሌሎች ሁለት ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው የአራት ዓመት እስራት እና የ3 ሺህ ብር ቅጣት ተወስኖባቸው እንደነበር አይዘነጋም።
ተከሳሾቹ የወንጀል ሕጉን እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ተላልፈዋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው ከተፈረደባቸው በኋላ፣ ቀሲስ በላይ ከ 2 አመት የእስር ቆይታ በኋላ ዛሬ በይፋ ከእስር ተለቀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 210 |
| 9 | በባህርዳር ከተማ የቀን ሰራተኛው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆነ
👉 ሽልማቱ ከወሎ ወደ ባህር ዳር ደርሷል
የባህር ዳር ነዋሪው ወጣት ኃይሌ እስከዚያው መኮንን በቆረጠው ቶምቦላ ሎተሪ በ4ኛ ዕጣ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶሞቢል ዕድለኛ ሆኗል፡፡
ወጣት ኃይሌ በቀን ስራ የተሰማራ ሲሆን አልፎ አልፎ ህይወቱን ለመቀየር ብዙ ሥራዎችን ይሞክር እንደነበር ገልጾ፤ ከነዚህም አንዱ እና ዋነኛው ሎተሪን መቁረጥ እንደነበር የገለጸ ሲሆን እድልና አጋጣሚ ገጥሞ እድለኛ አድርጎኛል በማለት ሽልማቱን ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በተረከበበት ወቅት በደስታ ስሜት ውስጥ ሆኖ ገልጾልናል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 302 |
| 10 | የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት በርካታ ተዋጊዎችን በማንቀሳቀስ ላይ መኾኑን አስታወቀ።
ወደ ብሉ ናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ የተንቀሳቀሱት ተዋጊዎች የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ለመውጋት ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር የወገኑ ኃይሎች እንደሆኑ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ከተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ጀምሮ በግዛቲቱ በርካታ አካባቢዎች በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ።
ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክ ከተማ ከአንድ ሳምንት በፊት ከሱዳን ጦር ሠራዊት መንጠቁ ይታወሳል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 225 |
| 11 | በቻይና ጎዳናዎች ላይ ስራ የጀመረው የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የወደፊቱ የትራፊክ ቁጥጥር አዲሱ ምዕራፍ
በምስራቅ ቻይና ዢጂያንግ ግዛት በምትገኘው ዮንግካንግ ከተማ፣ የትራፊክ ፍሰትን የመቆጣጠር እና የማስተካከል ስራ የሚያግዝ የሮቦት ትራፊክ ፖሊስ የመጀመሪያ የሙከራ ስራውን በይፋ ጀምሯል።
ይህ የቴክኖሎጂ ድንቅ ውጤት የሆነው ሮቦት ለ30 ደቂቃ ብቻ በመብራት ከተሞላ በኋላ ለአራት ሰዓታት ያህል ያለምንም እረፍት በተከታታይ መስራት የሚችል ነው።
የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው የመንገድ መገናኛዎች ላይ የሚከናወኑ መደበኛና ተደጋጋሚ ተግባራትን በብቃት ለማከናወን ተቀርጾ የተሰራ ነው።
ሮቦቱ በተለይም አሽከርካሪዎችንና እግረኞችን በስርዓት የመምራት፣ የመንገድ ላይ ደህንነት ማሳሰቢያዎችን የመስጠትና በትራፊክ መጨናነቅ ወቅት የትራፊክ ፖሊሶችን ስራ በከፍተኛ ደረጃ የማቃለል ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል።
ይህ የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ውጤት የከተሞችን የመንገድ ደህንነትና የትራፊክ አስተዳደር ወደ አዲስ የዘመናዊነት ደረጃ የሚያሸጋግር ድንቅ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።
