Fresh መረጃ | FreshNews
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Fresh መረጃ | FreshNews
تُعد قناة Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 55 337 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 070 في فئة التعليم والمرتبة 595 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 55 337 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -859، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -78، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 4.02%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 3.22% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 226 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 780 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 9.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ።
ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇
@Freshes_newsbot
Fresh News,Fresh Updates.”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 05 سبتمبر | 0 | |||
| 04 سبتمبر | 0 | |||
| 03 سبتمبر | 0 | |||
| 02 سبتمبر | 0 | |||
| 01 سبتمبر | 0 |
| 2 | ኢትዮጵያ በ83 ቢ. ብር ወጪ 16
ግዙፍ መርከቦችን ልትገዛ ነው
ኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን የሎጂስቲክስ አቅርቦት ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት አቅዳለች። በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ የሚከናወነው ይህ የግዥ እቅድ አሁን ካሉት 10 መርከቦች በተጨማሪ የሚከናወን ሲሆን፣ ቀደም ሲል ከነበሩት ከ25 ሺህ እስከ 28 ሺህ ቶን አቅም በበለጠ ከ50 ሺህ እስከ 63 ሺህ ቶን የመሸከም አቅም ያላቸው ግዙፍ መርከቦችን የሚያካትት ነው።
የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ እንደገለጸው፣ በአሁኑ ወቅት ከስድስት መርከቦች በላይ ሕጋዊ የግዥ ሥርዓት በሂደት ላይ ይገኛል። አዲሶቹ መርከቦች ስትራቴጂክ ግብዓቶችን በብቃት በማስገባትና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በወቅቱ በመላክ የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 606 |
| 3 | #NGATResult
ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
@Seledadotio
@Seledadotio | 780 |
| 4 | ለስራ አጦች ደመወዝ መክፈል ተጀመረ‼️
አልጀርያ ስራ አጥ ለሆኑ ወጣቶቿ ደምሞዝ መክፈል ጀመረች
የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ለዜጎቿ የዘረጋችው አስደናቂ የማህበራዊ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመላው አፍሪካ ከፍተኛ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል።
ሀገሪቱ የተፈጥሮ ሀብቷን እና የኢኮኖሚ አቅሟን ቀጥታ የዜጎቿን ህይወት ለማሻሻል በሚያስችሉ ዘመናዊ ውሳኔዎች ላይ በመመደብ በአፍሪካ አዲስ ምሳሌነቷን እያሳየች ነው።
ሀገሪቷ ስራ ለሌላቸው ወጣቶች በወር 96 ዶላር ድጋፍ ታደርጋለች።
ይህ ድጋፍ ወጣቶች ስራ እስኪያገኙ ድረስ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን እንዲሸፍኑ የሚያስችል ሲሆን ከገንዘቡ በተጨማሪ ነፃ የጤና መድህን አገልግሎትም ያካትታል ተብሏል።
በወር ከ 216 ዶላር በታች የሚያገኙ ዜጎች ምንም አይነት የገቢ ግብር እንዳይከፍሉ አድርጋለች።
በተጨማሪም አነስተኛ የደመወዝ ወለል ወደ 170 ዶላር ከፍ በማድረግ የዜጎችን የመግዛት አቅም እንዲሻሻል አድርጋለች።
ከዚህ በተጨማሪም ለህዝቧ በሙሉ ነፃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት አረጋግጣለች።
አልጄሪያ ግዙፍ የተፈጥሮ ጋዝ እና የሃይል አቅሟን በመጠቀም 100 በመቶ ለሚጠጉ ዜጎቿ ሙሉ በሙሉ ተራሽ እና ነፃ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማድረስ ችላለች።
ይህም በገጠር እና በከተማ የሚኖሩ ዜጎቿ በእኩል መሰረታዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል ነው የተባለው።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 006 |
| 5 | በሁለት ወራት ዉስጥ ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ነፃ የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል ተባለ
