ch
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

前往频道在 Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

显示更多

📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览

频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 56 789 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 021,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 558

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 56 789 名订阅者。

根据 22 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 364,过去 24 小时变化为 -29,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.68%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.52% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 092 次浏览,首日通常累积 1 434 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

凭借高频更新(最新数据采集于 23 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

56 789
订阅者
-2924 小时
-3117
-1 36430

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+1
在7个频道中
六月 '26
+2
在8个频道中
Get PRO
五月 '260
在8个频道中
Get PRO
四月 '26
+3
在8个频道中
Get PRO
三月 '26
+1 303
在14个频道中
Get PRO
二月 '260
在4个频道中
Get PRO
一月 '260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '250
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+1
在6个频道中
Get PRO
十月 '250
在4个频道中
Get PRO
九月 '250
在3个频道中
Get PRO
八月 '250
在1个频道中
Get PRO
七月 '250
在2个频道中
Get PRO
六月 '250
在6个频道中
Get PRO
五月 '250
在2个频道中
Get PRO
四月 '250
在2个频道中
Get PRO
三月 '250
在10个频道中
Get PRO
二月 '250
在18个频道中
Get PRO
一月 '25
+44
在10个频道中
Get PRO
十二月 '24
+1 502
在16个频道中
Get PRO
十一月 '24
+4 897
在9个频道中
Get PRO
十月 '24
+10 897
在6个频道中
Get PRO
九月 '24
+13 478
在5个频道中
Get PRO
八月 '24
+17 234
在5个频道中
Get PRO
七月 '24
+9 021
在5个频道中
Get PRO
六月 '24
+20
在7个频道中
Get PRO
五月 '24
+351
在14个频道中
Get PRO
四月 '24
+847
在16个频道中
Get PRO
三月 '24
+558
在33个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 785
在15个频道中
Get PRO
一月 '24
+3 011
在18个频道中
Get PRO
十二月 '23
+3 094
在23个频道中
Get PRO
十一月 '23
+730
在120个频道中
Get PRO
十月 '23
+13 017
在37个频道中
Get PRO
九月 '23
+26 548
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+2 062
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+2 838
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+554
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+672
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+1 658
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+3 193
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+1 734
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+895
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+1 925
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+642
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+99
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+547
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+1 026
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+1 241
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+1 528
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+2 018
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+329
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+370
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+390
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+639
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+596
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+736
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+1 209
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+1 351
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+1 280
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+1 459
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
23 七月0
22 七月0
21 七月0
20 七月0
19 七月0
18 七月0
17 七月0
16 七月0
15 七月0
14 七月0
13 七月0
12 七月0
11 七月0
10 七月0
09 七月0
08 七月0
07 七月0
06 七月0
05 七月0
04 七月0
03 七月0
02 七月+1
01 七月0
频道帖子
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ
