ar
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

الذهاب إلى القناة على Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Fresh መረጃ | FreshNews

تُعد قناة Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 56 739 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 023 في فئة التعليم والمرتبة 561 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 56 739 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -1 388، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -41، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.63‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.52‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 060 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 428 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

56 739
المشتركون
-4124 ساعات
-3147 أيام
-1 38830 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+1
في 7 قنوات
يونيو '26
+2
في 8 قنوات
Get PRO
مايو '260
في 8 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+3
في 8 قنوات
Get PRO
مارس '26
+1 303
في 14 قنوات
Get PRO
فبراير '260
في 4 قنوات
Get PRO
يناير '260
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '250
في 2 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+1
في 6 قنوات
Get PRO
أكتوبر '250
في 4 قنوات
Get PRO
سبتمبر '250
في 3 قنوات
Get PRO
أغسطس '250
في 1 قنوات
Get PRO
يوليو '250
في 2 قنوات
Get PRO
يونيو '250
في 6 قنوات
Get PRO
مايو '250
في 2 قنوات
Get PRO
أبريل '250
في 2 قنوات
Get PRO
مارس '250
في 10 قنوات
Get PRO
فبراير '250
في 18 قنوات
Get PRO
يناير '25
+44
في 10 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+1 502
في 16 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+4 897
في 9 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+10 897
في 6 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+13 478
في 5 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+17 234
في 5 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+9 021
في 5 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+20
في 7 قنوات
Get PRO
مايو '24
+351
في 14 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+847
في 16 قنوات
Get PRO
مارس '24
+558
في 33 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+1 785
في 15 قنوات
Get PRO
يناير '24
+3 011
في 18 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+3 094
في 23 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+730
في 120 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+13 017
في 37 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+26 548
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+2 062
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+2 838
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+554
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+672
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+1 658
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+3 193
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+1 734
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+895
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+1 925
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+642
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+99
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+547
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+1 026
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+1 241
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+1 528
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+2 018
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+329
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+370
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+390
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+639
