ch
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

前往频道在 Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

显示更多

📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览

频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 56 906 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 006,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 556

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 56 906 名订阅者。

根据 19 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 412,过去 24 小时变化为 -60,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.77%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.61% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 145 次浏览,首日通常累积 1 484 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

凭借高频更新(最新数据采集于 20 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

56 906
订阅者
-6024 小时
-3067
-1 41230

数据加载中...

吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+1
在7个频道中
六月 '26
+2
在8个频道中
Get PRO
五月 '260
在8个频道中
Get PRO
四月 '26
+3
在8个频道中
Get PRO
三月 '26
+1 303
在14个频道中
Get PRO
二月 '260
在4个频道中
Get PRO
一月 '260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '250
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+1
在6个频道中
Get PRO
十月 '250
在4个频道中
Get PRO
九月 '250
在3个频道中
Get PRO
八月 '250
在1个频道中
Get PRO
七月 '250
在2个频道中
Get PRO
六月 '250
在6个频道中
Get PRO
五月 '250
在2个频道中
Get PRO
四月 '250
在2个频道中
Get PRO
三月 '250
在10个频道中
Get PRO
二月 '250
在18个频道中
Get PRO
一月 '25
+44
在10个频道中
Get PRO
十二月 '24
+1 502
在16个频道中
Get PRO
十一月 '24
+4 897
在9个频道中
Get PRO
十月 '24
+10 897
在6个频道中
Get PRO
九月 '24
+13 478
在5个频道中
Get PRO
八月 '24
+17 234
在5个频道中
Get PRO
七月 '24
+9 021
在5个频道中
Get PRO
六月 '24
+20
在7个频道中
Get PRO
五月 '24
+351
在14个频道中
Get PRO
四月 '24
+847
在16个频道中
Get PRO
三月 '24
+558
在33个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 785
在15个频道中
Get PRO
一月 '24
+3 011
在18个频道中
Get PRO
十二月 '23
+3 094
在23个频道中
Get PRO
十一月 '23
+730
在120个频道中
Get PRO
十月 '23
+13 017
在37个频道中
Get PRO
九月 '23
+26 548
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+2 062
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+2 838
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+554
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+672
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+1 658
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+3 193
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+1 734
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+895
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+1 925
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+642
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+99
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+547
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+1 026
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+1 241
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+1 528
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+2 018