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ባለፉት ሁለት ወራት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት ማግኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ ።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ እንደተናገሩት በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ለ20 ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አገልግሎቱን አግኝተዋል ።
በመርሃ ግብሩ ከተለያዩ የጤና ተቋማትና የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ዜጎች የሕክምና ምርመራና ሌሎች ነፃ የጤና አገልግሎቶችን ማግኘታቸው ተገልጿል ።
በተመሳሳይ መልኩ የደም እጥረትን ለመቀነስ በተደረገው ጥረት 160 ሺህ ዩኒት ደም መሰብሰቡን ዶክተር ደረጄ መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል ።
በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ 70 ሺህ ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎቶችም መሰጠታቸውን የጤና ሚኒስቴር ደኤታው አክለዋል ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደገለጸው የበጎ ፈቃድ የጤና አገልግሎቱ በተለይም የህክምና ወጪን በመሸፈን የመታከም አቅም ለሌላቸው ዜጎች እፎይታን የሰጠ ነዉ ብለዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል | 966 |
| 6 | የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ ገንዘብ ለማስተላለፍ የሚያስችል ‘CoopRemit’ የተሰኘ አዲስ የሬሚታንስ መተግበሪያ ሥራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ።
ባንኩ ነሀሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ያደረገው ይህ መተግበሪያ፤ ደንበኞች ከ‘App Store’ እና ‘Play Store’ በቀላሉ በማውረድ ሊጠቀሙበት የሚችሉ ሲሆን፣ በገበያ ዋጋ ላይ የተመሰረተ ከፍተኛ የምንዛሪ ዋጋ (Best Rate) የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መተግበሪያው የሌሎች ተቋማትን ዕለታዊ የምንዛሪ ተመን በማነጻጸር የተሻለውን መምረጥ የሚያስችል በመሆኑ ደንበኞች መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡ ያግዛቸዋል።
በተጨማሪም ከውጭ የሚላከው ገንዘብ ወደ ኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክም ሆነ ወደ ሌሎች የሀገር ውስጥ ባንኮች ሂሳብ በቀጥታ፣ በፈጣንና በአስተማማኝ ሁኔታ የሚደርስ ነው ተብሏል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደርቤ አስፋው እንደተናገሩት፤ ደንበኞች ገንዘባቸውን በቪዛ፣ በማስተር ካርድ፣ በአፕል ፔይ ወይም በጉግል ፔይ በመጠቀም በቀጥታ በ‘CoopRemit’ መተግበሪያ በኩል መላክ ይችላሉ።
#ዳጉ_ጆርናል | 918 |
| 7 | የሱዳኑ ጦር መሪ አብዱል ፋታህ
አል-ቡርኻን አስመራ ገቡ
የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር ጄነራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን ኤርትራ የገቡ ሲሆን አስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አል-ቡርኻን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ጋር ውጊያ ውስጥ ከገቡ ወዲህ ዋነኛ ደጋፊያቸው ወደ ሆነችው ኤርትራ ሲያቀኑ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
የኤርትራ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል እንደገለጹት፣ የጄነራል አል-ቡርኻን ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረግ መደበኛ የምክክር አካል ነው። ሁለቱ መሪዎች በቆይታቸው የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 986 |
| 8 | ሰበር - ቻይና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝው አዲስ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቀደች‼
የቻይና ብሔራዊ የመድኃኒትና የሕክምና ምርቶች አስተዳደር NEO የተሰኘውን የሳንቲም ያህል መጠን ያለው አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ (BCI) ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ሰጥቷል።
📌 ቴክኖሎጂው ምንድን ነው?
በጽንግሁዋ ዩኒቨርሲቲ እና በኒውራክል ቴክኖሎጂ የተገነባው ይህ መሳሪያ፣ ከምርምር ማዕከላት ውጭ የሰዎችን የእንቅስቃሴ አቅም ለመመለስ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ያገኘ በዓለማችን የመጀመሪያው በአእምሮ ውስጥ የሚተከል ቴክኖሎጂ ሆኗል።
📌ከኢሎን መስክ Neuralink በምን ይለያል?
