ch
Feedback
Fresh መረጃ | FreshNews

Fresh መረጃ | FreshNews

前往频道在 Telegram

Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

显示更多

📈 Telegram 频道 Fresh መረጃ | FreshNews 的分析概览

频道 Fresh መረጃ | FreshNews (@freshmerejaet) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 55 863 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 043,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 587

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 55 863 名订阅者。

根据 25 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -730,过去 24 小时变化为 79,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.82% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 004 次浏览,首日通常累积 1 573 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Fresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.

凭借高频更新(最新数据采集于 26 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

55 863
订阅者
+7924 小时
+1467
-73030

数据加载中...

吸引订阅者
八月 '26
八月 '26
+298
在8个频道中
七月 '26
+1
在9个频道中
Get PRO
六月 '26
+2
在8个频道中
Get PRO
五月 '260
在8个频道中
Get PRO
四月 '26
+3
在8个频道中
Get PRO
三月 '26
+1 303
在14个频道中
Get PRO
二月 '260
在4个频道中
Get PRO
一月 '260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '250
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+1
在6个频道中
Get PRO
十月 '250
在4个频道中
Get PRO
九月 '250
在3个频道中
Get PRO
八月 '250
在1个频道中
Get PRO
七月 '250
在2个频道中
Get PRO
六月 '250
在6个频道中
Get PRO
五月 '250
在2个频道中
Get PRO
四月 '250
在2个频道中
Get PRO
三月 '250
在10个频道中
Get PRO
二月 '250
在18个频道中
Get PRO
一月 '25
+44
在10个频道中
Get PRO
十二月 '24
+1 502
在16个频道中
Get PRO
十一月 '24
+4 897
在9个频道中
Get PRO
十月 '24
+10 897
在6个频道中
Get PRO
九月 '24
+13 478
在5个频道中
Get PRO
八月 '24
+17 234
在5个频道中
Get PRO
七月 '24
+9 021
在5个频道中
Get PRO
六月 '24
+20
在7个频道中
Get PRO
五月 '24
+351
在14个频道中
Get PRO
四月 '24
+847
在16个频道中
Get PRO
三月 '24
+558
在33个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 785
在15个频道中
Get PRO
一月 '24
+3 011
在18个频道中
Get PRO
十二月 '23
+3 094
在23个频道中
Get PRO
十一月 '23
+730
在120个频道中
Get PRO
十月 '23
+13 017
在37个频道中
Get PRO
九月 '23
+26 548
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+2 062
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+2 838
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+554
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+672
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+1 658
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+3 193
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+1 734
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+895
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+1 925
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+642
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+99
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+547
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+1 026
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+1 241
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+1 528
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+2 018
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+329
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+370
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+390
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+639
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+596
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+736
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+1 209
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+1 351
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+1 280
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+1 459
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
26 八月0
25 八月+79
24 八月+198
23 八月+4
22 八月+17
21 八月0
20 八月0
19 八月0
18 八月0
17 八月0
16 八月0
15 八月0
14 八月0
13 八月0
12 八月0
11 八月0
10 八月0
09 八月0
08 八月0
07 八月0
06 八月0
05 八月0
04 八月0
03 八月0
02 八月0
01 八月0
频道帖子
የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ ደረሰ የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ
የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ ደረሰ የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ አጠቃላይ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር መብራቱ ተሾመ ገልፀዋል። 201 ሜትር ርዝመት ያለው የግድብ ግንባታው 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የአፈር ቁፋሮ በማካሄድ አጠቃላይ ግድቡ ከሚፈልገው 7 ነጥብ 72 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ውስጥ 81 ነጥብ 2 በመቶው ማለትም 6 ነጥብ 27 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት (RCC) ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። የኃይል ማመንጫ ቤቱ የቁፋሮ ሥራ እንዲሁም የሲቪል ሥራው የመጀመሪያ ደረጃ የኮንክሪት ሙሌት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም ተናግረዋል። የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራውን በታቀደው ጊዜ ለማጠናቀቅ ዕቃዎች በበርካታ ፋብሪካዎች እንዲመረቱ መደረጉንም ገልጸዋል። የፋይናንስ አቅርቦት በተለይም የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ተያያዥ ችግሮች በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሮ መቆየቱን ያስታወሱት ኢንጂነር መብራቱ፣ አሁን ላይ ተቋሙ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልገውን ፋይናንስ በራሱ በመሸፈኑ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል ብለዋል። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH