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+329
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+370
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+390
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+639
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+596
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+736
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+1 209
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+1 351
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+1 280
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+1 459
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
20 七月0
19 七月0
18 七月0
17 七月0
16 七月0
15 七月0
14 七月0
13 七月0
12 七月0
11 七月0
10 七月0
09 七月0
08 七月0
07 七月0
06 七月0
05 七月0
04 七月0
03 七月0
02 七月+1
01 七月0
频道帖子
በኢትዮጵያ መካንነት ከፍተኛ የጤና ችግር እየሆነ መምጣቱ ተነገረ የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመ
በኢትዮጵያ መካንነት ከፍተኛ የጤና ችግር እየሆነ መምጣቱ ተነገረ   የመካንነት ችግር በሴቶች ፣በወንዶች እንዲሁም በሁለቱም አጋሮች በጋራ ሊከሰት እንደሚችል የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።በኢትዮጵያ የመካንነት ችግር ከሚጠበቀው በላይ ከፍተኛ መሆኑን በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት እንዲሁም የመካንነት ሰብ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶክተር በላይ ቤተማሪያም ከብስራት ሬድዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።   ከጥንዶች መካከል ከ20 እስከ 25 በመቶ የሚሆኑት በዚህ ችግር እንደሚጠቁ ተናግረዋል።በኢንፌክሽን ምክኒያት የሚከሰት የማህፀን ቱቦ መዘጋት በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር 35 በመቶ ድርሻ እንዳለዉ ሰብ ስፔሻሊስቱ አስገንዝበዋል ።በባክቴሪያ ፣በፈንገስ እና በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት የሴቶች የመራቢያ አካል ወይም የማህፀን ኢንፌክሽን ህክምና ካላገኘ እና በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ መካንነትን ሊያስከትል ይችላል።   እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ 20 በመቶ የሚሆነው በወንድ በኩል የሚኖር መካንነት ነው።በጭንቅላት ውስጥ የሚመረት ሆርሞን ማነስ ፣በዘር ፍሬ ላይ የሚያጋጥም ስፐርም የማምረት ችግር ፣የወንድ የዘር ቱቦ መዘጋት እንዲሁም ምክንያቱ የማይታወቅ የወንድ መካንነት ዋና ዋናዎቹ መንስኤዎች ናቸው ።   የእንቁላል መፈጠር ወይም መለቀቅ ችግር ፤ በሆርሞን መዛባት  ወይም በእድሜ ምክኒያት እንቁላል በወር አበባ ዑደት ውስጥ አዘውትሮ አለመፈጠር በሴቶች ላይ ለሚከሰት የመካንነት ችግር ዋነኛቹ ምክኒያቶች መሆናቸውን ዶክተር በላይ አስረድተዋል።   @Addis_News @Addis_News

2
‹‹በኤሌክትሪክ ክፍያ ላይ የታየው ለውጥ አዲስ ጭማሪ ሳይሆን ቀድሞ የተወሰነ ማስተካከያ ሂደት ነው››-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ በደንበኞች ላይ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ ክፍያ ቀደም ሲል በስትራቴጂው መሠረት የተወሰነ መሆኑን አስታዉቋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ይኸይስ ስዩም ለኢትዮ ኤፍኤም 107.8 እንደገለጹት፤ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር ላይ የተጀመረው የታሪፍ ማሻሻያ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ በ24 የሩብ ዓመታት ተከፋፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። ይህ የታሪፍ ማስተካከያ ተቋሙ ከአራት ዓመት በኋላ የሚሰበሰበውን አጠቃላይ ክፍያ በመስከረም 2017 ዓ.