Fresh መረጃ | FreshNews
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Fresh መረጃ | FreshNews
تُعد قناة Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 56 645 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 025 في فئة التعليم والمرتبة 563 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 56 645 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 24 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -1 416، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -69، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.56%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.51% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 018 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 421 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ።
ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇
@Freshes_newsbot
Fresh News,Fresh Updates.”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 25 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 25 يوليو | 0 | |||
| 24 يوليو | 0 | |||
| 23 يوليو | 0 | |||
| 22 يوليو | 0 | |||
| 21 يوليو | 0 | |||
| 20 يوليو | 0 | |||
| 19 يوليو | 0 | |||
| 18 يوليو | 0 | |||
| 17 يوليو | 0 | |||
| 16 يوليو | 0 | |||
| 15 يوليو | 0 | |||
| 14 يوليو | 0 | |||
| 13 يوليو | 0 | |||
| 12 يوليو | 0 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | 0 | |||
| 09 يوليو | 0 | |||
| 08 يوليو | 0 | |||
| 07 يوليو | 0 | |||
| 06 يوليو | 0 | |||
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | 0 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | 0 |
| 2 | ከ10ሩ ንዑስ ቡድኖች የመነጩ ሃሳቦች ለ50ዎቹ ቡድን አባላት እየቀረቡ ነው - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከ10ሩ ንዑስ ቡድኖች የመነጩ ሃሳቦች ተጠናክረው በሰብሳቢዎቻቸው እና ጸሃፊዎቻቸው አማካኝነት ለ50ዎቹ ቡድን አባላት መቅረብ መጀመራቸው ገለፁ።
ዋና ኮሚሽነሩ የምክክር ሂደቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፥ በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ለውይይት አመቺ ይሆን ዘንድ 50 ተመካካሪዎች ባሉበት ቡድን ውስጥ ተሳታፊዎች አስር አስር ሆነው የምክክር ሂደቱን በአግባቡ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በዚህ መዋቅር መሰረት፣ እያንዳንዳቸው 10 አባላት ያሏቸው ንዑስ ቡድኖች ሲወያዩባቸው የቆዩትን በርካታ ሃሳቦች፣ አመለካከቶችና ምልከታዎች ከማመንጨት ተሻግረው ወደ ማጠናከር መሸጋገራቸውን ተናግረዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ እነዚህ በጥንቃቄ የተደራጁና የተጠናከሩ የውይይት ውጤቶችም በአሁኑ ሰዓት በየንዑስ ቡድኖቹ ሰብሳቢዎችና ጸሃፊዎች አማካኝነት 50 ተመካካሪዎች ለያዙት ቡድኖች በንቃት እየቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ አሰራር በየ 10ሩ አነስተኛ ቡድኖች ውስጥ የተነሱትን ስጋቶችና ተስፋዎች ሳይቀነሱና ሳይበታተኑ፣ ለሰፊው የ50ዎቹ ቡድን ውይይት ወጥና ጠንካራ ግብዓት እንዲሆኑ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛልም ብለዋል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 884 |