የኢሎን መስክ ኒውራሊንክ (Neuralink) አሁንም በሰው ልጅ ላይ በሚደረግ የሙከራ ደረጃ ላይ ብቻ የሚገኝ ሲሆን፣ NEO ግን ደህንነቱን ባስቀደመው ልዩ ዲዛይኑ ምክንያት በፍጥነት የንግድ ፈቃድ ማግኘት ችሏል።
📌መሳሪያው የአእምሮ ክፍሎችን ጥሶ ከመግባት ይልቅ 8 ሴንሰሮቹ ከአእምሮ ውጫዊ ሽፋን (dura mater) ላይ የሚያርፉ በመሆናቸው የህብረህዋሳት ጉዳትንና የደም መፈሰስን በእጅጉ ይቀንሳል።
📌 ይህ ፈቃድ በፅኑ የአንገት አጥንትና የሕብረ-ሰstandard አደጋ ምክንያት ሙሉ በሙሉ የእጅና የእግር ሽባነት ለገጠማቸው፣ ነገር ግን የተወሰነ የእጅ እንቅስቃሴ ላላቸው ከ18 እስከ 60 ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ አዋቂዎች የተፈቀደ ነው።
📌በ11 ሆስፒታሎች ውስጥ በተደረጉ የሕክምና ሙከራዎች፣ ስርዓቱ በቤት ውስጥ በአእምሮ እዘዛ ዕቃዎችን የመጨበጥ ድጋፍ በመስጠት 100% ስኬት አስመዝግቧል።
ቴክኖሎጂው የሰዎችን የሃሳብ ፍላጎት በመተርጎም ከሮቦቲክ የእጅ ጓንት ጋር በማያያዝ፣ ታካሚዎች እንደ መብላትና መጠጣት ያሉ የዘወትር ተግባራቸውን በራሳቸው እንዲያከናውኑ አስችሏቸዋል።
👇እዚህ ድምፅ ይስጡ👇
https://yekinlibochaward.org/nominees/wasu-mohammed
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 | 1 |
| 9 | በካፋ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ገደማ በወረዳው ቦባ በላ ቀበሌ በተለምዶ ቄነች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መከሰቱ ተገልጿል።
በዚህም ኮድ 3-32226 የሆነ ኤፍ ኤስ አር ጭነት መኪና ተገልብጦ በደረሰው አደጋ የአሽከርካሪውና የረዳቱ ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በአደጋው በንብረት ላይም ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ የተገለፀ ሲሆን የአደጋው ትክክለኛ መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል።አካባቢው ተደጋጋሚ አደጋ የሚደርስበት ሲሆን እና ከፍተኛ ቁልቁለት ያለው ቦታ በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት የሚመለከተው አካል ተገቢውን መፍትሄ እንዲያፈላልግ ጥሪ ቀርቧል።
በመሆኑም አሽከርካሪዎች በአካባቢው ሲያልፉ ፍጥነታቸውን በመቀነስ በጥንቃቄ ሊያሽከረክሩ ይገባል ሲሉ ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 1 029 |
| 10 | ቡና አብዝቶ መጠጣት የእንቅልፍ ጊዜን ቢያሳጥርም ጥልቀቱን እንደሚጨምር ተነገረ
በቀን አራት ወይም ከዚያ በላይ ሲኒ ቡና መጠጣት የእንቅልፍ ቆይታን ያሳጥራል፤ ሆኖም በእንቅልፍ ወቅት የሚገኘውን ጥልቅ እረፍት እንደሚጨምር አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ።
በስዊዘርላንዱ ተመራማሪ በቤንጃሚን ስተኪ የተመራው ይህ ጥናት፣ የዩኬ ባዮባንክ እና የHypnoLaus መረጃዎችን በመተንተን የተሰራ ነው።
ተመራማሪዎቹ እንዳረጋገጡት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ካፌይን መውሰድ የእንቅልፍ ሰዓትን በ11 ደቂቃ ያህል ያሳጥራል።
ነገር ግን፣ የሰውነት ህዋሳትን ለማደስ እና ኃይልን ለማገገም ወሳኝ የሆነው "የዝቅተኛ ሞገድ እንቅልፍ" ጥልቀት ይጨምራል።
ሳይንቲስቶች እንደሚሉት፣ ይህ የሰውነት ተፈጥሯዊ ምላሽ ሲሆን፣ ያጣውን አጭር የእንቅልፍ ሰዓት በጥልቅ እንቅልፍ ለማካካስ የሚያደርገው ጥረት ነው።
ጥናቱ ቡና የእንቅልፍ መጠንን ቢቀንስም፣ የጥራት መጠኑ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር አመልክቷል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 025 |
| 11 | ብልፅግና ከ70-80% አዲስ ተሿሚዎች‼️
ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤትን ተከትሎ በሚመሰርተው መንግስት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆነውን ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሰኑ ተሰማ።
የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህንን ውሳኔያቸውን በሚንስትር እንዲሁም ሚንስትር ዲኤታ ቦታዎች ላይ እየሠሩ ለሚገኙ ተሿሚዎች ማሳወቃቸውን የገለጡልን ምንጮች፤ ረዘም ላሉ ዓመታት በአመራርነት ያገለገሉ ተሿሚዎች ራሳቸውን ለሌላ ተልዕኮ እንዲያዘጋጁ እንደተነገራቸው ጠቁመዋል።
ይህም በሚንስትር እንዲሁም በሚንስትር ዲኤታነት እያገለገሉ ከሚገኙ ተሿሚዎች መካከል በአምባሳደርነት የሚሾሙ እንደሚኖሩ ጠቋሚ መሆኑን ሰምተናል።
ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ሚንስትሮችንና ሚንስትር ዲኤታዎችን በሰበሰቡበት መድረክ “ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ ለውጥ ይደረጋል” ሲሉ መናገራቸውን የገለጡልን ምንጫችን፤ ከዚህ ውሳኔያቸው በኋላ ከሚንስትሮች እና ሚንስትር ዲኤታዎች ጋር ለቀናት ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ነግረውናል።
ጠቅላይ ሚንስትሩ ከአምስት ዓመታት በፊት ካቢኔያቸውን ባዋቀሩበት ወቅት፤ ከ22ቱ የሚንስትርነት ቦታዎች መካከል ሦስቱን ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን፤ በአሁኑ የካቢኔ ምርጫም የሚንስትርነት ሹመት የሚሰጣቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የሚኖሩበት ዕድል ሰፊ መሆኑን ምንጮች ነግረውናል።
ዋዜማ ያነጋገረቻቸው የፓርቲዎች አመራሮች፤ ከሹመት ጋር በተያያዘ እስካሁን ለፓርቲያቸው የቀረበ ጥያቄ አለመኖሩን የገለጹ ቢሆንም፤ ሹመት እንደሚሰጣቸው ቃል እንደተገባላቸው የሚገልጡ የፓርቲ አመራሮች መኖራቸውን ሰምተናል።
እየተካሄዱ ያሉ ስብሰባዎች ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ሚንስትሮችን ለብቻ፤ ሚንስትር ዲኤታዎችንም ለብቻ ሰብስበው ማነጋገራቸውን የገለጡልን ምንጮች፤ በስብሰባዎቹ ያለፉት ዓመታትን ከመገምገም ባለፈ አዲስ የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ውይይት እየተካሄደባቸው ነው።
በስብሰባዎቹ ከሚቀርቡ ሰነዶች ባሻገር፤ የቡድን ውይይቶች እየተካሄዱ መሆናቸውንም ሰምተናል።
ሚንስትሮች ስብሰባ ማድረግ ከጀመሩ ሁለተኛ ሳምንት ያስቆጠሩ ሲሆን በዚህኛው ሳምንት የተጀመረው የሚንስትር ዲኤታዎች ስብሰባ ደግሞ ስልክ ይዞ መግባት የተከለከለበት መሆኑን አውቀናል።
አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እየተካሄደ እንደሆነ የተነገረለት ይህ ስብሰባ ለተጨማሪ ቀናት እንደሚቀጥልም ምንጮች ጠቁመዋል።Via : ዋዜማ
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 249 |
| 12 | ህንዳውያን የአሜሪካን ግሪን ካርድ ለማግኘት 179 ዓመታት መጠበቅ አለባቸው ተባለ
በናሽናል ፋውንዴሽን ፎር አሜሪካን ፖሊሲ የወጣው አዲስ ሪፖርት እንደሚያመላክተው ህንዳያውያን የቋሚ ነዋሪነት ፈቃድ ወይም ግሪን ካርድ ለማግኘት አሁን ላይ የ179 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ ይጠብቃቸዋል።
ይህ እጅግ ረጅም የጥበቃ ጊዜ በስራ ላይ በተመሰረተው የሁለተኛ ደረጃ ቅድሚያ የቪዛ ምድብ ላይ የሚታይ ሲሆን፣ ለመዘገየቱም ዋነኛው ምክኒያት በከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ የተከማቸው በርካታ የኢሚግሬሽን አመልካቾች ማመልከቻ መደራረብ እንደሆነ ተገልጿል።
ለጉዳዩ በዋነኛነት እንደ ምክኒያት የሚጠቀሰው ያልተጣራው የኢሚግሬሽን ማመልከቻ ክምችት ነው። የአሜሪካ ኮንግረስ እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ በስራ ምክኒያት የሚሰጡ የግሪን ካርድ ፈቃዶችን ቁጥር በዓመት በ140ሺ እንዲወሰን ገደብ ጥሎ ነበር። ይህም ቁጥር ከፍተኛ ሙያ ያላቸውን ሰራተኞች እና ጥገኞቻቸውን በአንድ ላይ የሚያጠቃልል ነው። በተጨማሪም የትኛውም ሀገር ከጠቅላላው የዓመቱ የግሪን ካርድ ኮታ ከ7 በመቶ በላይ ማግኘት አይችልም። እነዚህ ገደቦች የዓለም ሀገራትን ተሳትፎ ብዝሃነት ለማረጋገጥ እና ከአሜሪካ ቅድሚያ ፖሊሲ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ታስበው የተዘጋጁ ናቸው።
