Fresh መረጃ | FreshNews
前往频道在 Telegram
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
显示更多📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览
频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 56 739 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 023,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 561 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 56 739 名订阅者。
根据 23 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 388,过去 24 小时变化为 -41,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.63%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.52% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 060 次浏览,首日通常累积 1 428 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ።
ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇
@Freshes_newsbot
Fresh News,Fresh Updates.”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
56 739
订阅者
-4124 小时
-3147 天
-1 38830 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+1
在7个频道中
六月 '26
+2
在8个频道中
Get PRO
五月 '260
在8个频道中
Get PRO
四月 '26
+3
在8个频道中
Get PRO
三月 '26
+1 303
在14个频道中
Get PRO
二月 '260
在4个频道中
Get PRO
一月 '260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '250
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+1
在6个频道中
Get PRO
十月 '250
在4个频道中
Get PRO
九月 '250
在3个频道中
Get PRO
八月 '250
在1个频道中
Get PRO
七月 '250
在2个频道中
Get PRO
六月 '250
在6个频道中
Get PRO
五月 '250
在2个频道中
Get PRO
四月 '250
在2个频道中
Get PRO
三月 '250
在10个频道中
Get PRO
二月 '250
在18个频道中
Get PRO
一月 '25
+44
在10个频道中
Get PRO
十二月 '24
+1 502
在16个频道中
Get PRO
十一月 '24
+4 897
在9个频道中
Get PRO
十月 '24
+10 897
在6个频道中
Get PRO
九月 '24
+13 478
在5个频道中
Get PRO
八月 '24
+17 234
在5个频道中
Get PRO
七月 '24
+9 021
在5个频道中
Get PRO
六月 '24
+20
在7个频道中
Get PRO
五月 '24
+351
在14个频道中
Get PRO
四月 '24
+847
在16个频道中
Get PRO
三月 '24
+558
在33个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 785
在15个频道中
Get PRO
一月 '24
+3 011
在18个频道中
Get PRO
十二月 '23
+3 094
在23个频道中
Get PRO
十一月 '23
+730
在120个频道中
Get PRO
十月 '23
+13 017
在37个频道中
Get PRO
九月 '23
+26 548
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+2 062
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+2 838
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+554
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+672
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+1 658
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+3 193
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+1 734
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+895
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+1 925
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+642
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+99
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+547
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+1 026
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+1 241
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+1 528
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+2 018
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+329
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+370
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+390
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+639
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+596
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+736
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+1 209
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+1 351
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+1 280
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+1 459
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 24 七月 | 0 | |||
| 23 七月 | 0 | |||
| 22 七月 | 0 | |||
| 21 七月 | 0 | |||
| 20 七月 | 0 | |||
| 19 七月 | 0 | |||
| 18 七月 | 0 | |||