| 3 | የሳኡዲው ልዑል አብደላህ ቢን ፋህድ
በለንደን ሆቴል ሞቶ ተገኘ
በለንደን ኬንሲንግተን በሚገኘው ማሪዮት ሆቴል የ29 ዓመቱ የሳዑዲ ልዑል አብደላህ ቢን ፋህድ ሕይወት ማለፉን የብሪታንያ የሕክምና ምርመራ ባለሥልጣን አስታወቀ።
ዋና ዋና ነጥቦች፡
የሞቱ ምክንያት፡ ታህሳስ 15 ቀን 2025 (እ.አ.አ) በሆቴል መታጠቢያ ቤት ውስጥ ሞቶ ሆኖ የተገኘው ልዑሉ፣ ሕይወቱ ያለፈው ከፍተኛ መጠን ያለው አልኮል እና የአደንዛዥ ዕፅ ከአልኮል ጋር በመቀላቀሉ በተከሰተ የልብ ምት መቆም ነው።
የተገኙ ንጥረ ነገሮች፡ በደም ምርመራው መሰረት ከአልኮል እና ከGHB በተጨማሪ የካናቢስ እና የጭንቀት ማስታገሻ መድሃኒቶች (እንደ Xanax ያሉ) በስርዓተ-ህዋሱ ውስጥ ተገኝተዋል።
የህክምና ታሪክ፡ ልዑሉ ከዚህ ቀደም ከአልኮልና ከሐኪም ማዘዣ መድሃኒቶች ሱሰኝነት ጋር ይታገል ነበር፤ በለንደን እና በሰሜን ማገገሚያ ማዕከላትም ሕክምናዎችን ተከታትሎ ነበር።
የባለሥልጣኑ ውሳኔ፡ የሕክምና ባለሙያዎች እሱ ከህክምና ሲወጣ ራሱን የማጥፋት አደጋ ላይ እንዳልነበር ቢናገሩም፣ ረዳት ባለሥልጣኑ ጂን ሀርኪን ክስተቱን እንደ «አደጋ» ፈርጀውታል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 097 |
| 4 | የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT Exam) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ‼️
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም የሚሰጠውን መደበኛ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test/ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ፈተናውን ለመውሰድ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ ምዝገባ የሚካሄደው ከሀምሌ 15 – 25/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ ገብታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለፈተናውም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን። የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ፡- https://ngat.ethernet.edu.et
#ማሳሰቢያ:-
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ።
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) መሆኑን አውቃችሁ በቴሌ ብር በኩል በምዝገባው ወቅት የሚፈጸም ይሆናል
ምዝገባው የሚከናወነው በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የፈተና ጣቢያውን በሚመለከት ግን ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 096 |
| 5 | ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግዙፍ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ እያጠናቀቀች ነው
ኢትዮጵያ ጥሬ ወርቅን ወደ ዱባይ በመላክ ለብዙ አስርት ዓመታት ስታካሂድ የቆየችውን አሰራር በማቆም የመጀመሪያውን ግዙፍ ሀገር በቀል የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ለማስጀመር የመጨረሻ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በሀገሪቱ የሚመረተው ማናቸውም ወርቅ ወደ ውጭ አገር ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ የወርቅ አሞሌዎች ሆነው መጣራት ይኖርባቸዋል።