@Addis_News
@Addis_News | 1 584 |
| 12 | የሆንግ ኮንግ አክቲቪስት ጆሹዋ ዎንግ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ ጥፋተኛነቱን አመነ
ታዋቂው የሆንግ ኮንግ የዴሞክራሲ መብት ተሟጋች ጆሹዋ ዎንግ፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር አብሮ በመስራት እና ማዕቀብ እንዲጣል በመጠየቅ በብሔራዊ ደህንነት ሕግ የቀረበበትን ክስ ፍርድ ቤት ቀርቦ አምኗል።
የ29 ዓመቱ አክቲቪስት እ.ኤ.አ በ2020 በቻይና እና በሆንግ ኮንግ ላይ ማዕቀብ ወይም ማገጃ እንዲጣስ የውጭ ሀገራትን ጠይቋል በሚል በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሷል።ወንጀሉ ከ3 እስከ 10 ዓመታት የሚደርስ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ድርጊቱ ከባድ አደጋ አደረሰ ተብሎ ከታመነ እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ሊደርስበት ይችላል።
ዎንግ በአሁኑ ወቅት በመንግስት ላይ በማመፅ ወንጀል የተበየነበትን የአምስት ዓመት ገደማ ቅጣት በመፈጸም ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ከእስር ይፈታል ተብሎ ይጠበቅ ነበር።
ዓቃቤ ሕግ እንዳስታወቀው፣ ዎንግ ዓለም አቀፍ ማዕቀብ እንዲጣል ለመጠየቅ መጣጥፎችን የጻፈና የቀድሞዋ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ ከበርካታ የውጭ ሀገር ፖለቲከኞች ጋር ተገናኝቷል።
ክሶቹ ሲነበቡለት በታላቅ ድምፅ ጥፋተኛ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣ የምዕራባውያን ዲፕሎማቶችም በችሎቱ ላይ ተገኝተዋል። የቅጣት ውሳኔው የሚሰጥበት ቀን በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል።
ሰላማዊ ነጋሲ
@Ethionews433 @Ethionews433 | 1 440 |
| 13 | የብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ቢሮውን በአዲስ አበባ ከፈተ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በብራዚል ጉብኝታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ያደረጉትን ውይይት መነሻ በማድረግ ቢሮው መከፈቱን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር መለስ ዓለም ገልጸዋል።
ተቋሙ ቢሮውን በአዲስ አበባ መክፈቱ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትብብርን በማላቅ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተመላክቷል።
ሀገራቱ የብሪክስ አባል እንደመሆናቸው ትብብራቸውን ወደ ተጨባጭ የንግድ ዕድሎች ለመቀየር እገዛ እንደሚያደርግም ነው የተገለጸው፡፡
በተጨማሪም የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያና በምስራቅ አፍሪካ ገበያ ያሉ የንግድ እድሎችን ለመመልከት የሚያስችል ነው፡፡
በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የሚገኙ ባለሀብቶች በብራዚል ያለውን ዕድል ለመመልከት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 526 |
| 14 | የደቡብ ኮሪያ ጠንቋዮች AI ገቢያችንን ክፋኛ ቀንሶብናል ብለው አማረሩ
በቴክኖሎጂ ምጥቀት ቀዳሚ ከሆኑት የዓለማችን አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ደቡብ ኮሪያ፣ የቅርብ ጊዜው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ዕድገት የዘመናት ታሪክ ባለው የባህላዊ ዕድል ትንበያ (ጥንቆላ) ኢንደስትሪ ላይ ከፍተኛ አደጋ እየደቀነ መሆኑ ተሰማ።
በአገሪቱ የሚገኙ ታዋቂ ዕድል ተንባዮችና ጠንቋዮች ወደ እነርሱ ይመጡ የነበሩ ደንበኞቻቸው ፊታቸውን ወደ AI ቴክኖሎጂ በማዞራቸው ምክንያት ሥራቸው ክፉኛ እንደ ተቀዛቀዘባቸው በምሬት በመግለጽ ላይ ናቸው።