| 17 七月 | 0 | |||
| 16 七月 | 0 | |||
| 15 七月 | 0 | |||
| 14 七月 | 0 | |||
| 13 七月 | 0 | |||
| 12 七月 | 0 | |||
| 11 七月 | 0 | |||
| 10 七月 | 0 | |||
| 09 七月 | 0 | |||
| 08 七月 | 0 | |||
| 07 七月 | 0 | |||
| 06 七月 | 0 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | 0 | |||
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | +1 | |||
| 01 七月 | 0 |
频道帖子
ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት ስኬቱን በማስመልከት ለደንበኞቹ የነጻ የኢንተርኔት እና የድምጽ አገልግሎቶችን አቅርቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ ያቀረበው አገልግሎት
• 1.5 ጂቢ (GB) የኢንተርኔት ዳታ፣
• 15 ደቂቃ የድምፅ ጥሪ፣ እና
• 30 አጭር የጽሑፍ መልዕክቶች (SMS) ያካተተ ነው።
የቴሌብር ሱፐርአፕ (telebirr SuperApp) ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ተጨማሪ 500 ሜጋ ባይት (MB) ዳታ የተሰጠ ሲሆን፣ ያልተገደበ ጥቅል ተጠቃሚ ለሆኑ ደንበኞች ደግሞ የ10 ደቂቃ ነፃ የዓለም አቀፍ ጥሪ ስጦታ መዘጋጀቱን ገልጿል።
ይህ ነጻ አገልግሎት ከሐምሌ 17 እስከ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ፣ ከለሊቱ 6:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ድረስ የሚያገለግል መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል።
@Addis_News
| 2 | የ4 ዓመት ህጻን ልጅ በማገት 5 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ባልና ሚስት በጽኑ እስራት ተቀጡ
ወንጀሉ የተፈፀመው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ከጠዋቱ 3 ሰአት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቀጠና አራት እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪ መታደል ታደሰ በ4ሺ ብር የወር ደመወዝ በቤት ሰራተኝነት በአቶ መልካሙ ረዳቴ እና በወ/ሮ ጥጋብ ጌታሁን መኖሪያ ቤት ትቀጠራለች።
ግለሰቧ በተቀጠረች በ10ኛ ቀን የቀጣሪዎቿን ወደ ስራ መሄድን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የ4 አመት እድሜ ያለውን ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ችብስ ልግዛልህ በማለት ይዛው ትሰወራለች።የህፃኑ ወላጆች ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ልጃቸውን እና የቀጠሯትን የቤት ሰራተኛ ከቤት ያጧቸዋል።
የቤት ሰራተኛቸው የትዳር አጋር የሆነው ግለሰብ ወደህጻኑ ወላጅ አባት ስልክ በመደወል ልጅህን አግተንዋል 5 ሚሊየን ብር አምጣ ብሎ ስልኩን ይዘጋል ። የልጃቸውን መታገት ተደውሎ የተነገራቸው ወላጅ አባት እና እናትም ለአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ያመለክታሉ።
ፖሊስ የቤት ሠራተኛዋ መታደል ታደሰ ከትዳር አጋሯ መሠረት አየለ ጋር በመሆን ወደ ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሀን ከተማ ጫጫ ክፍለ ከተማ ህፃኑን እንደወሰዱት ይደርስበታል።
ኋላም ተጠርጣሪዎች ቤት ተከራይተው ልጁን ካስቀመጡበት በቁጥጥር ስር በማዋል ታግቶ የነበረው ህፃን ዮሴፍ መልካሙን ከነሙሉ ጤንነቱ ለወላጆቹ አስረክቧል። የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል።
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ ጥፋተኛ ሆነው በማግኘቱ 1ኛ:- ተከሳሽ መታደል ታደሰ በ8አመት ከ4ወር 2ኛ :-ተከሳሽ መሰረት አየለ ደግሞ በ7አመት ከ9ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል ።
@Addis_News | 381 |
| 3 | ኢራን ‘በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ሀብታም ሀገር ልትሆን ትችላለች’ስትል አሜሪካ ተናገረች
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢራን “በአክራሪመሪዎች የምትመራ ሀገር” መሆኗን በመግለጽ፣ እነዚህ መሪዎች ስለ ኢኮኖሚ ጉዳዮች “ምንም ግንዛቤ የሌላቸው” መሆናቸውን ተናግረዋል።“ሀገራቸውን እያወደሙ ነው” ያሉት ሩቢዮ፣ “ኢራን ብትፈልግ ኖሮ በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ሀብታም ሀገር ልትሆን ትችል ነበር” ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
“ነገር ግን በምትኩ ገንዘባቸውን ወስደው ለሂዝቦላህ፣ ለሃማስ እና ለሁቲዎች ይሰጡታል። ለሺዓ ታጣቂ ቡድኖች እንዲሁም በመላው ዓለም ሽብርተኝነት ለመደገፍ ያውሉታል።” ሲሉ አክለዋል፡፡ሩቢዮ ንግግራቸውን ሲቀጥሉ፣ የአሜሪካ ዋና ትኩረት “ከኑክሌር ነጻ የሆነች ኢራን” መሆኗን አስረድተዋል።
“የኑክሌር ጦር መሳሪያ ሊኖራቸው አይገባም፤ እስቲ ለዓለም ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አስቡት።” ሲሉም ስጋትነቱን ጠቅሰዋል፡፡የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቅርቡ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር ስለታወጀው የኒውክሌር ስምምነት መግለጫ ሰጥተዋል።ዋሽንግተን እና ሪያድ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር በሚያደርጉት ጥረት መካከል፣ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ በሲቪል የኑክሌር ትብብር ላይ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡
የአሜሪካ የኢነርጂ መምሪያ፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች ለሳውዲ አረቢያ የኑክሌር ቴክኖሎጂ እንደሚያቀርቡ በመግለጽ ስምምነቱን ታሪካዊ ሲል አወድሶታል።
በስምዖን ደረጄ
@Ethionews433 @Ethionews433 | 611 |
| 4 | ጄነራል ታደሰ ወረደ ወዴት ተሰወሩ?