ይህ አዲስ አሰራር የሀገሪቱን የኤክስፖርት ገቢ ከፍ የሚያደርግ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን የሚያጠናክር እና ሕገ-ወጥ የወርቅ ኮንትሮባንድን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ እንደሚሆን ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የመጨረሻውን የፍተሻ ምዕራፍ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ዘመናዊ ተቋም በበቀጣይ ዓመት ሥራ የሚጀምር ሲሆን እንደ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ያሉ አበይት የማዕድን ልማቶችን ጨምሮ እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የወርቅ ምርት ሙሉ በሙሉ የሚያስተናግድ ይሆናል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
--ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja | 1 282 |
| 6 | መነጋገሪያ የሆነው ቪዲዮ‼️
በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ስልጠና ተከትሎ የተለቀቀው ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል።
ይህ ከላይ የሚታው ቪዲዮ ወታደራዊ ስልጠና ሲሆን ይህ ስልጠና ከደን ቅጠል ጋር በመመሳሰል (Leafe Mimicry) ከድሮን ጥቃት ለማምለጥ የተደረገ ያለ ስልጠና ነው ተብሏል።
Leafe mimicry በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት ተግባራዊ ተደርጎ እንደነበር ይነገራል።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 468 |
| 7 | #ሱዳን የኬሚካል መሣሪያዎች ጥቅም ላይ መዋልን በተመለከተ #አሜሪካ እንድታጣራ የቀረበላትን ጥሪ ችላ ብላለች ስትል ከሰሰች
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (አርኤስኤፍ) ጋር በሚደረገው ውጊያ የሱዳን ጦር ኃይል የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅሟል በሚል የቀረበውን ክስ አሜሪካውያን ባለሙያዎች በአካል ተገኝተው እንዲያጣሩ የቀረበውን ጥሪ ዋሽንግተን ችላ ብላለች ሲል ከሰሰ። ሚኒስቴሩ የአሜሪካ መንግሥት በቅርቡ የጣለው ማዕቀብ የፖለቲካ ውሳኔ እንጂ በማስረጃ የተደገፈ አይደለም ሲል አጣጥሎታል።
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፥ በሁለትዮሽ የትብብር ማዕቀፍ አማካኝነት አሜሪካውያን ባለሙያዎች በስፍራው ተገኝተው «የመስክ ምርመራ እና ቀጥተኛ ማረጋገጫ» እንዲያካሂዱ የቀረበውን ጥሪ አሜሪካ ሳትቀበለው ቀርታለች ብሏል። ሚኒስቴሩ አክሎም፥ ይህ አካሄድ እውነታውን ለማጣራት ከሁሉም በላይ አስተማማኝ እና ገለልተኛ መንገድ ነበረ ሲል ገልጿል።
«የሱዳን መንግሥት በጋራ ማዕቀፉ በኩል አሜሪካውያን ባለሙያዎች ወደ ሱዳን መጥተው የጦር ኃይሉ የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅሟል በሚል የቀረበውን ክስ በቀጥታ እንዲያጣሩ ጥሪ ቢያቀርብም፥ ከአሜሪካ ወገን ግን ለዚህ ጥሪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል» ሲል መግለጫው ያመላክታል።
የሱዳን መንግሥት ይህንን መግለጫ ያወጣው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ሱዳን የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅማለች የተባለውን ክስ እውቅና ለመስጠትም ሆነ ችግሩን ለመፍታት ትርጉም ያለው እርምጃ ለመውሰድ አልፈለገችም ማለቱን ተከተሎ ነው።
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid0zwSNZqYKUQthByxTcAvhz5NySeWzigdzPJpapznpCCznDvEy4KnU6FH4DAsj36ukl | 1 385 |
| 8 | የአገው ፈረስ ባህልን በአለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ የሚያስችለው ሰነድ ለዮኔስኮ ሊላክ ነው