ም ላይ በአንድ ጊዜ ማስከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የመክፈል አቅም ታሳቢ በማድረግ በጥቂት በጥቂቱ ከፋፍሎ እንዲከፍል የተዘረጋ ስትራቴጂ ነው በማለት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ ያለው ታሪፍ ዝቅተኛውን የኅብረተሰብ ክፍል በልዩ ሁኔታ ለመደገፍ  የመንግሥት ድጎማ የሚደረግበት ነው ያሉ ሲሆን፣ እስከ 50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት 96 ሳንቲም ብቻ እንዲከፍሉ እየተደረገ እንደሆነ ገልጸዋል። ዶ/ር ይኸይስ አክለውም፤ እስከ 2መቶ ኪሎ ዋት የሚጠቀም ማንኛውም ደንበኛ በትክክለኛው የታሪፍ ዋጋ ሳይሆን በድጎማ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ብለዋል። ደንበኞች በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ ኃይል ሲገዙ ስለሚገጥማቸው የዋጋ ልዩነት ሲያብራሩም፤ የዋጋ አተማመን ሥርዓቱ በ30 ቀናት ውስጥ የተጠቀሙትን አጠቃላይ የኃይል መጠን በአንድ ላይ ደምሮ ስለሚያሰላው የኪሎ ዋት መጠኑ ሲጨምር ታሪፉም አብሮ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል። ይህንን ሁኔታ ተከትሎ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት ተቋሙ በየክፍለ ከተማው ከነዋሪዎች ጋር ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለፉት 15 ቀናት ውስጥም ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሚዲያ አካላት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል። ኢትዮ ኤፍ ኤም @Freshmerejaet @Freshmerejaet
461
3
አንድ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመመስረት ስምምነት ተፈራረመ ​የቻይናው ሑይቹዋን ዮንግዩ ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ሰርቪስ (Huichuan Yongyu Supply C
አንድ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመመስረት ስምምነት ተፈራረመ ​የቻይናው ሑይቹዋን ዮንግዩ ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ሰርቪስ (Huichuan Yongyu Supply Chain Management Service Co., Ltd.) በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመመስረት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን ኮሚሽኑ አስታወቀ። ​ስምምነቱ የተፈረመው የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነሮች ዳጋቶ ኩምቤ እና ዚናቡ ይርጋ ከቻይናው ኩባንያ ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር በኢትዮጵያ የቡና ማቀነባበር ዘርፍ ባሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ከተወያዩ በኋላ ነው። ​እንደ ኮሚሽኑ ገለጻ፣ አቶ ዳጋቶ የቡና መገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ በ2018 የኢትዮጵያ በጀት ዓመት ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳን ገልጸው፤ ነገር ግን የአገሪቱ የወጪ ንግድ አብዛኛው አሁንም እሴት ሳይጨመርበት በጥሬው የሚላክ መሆኑን ጠቁመዋል። ​ኩባንያው ለቡና ብቻ በተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ፓርክ ላይ ለመሰማራት ያቀደው ኢንቨስትመንት፣ ኢትዮጵያ እሴት የተጨመረባቸው የቡና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ስትራቴጂዋን ለመደገፍ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።​ኮሚሽኑ እንዳለው፣ አቶ ዚናቡ ፕሮጀክቱን ወደ ሥራ ለማስገባት እንዲረዳ ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እና የኢንቨስትመንት ማመቻቸት እንደሚያደርግ ለኩባንያው ልዑክ አረጋግጠውላቸዋል። መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! ---ETHIO-MEREJA--    T.me/ethio_mereja
723
4
የህንድ ዋና ከተማ ዴሊ የትምህርት ሚኒስትሩ ስልጣን እንዲለቁ በሚጠይቁ ሰልፈኞች ተጥለቅልቃለች በሺዎች የሚቆጠሩ ህንዳውያን ሰልፈኞች የፖሊስን እገዳ በመጣስ የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስትር ከስልጣናቸው+2
የህንድ ዋና ከተማ ዴሊ የትምህርት ሚኒስትሩ ስልጣን እንዲለቁ በሚጠይቁ ሰልፈኞች ተጥለቅልቃለች በሺዎች የሚቆጠሩ ህንዳውያን ሰልፈኞች የፖሊስን እገዳ በመጣስ የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስትር ከስልጣናቸው እንዲወርዱ በመጠየቅ በዋና ከተማዋ ዴሊ ግዙፍ ተቃውሞ እያካሄዱ እንደሚገኙ ዘ ጋርድያን ዘግቧል። የሰልፉ ዋና ጥያቄ የህክምና ትምህርት መግቢያ ፈተና ተሰርቆ መሸጡን እና ፈተናው ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ መደረጉን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስትሩ ዳርሜንድራ ፕራዳን ከስልጣን እንዲለቁ ነው። ከ2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ለ130,000 ቦታዎች የሚፎካከሩበት ይህ ፈተና መሰረዙ ከፍተኛ ቀውስ የፈጠረ ሲሆን፣ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ከ20 በላይ ተማሪዎች ህይወታቸውን ማጥፋታቸው ተነግሯል። ይህ ሰልፍ ህንድ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ካየቻቸው ትልልቅ መንግስታዊ ተቃውሞዎች አንዱ እንደሆነ ተገልጻል። በአብዛኛው በተማሪዎች እና በወጣቶች የተሞላው ሰልፉ ከሰኞ ማለዳ ጀምሮ በዴሊ እምብርት በሚገኙ ጎዳናዎች ላይ በመሰብሰብ መንግስትን የሚቃወሙ መፈክሮችን ያሰማ ነበር። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