በወላይታ ሶዶ ከተማ ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ   በወላይታ ሶዶ ከተማ በህግ የተከለከለውን ፌስታል ሲጠቀሙ በተገኙ 130 ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱን የከተማው የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽ/ቤት አስታውቋል።እርምጃው በአብዛኛው በሱቆችና በንግድ ተቋማት ላይ የተወሰደ ሲሆን ከየካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄደው ክትትል የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።   የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ለማ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1387/2017ን በመተላለፍ ፌስታል በመያዝ እና ለንግድ አገልግሎት ጥቅም ላይ ሲያውሉ በተገኙ 130 አካላት ላይ በህጉ መሠረት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።በቅርቡ ከተወሰዱ እርምጃዎች መካከል አንድ ነጋዴ 17 ኩንታል ማዳበሪያ ይዞ በመገኘቱ የተወረሰበት ሲሆን በ50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ጨምር እንዲቀጣ ተደርጓል።   በመሆኑም ግለሰቦችና ተቋማት ፌስታል መጠቀም በህግ የተከለከለ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ህጉን ሊያከብሩ ይገባል ሲሉ አቶ ጴጥሮስ ለማ  ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በአዋጁ መሰረት ፌስታል ይዞ የተገኘ ግለሰብ  በ2 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።እንዲሁም በተቋም ደረጃ ፌስታል ያከማቸ፣ የሸጠ ወይም ለንግድ ዓላማ እንደ እቃ መያዣ ያቀረበ ተቋም እስከ 200 ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እና ባለንብረቶችም  እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንደሚቀጡ በአዋጁ ተጠቅሷል ።   @Seledadotio @Seledadotio

2
ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊዮን በላይ መድረሱን አስታወቀ ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለጋዜጠኞች በሰጠዉ መግለጫ አቅርቧል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስ
ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ90 ሚሊዮን በላይ መድረሱን አስታወቀ   ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለጋዜጠኞች በሰጠዉ መግለጫ አቅርቧል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት የሞባይል ጣቢያዎች ከ10 ሺህ በላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።    በበጀት ዓመቱ የ4ጂ ኔትወርክ  አገልግሎት  እየተስፋፋ ሲሆን  በዚህም 264 ከተሞችን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል። በተጨማሪም ሰባት ከተሞች በአምስተኛ ትዉልድ (5ጂ) ኔትወርክ ተጠቃሚ መሆን  የቻሉ ሲሆን በአጠቃላይ በአሁን ሰዓት 33 ከተሞች  የ5ጂ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፤ ይህ ደግሞ  10.2ሚሊዮን ደንበኞችን  ማስተናገድ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።   ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 90 .1 ሚሊዮን   መድረሱን ገልጿል። ይህም የእቅዱን 101.7 በመቶኛ  ማሳካት ያስቻለ ነው ተብሏል ። ከዚህም ውስጥ የድምጽ ተጠቃሚዎች 86.9 ሚሊዮን ፣ ብሮድባንድ 51.5 ሚሊዮን ፣ ፊክስድ ብሮድባንድ 1 ሚሊዮን ያካተተ ነው ። የፊክስድ ብሮድባንድ ተጠቃሚዎችን 1 ሚሊዮን ማድረስ በእቅድ ደረጃ የተያዘ መሆኑን ስራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።   ተቋሙ 470 የሚሆኑ ምርት እና አገልግሎቶችን ያቀረበ ሲሆን 193 የሚሆኑት አዳዲስ ናቸው። በዚህ ዓመት ደንበኞች እንዴት የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቶችን መጠቀም አለባቸው የሚለውን ትኩረት በማድረግ ደንበኞችን  ከስተመር ኢዱኬሽን በሚል  አገልግሎት የመስጠት ስራ እየጠተገበረ እንደሚገኝ ተገልጿል።   በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
612
3
አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇 ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️ ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ
አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇 ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️ ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል። ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም። አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም። አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ @Addis_Reporter @Addis_Reporter
661
4
የዝናብ ሁኔታ‼️ በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል። በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን  ይኖራቸዋል። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች  ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች  ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል። ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 033
5
እስራኤል የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አወደሰች በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ
እስራኤል የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አወደሰች በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭራሃም ንጉሴ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚና የኢንዱስትሪ እድገት በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ አድናቆታቸውን ለግሰዋል። ይህ የእስራኤል ድጋፍ የመጣው የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያ ግድቡን በብቸኝነት እያንቀሳቀሰች ነው ሲሉ ከከሰሱ በኋላ ሲሆን፣ አምባሳደሩ በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር የእስራኤል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በእርሻ፣ በጠብታ መስኖና በዓሣ ሀብት ልማት ላይ ለመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በሌላ በኩል በካይሮና በአዲስ አበባ መካከል ያለው የቃላት ልውውጥ እና ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት እየጨመረ መጥቷል። ግብፅና ሱዳን ያለ ህጋዊ ስምምነት ግድቡን መሙላትና ማካሄድ የውሃ ደህንነታችንን ይጎዳል ሲሉ ሲቃወሙ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ የ4 ቢሊዮን ዶላሩ ግድብ በታችኞቹ ሀገራት ላይ ምንም ዓይነት ጎጂ ተጽዕኖ እንደማያደርስና ለሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት ወሳኝ መሆኑን አጥብቃ ትገልጻለች። @Seledadotio @Seledadotio
1 045
6
ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500
ብሄራዊ ባንክ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ሊያካሂድ ነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 ዓ.ም የፋይናንስ ዓመት የመጀመሪያው ሩብ በንግድ ባንኮች በኩል 500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ወደ ገበያው ለማስገባት አቅዷል። ማዕከላዊ ባንኩ በነሐሴ እና መስከረም ወራት አራት መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ገልጿል። በእያንዳንዱ ጨረታም 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች እንደሚቀርብ አስታውቋል። @Seledadotio @Seledadotio
1 095
7
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰ+3
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio
1 547
8
የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ጀምሮ ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታወ 👉 ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17
የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ጀምሮ ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ አስታወ 👉 ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል   የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት የሚቆይ ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ፣ የጤና ምክር እና የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎች አገልግሎቱን ያገኛሉ።   አገልግሎቱ ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የሚሰጥ መሆኑን በመግለፅ  በስፔሻሊስት እና በሰብስፔሻሊስት ሀኪሞች ይከናወናል።የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ የጤና ምርመራን ማበረታታት  ነው የተባለ ሲሆን በተለይም አቅም ለሌላቸው ዜጎች የሕክምና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።   በነፃ ከሚሰጡት አገልግሎቶች ውስጥ የውስጥ ደዌ፣ የማህፀንና ፅንስ ሕክምና፣ የመለስተኛ ቀዶ ህክምና፣ የጥርስ ፣ የሥነ አዕምሮ ሕክምና፣ የልብ ምርመራ እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በየቀኑ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ በቁስቋም በሚገኘው የመኪና ማቆሚያ ስፍራ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የጤና ምርመራ ወይም ሕክምና የሚፈልጉ ዜጎች በተጠቀሰው ቦታ በመገኘት አገልግሎቱን መጠቀም እንደሚችሉ ዶክተር አብርሃም እሸቱ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
1 446
9
በትግራይ ብርቱ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ፡፡ በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው+1
በትግራይ ብርቱ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ቀጠፈ፡፡ በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ ተቃራኒ የአየር ሁኔታዎች በሕዝብና በግብርና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆናቸው ተገልጿል። በአንድ በኩል በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ሲቀጥፍ፣ በአዝርእትና በመስኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተነግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ 176 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳላገኙ ተገልጿል። በማዕከላዊ ዞን ወረዳ ቀይሕ ተኽሊ ዶክተር አታኽልቲ ቀበሌ ገበሬ ማህበር፣ ለሁለት ሰዓታት ያለማቋረጥ የዘነበው በረዶ አዘል ከባድ ዝናብ የአንድ ሕፃንን ሕይወት ከመቅጠፉ በተጨማሪ በአዝርእትና በመስኖ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል። በተመሳሳይ በዞኑ ወረዳ አሕፈሮም ሴሮ ቀበሌ የዘነበው ብርቱ ዝናብም በአዝርእትና በአትክልት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን አስታውቋል። በሌላ በኩል የትግራይ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ ትላንት ባወጣው መረጃ፤ በክልሉ ከሚገኙ 600 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት መካከል 176 በሚሆኑት እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ አስታውቋል። ይህ ሁኔታ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፤ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ የዝናብ እጥረት በእርሻ ሥራና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ያሳያል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 358