በአማራ ክልል የሚገኙ የመስህብ ሀብቶችን በማልማትና በማስተዋወቅ ፣የባህልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪውን በማሳደግ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ እምቢአለ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የአዊ ብሄረሰብ መለያ የሆነውን የአገው ፈረስ ባህልን በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት(ዮኔስኮ) ለማስመዝገብ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።
ይህን ታሪካዊ ክብረ በአል በሰው ልጅ ወካይ የማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርስነት ለማስመዝገብ ታቅዷል፡፡ የአገው ፈረሰኞች ማህበር አባላት፣ የዞን፣ የክልልና የፌዴራል ባለድርሻ አካላትና የማህበረሰቡ ተወካዮች በተገኙበት የመጨረሻው የሰነድ ውይይት በባህርዳር ከተማ ተደርጓል።በውይይቱ ወቅት የሚያዳብሩ ሀሳቦችን በግብዓትነት በመቀበል ሰነዱን ማሻሸል እንደተቻለ አቶ አበበ ገልፀው አሁን ላይ ለዩኔስኮ ለመላክ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል በማለት ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ይህም የአዊ ዞንን ብሎም ክልሉን ከማስተዋወቅ ባለፈ እንደ ሀገር የሚያበረክተው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የጎላ እንደሆነ ተነግሯል ።ታሪካዊ ፣ ባህላዊ እንዲሁም ሀይማኖታዊ ዳራ ያለውና በየዓመቱ ጥር 23 ቀን ላይ የሚከበረው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ክብረ በዓል የፈረስ ሸርጥ፣ ጉግስ እና የሽምጥ ግልቢያ ውድድሮችን ያካትታል።የአገው ፈረሰኞች የነፃነት ተጋድሎ ያስመሰከሩ እና በዓድዋ ጦርነትም ጀግንነታቸውን ያሳዩ መሆናቸውን ታሪክ ያስረዳል፡፡
በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 333 |
| 9 | ለ17 ዓመታት በሕመም ፈቃድ 1 ሚሊዮን ዩሮ የተቀበለችው መምህርት ትምህርት ቤቷን ከሰሰች
በጀርመን የምትገኝ የ62 ዓመት የሙያ ትምህርት ቤት መምህርት ለ17 ዓመታት በሕመም ፈቃድ ላይ ሆና 1 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ ደመወዝ ከተከፈላት በኋላ፣ ትምህርት ቤቱ በጡረታ በማሰናበቱ ምክንያት ክስ አቀረበች።
መምህርቷ እ.ኤ.አ. ከ2009 ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት ገብታ የማታውቅ ቢሆንም፣ የሕክምና ማስረጃዎችን እያቀረበች ሙሉ ደመወዟን ስትቀበል ቆይታለች።
አዲሱ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ባደረገው ማጣራት ግን በእነዚህ ሁሉ ዓመታት በአስገዳጅ የመንግስት ሕክምና ምርመራ እንድታልፍ አለመደረጉ ተገልጧል።
በተጨማሪም መምህርቷ በሕመም ፈቃድ ላይ በነበረችበት ጊዜ የግል የሕክምና ድርጅት ከፍታ ስትሰራ እንደነበር ተጠራጥሮ የዱይስበርግ ግዛት ዐቃቤ ሕግ ምርመራ ጀምሮባታል።
ማጭበርበሯ ከተረጋገጠ የተከፈላትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እንድትመልስና በወንጀል እንድትጠየቅ ሊደረግ ይችላል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ሰሞኑ ዘግበዋል።
Via fidel
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 306 |
| 10 | ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት_ባንክ የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት ትልቅ እልቂት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠነቀቀ
የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት ባንክ አካባቢዎች የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት እየጨመረ በመምጣቱ ተጨማሪ እልቂቶችን ሊያስከትል እንደሚችል በማስጠንቀቅ የእስራኤል መንግሥት ጥቃቶችን ከመከላከል መቆጠቡን እና ተጠያቂነት ላለመኖር ድርጊቶች መንገድ መክፈቱን ከሰሰ።