940
5
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ተለቋል። ተማሪዎች ቀጥሎ ባለው ሊንክ መለያ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ 👇 http
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ተለቋል።   ተማሪዎች ቀጥሎ ባለው ሊንክ መለያ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ 👇 http://ce.ministry.et   @Seledadotio @Seledadotio
1 099
6
ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ ከፍተኛ የባለስቲክ ሚሳይል ጥቃት ፈፀመች ሩሲያ በዩክሬን ላይ ተከታታይ የባለስቲክ ሚሳይል እና የድሮን ጥቃቶችን የፈፀመች ሲሆን፣ በዚህም ቢያንስ ስምንት ሰዎች መሞታቸውን
ሩሲያ በዩክሬን ከተሞች ላይ ከፍተኛ የባለስቲክ ሚሳይል ጥቃት ፈፀመች ሩሲያ በዩክሬን ላይ ተከታታይ የባለስቲክ ሚሳይል እና የድሮን ጥቃቶችን የፈፀመች ሲሆን፣ በዚህም ቢያንስ ስምንት ሰዎች መሞታቸውንና በደርዘን የሚቆጠሩ መቁሰላቸውን ባለስልጣናት ገልፀዋል። በሰሜን ምስራቋ ከተማ ካርኪቭ አራት ሰዎች ሲገደሉ፣ በዋና ከተማዋ ኪየቭ ደግሞ አንዲት አረጋዊት ሴት ህይወታቸው አልፏል። በተጨማሪም በደቡባዊቷ ዛፖሪዝሂያ ሁለት ሰዎች፣ እንዲሁም በሰሜን ምስራቋ ሱሚ አንድ ሰው ህይወታቸውን አጥተዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ፣ በኪዬቭ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ሩሲያ እ.ኤ.አ. በ2022 ሙሉ ወረራ ከጀመረች ወዲህ ከተፈጸሙት "እጅግ ከፍተኛ ከሆኑ የባለስቲክ ሚሳይል ጥቃቶች አንዱ" እንደሆነ ተናግረዋል። እሁድ ከሰዓት በተፈፀመ ሌላ የሩሲያ ጥቃት በቱርክ ባለቤትነት ስር ያለ እና እህል የጫነ የሲቪል የጭነት መርከብ በጥቁር ባህር ውስጥ በሩሲያ ሚሳይሎች ተመትቶ አምስት ሰዎች መሞታቸውን የዩክሬን የባህር ኃይል አስታውቋል። ሩሲያ ተፈፀመ በተባለው ጥቃት ዙሪያ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት አስተያየት አልሰጠችም። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
1 146
7
5ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ከሐምሌ 09/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተሰጠውን 5ኛው ዙር ፈተና፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላ
5ኛው ዙር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ከሐምሌ 09/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተሰጠውን 5ኛው ዙር ፈተና፤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይን (CBT) ወስደዋል፡፡ በዛሬው የመጨረሻ ቀን ፈተና በጠዋቱ ክፍለጊዜ የታሪክ ትምህርት ፈተና እየተሰጠ ሲሆን፤ ከሰዓት የኢኮኖሚክስ ትምህርት ፈተና ይሰጣል፡፡ የመጨረሻው 6ኛ ዙር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መልቀቂያ ፈተና ከነገ ሐምሌ 14/2018 ዓም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡  ምስል፦ ቦረና ዩኒቨርሲቲ @Yenetube @Fikerassefa
1 252
8
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያ+1
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል። ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል። ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል። ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል። @Seledadotio @Seledadotio
1 238
9
#Update በሶማሊ ክልል በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ 12 ሰዎችን ለመቅበር የሄዱ ሶስት ሰዎች በአፈር መደርመስ ህይወታቸው አለፈ በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን ቀብሪበያህ ወረዳ ጉዮው ቀበሌ በተከሰ+2