በዋና ከተማዋ ሴኡል ዳርቻ በሚገኘውና በባህላዊ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) መንደርነቱ በሚታወቀው ‘ሚያ መንደር’ ውስጥ አሁን ላይ የደንበኞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ቀንሷል።
ቀደም ባሉ ዓመታት የደቡብ ኮሪያ ነዋሪዎች ስለ ጤናቸው፣ ትዳር፣ ፍቅር፣ ገንዘብ እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸው ለመጠየቅ ወደዚህ መንደር በብዛት ይጎርፉ ነበር። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ አብዛኞቹ ዜጎች በአካል ወደ መንደሩ ከመሄድ ይልቅ በኢንተርኔት አማካኝነት እንደ ChatGPT እና Gemini ያሉ የ-AI መተግበሪያዎችን በመጠቀም ዕድላቸውን መተንበይ መምረጣቸው ተገልጿል።
በዚሁ መንደር ውስጥ ከቀሩት ጥቂት ዕድል ተንባዮች መካከል አንዷ የሆኑት የ86 ዓመቷ አዛውንት ሶንግ ኦ-ሱን ሁኔታውን ሲያስረዱ፣ እሳቸው አሁንም ከዘመናዊው የኢንተርኔት ዓለም ርቀው እንደሚኖሩና ዕድልን ለመተንበይ “አራቱ የዕጣ ፈንታ ምሰሶዎች” (Saju) የሚባለውን የኮሪያ ጥንታዊ ኮከብ ቆጠራ ዘዴ በብሬይል መጽሐፍ እያነበቡ እንደሚጠነቁሉ ገልጸዋል።
አዛውንቷ ባለፉት 40 ዓመታት ያካበቱት ይህ የሰዎች ስነ-ልቦና የመረዳትና የማማከር ልምድ AI በቀላሉ ሊተካው የማይችለው የላቀ ሰብአዊ ችሎታ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። “በሕይወት የመኖር ተስፋ ቆርጠው ለመሞት እንኳ ወደ እኔ የመጡ ሰዎችን አሳምኜና አጽናንቼ ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉ አድርጌያለሁ” ሲሉም የሥራቸውን ማኅበራዊ ፋይዳ ያስረዳሉ።
ይሁን እንጂ የኢኮኖሚው እውነታ ሌላ ሆኗል። ቀደም ሲል በአካባቢው ከ 70 እስከ 80 የሚደርሱ ጠንቋዮች በሥራ ላይ የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ቁጥራቸው ከ20 በታች ዝቅ ብሏል። እንደ ‘ኢንኖፎሬስት’ (Innoforest) የተባለው የደቡብ ኮሪያ የጀማሪ ኩባንያዎች ትንተና ድርጅት መረጃ መሠረት፣ በአገሪቱ ያለው የዕድል ትንበያ ገበያ እጅግ ግዙፍና በ 2024 ብቻ በግምት 986 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የደረሰ ቢሆንም፣ አብዛኛው የገበያ ድርሻ ግን ወደ ዘመናዊ መተግበሪያዎች እየተዛወረ ነው።
ለዚህ ሽግግር ዋነኛው ምክንያት የዋጋና የቅልጥፍና ጉዳይ መሆኑ ይነገራል። የ-AI መተግበሪያዎች አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በነጻ ወይም በጣም በዝቅተኛ ክፍያ በሰከንዶች ውስጥ የሚሰጡ ሲሆን፣ በአንጻሩ እንደ ወይዘሮ ሶንግ ያሉ ባህላዊ ባለሙያዎች ለአንድ የዕድል ትንበያ ክፍለ-ጊዜ እስከ 35 ዶላር ገደማ ያስከፍላሉ። ይህ የዋጋ ልዩነትና የቴክኖሎጂው ተደራሽነት፣ ወጣቱ የኮሪያ ትውልድ ከባህላዊው መንደር ይልቅ ስማርት ፎኑን እንዲመርጥ ማድረጉን የዘርፉ ታዛቢዎች ገልጸዋል።
45% - 55% የሚጠጉ ደቡብ ኮርያውያን በህይወት ዘመናቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ የህይወት እጣ ፋንታቸው እንዲተነበይላቸው በመፈለግ ወደ ዕድል ተንባዮች (ጠንቋዮች) ቤት ያመራሉ።
Via መዝናኛ ሚዲያ
ዳጉ_ጆርናል
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 549 |
| 15 | ✨ ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨
🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው!
🎁 አስደሳች ቦነሶች
💰 የማሸነፍ እድሎች
⚡ ቀላል እና ፈጣን ተሳትፎ
🎊 በየቀኑ አዲስ ደስታ
🏆 አሸናፊ የመሆን እድል
📍ባሉበት ሁነው በ ስልክዎ የሚዝናኑበት ጨዋታ
🌟 ዕድል ለሚሞክሩት በሩን ትከፍታለች!
🌟 ድል ለሚደፍሩት ትመጣለች!
🔥 ዛሬ ይቀላቀሉ!
🔥 ይጫወቱ!
🔥 ይዝናኑ!