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ በመቀሌ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መሰወራቸው ተሰማ። እስከ ማክሰኞ ጠዋት ድረስ መኖሪያ ቤታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚጠበቅና በጥበቃ ተሽከርካሪዎች የተከበበ የነበረ ቢሆንም፣ ከማክሰኞ ምሽት ጀምሮ ግን አብረዋቸው የነበሩ ጥበቃዎችና ሰራተኞች ከአካባቢው ሙሉ በሙሉ ጠፍተዋል።
ጄነራሉ ከጥቂት ቀናት በፊት ከአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር እንዳይገናኙ በትግራይ ጸጥታ ቢሮ ተከልክለው እንደነበርና ቤተሰቦቻቸውም ስለ ደህንነታቸው ስጋት አድሮባቸው እንደነበር ይታወቃል።
ጄነራል ታደሰ ወረደ በፌደራል መንግሥት ዳግም በተሾሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ በሕወሓት ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የሚታወስ ነው። ከኃላፊነታቸው ከመነሳታቸው በፊትም ጊዜያዊ አስተዳደሩን በኃይል ለመገልበጥ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ክልሉን ወደ አዲስ ጦርነት እንደሚያስገባ አስጠንቅቀው ነበር።
በአሁኑ ወቅት በሕወሓት እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው የፖለቲካ ውጥረት በጨመረበት ሁኔታ፣ የጄነራሉ ከአካባቢው መሰወር በትግራይ ክልል አዲስ የጸጥታ ስጋት ደቅኗል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 267 |
| 5 | በሩሲያ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ የመጸዳጃ ቤት ዉሃ የመጠጣት ውድድር ማዘጋጀቱ ዉዝግብ አስነሳ
በሩሲያ ስታቭሮፖል የሚገኝ አንድ የቧንቧ ሥራ ኩባንያ፣ በቅርቡ "Game of Thrones" በሚል ያልተለመደ ውድድር ምክንያት በኢንተርኔት ላይ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በዚህ ውድድር ላይ ተሳታፊዎች አዲስ ከሆኑ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫዎች ውስጥ፣ ትላልቅ የመምጠጫ ቱቦዎችን በመጠቀም "አልኮል ያልያዘ ጋዝ ያለው መጠጥ" እንዲጠጡ ይጠበቅባቸው ነበር፤ መጠጡን በፍጥነት የጨረሰውም አሸናፊ ተብሎ ተለይቷል።
በስታቭሮፖል ከተማ በሚገኝ የ"ዶሚክስ" መደብር ውስጥ የተካሄደው ይህ ያልተለመደ ውድድር፣ በርካታ ተሳታፊዎች የ100,000 ሩብል (1,276 የአሜሪካ ዶላር) ሽልማት ለማግኘት ሲሉ ከመጸዳጃ ቤት ጎድጓዳ ሳህን ውስጥ በፍጥነት እንዲጠጡ የሚያስገድድ ነበር። ተወዳዳሪዎቹ በሰባት ሰዎች ቡድን የተከፋፈሉ ሲሆን፣ ፈጣኑ ጠጪ ወደ ሁለተኛው ዙር ያልፍ ነበር።
በውድድሩ ሁለተኛ ምዕራፍ፣ ከቀዳሚው ዙር ያለፉት ሰባቱ አሸናፊዎች በተዘጋ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ላይ በተቻለ መጠን ረጅም ጊዜ መቀመጥ ነበረባቸው፤ በመጨረሻም መቀመጥ የቻለው ሰው የዚህ ያልተለመደ ዉድድር አሸናፊ ተብሎ ታዉጇል።
በቤዛዊት አራጌ
@Addis_News
@Addis_News | 1 321 |
| 6 | በጅጅጋ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ
በጅጅጋ ከተማ በካራማራ ክፍለ-ከተማ ልዩ ስሙ 10ኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሀምሌ 15 ቀን ማምሻውን በተከተሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
አደጋውን ያደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-85725 ኢቲ የሆነ ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ሲሆን በአደጋው ህይወታቸው ካለፉ 7 ሰዎች መካከል 5 ወንዶች ሲሆኑ 2ቱ ደግሞ ሴቶች ናቸው።
አደጋው እንደደረሰ የአምቡላንስ ድንገተኛ አደጋ ደራሽ ሰራተኞች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የቪአይፒ ፀጥታ አካላት በፍጥነት በስፍራው በመገኘት ጉዳት የደረሰበትን ህጻን ወደ ህክምና ተቋም ያጓጓዙ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል።
ፖሊስ የአደጋውን ዝርዝር ምርመራ ውጤት በቀጣይ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ መገለፁን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።
#ዳጉ_ጆርናል | 1 304 |
| 7 | 120 ስልክ ሿሿ ያደረገው ግለሰብ….