ሐምሌ 17 በወጣው መግለጫ፣ ድርጅቱ ናብሉስ አቅራቢያ በሚገኘው የታል የፍልስጤም መንደር ላይ በተፈጸሙ ሁለት ጥቃቶች የአራት ፍልስጤማውያን እና የሁለት እስራኤላውያን ሕይወት ማለፉን ገልጿል።
የመብት ተሟጋች ቡድኑ እንደገለጸው፣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት፤ በአካባቢው የሰፈሩ የታጠቁ እስራኤላውያን በፍልስጤም ማህበረሰቦች ላይ ጥቃት የሚያሰነዝሩበትን፣ የእስራኤል ወታደሮች ደግሞ በጥቃቱ የሚሳተፉበትን ወይም ጣልቃ ከመግባት የሚቆጠቡበትን ሰፊ ክስተት ያመላክታል። በጥቃቶቹ ላይ ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ ከእስራኤል መንግሥት የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የሕግ ድጋፍ እንደሚያገኙ ድርጅቱ አክሎ ገልጿል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
--ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja | 1 442 |
| 11 | በቢሾፍቱ የኢትዮ ቴሌኮም የመሰረተ ልማት አውታር ላይ ዘረፋ የፈጸሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ
በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ውስጥ በኢትዮ ቴሌኮም የመሰረተ ልማት አውታር ላይ ዘረፋ የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በእስራት እንዲቀጡ ተወስኗል።የከተማው አቃቤ ሕግ ጽሕፈት ቤት የኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ምርመራ ሂደት እንዳስታወቀው፣ ተከሳሾች ሃሮን ዮሴፍ እና ተገኔ ተሾመ የኢትዮ ቴሌኮም ንብረት የሆኑ የሲሲቲቪ ኬብል ሽቦዎችን ዘርፈው ሊሰወሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ወንጀሉ የተፈጸመው በቢሾፍቱ ከተማ ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ኤረር ወረዳ «ጎልደን ሆቴል» ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ ሰባት ሰዓት ላይ መሆኑ ተገልጿል።ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቤ ሕግ የላከ ሲሆን፣ አቃቤ ሕግም የኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 464/2005 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 4ን በመጥቀስ በቁጥጥር ስር በዋሉት ግለሰቦች ላይ ክስ መስርቶባቸዋል።
ጉዳዩን የተመለከተው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ተከሳሾቹ በሕዝብ መሰረተ ልማት ላይ የፈጸሙት የዘረፋ ወንጀል በአቃቤ ሕግ ማስረጃ በበቂ ሁኔታ በመረጋገጡ እያንዳንዳቸው በ4 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፋል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 352 |
| 12 | እንደ Opta ዘገባ የአለማችን ምርጥ 100 ሊጎች...
1. ፕሪሚየር ሊግ
2. ላሊጋ
3. ቡንደስሊጋ
.
.
18. MLS
.
41. ሳውዲ ፕሮ ሊግ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 386 |
| 13 | የዓለም የምግብ ፕሮግራም፣ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ኢትዮጵያ ውስጥ የሰብዓዊ ድጋፎቼን ለመቀጠል 182 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል አለ።
ድርጅቱ፣ በተያዘው አውሮፓዊያን ዓመት ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታዎቹ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት እንደገጠመው ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ላይ ገልጧል።