🔥 ዕድልዎን ይሞክሩ
@BellaBingo1bot
ለማንኛውም እገዛ --09 72 75 73 19 ይደውሉ
💙 Bella Bingo – የደስታ፣ የዕድል እና የአሸናፊዎች ምርጫ! | 1 476 |
| 16 | የአስመራ ነዋሪዎች በንጹህ ውሃ አጥረት
ምክንያት ቀይ ባህርን ለመጠጣት ተገደዋል ተባለ‼️
በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚኖሩ ዜጎች በከባድ የውሃ እጥረት ምክንያት የዕለት ተዕለት ህይወታቸው መስተጓጎሉንና ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ልብስ ማጠብ እና የንጽህና መጠበቂያ የሚሆኑ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለመጠበቅ ሲሉ የውሃ አጠቃቀማቸውን እጅግ ለመቀነስና አማራጭ የውሃ ምንጮችን በፍለጋ ለመንከራተት መገደዳቸውን ገልጸዋል።
የችግሩ አሳሳቢነት የከፋባቸው አያሌ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚናገሩት መደበኛ የቧንቧ ውሃ ማግኘት ካቆመ ቆይቷል፤ በዚህም ምክንያት የውሃ ቦቴዎችን በመጠበቅ በውድ ዋጋ ውሃ ለመግዛት ተገደዋል። ሁኔታው ይበልጥ አሳዛኝ የሚሆነው ደግሞ አቅም በሌላቸው ዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ሲሆን አንዳንዶቹ የዝናብ ውሃ ለመሰብሰብ ሲጠባበቁ ሌሎች ደግሞ ከቀይ ባህር የሚጓጓዘውን የጨው ውሃ ለተለያዩ ፍጆታዎች ለማዋል እስከመገደድ ደርሰዋል።
ባለፈው ሐምሌ ወር የወጣ አንድ ጥናት እንዳመለከተው በኤርትራ እየተባባሰ ለመጣው የውሃ አቅርቦት ችግር በምክንያትነት የተጠቀሱት የአየር ንብረት ለውጥ፣ የቆዩና የወደሙ መሰረተ ልማቶች እንዲሁም ደካማ የውሃ አስተዳደር ስርዓት ናቸው።
ጥናቱ አክሎም በአሁኑ ወቅት የሚገኘው የውሃ አቅርቦት መደበኛ ያልሆነና ለጤና አስተማማኝ እንዳልሆነ በማስገንዘብ ሊከሰት የሚችለውን የጤና አደጋ ጠቁሟል።
ይህ ደረቅ ወቅቶች በመጡ ቁጥር ተደጋገሞ የሚከሰተው የውሃ እጥረት በነዋሪዎች የኢኮኖሚ አቅም ላይም የከፋ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የውሃ ግዥ ወጪ እየጨመረ መምጣቱ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ያላቸውን ትንሽ ገቢ ለውሃ እንዲያወጡ በማስገደድ ተጨማሪ የኑሮ ውድነት ፈጥሮባቸዋል።
አሁን ላይ በአስመራ እየታየ ያለው ይህ ቀውስ በከተማዋ ያለውን የዘለቀ የመሰረተ ልማት ውድቀትና የመሰረታዊ አገልግሎቶች ማጣት አጉልቶ የሚያሳይ አሳሳቢ ክስተት ሆኗል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 508 |
| 17 | መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ጅማሮ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገበበት ነው ብለዋል፡፡
በዚህም ምክንያት መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች እንደሚከበሩ አመልክተዋል፡፡
ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን - ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ተላቅቃ ወደ ፈጣንና እመርታዊ የእድገት ምህዋር መግባቷን የምናሳይበት ቀን ነው ብለዋል፡፡
ይህ ዕለት በሁሉም ዘርፍ የተሰሩ ሥራዎችን እመርታዊ ለውጥ የምናስገነዝብበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡
ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን - 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ መሸጋገር የጀመረችበት ቀን በመሆኑ ዕለቱ የማንሰራራት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን በሚል ስያሜ ይከበራል፤ ኢትዮጵያ ለዘመናት በጽናት ጠብቃው የኖረችውን ነጻነትና ሉዓላዊነት ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን ለማስገንዘብ ዕለቱ የጽናት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡
ጳጉሜን 4 - የኅብር ቀን - ኢትዮጵያ የብዝሃ ማንነቶች ሀገር እንደመሆኗ ብዝሃነት ጌጣችንና ኅብረታችን ነው፤ ኅብረታችን ደግሞ የአንድነትና የጥንካሬያችን ምንጭ መሆኑን በማውሳት፤ ዕለቱ የኅብር ቀን መባሉን አስረድተዋል፡፡
ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ዓላማውም ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሰራች እንደምትገኝ ማስገንዘብ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
@Addis_News
@Addis_News | 1 710 |
| 18 | አሜሪካ በፈፀመችው የቦምብ ጥቃት በሰርግ ቦታ ላይ የነበሩ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውንየኢራን ቀይ መስቀል ማህበር ገለፀ ።