በኡጋንዳ በቀን 120 ስልኮችን የሰረቀው ግለሰብ ከስልኮቹ ጋር የተያዘ ሲሆን፣ «ስልኮቻችሁ የተሰረቁባችሁ ሰዎች ወደ ኡጋንዳ ፖሊስ ጣቢያ እየመጣችሁ ተቀበሉ» ተብሏል።
የሚገርመው ነገር፣ ስልኮቹ የስክሪን ምስላቸው (Screen saver) እንኳን ሳይቀየር እንደነበረው ነው ያሉት።
ያ ማለት የተሰረቀባቸው ሰዎች በስክሪናቸው ላይ ያደረጉት ምስል የራሳቸው ከሆነ በቀላሉ ስልካቸውን ማግኘት ይችላሉ ማለት ነው።
ስለዚህ ለክፉም ለደጉም የስልካችሁን Screen Saver የራሳችሁን አድርጉት።
ህዝቡም ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየተመመ ነው።
Via Uganda Police
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 433 |
| 8 | የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ያለመ ስብሰባ በኤርትራ ድንበር ተደረገ፣ስብሰባውን የመሩት አቶ አማኑኤል አሰፋ ናቸው።
ሕወሓት የብልጽግናን መንግስት አስወግዳለሁ እያለ ነው፡፡ ቡድኑ ካለፈው እሁድ አንስቶ 'ህልውናችን የሚረጋገጠው በብልጽግና መቃብር ላይ ነው' በሚል መሪቃል ስብሰባዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በእነዚህ ስብሰባዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ የሕወሓት አመራሮች ‹‹ብልጽግናን ከስልጣን ማስወገድ አለብን›› በማለት በግላጭ እየተናገሩ ነው፡፡
በሚዲያዎቻቸውም የፌደራል መንግስቱን 'ጄንኖሳይዳዊ አገዛዝ' የሚል ስያሜ ሰጥተው በትግራይ ቴሌቪዥን ጭምር ዜና መስራት ጀምረዋል። የፌደራል መንግሥቱ ለህወሓት የጦርነት ጉሰማ በቀጥታ የሰጠው ምላሽ የለም።
@Yenetube @Fikerassefa | 1 352 |
| 9 | ለምክክር ጉባዔ መጥታ ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት የልጇን ሥም "ኮሚሽን" አለችዉ
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወክላ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
ባሳለፍነው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ የነበረች የጋምቤላ ክልል ተወካይዋ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላ ስሙም "ምክክር" መባሉ የሚታወስ ነው።
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ የመጣችው ሌላኛዋ የምክክሩ ተሳታፊ ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ በተመሳሳይ ወንድ ልጅ በሰላም የተገላገለች ሲሆን፥ ስሙንም "ኮሚሽን" ብላዋለች።
የመውለጃ ጊዜዬ እየደረሰ መሆኑን ባውቅም ለኢትዮጵያዊያን አብሮነትና ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ በሚመከርበት በዚህ ጉባኤ መሳተፍ አለብኝ በሚል አቋም ተገኝቻለሁ ብላለች፡፡
በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገራችን ይበጃል የምትለውን ሀሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ የቆየች ሲሆን፥ በዚህ ታሪካዊ ወቅት ልጇን በመገላገሏ መደሰቷን ገልጻለች።
ዘገባዉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሚዲያ ነዉ።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 408 |
| 10 | በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ
በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የከተማው የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽ/ቤት አስታውቋል።እርምጃው በአብዛኛው በሱቆችና በንግድ ተቋማት ላይ የተወሰደ ሲሆን ከየካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ክትትል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ለማ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በመተላለፍ ፌስታል በመያዝ እና ለንግድ አገልግሎት ጥቅም ላይ ሲያውሉ በተገኙ 130 አካላት ላይ በህጉ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በቅርቡ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል አንድ ነጋዴ 17 ኩንታል ማዳበሪያ ይዞ በመገኘቱ የተወረሰበት ሲሆን በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ጨምር እንዲቀጣ ተደርጓል።
በመሆኑም ግለሰቦችና ተቋማት ፌስታል መጠቀም በህግ የተከለከለ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ህጉን ሊያከብሩ ይገባል ሲሉ አቶ ጴጥሮስ ለማ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በአዋጁ መሰረት ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ በ2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።እንዲሁም በተቋም ደረጃ ፌስታል ያከማቸ፣ የሸጠ ወይም ለንግድ ዓላማ እንደ እቃ መያዣ ያቀረበ ተቋም እስከ 200 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ባለንብረቶችም እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ ተጠቅሷል ።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 503 |