እስከ ቀጣዩ ነሃሴ ወር በአገሪቱ ውስጥ የስብዓዊ እርዳታውን ለማስቀጠል ለእያንዳንዱ የምግብ እህል ተረጂ ከመደበው መደበኛ ራሽን ላይ 60 በመቶውን ለመቀነስ እንደተገደደም ድርጅቱ ጠቅሷል።
የአገሪቱ የሰብዓዊ እርዳታ ፍላጎት ከፍተኛ የኾነው፣ ግጭት፣ መፈናቀል እንዲሁም የኢኮኖሚ እና ከአየር ንብረት ጋር የተያያዙ ጫናዎች በተጋላጭ ማኅበረሰቦች ላይ በሚያሳድሩት ጉዳት ሳቢያ ነው ብሏል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 475 |
| 14 | መረጃ‼️
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ካቀረበችው የአበባ፣ የፍራፍሬ እና የአትክልት ምርት ግማሽ ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ አገኘች።
አገሪቱ በበጀት ዓመቱ ከዘርፉ ካገኘችው 490 ሚሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ ውስጥ፣ የአበባ ምርት 412 ሚሊዮን ዶላር በማስገባት ከፍተኛውን ድርሻ መያዙን ግብርና ሚንስቴር አስታውቋል።
ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የአትክልት ምርቶች 57 ሚሊዮን ዶላር ሲገኝ፣ ከፍራፍሬ ምርቶች ደሞ 21 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል ተብሏል፡፡
ኾኖም አገሪቱ ይህን ገቢ ያገኘችው ምን ያህል ቶን ምርቶች ለውጭ ገበያ አቅርባ እንደሆነ ሚንስቴሩ አልጠቀሠም።
ኢትዮጵያ በ2019 በጀት ዓመት 357 ሺሕ 457 ቶን አበባ፣ አትክልት እና ፍራፍሬ ለውጭ ገበያ በማቅረብ፣ 575 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዳለች ተብሏል፡፡
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 491 |
| 15 | #ሱዳን የኬሚካል መሣሪያዎች ጥቅም ላይ መዋልን በተመለከተ #አሜሪካ እንድታጣራ የቀረበላትን ጥሪ ችላ ብላለች ስትል ከሰሰች
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (አርኤስኤፍ) ጋር በሚደረገው ውጊያ የሱዳን ጦር ኃይል የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅሟል በሚል የቀረበውን ክስ አሜሪካውያን ባለሙያዎች በአካል ተገኝተው እንዲያጣሩ የቀረበውን ጥሪ ዋሽንግተን ችላ ብላለች ሲል ከሰሰ። ሚኒስቴሩ የአሜሪካ መንግሥት በቅርቡ የጣለው ማዕቀብ የፖለቲካ ውሳኔ እንጂ በማስረጃ የተደገፈ አይደለም ሲል አጣጥሎታል።
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፥ በሁለትዮሽ የትብብር ማዕቀፍ አማካኝነት አሜሪካውያን ባለሙያዎች በስፍራው ተገኝተው «የመስክ ምርመራ እና ቀጥተኛ ማረጋገጫ» እንዲያካሂዱ የቀረበውን ጥሪ አሜሪካ ሳትቀበለው ቀርታለች ብሏል። ሚኒስቴሩ አክሎም፥ ይህ አካሄድ እውነታውን ለማጣራት ከሁሉም በላይ አስተማማኝ እና ገለልተኛ መንገድ ነበረ ሲል ገልጿል።
«የሱዳን መንግሥት በጋራ ማዕቀፉ በኩል አሜሪካውያን ባለሙያዎች ወደ ሱዳን መጥተው የጦር ኃይሉ የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅሟል በሚል የቀረበውን ክስ በቀጥታ እንዲያጣሩ ጥሪ ቢያቀርብም፥ ከአሜሪካ ወገን ግን ለዚህ ጥሪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል» ሲል መግለጫው ያመላክታል።
የሱዳን መንግሥት ይህንን መግለጫ ያወጣው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ሱዳን የኬሚካል መሣሪያዎችን ተጠቅማለች የተባለውን ክስ እውቅና ለመስጠትም ሆነ ችግሩን ለመፍታት ትርጉም ያለው እርምጃ ለመውሰድ አልፈለገችም ማለቱን ተከተሎ ነው።
https://www.facebook.com/AddisstandardAmh/posts/pfbid0zwSNZqYKUQthByxTcAvhz5NySeWzigdzPJpapznpCCznDvEy4KnU6FH4DAsj36ukl | 1 626 |
| 16 | በኮንጎ በተከሰተው ኤቦላ በሽታ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ ማለፉ ተገለጸ
በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በኤቦላ በሽታ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ ማለፉን ይፋዊ መረጃዎች ያመለከቱ ሲሆን፣ የህክምና ባለሙያዎች የታጣቂዎች ጥቃት፣ በክሊኒኮች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እና ሰፊ የቁሳቁስ እጥረቶችን ተቋቁመው የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር እየታገሉ ይገኛሉ።
የኮንጎ የህዝብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ረቡዕ ዕለት እንዳስታወቀው፣ በኤቦላ በሽታ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ወደ 2,536 አድጓል። የሞቱት ሰዎች ቁጥርም ከ1,000 አልፎ 1,033 መድረሱን አክሎ ገልጻል።
ለ17ኛ ጊዜ የተከሰተው የኮንጎ የኤቦላ ወረርሽኝ በግንቦት ወር ላይ ይፋ የተደረገ ቢሆንም፣ ባለሙያዎች ግን የበሽታው ስርጭት ከሳምንታት በፊት መሰራጨት እንደጀመረ ያምናሉ።
ወረርሽኙ የተከሰተው እስከ 40 በመቶ የሞት መጠን ባለው «ቡንዲቡግዮ» (Bundibugyo) አማካይነት ሲሆን፣ እስካሁን የጸደቀ ክትባት የለውም።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 484 |
| 17 | 📢የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት🎯
ነገ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:-
✅ከጠዋቱ 1:00 – 11:00
👉ገርጅ መብራት ሃይል፣ ጃክሮስ፣ የረር ሆስፒታል፣ ጎሮ፣ ICMC ሆስፒታል፣ እስኩል ኦፍ ቱሞሮ፣ ቦሌ ሚካኤል፣ መሪ መስጅድ፣ ሳፋሪ እና ፉሪ፣ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2:00 – 9:30
👉ሆለታ፣ ህዳሴ፣ መናገሻ፣ ቡረዩ ከተማ አስተዳደር፣ ቡራዩ ኢንዱስትሪ መንደር እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2:00 – 6:00
👉ደብረ ብርሃን ከተማ ውሃ አቅርቦት፣ አልዩ አምባ፣ ሃኪም ግዛው ሆስፒታል፣አስራት ወ/ኢየሱስ ካምፓስ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2:00 – 12:00
👉መቀሌ ቀበሌ 18፣ ዲያስፖራ ሰፈር፣ ቀዳማይ ወያነ፣ ማጅክ ትምህርትቤት፣ ደብረ ዳሞ፣ አብርሃ ካስት፣ ሃውልቲ ሰማታት፣ DW ቢሮ፣ ፕላኔት ሆቴል እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2:30 – 10:30
👉ሱሉልታ 10 ኪሎ በከፊል፣ ዶሮ እርባታ፣ ቀንብሬ፣ አፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ጭሮ ከተማ፣ኦዳቡልቱ ዩንቨርሲቲ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3:00 – 8:00
👉ቤተ መንግስት፣ ቴክስታይል፣ ሐሙሲት ወጪ መስመሮች እንዲሁም ከባህርዳር ቁጥር 1 እና ከወረታ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሃይል የሚያገኙ አካባቢዎች፣
✅እንዲሁም ከሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ ጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ንጋቱ 12፡00 ድረስ:-
👉ከሻሸመኔ ወደ አዳሚ ቱሉ የሚሄደው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
👉 በአሰላ፣ በአዳሚቱሉ፣ በቡታጅራ፣ በወራቤ፣ በቡኢ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 500 |
| 18 | ሃዉቲ በቀይ ባህር ላይ የሚፈጽመዉን ጥቃት ስዊዲን አወገዘች
ስዊድን የሃዉቲ በሳውዲ አረቢያ ላይ የተሰነዘሩትን ዛቻዎች እንዲሁም ቡድኑ በቀይ ባህር የንግድ መርከቦች ላይ የሰነዘረውን ጥቃት አጥብቃ አውግዛለች።“በሳውዲ አረቢያ መንግሥት ላይ የተሰነዘሩትን ዛቻዎች እና በቀይ ባህር የንግድ መርከቦች ላይ የተሰነዘሩትን ጥቃቶች አጥብቀን እናወግዛለን” ሲሉ የስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሪያ ማልመር ስቴነርጋርድ በኤክስ ላይ ጽፈዋል።