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+596
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+736
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+1 209
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+1 351
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+1 280
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+1 459
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
24 يوليو0
23 يوليو0
22 يوليو0
21 يوليو0
20 يوليو0
19 يوليو0
18 يوليو0
17 يوليو0
16 يوليو0
15 يوليو0
14 يوليو0
13 يوليو0
12 يوليو0
11 يوليو0
10 يوليو0
09 يوليو0
08 يوليو0
07 يوليو0
06 يوليو0
05 يوليو0
04 يوليو0
03 يوليو0
02 يوليو+1
01 يوليو0
منشورات القناة
ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት ስኬቱን በማስመልከት ለደንበኞቹ የነጻ የኢንተርኔት እና የድምጽ አገልግሎቶችን አቅርቧል። ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ ያቀረበው አገልግሎት • 1.5 ጂቢ (GB) የኢን
ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት ስኬቱን በማስመልከት ለደንበኞቹ የነጻ የኢንተርኔት እና የድምጽ አገልግሎቶችን አቅርቧል። ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ ያቀረበው አገልግሎት • 1.5 ጂቢ (GB) የኢንተርኔት ዳታ፣ • 15 ደቂቃ የድምፅ ጥሪ፣ እና • 30 አጭር የጽሑፍ መልዕክቶች (SMS) ያካተተ ነው። የቴሌብር ሱፐርአፕ (telebirr SuperApp) ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ተጨማሪ 500 ሜጋ ባይት (MB) ዳታ የተሰጠ ሲሆን፣ ያልተገደበ ጥቅል ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ደግሞ የ10 ደቂቃ ነፃ የዓለም አቀፍ ጥሪ ስጦታ መዘጋጀቱን ገልጿል። ይህ ነጻ አገልግሎት ከሐምሌ 17 እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ፣ ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ድረስ የሚያገለግል መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል። @Addis_News

2
የ4 ዓመት ህጻን ልጅ በማገት 5 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ባልና ሚስት በጽኑ እስራት ተቀጡ ወንጀሉ የተፈፀመው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ከጠዋቱ 3 ሰአት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቀጠ
የ4 ዓመት ህጻን ልጅ በማገት 5 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ባልና ሚስት በጽኑ እስራት ተቀጡ ወንጀሉ የተፈፀመው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ከጠዋቱ 3 ሰአት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቀጠና አራት እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው። ተጠርጣሪ መታደል ታደሰ በ4ሺ ብር የወር ደመወዝ በቤት ሰራተኝነት በአቶ መልካሙ ረዳቴ እና በወ/ሮ ጥጋብ ጌታሁን መኖሪያ ቤት ትቀጠራለች። ግለሰቧ በተቀጠረች በ10ኛ ቀን የቀጣሪዎቿን ወደ ስራ መሄድን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የ4 አመት እድሜ ያለውን ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ችብስ ልግዛልህ በማለት ይዛው ትሰወራለች።የህፃኑ ወላጆች ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ልጃቸውን እና የቀጠሯትን የቤት ሰራተኛ ከቤት ያጧቸዋል። የቤት ሰራተኛቸው የትዳር አጋር የሆነው ግለሰብ ወደህጻኑ ወላጅ አባት ስልክ በመደወል ልጅህን አግተንዋል 5 ሚሊየን ብር አምጣ ብሎ ስልኩን ይዘጋል ። የልጃቸውን መታገት ተደውሎ የተነገራቸው ወላጅ አባት እና እናትም ለአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ያመለክታሉ። ፖሊስ የቤት ሠራተኛዋ መታደል ታደሰ ከትዳር አጋሯ መሠረት አየለ ጋር በመሆን ወደ ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሀን ከተማ ጫጫ ክፍለ ከተማ ህፃኑን እንደወሰዱት ይደርስበታል። ኋላም ተጠርጣሪዎች ቤት ተከራይተው ልጁን ካስቀመጡበት በቁጥጥር ስር በማዋል ታግቶ የነበረው ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ከነሙሉ ጤንነቱ ለወላጆቹ አስረክቧል። የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል። የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ ሆነው በማግኘቱ 1ኛ:- ተከሳሽ መታደል ታደሰ በ8አመት ከ4ወር 2ኛ :-ተከሳሽ መሰረት አየለ ደግሞ በ7አመት ከ9ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል ። @Addis_News
381
3
ኢራን ‘በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ሀብታም ሀገር ልትሆን ትችላለች’ስትል አሜሪካ ተናገረች የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢራን “በአክራሪመሪዎች የምትመራ ሀገር” መሆኗን በመግለጽ፣ እነዚህ መሪዎች