#Update በሶማሊ ክልል በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ 12 ሰዎችን ለመቅበር የሄዱ ሶስት ሰዎች በአፈር መደርመስ ህይወታቸው አለፈ በሶማሊ ክልል ፋፈን ዞን ቀብሪበያህ ወረዳ ጉዮው ቀበሌ በተከሰተ ከባድ የመኪና አደጋ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ይታወሳል። አደጋው ሊከሰት የቻለው እሁድ ረፋድ ሶስት ሰዓት ላይ አንድ የአይሱዚ መኪና «ፎርስ» ተብሎ ከሚጠራ ሌላ ተሽከርካሪ ጋር በድንገት በመጋጨቱ ሲሆን በዚሁ አሳዛኝ አጋጣሚ የ12 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል። በተጨማሪም በአደጋው ሦስት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።የደረሰውን የትራፊክ አደጋ ተከትሎ በቀብር ላይ በነበሩ ወገኖች ላይ የመቃብር ቦታ አፈር ተደርምሶ ተጨማሪ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ  ከ10 በላይ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ገልጿል ። ቢሮዉ ባወጣዉ መግለጫ ህይወታቸውን ያጡትን ወገኖች ለመቅበር እየተደረገ በነበረ የቀብር ሥነ ሥርዓት ደግሞ ሌላ አሳዛኝ ክስተት ማጋጠሙን ገልጿል ። የቀብር ስነስርአት በመፈፀም በነበሩ ሀዘንተኞች ላይ የመቃብር ቦታ በመደርመሱ ህይወታቸውን ካጡት 3 ሰዎች በተጨማሪ ከ10 በላይ ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
1 122
10
ኢራን በኢራቅ ውስጥ በፈጸመችው ጥቃት አንድ የአሜሪካ ወታደር ሲገደል ሌላ አንድ ወታደር ቆሰለ 👉 ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል በዮርዳኖስ በሚገኝ አንድ ወታደራዊ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት
ኢራን በኢራቅ ውስጥ በፈጸመችው ጥቃት አንድ የአሜሪካ ወታደር ሲገደል ሌላ አንድ ወታደር ቆሰለ 👉 ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል በዮርዳኖስ በሚገኝ አንድ ወታደራዊ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውን እና አንዱ መጥፋቱን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት ቢፈጠርም ቅዳሜ ዕለትም በቀጠለው የኢራን ጥቃት በሰሜናዊ ኢራቅ አንድ የአሜሪካ ወታደር መገደሉን የአሜሪካ ጦር አስታውቋል። የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ (ሴንትኮም) ወታደሩ የተገደለው "ያልፈነዳ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት" ሲሆን ሌላ የጦር ሰራዊት አባል ቆስሏል ብሏል። አሜሪካ እና ኢራን ለስምንተኛ ቀን የተኩስ ልውውጥ ውስጥ ይገኛሉ። ሁለቱም ወገኖች በቅርብ ቀናት ውስጥ ወሳኝ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን በመምታት እርስ በእርስ እየተካሰሱ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዋሽንግተን የኢራንን ወደቦች መዝጋትን እንደገና አጽድቃለች፤ቴህራን የሆርሙዝ ወሽመጥ ተዘግቶ በክልሉ ውስጥ ያሉትን የአሜሪካ አጋሮችን ኢላማ አድርጋለች። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
1 177
11
ስፔን አርጀንቲናን በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች *** የ2026 ዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ሲያገኘ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። 120 ደቂቃ በወሰደው ፍጻሜ ተቀይሮ የገባው ፌራ
ስፔን አርጀንቲናን በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች *** የ2026 ዓለም ዋንጫ ዛሬ ፍጻሜውን ሲያገኘ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 አሸንፋለች። 120 ደቂቃ በወሰደው ፍጻሜ ተቀይሮ የገባው ፌራን ቶሬስ የስፔንን ግብ አስቆጥሯል። በአርጀንቲና በኩል መደበኛ 90 ደቂቃው መጠናቀቂያ ላይ የቼልሲው አማካይ ኢንዞ ፈርናንዴዝ ፓው ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። የ2010 የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮኗ ስፔን በታሪኳ ለ2ኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያነሳችበት ሆኗል። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫን ለ2ኛ ተከታታይ ጊዜ ለመውሰድ ለፍጻሜ ብትደርስም ሳይሳካላት ቀርቷል። @Seledadotio @Seledadotio
1 282
12
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኤርትራ እና ሶማሊያ አቻዎቻቸው ጋር በቀጣናዊ ትብብር ዙሪያ ውይይት አደረጉ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 🇪🇬 ዛሬ ዕሑድ በካይሮ በተለያዩ መድረኮች በተደረጉ ስብሰባዎች+1