10
ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013
ጄኤፍኤም 106.7 የሬዲዮ ጣቢያ ለ6 ወራት ታገደ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባደረገው የይዘት ክትትልና የኢንስፔክሽን ምልከታ ጄኤፍኤም 106.7 የብሮድካስት አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እና የፈቃድ ውል ስምምነቱን አልጠበቀም ሲል አስታውቋል። ጣቢያው 60% የሚሆነውን ስርጭት ለፈቃድ አካባቢው የማዋል፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን የማቅረብ፣ እንዲሁም ሀገራዊ እና ህገ-መንግስታዊ እሴቶችን የማጠናከር ግዴታዎቹን አልተወጣም ተብሏል። ባለሥልጣኑ በተደጋጋሚ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም መሻሻል ባለመታየቱ እርምጃው ሊወሰድበት ችሏል። በዚህም መሠረት የሬዲዮ ጣቢያው ከተሰጡት ማስጠንቀቂያዎች በኋላ አስፈላጊዎቹን ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ አሟልቶ እስኪገኝ ድረስ ለቀጣዮቹ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ በሙሉ ታግዷል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡ @Addis_News
1 291
11
በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ ከ140 በላይ ስደተኞች ሕይወታቸው ማለፉ ተነገረ ወደ አውሮፓ ለማቅናት ከአፍሪካ የተነሱ ከ140 በላይ ስደተኞች በሞሪታኒያ የባሕር ዳርቻ መሞታቸው ወይም የደረሱበት መጥፋቱ ተነግሯል። 160 ሰዎችን አሳፍራ ከጋምቢያ የተነሳችው ጀልባ ነዳጅ በመጨረሷ ምክንያት ለ25 ቀናት በባሕር ላይ ስትንሳፈፍ መቆየቷን የሞሪታኒያ የባሕር ጠረፍ ጥበቃ ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) እንዳስታወቀው ከሐምሌ 14 እስከ 18 በተደረጉ የነፍስ አድን ዘመቻዎች ቢያንስ 143 ሰዎች የሞቱ ወይም የጠፉ ሲሆን በሕይወት ከተረፉት መካከል ሙሉ ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ሁለት ሕፃናት በሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ተመላክቷል። ኤጀንሲው ከሞሪታኒያ ተነስቶ ወደ ስፔን ካናሪ ደሴቶች የሚወስደውን የአትላንቲክ መስመር "በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አደገኛ የፍልሰት መንገዶች አንዱ" ሲል የገለጸው ሲሆን ከመጠን በላይ መጫን እና ለባሕር ጉዞ የማይመቹ ጀልባዎችን መጠቀም ለአደጋው መበራከት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ጠቁሟል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 449
12
ኢትዮጵያ የተቆላ ቡናን በኦንላይን አማካኝነት ለአለም ገበያ ልታቀርብ ነው ዲኤችኤል ኤክስፕረስ ኢትዮጵያ እና ኢኤክስኤም ግሎባል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የኢትዮጵያን የመጀመሪያውን የበርካታ ብራንዶች የ+2
ኢትዮጵያ የተቆላ ቡናን በኦንላይን አማካኝነት ለአለም ገበያ ልታቀርብ ነው   ዲኤችኤል ኤክስፕረስ ኢትዮጵያ እና ኢኤክስኤም ግሎባል ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የኢትዮጵያን የመጀመሪያውን የበርካታ ብራንዶች የተቆላ ቡና የኢ-ኮሜርስ የውጪ ንግድ መድረክ በይፋ አስጀምረዋል፡፡ይህም የአገር ውስጥ ቡና ቆይዎች ሙሉ የተቀናጀ የውጪ ንግድ መፍትሔ ተጠቃሚ እንዲሆኑና ዓለም አቀፍ ገበያዎችን በቀጥታ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።   የኢኤክስኤም ግሎባል ዋና ሥራአስፈጻሚ አቶ ኢምራን ኑርሁሴን ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ይህ መድረክ በኢትዮጵያ ቡና ቆይዎች እና በዓለም ዙሪያ ባሉ የቡና አፍቃሪዎች መካከል ቀጥተኛ ድልድይ ይፈጥራል። ዲጂታል ፈጠራን፣ የደንብ ተገዢነት ሙያዊ ብቃትን እና የገበያ ተደራሽነትን በማጣመር፣ የኢትዮጵያ የቡና ብራንዶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ ከፍተኛ እሴት በአገር ውስጥ እንዲቀርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል ። ይህ አዲስ መድረክ፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች ከተለያዩ ብራንዶች አዲስ የተቆላ የኢትዮጵያ ቡናን በአንድ የኦንላይን የገበያ ቦታ ገዝተው በጥቂት ቀናት ውስጥ እንዲረከቡ ያደርጋል።   ደንበኞች አሥር የኢትዮጵያ ቡና ብራንዶችን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፣ ከስፔሻሊቲ ቡናዎች ጀምሮ እስከ ከፍተኛ መጠን ያላቸው የንግድ ምርቶች ድረስ ማዘዝ ይችላሉ።ኢትዮጵያ የቡና መገኛ እንደመሆኗ በልዩ የቡና ምርቶቿ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትታወቃለች። ይህ ተነሳሽነት የተቆላ ቡና ኤክስፖርትን በማበረታታት የአገር ውስጥ ድርጅቶች ከዓለም አቀፍ ደንበኞች ጋር በቀጥታ እንዲገናኙና ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እሴት በአገር ውስጥ እንዲቀርብ በማድረግ ረገድ ትልቅ እገዛ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል ።   በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
1 616
13
እናትን ገድሎ ልጃቸውን የደፈረው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀ
እናትን ገድሎ ልጃቸውን የደፈረው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀጣ የኮንታ ልዩ ወረዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላለፈ። ተከሳሹ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከገበያ ስትመለስ የነበረችውን የ15 ዓመት ታዳጊ ጠልፎ ወደ ጫካ በመውሰድ ሊደፍራት ሲታገል፣ የልጇን ጩኸት ሰምታ የደረሰችውን እናት ወይዘሮ አይናቴ ኬቶን በጩቤ ወግቶ በመግደል ገደል ውስጥ ወርውሯታል። ተከሳሹ እናትን በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ካደባየ በኋላ የጠለፋትን ታዳጊ ልጅ አስገድዶ መድፈሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እና የዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች አረጋግጠዋል። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፣ ተከሳሹ በፈጸማቸው በጭካኔ የመግደል፣ በታዳጊ ልጅ ጠለፋ እና በአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች ጥፋተኛ በማለቱ የሞት ቅጣት እንዲወሰንበት አድርጓል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 452
14
ኮስትሸሪንግ❌‼️ የኬንያ መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በበጀት ሊሸፈን መሆኑን አስታወቀ‼️ የኬንያ መንግስት ከሚቀጥለው መስከረም 2026 ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆ
ኮስትሸሪንግ❌‼️ የኬንያ መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ በሙሉ በበጀት ሊሸፈን መሆኑን አስታወቀ‼️ የኬንያ መንግስት ከሚቀጥለው መስከረም 2026 ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የሚገቡ ሁሉንም ተማሪዎች ትምህርት ሙሉ በሙሉ በመንግስት በጀት እንደሚሸፈን ይፋ አደረገ። ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ አዲሱ የትምህርት ፋይናንስ ማዕቀፍ ከቤተሰብ ኢኮኖሚያዊ አቅም ውጪ በውጤት ላይ ብቻ የተመሠረተ እንደሆነ ገልጸዋል። ቀደም ሲል ተግባራዊ ተደርገው የነበሩት የዩኒቨርሲቲ በጀት አሰጣጥ ሥርዓቶችና የብድር ድብልቅ ሞዴሎች ተቋማቱንና ተማሪዎችን በቂ ድጋፍ ማድረግ ባለመቻላቸው መቋረጣቸውን ተናግረዋል። አዲሱ ሥርዓት ወላጆች በፈቃደኝነት ካልሆነ በስተቀር ምንም አይነት የክፍያ ጫና እንዳይኖርባቸው የሚያደርግና ድህነት ትምህርት እንዳያስተጓጉል የሚያስችል ነው ተብሏል። ለዚህም እንዲመች ፓርላማው የከፍተኛ ትምህርት ብድር ቦርድን ጨምሮ አስፈላጊውን የህግ ማሻሻያ በፍጥነት እንዲያጸድቅ ተጠይቋል። @Addis_News @Addis_News
1 527
15
በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18
በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18 ዓመቷ መስማት የተሳናት ወጣት ተዋናይት ኬይሊ ሆትል ማክሰኞ ጠዋት በደረሰባት ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፉን ፎክስ ኒውስ አረጋግጧል። የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል። ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል። ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች። በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች። መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!      ---ETHIO-MEREJA--       T.me/ethio_mereja
1 545
16
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰ
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ። " ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው። ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል። ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል። የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 495
17
አሜሪካ የእንግሊዝ ወታደራዊ ጣቢያዎችን ተጠቅማ ኢራንን እንድታጠቃ እንድትሰነዝር ተፈቀደላት አዲሱ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሃም አሜሪካ በእንግሊዝ ወታደራዊ ጣቢያዎች በመጠቀም በኢራን
አሜሪካ የእንግሊዝ ወታደራዊ ጣቢያዎችን ተጠቅማ ኢራንን እንድታጠቃ እንድትሰነዝር ተፈቀደላት አዲሱ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሃም አሜሪካ በእንግሊዝ ወታደራዊ ጣቢያዎች በመጠቀም በኢራን ላይ ጥቃት እንድታካሂድ መፍቀዳቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል። የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት ጥቃቱን "የመከላከል እርምጃ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ ይህ ውሳኔ በሁለቱ ሀገራት ወታደራዊ ትብብርና በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ላይ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት እንደሚችል ተመልክቷል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
1 399
18
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካ
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ከተቀሰቀሰ ወዲህ ዋሽንግተን እስከ አሁን 37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን የአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት አስታውቀዋል። ይህ ወጪ ባለፈው ግንቦት ወር ከተደረገው ግምት ጋር ሲነጻጸር የ8 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ አሁንም ተጨማሪ በጀት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። ሚኒስትሩ በሴኔት የገንዘብ ድልድል ኮሚቴ ፊት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ ፣ ኮንግረሱ አስቸኳይ ተጨማሪ በጀት ካላፀደቀ የሀገሪቱ ወታደራዊ ስልጠናዎች ሊስተጓጎሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። ሄግሴት ለመከላከያ መስሪያ ቤታቸው (ፔንታጎን) 87 ቢሊዮን ዶላር እንዲፈቀድ የጠየቁ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 67 ቢሊዮን ዶላሩ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚካሄዱ ወታደራዊ ዘመቻዎች የሚውል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የበጀት ጥያቄ የቀረበው በመካከለኛው ምስራቅ ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች በተገደሉበት እና ጦርነቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በደረሰበት ወቅት ነው። ዋይት ሃውስ ለቀጣዩ የበጀት ዓመት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ለፔንታገን እንዲመደብ መጠየቁ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህም የአሜሪካን ወታደራዊ ወጪ በታሪክ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያደርሰዋል። አሜሪካ በኢራን ላይ ለ11 ተከታታይ ቀናት ጥቃት መሰንዘሯን የቀጠለች ሲሆን ኢራንም በአሜሪካ እና በአጋሮቿ ላይ የአጸፋ ጥቃት በመሰንዘር ላይ ትገኛለች። ዘገባው የቢቢሲ ነው @Addis_News @Addis_News
1 404
19
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ከአንድ ሚሊየን በላይ ቪዛ ሰጥታለች- የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አገልግሎቱ በ2018 የበጀት ዓመት ከ1.04 ሚሊየን በላይ የቪዛ አገልግሎቶችን መስጠቱን ገለፀ። የአገል
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ከአንድ ሚሊየን በላይ ቪዛ ሰጥታለች- የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አገልግሎቱ በ2018 የበጀት ዓመት ከ1.04 ሚሊየን በላይ የቪዛ አገልግሎቶችን መስጠቱን ገለፀ። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ተቋሙ ከሶስት ዓመት በፊት 2መቶ76 ሺህ ቪዛ ብቻ በአመት ውስጥ መስጠቱን አስታውሰው፤ በ2018 በጀት ዓመት 1.04 ሚሊየን ቪዛ በመስጠት ከአራት እጥፍ በላይ እድገት ማስመዝገቡን አንስተዋል። አገልግሎቱ የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓቱን ማሻሻሉ፣ የዲጂታል አገልግሎትን ማስፋፋቱና የአየርና የየብስ ድንበር አስተዳደር አገልግሎትን ማዘመኑን ተከትሎ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን በማንሳት አዲስ የተጀመሩት የStopover እና Transit ቪዛ አገልግሎቶች የቱሪዝምና የጉዞ እንቅስቃሴን እያበረታቱ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሯ ገልጸዋል። ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት አክለውም፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ1መቶ94 በላይ ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ እንዲገቡ  በኢ-ቪዛ (e-Visa)፣ በውጭ ሀገራት በሚገኙ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ተቋማት እና በመድረሻ ቪዛ (Visa on Arrival) አማራጮች አገልግሎት እየሰጠች ትገኛለች በማለት የአገልግሎቱን አድማስ አብራርተዋል። የቱሪዝም ፍሰትን ለማሳደግ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትንና የንግድ ግንኙነትን ለማበረታታት እንዲሁም የሰዎችን ነፃ እንቅስቃሴ ለማቀላጠፍ የተወሰደ እርምጃ የሀገሪቱን ብልፅግና የሚያፋጥን የዜጎችን የመንቀሳቀስ መብት ያከበረ መሆኑን ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ተናግረዋል። ወደፊትም ዘመናዊና ቀልጣፋ የቪዛና ሌሎችም የኢሚግሬሽን አገልግሎቶችን በማስፋት እና በማዘመን ኢትዮጵያን ለዓለም አቀፍ ተጓዦችና ባለሀብቶች ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። @Seledadotio @Seledadotio
1 407
20
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። ከንቲባዋ ይህን ያስታወቁት፣ በከተማ አስተዳደሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው። እንደ ከንቲባዋ ገለጻ፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ መሆን እንደሌለባት ቀደም ሲል የተደረሰውን ስምምነት የሚጥሱ አካላት ተጨማሪ ዕድል እንደማይሰጣቸው አስጠንቅቀዋል። በሌላ በኩል፣ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ፣ በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያለ የደህንነት ችግር በሰላም መጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል። በተጨማሪም፣ የከተማዋ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት መዘመኑ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጥናት መሠረት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአፍሪካ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ ከተሞች መካከል በአሠራር ደረጃ አንደኛ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባ አዳነች አክለውም፣ በጤናው ዘርፍ የሕክምና ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባርና የአገልግሎት ጥራት መሻሻሉን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የጤና አገልግሎትና የመሠረተ ልማት ሥራዎችም ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነጻጸሩ በእጥፍ መጨመራቸውን ገልጸዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 610