በመሆኑም እንደ ህንድ ያሉ በከፍተኛ የህዝብ ቁጥር የሚታወቁ ሀገራት እንደ አይስላንድ ወይም ሉክሰምበርግ ካሉ አነስተኛ ህዝብ ካላቸው ሀገራት ጋር ሲነጻጸሩ በከፍተኛ ደረጃ ተጎጂ ሆነዋል። በዚህም የተነሳ በርካታ ህንዳውያን በኢሚግሬሽን ሂደቱ መጨናነቅ የተነሳ 179 ዓመታት ለመጠበቅ ተገደዋል።
ኤንኤፍኤፒ (NFAP) ስሌቱን ያዘጋጀው ያለፉትን አምስት ዓመታት መረጃዎች መነሻ በማድረግ ነው። ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ብቻ 264ሺ 521 ህንዳውያን የቪዛ አመልካች የነበሩ ቢሆንም ግሪን ካርድ ማግኘት የቻሉት 12ሺ 262 ያህሉ ብቻ ናቸው። ይህም ማለት በየዓመቱ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ህንዳውያን አመልካቾች እና ጥገኞቻቸው ቪዛ ሳያገኙ ወደ ነባሩ የተከማቸ የጥበቃ ዝርዝር ውስጥ ይገባሉ።
አሁን ላይ ያለው የጥበቃ ዝርዝር ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ህንዳውያንን ያቀፈ ሲሆን ይህንን ማመልከቻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እና ለእያንዳንዱ አመልካች ግሪን ካርድ ለመስጠት በግምት 179 ዓመታት ይወስዳል። ይህም በአሁኑ አሰራር ሂደት ማለፍ በተግባር የማይቻል መሆኑን ያሳያል። በተጨማሪም ከወላጆቻቸው ጋር ጥገኛ ሆነው ወደ አሜሪካ የገቡ ህፃናት ዕድሜያቸው 21 ሲሞላ የጥገኛነት መብታቸውን ያጣሉ። በመሆኑም ሀገሪቱን ለቀው ለመውጣት ይገደዳሉ ወይም ጊዜያዊ የሰራተኛ ቪዛ ለማግኘት መታገል ይኖርባቸዋል።
ዕድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ ህጋዊ መብታቸውን የሚያጡ ጥገኞች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ሁኔታው ለህንዳውያን እጅግ አሳሳቢ ሆኗል። እነዚህ ህንዳውያን ሙሉ ህይወታቸውን በሀገሪቱ ያሳለፉ ቢሆንም ኮሌጅ እንደጨረሱ እንደ ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ ይቆጠራሉ።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 277 |
| 13 | በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የሰብል አምራቾች እና አግሮ ቢዝነስ ኤክስፖ ሊካሄደ ነው
የኢትዮጵያ ሰብል አምራቾችና ላኪዎች ዘርፈ-ብዙ ማህበር ከኖርዲክ ትሬዲንግ፣ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ሰብል አምራቾችና ኤግሪ-ቢዝነስ ኤክስፖ ሊያካሄድ መሆኑን አስታውቋል።
ኤክስፖው የኢዮጵያን የሰብል ምርቶች፣ የግብርና ማቀነባበርና የኤክስፖርት አቅም፣ የግብርና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎችንና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማስተዋወቅ ያለመ ነው ተብሏል።
ኤክስፖው ለሦስት ተከታታይ ቀናት በኮንቬንሽን ማዕከል የሚካሄድ ሲሆን፣ የሰብል አምራቾችና ላኪዎች፣ የግብርና ምርት አቀናባሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ገዢዎችና አከፋፋዮች፣ የግብርና ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች፣ የፋይናንስና የልማት ተቋማት እንዲሁም የመንግሥት ባለሥልጣናትና ፖሊሲ አውጪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ኤክስፖው በተለይም የቀጥታ የገበያ ትስስር እንዲፈጠር፣ የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር እንዲጎለብት እና የምርቶች እሴት እንዲጨምር ዕድል ይፈጥራል ተብሏል።
ከጥር 26 እስከ 29 የሚዘጋጀው ኤክስፖው የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለመሳብ፣ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና የገበሬዎችን ገቢ ለማሳደግ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከ150 እስከ 200 የሚደርሱ ሀገር በቀል እና ዓለም አቀፍ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት ኤክስፓው በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች፣ አምራቾች፣ ላኪዎች፣ የፋይናንስና የኢንሹራንስ ተቋማት በኤክስፖው እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።
ሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 1 753 |
| 14 | ለአዲስ ዓመት የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ 1,200 ብር እንዲሆን ከሥጋ ቤቶቹ ጋር ስምምነት መደረጉ ተገለጸ
ለተቃረበው የ2019 አዲስ ዓመት በዓል የሸማቹን እንግልትና ያልተገበበ የዋጋ ጭማሪ ለመግታት ያለመ አዲስ ውሳኔ ተ አስተላለፈ።
የአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በመዲናዋ ከሚገኙ 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች ጋር ባደረገው ዝርዝር ውይይት፣ አንድ ኪሎ የበሬ ሥጋ በ1,200 ብር ብቻ ለሕዝብ እንዲቀርብ መግባባት ላይ መድረሱን አስታውቋል።
የበዓላት ወቅት የመገበያያ ዋጋ ንረትና የአቅርቦት እጥረት የሚፈጥረውን ጫና ለማቃለል ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የገለጸው ኮሚሽኑ፣ ሸማቾች በየአካባቢያቸው በሚገኙ ማኅበራት በኩል ምርቱን በቀላሉ ማግኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል።
በሁሉም 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች አንድ ኪሎ ሥጋ ከ1,200 ብር በላይ እንዳይሸጥ ስምምነት ተደርሷል።
መንግሥት ከአርሶ አደሮችና ከበሬ አቅራቢዎች ጋር ቀጥተኛ የገበያ ትስስር በመፍጠሩ በሥጋ ቤቶች በኩል የነዳጅና የአቅርቦት ምክንያት አቤቱታ እንደማይኖር ተገልጻል።
ከሥጋ በተጨማሪ ሌሎች የበዓል ሸመታዎችን ከእሁድ ገበያዎችና ከኅብረት ሥራ ማኅበራት ሱቆች በቅናሽ ዋጋ መገበያየት እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።
ከተቀመጠው የዋጋ ተመን በላይ በሚሸጡ ሥጋ ቤቶች ላይ ኅብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
| 1 734 |
| 15 | የ14 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ ደፍሮ ቤተክርስቲያ ደጃፍ ጥሏት የሄደው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።
በደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር በመንቆረር ክፍለከተማ ቀበሌ 05 ሰፈር 7 ተከሳሽ ውቤመኮነን የ14 ዓመት ታዳጊን በማታለል ከመኖሪያ ቤቱ ወስዶ አስገድዶ በመድፈር ወንጀል ክስ ተመስርቶበት ምርመራ መጣራቱን ፖሊስ ገልጿል።
የፖሊስ የምርምራ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ ውቤ መኮንን በቀን ነሐሴ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ ቀበሌ 05 ሰፈር 07 ልዩ ቦታው አራግፋ አካባቢ የ14 ዓመት ታዳጊ ህፃን በማታለል ከመኖሪያ ቤቷ ደልሎ በመውሰድ ካሳደራት በኋላ አስገድዶ ደፍሯታል። ከድርጊቱ በኋላም ታዳጊዋን በቤተክርስቲያን አካባቢ ጥሏት የሄደ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ መሰረት በተደረገ ፍለጋ ተጎጅዋ ልትገኝ ችላለች።
ፖሊስ ባደረገው ያልተቆራረጠ ክትትልና የቁስና የሰው ማስረጃዎችን የመሰብሰብ ተግባር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። በተጨማሪም ተጎጂዋ ታዳጊ ወደ ህክምና ተቋም እንድትወሰድ በማድረግ አስፈላጊው ምርመራና ህክምና እንዲደረግላት መደረጉን የ3ኛ ፖሊስጣቢያ የወንጀል ምርምራ ክፍል ሀላፊ ምክትል ኮማንደር መልካም አይቸው ገልጸዋል።
በቀን ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ተከሳሽ ውቤ መኮንን ወንጀሉን ስለመፈጸሙ በሰው እና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጡ በ7 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ መተላለፉን ከከተማው ፖሊስ ማህበራዊ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 650 |
| 16 | ✨ ብዙ ሰዎች እድልን ይጠብቃሉ፤ ጥቂቶች ግን ይሞክራሉ። እርስዎስ ከየትኞቹ ውስጥ ነዎት? ✨
🎉 Bella Bingo የደስታ፣ የመዝናኛ እና የአሸናፊነት ቦታ ነው!