| 11 | ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊዮን በላይ መድረሱን አስታወቀ
ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለጋዜጠኞች በሰጠዉ መግለጫ አቅርቧል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት የሞባይል ጣቢያዎች ከ10 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
በበጀት ዓመቱ የ4ጂ ኔትወርክ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲሆን በዚህም 264 ከተሞችን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል። በተጨማሪም ሰባት ከተሞች በአምስተኛ ትዉልድ (5ጂ) ኔትወርክ ተጠቃሚ መሆን የቻሉ ሲሆን በአጠቃላይ በአሁን ሰዓት 33 ከተሞች የ5ጂ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፤ ይህ ደግሞ 10.2ሚሊዮን ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 90 .1 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል። ይህም የእቅዱን 101.7 በመቶኛ ማሳካት ያስቻለ ነው ተብሏል ። ከዚህም ውስጥ የድምጽ ተጠቃሚዎች 86.9 ሚሊዮን ፣ ብሮድባንድ 51.5 ሚሊዮን ፣ ፊክስድ ብሮድባንድ 1 ሚሊዮን ያካተተ ነው ። የፊክስድ ብሮድባንድ ተጠቃሚዎችን 1 ሚሊዮን ማድረስ በእቅድ ደረጃ የተያዘ መሆኑን ስራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።
ተቋሙ 470 የሚሆኑ ምርት እና አገልግሎቶችን ያቀረበ ሲሆን 193 የሚሆኑት አዳዲስ ናቸው። በዚህ ዓመት ደንበኞች እንዴት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን መጠቀም አለባቸው የሚለውን ትኩረት በማድረግ ደንበኞችን ከስተመር ኢዱኬሽን በሚል አገልግሎት የመስጠት ስራ እየጠተገበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል | 1 375 |
| 12 | አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇
ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️
ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው።
ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል።
ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም።
አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም።
አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 1 363 |
| 13 | የዝናብ ሁኔታ‼️
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 562 |
| 14 | እስራኤል የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አወደሰች
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ አድናቆታቸውን ለግሰዋል።
ይህ የእስራኤል ድጋፍ የመጣው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያ ግድቡን በብቸኝነት እያንቀሳቀሰች ነው ሲሉ ከከሰሱ በኋላ ሲሆን፣ አምባሳደሩ በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በእርሻ፣ በጠብታ መስኖና በዓሣ ሀብት ልማት ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በካይሮና በአዲስ አበባ መካከል ያለው የቃላት ልውውጥ እና ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት እየጨመረ መጥቷል። ግብፅና ሱዳን ያለ ህጋዊ ስምምነት ግድቡን መሙላትና ማካሄድ የውሃ ደህንነታችንን ይጎዳል ሲሉ ሲቃወሙ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ የ4 ቢሊዮን ዶላሩ ግድብ በታችኞቹ ሀገራት ላይ ምንም ዓይነት ጎጂ ተጽዕኖ እንደማያደርስና ለሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት ወሳኝ መሆኑን አጥብቃ ትገልጻለች።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 596 |
| 15 | ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ወደ ገበያው ለማስገባት አቅዷል።
ማዕከላዊ ባንኩ በነሐሴ እና መስከረም ወራት አራት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ገልጿል።
በእያንዳንዱ ጨረታም 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች እንደሚቀርብ አስታውቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 571 |
| 16 | የድሮን ጥቃት‼️
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 041 |
| 17 | የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ጀምሮ ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታወ
👉 ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል
የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ፣ የጤና ምክር እና የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎች አገልግሎቱን ያገኛሉ።