ኢራን ‘በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ሀብታም ሀገር ልትሆን ትችላለች’ስትል አሜሪካ ተናገረች   የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢራን “በአክራሪመሪዎች የምትመራ ሀገር” መሆኗን በመግለጽ፣ እነዚህ መሪዎች ስለ ኢኮኖሚ ጉዳዮች “ምንም ግንዛቤ የሌላቸው” መሆናቸውን ተናግረዋል።“ሀገራቸውን እያወደሙ ነው” ያሉት ሩቢዮ፣ “ኢራን ብትፈልግ ኖሮ በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ሀብታም ሀገር ልትሆን ትችል ነበር” ሲሉ አክለው ገልጸዋል።   “ነገር ግን በምትኩ ገንዘባቸውን ወስደው ለሂዝቦላህ፣ ለሃማስ እና ለሁቲዎች ይሰጡታል። ለሺዓ ታጣቂ ቡድኖች እንዲሁም በመላው ዓለም ሽብርተኝነት ለመደገፍ ያውሉታል።” ሲሉ አክለዋል፡፡ሩቢዮ ንግግራቸውን ሲቀጥሉ፣ የአሜሪካ ዋና ትኩረት “ከኑክሌር ነጻ የሆነች ኢራን” መሆኗን አስረድተዋል።   “የኑክሌር ጦር መሳሪያ ሊኖራቸው አይገባም፤ እስቲ ለዓለም ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አስቡት።” ሲሉም ስጋትነቱን ጠቅሰዋል፡፡የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቅርቡ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር ስለታወጀው የኒውክሌር ስምምነት መግለጫ ሰጥተዋል።ዋሽንግተን እና ሪያድ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር በሚያደርጉት ጥረት መካከል፣ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ በሲቪል የኑክሌር ትብብር ላይ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡   የአሜሪካ የኢነርጂ መምሪያ፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች ለሳውዲ አረቢያ የኑክሌር ቴክኖሎጂ እንደሚያቀርቡ በመግለጽ ስምምነቱን ታሪካዊ ሲል አወድሶታል። በስምዖን ደረጄ @Ethionews433 @Ethionews433
611
4
ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ? የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል። ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል። ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር። በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 267
5
በሩሲያ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ የመጸዳጃ ቤት ዉሃ የመጠጣት ውድድር ማዘጋጀቱ ዉዝግብ አስነሳ በሩሲያ ስታቭሮፖል የሚገኝ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ፣ በቅርቡ "Game of Thrones" በሚል ያል
በሩሲያ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ የመጸዳጃ ቤት ዉሃ የመጠጣት ውድድር ማዘጋጀቱ ዉዝግብ አስነሳ   በሩሲያ ስታቭሮፖል የሚገኝ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ፣ በቅርቡ "Game of Thrones" በሚል ያልተለመደ ውድድር ምክንያት በኢንተርኔት ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊዎች አዲስ ከሆኑ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫዎች ውስጥ፣ ትላልቅ የመምጠጫ ቱቦዎችን በመጠቀም "አልኮል ያልያዘ ጋዝ ያለው መጠጥ" እንዲጠጡ ይጠበቅባቸው ነበር፤ መጠጡን በፍጥነት የጨረሰውም አሸናፊ ተብሎ ተለይቷል።   በስታቭሮፖል ከተማ በሚገኝ የ"ዶሚክስ" መደብር ውስጥ የተካሄደው ይህ ያልተለመደ ውድድር፣ በርካታ ተሳታፊዎች የ100,000 ሩብል (1,276 የአሜሪካ ዶላር) ሽልማት ለማግኘት ሲሉ ከመጸዳጃ ቤት ጎድጓዳ ሳህን ውስጥ በፍጥነት እንዲጠጡ የሚያስገድድ ነበር። ተወዳዳሪዎቹ በሰባት ሰዎች ቡድን የተከፋፈሉ ሲሆን፣ ፈጣኑ ጠጪ ወደ ሁለተኛው ዙር ያልፍ ነበር።   በውድድሩ ሁለተኛ ምዕራፍ፣ ከቀዳሚው ዙር ያለፉት ሰባቱ አሸናፊዎች በተዘጋ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ላይ በተቻለ መጠን ረጅም ጊዜ መቀመጥ ነበረባቸው፤ በመጨረሻም መቀመጥ የቻለው ሰው የዚህ ያልተለመደ ዉድድር አሸናፊ ተብሎ ታዉጇል። በቤዛዊት አራጌ @Addis_News @Addis_News
1 321
6
በጅጅጋ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ በጅጅጋ ከተማ በካራማራ ክፍለ-ከተማ ልዩ ስሙ 10ኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሀምሌ 15 ቀን ማምሻውን በተከተሰ ከባድ የትራፊክ አ+2
በጅጅጋ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ በጅጅጋ ከተማ በካራማራ ክፍለ-ከተማ ልዩ ስሙ 10ኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሀምሌ 15 ቀን ማምሻውን በተከተሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። አደጋውን ያደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-85725 ኢቲ የሆነ ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ሲሆን በአደጋው ህይወታቸው ካለፉ 7 ሰዎች መካከል 5 ወንዶች ሲሆኑ 2ቱ ደግሞ ሴቶች ናቸው። አደጋው እንደደረሰ የአምቡላንስ ድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሰራተኞች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የቪአይፒ ፀጥታ አካላት በፍጥነት በስፍራው በመገኘት ጉዳት የደረሰበትን ህጻን ወደ ህክምና ተቋም ያጓጓዙ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል። ፖሊስ የአደጋውን ዝርዝር ምርመራ ውጤት በቀጣይ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ መገለፁን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ዘግቧል። #ዳጉ_ጆርናል
1 304
7
120 ስልክ ሿሿ ያደረገው ግለሰብ…. በኡጋንዳ በቀን 120 ስልኮችን የሰረቀው ግለሰብ ከስልኮቹ ጋር የተያዘ ሲሆን፣ «ስልኮቻችሁ የተሰረቁባችሁ ሰዎች ወደ ኡጋንዳ ፖሊስ ጣቢያ እየመጣችሁ ተቀበሉ» ተ
120 ስልክ ሿሿ ያደረገው ግለሰብ…. በኡጋንዳ በቀን 120 ስልኮችን የሰረቀው ግለሰብ ከስልኮቹ ጋር የተያዘ ሲሆን፣ «ስልኮቻችሁ የተሰረቁባችሁ ሰዎች ወደ ኡጋንዳ ፖሊስ ጣቢያ እየመጣችሁ ተቀበሉ» ተብሏል። የሚገርመው ነገር፣ ስልኮቹ የስክሪን ምስላቸው (Screen saver) እንኳን ሳይቀየር እንደነበረው ነው ያሉት። ያ ማለት የተሰረቀባቸው ሰዎች በስክሪናቸው ላይ ያደረጉት ምስል የራሳቸው ከሆነ በቀላሉ ስልካቸውን ማግኘት ይችላሉ ማለት ነው። ስለዚህ ለክፉም ለደጉም የስልካችሁን Screen Saver የራሳችሁን አድርጉት። ህዝቡም ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየተመመ ነው። Via Uganda Police @Seledadotio @Seledadotio