የኢራን ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው፣ በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል በሚገኝ የሰርግ ስነ-ሰርዓት ላይ በአሜሪካ ጥቃት ምክንያተት አራት ሰዎች (አንድ ህጻን ጨምሮ) ህይወታቸው አልፏል፤ ከ50 በላይ ሰዎችም ቆስለዋል።
ቀይ መስቀል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው ጽሁፍ፤ "በአሜሪካ የሚሳኤል ጥቃት የቦምብ ፍንጣሪ በሆርሞዝጋን ግዛት በሲሪክ ወረዳ ኩሄስታክ ከተማ የሰርግ ዝግጅት እየተካሄደበት በነበረ የመኖሪያ ቤት ላይ አርፎ የሰዎችን ህይወት አጥፍቱዋል" ብሏል።
ማህበሩ አክሎም "ከ50 በላይ ሰዎች ቆስለዋል፤ አንድን ህጻን ጨምሮ አራት ሰዎችም ሰማዕትነት ተቀብለዋል" ሲል ገልጿል።
የኢራን የመንግስት ይፋ ያደረገው ቪዲዮ፣ በሲሪክ በሚገኘው የሰርግ ስፍራ ላይ የደረሰውን ሰፊ ፍርስራሽ እና ጉዳት የሚያሳይ ሲሆን፣ በስተጀርባም የሰዎችን ድምጽና ጩኸት ማድመጥም ተችሏል።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እስካሁን ድረስ ስለተባለው ድርጊት መረጋገጥ የሰጡት አስተያየት የለም፤ነገር ግን ኢራን ለደረሰው ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ዝታለች፡፡
በደቡባዊቷ ሲሪክ ወረዳ የምትገኘው ስፍራ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ ትገኛለች።
ሀና ሰይፉ
@Ethionews433 @Ethionews433 | 1 619 |
| 19 | "መንግሥት ከተጠያቂነት ሊያመልጥ አይችልም!" - አብን
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሀን ላይ የተፈጸሙትን ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ የእምነት ተቋማት ውድመትና እገታዎችን በጽኑ ኮንኗል።
ንቅናቄው ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን አልተወጣም ሲል ከሷል።
ጥቃቱን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን እንደማይችል የገለጸው አብን፤ በጸጥታ መዋቅሩ ላይ ላለው ውድቀት የባለሥልጣናት ተጠያቂነት ሊረጋገጥ እንደሚገባ አሳስቧል።
አብን አክሎም የዜጎች የመኖር መብት ባልተከበረበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግና ማውራት እውነታውን መካድ ነው ብሏል።
ችግሩን ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመፍታት የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ፣ ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የምርመራ ሥርዓት እንዲዘረጋና ተፈናቃዮች በአስቸኳይ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 663 |
| 20 | በህንድ የቲክቶክ እይታ ለማግኘት ወደ አንበሳ ማቆያ የዘለለው ግለሰብ መነጋገሪያ ሆኗል
በህንድ ላሆር መካነ አራዊት ውስጥ አንድ የቲክቶክ ተጠቃሚ ለማህበራዊ ሚዲያ የሚሆን ቪዲዮ ለመቅረጽ ወደ አንበሶች ማቆያ ስፍራ ዘሎ ሲገባ በመታየቱ፣ ከፍተኛ የደህንነት ጉድለት ተከስቷል።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት የተሰራጨው ይህ ቪዲዮ፣ በስፍራው ስላለው የደህንነት አጠባበቅ ሁኔታ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
አንድ የቲክቶክ ተጠቃሚ የአንበሶች ማቆያ አቅራቢያ ወደሚገኘው የተከለከለ ቦታ እና ወደ አንበሳ ማቆያው ውስጥ በተደጋጋሚ የገባ ሲሆን፣ በስፍራው የነበሩት የደህንነት ሰራተኞችም እርምጃውን ማስቆም አልቻሉም።
ይህ ክስተት በስፍራው ስለሚተገበሩት የደህንነት አሰራሮች እና የደህንነት ሰራተኞች አፈጻጸም ላይ ጥያቄዎችን አስነስቷል።
የአራዊት መናፈሻው አስተዳደር፣ የደህንነት አሰራሮችን ለማጠናከር እንዲሁም የጎብኚዎችን እና የእንስሳትን ደህንነት ለማረጋገጥ አዲስ የደህንነት ኩባንያ እየተቀጠረ መሆኑን ገልጿል።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተወዳጅነትን ለማትረፍ (ቫይራል ለመሆን) ሲባል አንድ ግለሰብ ህይወቱን ለአደጋ ሲያጋልጥ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም።
ከዚህ ቀደም በክይበር ፓክቱንክዋ ግዛት ስዋት ወረዳ፣ አንድ ወጣት የቲክቶክ ተጠቃሚ ቪዲዮ እየቀረጸ ሳለ ሽጉጡን በድንገት በመተኮሱ ሕይወቱ አልፏል።
ለማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም ለቲክቶክ) አዳዲስ እና ልዩ በሆኑ መንገዶች ቪዲዮ የመቅረጽ አዝማሚያ የሚያስከትለውን የሞት አደጋ መቀነስ አልተቻለም፤ ልዩ በሆነ መልኩ ቪዲዮ የመቅረጽ ከፍተኛ ፍላጎትም ሕይወት ቀጥፏል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 791 |