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኤርትራ እና ሶማሊያ አቻዎቻቸው ጋር በቀጣናዊ  ትብብር ዙሪያ ውይይት አደረጉ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 🇪🇬 ዛሬ ዕሑድ በካይሮ በተለያዩ መድረኮች በተደረጉ ስብሰባዎች፣ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ከኤርትራ አቻቸው ኡስማን ሳሌህ እና ከሶማሊያ አቻቸው አብዱሰላም አብዲ አሊ ጋር መወያየታቸውን የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ስብሰባዎቹ የሁለትዮሽ ግንኙነትን፣ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ማጠናከር እና በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቅንጅት መሥራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት እንደተደረገባቸው ሚኒስቴሩ በመግለጫው አስታውቋል፡፡  @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 391
13
"ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ። ዓለማቀፍ የወንጀለ
"ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ። ዓለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እስራኤል በጋዛ ጦርነት የጦር ወንጀል ፈፅማለች በሚል በኔታንያሁና ሌሎች ሁለት ባለስልጣናት ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሳምንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመወያየት ወደ አሜሪካ ይጓዛሉ። ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያም ኔታንያሁ በሚመሯት የኒዮርክ ከተማ ከገቡ እንደሚታሰሩ ተናግረዋል። "በጉዳዩ ዙሪያ እየተወያየን ነው፤ ግን ህግ እንደ አዲስ አይፃፍም" ሲሉ አይሲሲ ያወጣውን መመሪያ እንደሚተገብሩ ጠቁመዋል። "በኒውዮርክ እስካለው ድረስ የከተማ ህግ አድርገው ብሎ የሚፈቅድልኝን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ" ብለዋል። ማምዳኒ "ኔታንያሁ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል ብየ አምናለሁ"ሲሉ ገልጸዋል። "እሱ ባለፉት አመታት በሰራቸው ወንጀሎች መቅረብ ያለበት ሄግ በሚገኘው ፍርድቤት ነው" ብለዋል። ከንቲባ ማምዳኒ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተው ነበር። ኔታንያሁ ከማምዳኒ ሹመት በኋላ ወደ አሜሪካ ቢያቀኑም ኒዮርክ ከተማ ግን አልገቡም። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከንቲባው ወደ ሚያስተዳድሯት ኒዮርክ የሚገቡት በመጪው መስከረም ወር በሚካሄደው የተመድ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ነው።   @Addis_News @Addis_News
1 703
14
ንጉሱ ከአልጋ ወራሹ ሶስተ ሰዓታት ብቻ ቀሩ!! የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ፤ ስፔን ከ አርጀንቲና፣ የዓለም ሻምፒዮን ከ አውሮፓ ሻምፒዮን ምሽተ 4 ሰዓት፡፡ ዓለም ዋንጫ በታሪኩ ከ1962 በኋላ በተከታታይ ዋ
ንጉሱ ከአልጋ ወራሹ ሶስተ ሰዓታት ብቻ ቀሩ!! የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ፤ ስፔን ከ አርጀንቲና፣ የዓለም ሻምፒዮን ከ አውሮፓ ሻምፒዮን ምሽተ 4 ሰዓት፡፡ ዓለም ዋንጫ በታሪኩ ከ1962 በኋላ በተከታታይ ዋንጫን ያነሳ ሀገር አላስመለከተንምና አርጀንቲና ይህን ታሪክ ለመድገም፤ ስፔን ደግሞ በ2010 በአፍሪካ ምድር ያነሳችውን ብቸኛ ዋንጫዋን ሁለት ልታደርግ የሚያደርጉት ፉክክር ሊጀምር ሰዓታት ብቻ ቀርተዋል። 23ኛው ዓለም ዋንጫ ዛሬ ምሽት 4ስፔን ከ አርጀንቲና በሚያደርጉት የፍፃሜ ጨዋታ ይደመደማል። የወቅቱ የአውሮፓ ሻምፒዮንና የቀደመው የዓለም ዋንጫ አሸናፊ፤ ለድሉ እንግዳ ያልሆኑበትን ዓለም ዋንጫ ዳግም ሊያነሱ የሜት ላይፍ ስታዲየሙን ጨዋታ እየተጠባበቁ ነው። ይህ የዓለም ዋንጫ የሁለት ትውልድ ክዋክብት ፉክክርም ነው። ሁለቱት በስፔን የካታላኑን ባርሴሎና ደምቀው ያደመቁት ኮከቦች የዚህ ፍፃሜ ጨዋታ ዐበይት ምልክቶች ናቸው። ሜሲ በባርሴሎና ያደረገው እና የሆነለት ሁሉ፣ ላሚን ያማልም ካምፕኑ ላይ ይደርስበታል ተብሎ የሚጠበቀው ስኬት ሁሉ የዚህ ጨዋታ ሌላኛው ነፀብራቅ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቅ ጉዳይ ነው። ላሚን ያማል በዓመትም ሆነ በስኬት ከዕድሜው እኩሌታ በላይ ከሚበልጠው ሊዮኔል ሜሲ ጋር ዙፋኑን የሚለዋወጡበት ሊሆንም ይችላል። ሁሉም ነገር ከሰዓታት በኋላ ይፈፀማል። ጥበቃው ሁሉ ያበቃል። የዓለም ዋንጫ ሊደመደም ሰዓታት ቀርተዉታል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ይታደሙበታል ተብሎ በሚጠበቀው አረጀንቲና ከ ስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ፤ ለ39 ቀናት ሲታይ የነበረው የእግር ኳስ ቲያትር መጋረጃው ይዘጋል። በዚህ ጨወታ ማን አሸንፎ ዋንጫውን ያነሳል ብላችሁ ታስባላችሁ? ግምታችሁን አጋሩን፡፡ @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 722