🎁 አስደሳች ቦነሶች
💰 የማሸነፍ እድሎች
⚡ ቀላል እና ፈጣን ተሳትፎ
🎊 በየቀኑ አዲስ ደስታ
🏆 አሸናፊ የመሆን እድል
📍ባሉበት ሁነው በ ስልክዎ የሚዝናኑበት ጨዋታ
🌟 ዕድል ለሚሞክሩት በሩን ትከፍታለች!
🌟 ድል ለሚደፍሩት ትመጣለች!
🔥 ዛሬ ይቀላቀሉ!
🔥 ይጫወቱ!
🔥 ይዝናኑ!
🔥 ዕድልዎን ይሞክሩ
@BellaBingo1bot
ለማንኛውም እገዛ --09 72 75 73 19 ይደውሉ
💙 Bella Bingo – የደስታ፣ የዕድል እና የአሸናፊዎች ምርጫ! | 1 580 |
| 17 | የህወሓት ድሮን ሰልጣኞች‼️
ህወሃት የድሮን ስልጠና የወሰዱ ከ15 በላይ ሰዎችን ወደ ራያ ማሰማራቱ ተሰማ።
ከእነዚህ ሰዎች ውስጥ የተወሰኑት አረብኛ የሚናገሩ ነጮች ናቸው ያሉት ምንጮቹ በራያ አላማጣ እንዲሁም ቅልሻ በሚባል አካባቢ ታይተዋል ብለዋል።
የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሶንጎ ኦባሳንጆ ህወሓት እና የፌደራል መንግስቱን ለማደራደር ጥረት ላይ መሆናቸው ይታወቃል።
Via : አዩዘሀበሻ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 596 |
| 18 | ያለፍላጎታቸው ሴቶችን በወሲብ ንግድ ላይ ያሰማሩት አምስት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡
በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ አስተዳደር በመጠጥ ግሮሰሪ ንግድ ፈቃድ ሽፋን ሴቶችን ያለ ፍላጎታቸው ለወሲብ ንግድ ሲዳርጉና ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩ አምስት ግለሰቦች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና የገንዘብ መቀጮ መቀጣታቸውን የከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል።
የሮቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ጌታቸው ታምሩ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት፣ ተከሳሾቹ በዘይበላ ወላሼ ቀበሌ «ኤል ክላሲኮ» የተባለ የምሽት ጭፈራ ቤት በመክፈት ሴቶችን በአስተናጋጅነት ካስቀጠሩ በኋላ በግዳጅ ለዝሙት አዳሪነት እንዲሰማሩ አድርገዋል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት አንደኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ የንግድ ፈቃዱን በማውጣትና ከሌሎች ተከሳሾች ጋር በመሆን የተቀጠሩ አስተናጋጆችን ያለፍላጎታቸው የግብረ-ሥጋ ድፍረት ጥቃት እንዲፈጸምባቸው ማድረጉ በበቂ ማስረጃ ተረጋግጧል።የቀረበውን የዐቃቤ ሕግ ክስና የፖሊስ ማስረጃ የመረመረው የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፋል።
በዚህም መሰረት 1ኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ ድርጊቱን በዋናነት በመምራትና በግዳጅ የመድፈር ጥቃት በመፈጸሙ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ200 ሺህ ብር መቀጮ፤ 2ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ደሴ በ10 ዓመት እስራት እና በ10 ሺህ ብር መቀጮ፤ 3ኛ ተከሳሽ ወርቁ ደሜ በ6 ዓመት እስራት እና በ45 ሺህ ብር መቀጮ፤ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ተመስገን ፍቃዱ እና ቤክና መሐመድ ደግሞ እያንዳንዳቸው በ1 ዓመት ከ8 ወር እስራትእንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 681 |
| 19 | በቀን በአማካኝ ለ20 ሰዎች የአእምሮ ህክምናን እየሰጠ እንደሚገኝ የወልቂጤ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡
ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ በጀመረበት ወቅት የአእምሮ ህክምናን በተመላላሽ ብቻ ይሰጥ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የቁሳቁስ ግብዓት እና የሰዉ ኃይልን በሟሟላት 34 አልጋዎችን ለታካሚዎች በማመቻቸት ጥራት ያለዉ የህክምና አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልጿል ።
ቀደም ባሉት ጊዜያት ህክምናዉን ፍለጋ ወደ ተለያዩ ሆስፒታሎች በመሄድ ማህበረሰቡ ላልተፈለገ ወጪ እና እንግልት ሲዳረግ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን የአእምሮ ህክምና ክፍሉ ተመራጭ በመሆኑ ራቅ ካሉ አከባቢዎች ጭምር አገልግሎቱን ፈልገዉ የሚመጡ ታካሚዎች መኖራቸው ተጠቁሟል ።
ሆስፒታሉ በቀን በአማካኝ 20 ለሚሆኑ ታካሚዎች የአእምሮ ህክምናን እየሰጠ እንደሚገኝ በሆስፒታሉ የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር ሰዋለም አናጋዉ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።እንደ ዶክተር ሰዋለም ገለፃ ከህፃናት አንስቶ እስከ አዛዉንት ድረስ አገልግሎቱን ፈልገዉ የሚመጡት ታካሚዎች ቢኖሩም አብዛኛዉን ቁጥር የሚይዙት ታካሚዎች ወጣቶች እና ጎልማሳዎች ናቸዉ ።
ይህም ሊሆን የቻለዉ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በመጨመሩ ምክኒያት ነዉ ተብሏል ። ሆስፒታሉ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በተመላላሽ ህክምና 4 ሺህ 600 ለሚሆኑ ታካሚዎች የአእምሮ ህክምና መስጠቱን ስፔሻሊስቱ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 659 |
| 20 | ህወሃት የፌደራል መንግስትን በድሮን ጥቃት ሲከስ የአላማጣ ባለስልጣናት ደግሞ ህወሃትን ወቀሱ
ህወሃት የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃቶችን እየፈጸሙ ነው ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የህወሃት ታጣቂዎች የህዝብ ትምህርት ቤቶችን ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይረዋል የሚሉ የአካባቢው ሪፖርቶች መውጣታቸውን ዶቼ ቬሌ ዘግቧል።
የህወሃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አሰግዶም በድሮን እና በሚግ ተዋጊ አውሮፕላኖች የታገዘው የአየር ጥቃት በአምስት ዞኖች በሚገኙ የህዝብ ተቋማት ላይ ማረፉን የገለጹ ሲሆን፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ደጀን ከተማ የሚገኝ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ መውደሙን፣ እንዲሁም በእንደርታ እና በራያ አዘቦ አርሶ አደሮችና የመኖሪያ መንደሮች መመታታቸውን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ከአላማጣ ከተማ የተገኙ አንድ የቀድሞ የአካባቢው ባለስልጣን ለዶቼ ቬሌ በሰጡት ተቃራኒ መረጃ፣ የህወሃት ኃይሎች አራት የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በአላማጣ የሚገኙ ስምንት ትምህርት ቤቶችን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የማዘጋጃ ቤት ህንፃዎችን በአሁኑ ወቅት ወደ ታጠቁ ወታደራዊ ይዞታነት እና መፈጠሪያነት ቀይረዋቸዋል ሲሉ ከሰዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 675 |