1 433
8
የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ያለመ ስብሰባ በኤርትራ ድንበር ተደረገ፣ስብሰባውን የመሩት አቶ አማኑኤል አሰፋ ናቸው። ሕወሓት የብልጽግናን መንግስት አስወግዳለሁ እያለ ነው፡፡ ቡድኑ ካለፈው እሁድ አን
የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ያለመ ስብሰባ በኤርትራ ድንበር ተደረገ፣ስብሰባውን የመሩት አቶ አማኑኤል አሰፋ ናቸው። ሕወሓት የብልጽግናን መንግስት አስወግዳለሁ እያለ ነው፡፡ ቡድኑ ካለፈው እሁድ አንስቶ 'ህልውናችን የሚረጋገጠው በብልጽግና መቃብር ላይ ነው' በሚል መሪቃል ስብሰባዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ የሕወሓት አመራሮች ‹‹ብልጽግናን ከስልጣን ማስወገድ አለብን›› በማለት በግላጭ እየተናገሩ ነው፡፡ በሚዲያዎቻቸውም የፌደራል መንግስቱን 'ጄንኖሳይዳዊ አገዛዝ' የሚል ስያሜ ሰጥተው በትግራይ ቴሌቪዥን ጭምር ዜና መስራት ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ ለህወሓት የጦርነት ጉሰማ በቀጥታ የሰጠው ምላሽ የለም። @Yenetube @Fikerassefa
1 352
9
ለምክክር ጉባዔ መጥታ ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት የልጇን ሥም "ኮሚሽን" አለችዉ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ
ለምክክር ጉባዔ መጥታ ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት የልጇን ሥም "ኮሚሽን" አለችዉ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች። ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ የነበረች የጋምቤላ ክልል ተወካይዋ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላ ስሙም "ምክክር" መባሉ የሚታወስ ነው። ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የመጣችው ሌላኛዋ የምክክሩ ተሳታፊ ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ በተመሳሳይ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን፥ ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች። የመውለጃ ጊዜዬ እየደረሰ መሆኑን ባውቅም ለኢትዮጵያዊያን አብሮነትና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ በሚመከርበት በዚህ ጉባኤ መሳተፍ አለብኝ በሚል አቋም ተገኝቻለሁ ብላለች፡፡ በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገራችን ይበጃል የምትለውን ሀሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ የቆየች ሲሆን፥ በዚህ ታሪካዊ ወቅት ልጇን በመገላገሏ መደሰቷን ገልጻለች። ዘገባዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ነዉ። @Seledadotio @Seledadotio
1 408
10
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ   በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የከተማው የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽ/ቤት አስታውቋል።እርምጃው በአብዛኛው በሱቆችና በንግድ ተቋማት ላይ የተወሰደ ሲሆን ከየካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ክትትል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።   የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ለማ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በመተላለፍ ፌስታል በመያዝ እና ለንግድ አገልግሎት ጥቅም ላይ ሲያውሉ በተገኙ 130 አካላት ላይ በህጉ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በቅርቡ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል አንድ ነጋዴ 17 ኩንታል ማዳበሪያ ይዞ በመገኘቱ የተወረሰበት ሲሆን በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ጨምር እንዲቀጣ ተደርጓል።   በመሆኑም ግለሰቦችና ተቋማት ፌስታል መጠቀም በህግ የተከለከለ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ህጉን ሊያከብሩ ይገባል ሲሉ አቶ ጴጥሮስ ለማ  ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በአዋጁ መሰረት ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ  በ2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።እንዲሁም በተቋም ደረጃ ፌስታል ያከማቸ፣ የሸጠ ወይም ለንግድ ዓላማ እንደ እቃ መያዣ ያቀረበ ተቋም እስከ 200 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ባለንብረቶችም  እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ ተጠቅሷል ።   @Seledadotio @Seledadotio
1 503
11
ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊዮን በላይ መድረሱን አስታወቀ ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለጋዜጠኞች በሰጠዉ መግለጫ አቅርቧል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስ
ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊዮን በላይ መድረሱን አስታወቀ   ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለጋዜጠኞች በሰጠዉ መግለጫ አቅርቧል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት የሞባይል ጣቢያዎች ከ10 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።    በበጀት ዓመቱ የ4ጂ ኔትወርክ  አገልግሎት  እየተስፋፋ ሲሆን  በዚህም 264 ከተሞችን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል። በተጨማሪም ሰባት ከተሞች በአምስተኛ ትዉልድ (5ጂ) ኔትወርክ ተጠቃሚ መሆን  የቻሉ ሲሆን በአጠቃላይ በአሁን ሰዓት 33 ከተሞች  የ5ጂ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፤ ይህ ደግሞ  10.2ሚሊዮን ደንበኞችን  ማስተናገድ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።   ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 90 .1 ሚሊዮን   መድረሱን ገልጿል። ይህም የእቅዱን 101.7 በመቶኛ  ማሳካት ያስቻለ ነው ተብሏል ። ከዚህም ውስጥ የድምጽ ተጠቃሚዎች 86.9 ሚሊዮን ፣ ብሮድባንድ 51.5 ሚሊዮን ፣ ፊክስድ ብሮድባንድ 1 ሚሊዮን ያካተተ ነው ። የፊክስድ ብሮድባንድ ተጠቃሚዎችን 1 ሚሊዮን ማድረስ በእቅድ ደረጃ የተያዘ መሆኑን ስራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።   ተቋሙ 470 የሚሆኑ ምርት እና አገልግሎቶችን ያቀረበ ሲሆን 193 የሚሆኑት አዳዲስ ናቸው። በዚህ ዓመት ደንበኞች እንዴት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን መጠቀም አለባቸው የሚለውን ትኩረት በማድረግ ደንበኞችን  ከስተመር ኢዱኬሽን በሚል  አገልግሎት የመስጠት ስራ እየጠተገበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።   በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
1 375
12
አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇 ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️ ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ
አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇 ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️ ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል። ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም። አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም። አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 363
13
የዝናብ ሁኔታ‼️ በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል። በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን  ይኖራቸዋል። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች  ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች  ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል። ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 562
14
እስራኤል የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አወደሰች በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ
እስራኤል የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አወደሰች በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ አድናቆታቸውን ለግሰዋል። ይህ የእስራኤል ድጋፍ የመጣው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያ ግድቡን በብቸኝነት እያንቀሳቀሰች ነው ሲሉ ከከሰሱ በኋላ ሲሆን፣ አምባሳደሩ በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በእርሻ፣ በጠብታ መስኖና በዓሣ ሀብት ልማት ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በሌላ በኩል በካይሮና በአዲስ አበባ መካከል ያለው የቃላት ልውውጥ እና ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት እየጨመረ መጥቷል። ግብፅና ሱዳን ያለ ህጋዊ ስምምነት ግድቡን መሙላትና ማካሄድ የውሃ ደህንነታችንን ይጎዳል ሲሉ ሲቃወሙ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ የ4 ቢሊዮን ዶላሩ ግድብ በታችኞቹ ሀገራት ላይ ምንም ዓይነት ጎጂ ተጽዕኖ እንደማያደርስና ለሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት ወሳኝ መሆኑን አጥብቃ ትገልጻለች። @Seledadotio @Seledadotio
1 596
15
ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500
ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ወደ ገበያው ለማስገባት አቅዷል። ማዕከላዊ ባንኩ በነሐሴ እና መስከረም ወራት አራት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ገልጿል። በእያንዳንዱ ጨረታም 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች እንደሚቀርብ አስታውቋል። @Seledadotio @Seledadotio
1 571
16
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰ+3
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio
2 041
17
የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ጀምሮ ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታወ 👉 ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17
የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ጀምሮ ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታወ 👉 ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል   የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ፣ የጤና ምክር እና የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎች አገልግሎቱን ያገኛሉ።   አገልግሎቱ ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የሚሰጥ መሆኑን በመግለፅ  በስፔሻሊስት እና በሰብስፔሻሊስት ሀኪሞች ይከናወናል።የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ የጤና ምርመራን ማበረታታት  ነው የተባለ ሲሆን በተለይም አቅም ለሌላቸው ዜጎች የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።   በነፃ ከሚሰጡት አገልግሎቶች ውስጥ የውስጥ ደዌ፣ የማህፀንና ፅንስ ሕክምና፣ የመለስተኛ ቀዶ ህክምና፣ የጥርስ ፣ የሥነ አዕምሮ ሕክምና፣ የልብ ምርመራ እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በየቀኑ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ በቁስቋም በሚገኘው የመኪና ማቆሚያ ስፍራ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የጤና ምርመራ ወይም ሕክምና የሚፈልጉ ዜጎች በተጠቀሰው ቦታ በመገኘት አገልግሎቱን መጠቀም እንደሚችሉ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
1 704
18
በትግራይ ብርቱ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ፡፡ በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው+1
በትግራይ ብርቱ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ፡፡ በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው ተገልጿል። በአንድ በኩል በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ በአዝርእትና በመስኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ 176 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳላገኙ ተገልጿል። በማዕከላዊ ዞን ወረዳ ቀይሕ ተኽሊ ዶክተር አታኽልቲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ ለሁለት ሰዓታት ያለማቋረጥ የዘነበው በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ከመቅጠፉ በተጨማሪ በአዝርእትና በመስኖ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል። በተመሳሳይ በዞኑ ወረዳ አሕፈሮም ሴሮ ቀበሌ የዘነበው ብርቱ ዝናብም በአዝርእትና በአትክልት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። በሌላ በኩል የትግራይ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ ትላንት ባወጣው መረጃ፤ በክልሉ ከሚገኙ 600 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት መካከል 176 በሚሆኑት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ አስታውቋል። ይህ ሁኔታ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፤ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ እጥረት በእርሻ ሥራና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ያሳያል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 559
19
ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013
ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እና የፈቃድ ውል ስምምነቱን አልጠበቀም ሲል አስታውቋል። ጣቢያው 60% የሚሆነውን ስርጭት ለፈቃድ አካባቢው የማዋል፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን የማቅረብ፣ እንዲሁም ሀገራዊ እና ህገ-መንግስታዊ እሴቶችን የማጠናከር ግዴታዎቹን አልተወጣም ተብሏል። ባለሥልጣኑ በተደጋጋሚ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም መሻሻል ባለመታየቱ እርምጃው ሊወሰድበት ችሏል። በዚህም መሠረት የሬዲዮ ጣቢያው ከተሰጡት ማስጠንቀቂያዎች በኋላ አስፈላጊዎቹን ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ አሟልቶ እስኪገኝ ድረስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ በሙሉ ታግዷል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡ @Addis_News
1 578
20
በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ ከ140 በላይ ስደተኞች ሕይወታቸው ማለፉ ተነገረ ወደ አውሮፓ ለማቅናት ከአፍሪካ የተነሱ ከ140 በላይ ስደተኞች በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ መሞታቸው ወይም የደረሱበት መጥፋቱ ተነግሯል። 160 ሰዎችን አሳፍራ ከጋምቢያ የተነሳችው ጀልባ ነዳጅ በመጨረሷ ምክንያት ለ25 ቀናት በባሕር ላይ ስትንሳፈፍ መቆየቷን የሞሪታኒያ የባሕር ጠረፍ ጥበቃ ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) እንዳስታወቀው ከሐምሌ 14 እስከ 18 በተደረጉ የነፍስ አድን ዘመቻዎች ቢያንስ 143 ሰዎች የሞቱ ወይም የጠፉ ሲሆን በሕይወት ከተረፉት መካከል ሙሉ ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ሁለት ሕፃናት በሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ተመላክቷል። ኤጀንሲው ከሞሪታኒያ ተነስቶ ወደ ስፔን ካናሪ ደሴቶች የሚወስደውን የአትላንቲክ መስመር "በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አደገኛ የፍልሰት መንገዶች አንዱ" ሲል የገለጸው ሲሆን ከመጠን በላይ መጫን እና ለባሕር ጉዞ የማይመቹ ጀልባዎችን መጠቀም ለአደጋው መበራከት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ጠቁሟል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 645