15
በአሜሪካ የኢትዮጵያ የፀሐይ ኃይል ምርቶች ላይ ምርመራ ተጀመረ የአሜሪካ ንግድ መምሪያ በኢትዮጵያ የሚመረቱ የፀሐይ ኃይል ምርቶች፣ በቻይና ላይ የተጣለውን የንግድ ታሪፍ ለመሸሽ የሚረዱ መሆናቸውን ለ
በአሜሪካ የኢትዮጵያ የፀሐይ ኃይል ምርቶች ላይ ምርመራ ተጀመረ የአሜሪካ ንግድ መምሪያ በኢትዮጵያ የሚመረቱ የፀሐይ ኃይል ምርቶች፣ በቻይና ላይ የተጣለውን የንግድ ታሪፍ ለመሸሽ የሚረዱ መሆናቸውን ለማጣራት ምርመራ ሊጀምር ነው። ይህ እርምጃ የተወሰደው የቻይና አምራቾች ኢትዮጵያን ተጠቅመው የአሜሪካን የንግድ ቀረጥ  ለመሻገር እየሞከሩ ነው በሚል ስምንት የአሜሪካ ኩባንያዎች ባቀረቡት አቤቱታ ነው። ከ2025 አጋማሽ ወዲህ ወደ አሜሪካ የሚገቡ የኢትዮጵያ የፀሐይ ኃይል ምርቶች በከፍተኛ ሁኔታ ማደጋቸው ለዚህ ምርመራ መነሻ ሆኗል። የአሜሪካ ንግድ መምሪያ የመጀመሪያ ደረጃ ውሳኔውን በታኅሣሥ 2026፣ የመጨረሻውን ደግሞ በግንቦት 2027 እንደሚሰጥ ይጠበቃል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 706
16
በትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይዎት አለፈ። በሶማሌ ክልል ቀብሪበያህ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፋ ሙሐመድ በቀብሪበያህ ወረዳ በደ+1
በትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይዎት አለፈ። በሶማሌ ክልል ቀብሪበያህ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፋ ሙሐመድ በቀብሪበያህ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ሕይዎታቸውን ባጡ ወገኖች የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። አደጋው ዛሬ ንጋት ላይ በቀበሪበያህ ወረዳ ጉዮው ቀበሌ በባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ እና በአይሱዙ ጭነት ተሽከርካሪ መካከል በደረሰ ግጭት በ12 ሰዎች ላይ የሞት እና በ3 ሰዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ የደረሰ ሲኾን የአደጋው መንስኤ በፖሊስ እየተጣራ እንደሚገኝ ከሶማሌ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 791
17
ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የአመራር ሹመት መምሪያ ይፈ አደረገ‼️ ትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የ
ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የአመራር ሹመት መምሪያ ይፈ አደረገ‼️ ትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የሚገዛ አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል። መመሪያው በብቃትና በውድድር ላይ የተመሰረተ አሰራርን ለማስፈን ያለመ ሲሆን፣የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የአንድ ጊዜ የስራ ዘመን 6 ዓመት እና የምክትል ፕሬዝዳንቶች 4 ዓመት መሆኑ ተነግሯል። በማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ በተከታታይ ሁለት ጊዜ በፕሬዝዳንትነት ያገለገለ አመራር በድጋሚ መወዳደር እንደማይችልም ተገልጿል። ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ ወንድ እጩዎች ቢያንስ የረዳት ፕሮፌሰርነትና ከዚያ በላይ ማዕረግ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን፣ቢያንስ 2 ዓመት በፕሬዝዳንትነት ወይም 3 ዓመት በምክትል ፕሬዝዳንትነት/ዲንነት ያገለገሉ መሆን እንደለባቸው ገልጿል። አመራሩ በየ 3 ወሩ በቦርዱ የሚገመገም መሆኑ እና ። ውጤቱ በሁለት ተከታታይ የስድስት ወር ግምገማዎች ከ60% በታች ከሆነ፣ በጤና እክል ወይም በዲሲፕሊን ጉድለት ከሃላፊነቱ እንዲነሳ ለሚኒስቴሩ ሀሳብ ይቀርባል ተብሏል። በምልመላና ምርጫ ሂደቱ ላይ ቅሬታ ያለው ተወዳዳሪ፣ ውጤቱ በይፋ በተገለጠ በ10 ቀናት ውስጥ ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ ቅሬታውን ማቅረብ እንደሚችል አረጋግጧል። ‎ @Seledadotio @Seledadotio
1 724
18
#እንድታውቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል። ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒ
#እንድታውቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል። ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ልጆች ዕድል እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎችም በውድድር ተደራሽ ይሆናል ብሏል። ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመስጠት ያቀደው 5 ኪሎ (በቀድሞው ድህረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) ሲሆን ምዝገባውም ማክሰኞ ሐምሌ 14 - ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል። ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ? - የመመዝገቢያ ክፍያ 1,000 ብር፤ - የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ እንዲሁም ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት፤ - 2 የወላጅ እና 4 የልጅ ፎቶግራፍ እንዲሁም ወላጆች ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል የሰው ሀብት ቢሮ የተመዝጋቢው ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ፤ - የመመዝገቢያ ክላሰር እና የክፍያ ደረሰኝ ዩኒቨረሲቲው በማኅበራዊ ሚዲያው ባወጣው መረጃ ወርኃዊ የተማሪዎች ክፍያን አላሳወቀም። @Addis_News @Addis_News
1 666
19
"የድሬክ እርግማን/መጥፎ እድል" አርጀንቲናን ከአለምሻምፒዮንነት ያስቀራት ይሆን? ድሬክ የምሽቱን የአለምዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ታሸንፋለች ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል። ድሬክ በተደጋጋሚ
"የድሬክ እርግማን/መጥፎ እድል" አርጀንቲናን ከአለምሻምፒዮንነት ያስቀራት ይሆን? ድሬክ የምሽቱን የአለምዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ታሸንፋለች ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል። ድሬክ በተደጋጋሚ እሱ ያሸንፋሉ ሲል ገንዘብ ያስያዘባቸዉ ቡድኖች ሲሸነፉ ታይቷል። በቅርቡ እንኳ በአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አርሰናል ፤ ፒኤስጂን ያሸንፋል ሲል አስይዞ ገንዘቡን ተበልቷል። ድሬክ በሌሎች ጨዋታዎችም እድል የማይቀናዉ ሲሆን የዛሬዉን ዉርርድ ካሸነፈ ግን 5.2 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ያሸንፋል። #ዳጉ_ጆርናል
1 648
20
#ጤናመረጃ ​የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች! ​የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው። ​1. ለአጥን
#ጤናመረጃ ​የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች! ​የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው። ​1. ለአጥንት ጥንካሬና ጤንነት፦ የሀበሻ ጎመን እጅግ ከፍተኛ የካልሲየም (Calcium) እና የቪታሚን ኬ (Vitamin K) ይዘት ስላለው፣ ለአጥንት መገንባት፣ ለጥንካሬ እና የአጥንት መሳሳትን ለመከላከል አስተዋጽኦ አለው። ​2. በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር፦ በውስጡ ባለው ከፍተኛ የቪታሚን ሲ መጠን ምክንያት፣ የሰውነትን በሽታ የመከላከል ሥርዓት በማገዝ ከኢንፌክሽኖች እና ከተለያዩ በሽታዎች ይጠብቃል። ​3. የደም ማነስን ለመከላከል፦ ጎመን በውስጡ ከፍተኛ የiron ማዕድን ይዟል። ይህም የሰውነታችንን ቀይ የደም ሴል ምርት በማገዝ የደም ማነስ ችግር እንዳይከሰት ትልቅ እገዛ ያደርጋል። ​4. ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፦ ልክ እንደ ጥቅል ጎመን ሁሉ፣ የሀበሻ ጎመንም ከፍተኛ የፋይበር (የቃጫ) ይዘት ስላለው የሆድ ድርቀትን ለመከላከል እና የአንጀትን ጤንነት ለመጠበቅ ይረዳል። ​5. ለአይን ጤንነትና እይታ፦ በአይን ላይ የሚመጡ የዕድሜ መግፋት ጉዳቶችን እና ሌሎች የዓይን በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸውን ሉቲን እና ቪታሚን ኤ በበቂ መጠን ይዟል። ​6.ለቆዳና ለፀጉር ውበት፦ በውስጡ የሚገኙት ቪታሚኖች (A,C,E) እና ፀረ-ኦክሲዳንቶች ለቆዳ ጤንነት፣ ለወጣትነት ገጽታ እና ለፀጉር ጥንካሬ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። ጠቃሚ ምክር :- የሀበሻ ጎመንን ከመጠን በላይ ሳያበስሉ (ሳይሞት) በመጠኑ አብስሎ መመገብ በውስጡ ያሉትን ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።(ኢትዮ-መረጃ) ​ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር! @Seledadotio @Seledadotio
1 662