“የባህር ደህንነት እና የመርከብ ነፃነት ለክልላዊ መረጋጋት እና ለአለም አቀፍ ንግድ መሠረታዊ ናቸው፣ እናም ከዓለም አቀፍ ሕግ ጋር በሚስማማ መልኩ መከበር አለባቸው” ሲሉ አክለዋል።ይህ መግለጫ የወጣው በኢራን የሚደገፈው የየመኑ ሃዉቲ ቡድን በሳውዲ አረቢያ ላይ የባህር ኃይል እገዳ ካወጀ እና በቀይ ባህር ውስጥ ሁለት የሳውዲ የነዳጅ ታንከሮችን ኢላማ ያደረገ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት ከፈፀመ በኋላ ሲሆን አንዱ የነዳጅ ታንከር በእሳት ተቃጥሏል።
በግጭቱ የተነሳ የመርከብ እንቅስቃሴ መስተጓጎል ቀጥሏል። የመርከብ ክትትል መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሐሙስ ዕለት አንድ መርከብ ብቻ የሆርሙዝን የባህር ወሽመጥ በተሳካ ሁኔታ አቋርጦ ነበር፣ ይህም ከግንቦት 7 ወዲህ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
በስምዖን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 526 |
| 19 | የኢራን ጦር ከቀድሞው ጊዜ በተሻለ ሁኔታ መዘጋጀቱን ቃል አቀባዩ ገለጹ
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል አሚር መሀመድ ኢራን ወታደራዊ ኃይሎች ከቀድሞው ጊዜ በበለጠ የዝግጅት አቅም ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል።
ለኢራን የመከላከያ ፕሬስ የዜና ወኪል በሰጡት ቃለ ምልልስ፤በተኩስ ማቆም ወቅት የተገኘውን ዕድል በመጠቀም የውጊያ ዝግጅታቸውንና የመዋጋት አቅማቸውን ማጠናከራቸውን ተናግረዋል።
ቃል አቀባዩ እንዳሉት፤ የኢራን ጦር ለማንኛውም ሊፈጠር ለሚችል ሁኔታ ዝግጅቱን አሻሽሎ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በጠላት ሊወሰድ የሚችለውን ማንኛውንም እርምጃ ቀላል በማድረግ እንደማይመለከቱት አስታውቀዋል።
አክለውም ጠላት በመሬት ኃይል ወረራ ቢፈጽም ከአየር ወይም ከሚሳኤል ጥቃቶች የበለጠ ተጋላጭ እንደሚሆን ገልጸው፤የመሬት ውጊያዎች በተቃዋሚው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ሰፊ እድል እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
የኢራን ጦር በመሬት ላይ በሚደረጉ ወታደራዊ ዘመቻዎች ውጤታማነቱና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅሙ ከፍተኛ እንደሚሆን አስረድተዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።
ትዕግስት ግርማ
@Ethionews433 @Ethionews433 | 1 665 |
| 20 | በደቡብ ወሎ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት አመት መመዝገብ የተቻለው 7 ቋሚ ቅርሶችን ብቻ መሆኑ ተነገረ
የደቡብ ወሎ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለመመዝገብ ካቀደዉ 16 ቋሚ ቅርሶች መካከል 7ቱን ብቻ በመመዝገብ የዕቅዱን 44 በመቶ ማሳካቱን ገልጿል ።
ከሀምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ እና በዞኑ በተከሰተዉ የፀጥታ ችግር ምክንያት ከቦታ ወደ ቦታ ተንቀሳቅሶ ለመስራት አስቸጋሪ በመሆኑና እስከአሁን ድረስም ችግሩ በመቀጠሉ በታቀደው መሠረት ማከናወን እንዳልተቻለ ተገልጿል ።
በዞኑ ቅርሶችን መመዝገብ የተጀመረዉ ከ2007 ዓ.ም አንስቶ መሆኑን ለብስራት ሬዲዮ የተናገሩት በደቡብ ወሎ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ አቶ ይድነቃቸዉ ጌታነህ ናቸዉ ።
በ2018 በጀት ዓመት የቅርስ ምዝገባ ማጠቃለያ በማድረግ በቀጣዮች ዓመታት ቅርሶችን የማልማትና የእንክብካቤ ስራ ለመስራት ታቅዶ የነበረ በመሆኑ በበጀት ዓመቱ እንዲመዘገቡ የታቀዱ ቅርሶች ከእቅድ በላይ እንደነበር አቶ ይድነቃቸው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 636 |