አገልግሎቱ ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የሚሰጥ መሆኑን በመግለፅ በስፔሻሊስት እና በሰብስፔሻሊስት ሀኪሞች ይከናወናል።የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ የጤና ምርመራን ማበረታታት ነው የተባለ ሲሆን በተለይም አቅም ለሌላቸው ዜጎች የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በነፃ ከሚሰጡት አገልግሎቶች ውስጥ የውስጥ ደዌ፣ የማህፀንና ፅንስ ሕክምና፣ የመለስተኛ ቀዶ ህክምና፣ የጥርስ ፣ የሥነ አዕምሮ ሕክምና፣ የልብ ምርመራ እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በየቀኑ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ በቁስቋም በሚገኘው የመኪና ማቆሚያ ስፍራ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የጤና ምርመራ ወይም ሕክምና የሚፈልጉ ዜጎች በተጠቀሰው ቦታ በመገኘት አገልግሎቱን መጠቀም እንደሚችሉ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 1 704 |
| 18 | በትግራይ ብርቱ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ፡፡
በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው ተገልጿል።
በአንድ በኩል በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ በአዝርእትና በመስኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል።
በሌላ በኩል ደግሞ 176 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳላገኙ ተገልጿል።
በማዕከላዊ ዞን ወረዳ ቀይሕ ተኽሊ ዶክተር አታኽልቲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ ለሁለት ሰዓታት ያለማቋረጥ የዘነበው በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ከመቅጠፉ በተጨማሪ በአዝርእትና በመስኖ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
በተመሳሳይ በዞኑ ወረዳ አሕፈሮም ሴሮ ቀበሌ የዘነበው ብርቱ ዝናብም በአዝርእትና በአትክልት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።
በሌላ በኩል የትግራይ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ ትላንት ባወጣው መረጃ፤ በክልሉ ከሚገኙ 600 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት መካከል 176 በሚሆኑት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ አስታውቋል።
ይህ ሁኔታ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፤ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ እጥረት በእርሻ ሥራና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ያሳያል።
@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH | 1 559 |
| 19 | ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እና የፈቃድ ውል ስምምነቱን አልጠበቀም ሲል አስታውቋል።
ጣቢያው 60% የሚሆነውን ስርጭት ለፈቃድ አካባቢው የማዋል፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን የማቅረብ፣ እንዲሁም ሀገራዊ እና ህገ-መንግስታዊ እሴቶችን የማጠናከር ግዴታዎቹን አልተወጣም ተብሏል።
ባለሥልጣኑ በተደጋጋሚ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም መሻሻል ባለመታየቱ እርምጃው ሊወሰድበት ችሏል።
በዚህም መሠረት የሬዲዮ ጣቢያው ከተሰጡት ማስጠንቀቂያዎች በኋላ አስፈላጊዎቹን ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ አሟልቶ እስኪገኝ ድረስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ በሙሉ ታግዷል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡
@Addis_News | 1 578 |
| 20 | በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ ከ140 በላይ ስደተኞች ሕይወታቸው ማለፉ ተነገረ
ወደ አውሮፓ ለማቅናት ከአፍሪካ የተነሱ ከ140 በላይ ስደተኞች በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ መሞታቸው ወይም የደረሱበት መጥፋቱ ተነግሯል።
160 ሰዎችን አሳፍራ ከጋምቢያ የተነሳችው ጀልባ ነዳጅ በመጨረሷ ምክንያት ለ25 ቀናት በባሕር ላይ ስትንሳፈፍ መቆየቷን የሞሪታኒያ የባሕር ጠረፍ ጥበቃ ገልጿል።
የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) እንዳስታወቀው ከሐምሌ 14 እስከ 18 በተደረጉ የነፍስ አድን ዘመቻዎች ቢያንስ 143 ሰዎች የሞቱ ወይም የጠፉ ሲሆን በሕይወት ከተረፉት መካከል ሙሉ ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ሁለት ሕፃናት በሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ተመላክቷል።
ኤጀንሲው ከሞሪታኒያ ተነስቶ ወደ ስፔን ካናሪ ደሴቶች የሚወስደውን የአትላንቲክ መስመር "በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አደገኛ የፍልሰት መንገዶች አንዱ" ሲል የገለጸው ሲሆን ከመጠን በላይ መጫን እና ለባሕር ጉዞ የማይመቹ ጀልባዎችን መጠቀም ለአደጋው መበራከት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ጠቁሟል።
@Freshmerejaet
@Freshmerejaet | 1 645 |