2
ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ
ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ ምክረ ሃሳብ እንዲያዘጋጅ የተሰየመው አስማሚ ኮሚቴ አሰራር የኮሚሽኑን ሕጋዊ ማዕቀፍ የጠበቀ አይደለም ብሏል። የፓርቲው መሪ አቶ እዮብ መስፍን እንደገለጹት፤ የኮሚቴው አወቃቀርና አካሄድ የኮሚሽኑን ሕግ ያልተከተለ በመሆኑ ፓርቲው አጠቃላይ ሂደቱን ውድቅ በማድረግ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ቅሬታ አቅርቧል። ኢዜማአክሎም በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ካለው ተቃውሞ በተጨማሪ፤ በምክክሩ ወቅት የቀረቡ 400 ያህል ምክረ ሃሳቦችና የውይይት ቃለ ጉባኤዎች ለሕዝብ ግልጽ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።" @Seledadotio @Seledadotio
708
3
የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢ
የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን  የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።አገልግሎቱ ባወጣው የወርሃዊ የዋጋ ንረት መረጃ፣ በሐምሌ ወር የተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ከባለፈው አመት ጋር ከነበረው 13.7 በመቶ  ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ አድርጓል።  ሰኔ ወር ላይ የነበረው 14.8 በመቶ ነበር። በዚህ ወር የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ ሲሆን፣ የምግብ ያልሆኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች የዋጋ ንረት ደግሞ 14.8 በመቶ ደርሷል ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።የዋጋ ንረቱ በ2018 ዓ.ም. መጀመሪያ ወራት ላይ በመቀነስ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ዳግም እየጨመረ የመጣ ሲሆን በመጋቢት ወር የነበረው የዋጋ ንረት ከወራት ዝቅተኛ ደረጃዎች አንዱ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት ግን ጭማሪ ታይቷል። በተለይም የምግብ ዋጋ ጭማሪ ለአጠቃላይ የዋጋ ንረቱ መጨመር ዋነኛ አስተዋጽዖ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ሲሆን የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ መድረሱ የዋጋ ጭማሪው በቤተሰቦች የዕለት ተዕለት ወጪ ላይ ጫና መፍጠሩን ያሳያል። ባለፈው አመት ከነበረው የዋጋ ግሽበት ከ13.7 በመቶ ጀምሮ በዓመቱ መካከል እስከ 9 በመቶ አካባቢ ዝቅ ብሎ ነበር።ይሁን እንጂ ነገር ዳግም በመጨመር በሰኔ 14.8 በመቶ እና በሐምሌ 15.3 በመቶ ደርሷል። በመሆኑም የቅርብ ወራት የዋጋ ንረት አዝማሚያ በኢትዮጵያ የእቃና የአገልግሎት ዋጋ ጭማሪው እንደገና እየተፋጠነ መምጣቱን ያሳያል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገልጿል። @YeneTube @FikerAssefa
995
4
በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የ+2
በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የኢራን የፔትሮሊየም ሚኒስትር ሞህሴን ፓክኔጃድ ይፋ አደረጉ። ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከተገኘው አጠቃላይ ክምችት ውስጥ ከ160 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚሆነው የተፈጥሮ ጋዝ በቀላሉ ወጥቶ ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ነው። አዲሱ የተፈጥሮ ጋዝ በጥራት ደረጃው «ጣፋጭ» (sweet gas) የሚባል ሲሆን፣ መርዛማ የሆነውን የሃይድሮጅን ሳልፋይድ (hydrogen sulphide) ጋዝ ይዘት አነስተኛ በመሆኑ ማውጣትና ማልማት የሚጠይቀውን ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል። ብሉምበርግ (Bloomberg) የዘርፉን ባለሙያዎች ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አዲሱ ክምችት ተለምቶ ሙሉ በሙሉ ወደ ምርት ለመግባት እና ለገበያ ለመቅረብ በርካታ ዓመታትን ሊወስድ ይችላል። ይህ አዲስ ጥራት ያለው የጋዝ ግኝት ይፋ የተደረገው፣ በቅርቡ ከተቀሰቀሰው የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኋላ በአሜሪካ እና በእስራኤል በጋራ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ምክንያት የኢራን የጋዝ ማውጫ ተቋማት፣ የነዳጅ ማከማቻዎች እና የትራንስፖርት መሠረተ-ልማቶች ከፍተኛ ውድመት በደረሰባቸው ወቅት ነው። @Addisinsider_ETH @Addisinsider_ETH
935
5
በቀን በአማካይ ከ 20 እስከ 35 እናቶች በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ይወልዳሉ። 2018 ላይ አንድም እናት በወሊድ ምክንያት ያልሞተበት መሆኑን ሆስፒታሉ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ከተማ አ
በቀን በአማካይ ከ 20 እስከ 35  እናቶች በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ይወልዳሉ። 2018 ላይ አንድም እናት በወሊድ ምክንያት ያልሞተበት መሆኑን ሆስፒታሉ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሩ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ ሆስፒታሎች አዱ የሆነው ​ጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ ያለ ትልቅ ሆስፒታል ሲሆን  በቀን በአማካይ ከ20 እስከ35 እናቶች እንደሚወልዱ  የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት  ዶክተር  እሸቱ ታደለ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። ሆስፒታሉ በወር ውስጥ ከ650 እስከ 700 እናቶች የወሊድ አገልግሎት የሚያገኙበት ትልቅ ተቋም መሆኑ ሀላፊው የተናገሩ ሲሆን ያለምንም ክፍያ በነፃ የወሊድ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም ተገልጿል። በሆስፒታሉ ህፃናት እና እናቶች ተገቢውን የህክምና አገልግሎት እንዲገኙ የፅንሰ-የነፍስ ጡር እናቶች እና የህፃናት ስፔሻሊስቶች በትስስር እየሰሩ እንደሚገኙ ያታወቀ ሲሆን በ2018 ዓመትም አንዲትም እና ከወሊድ ጋር በተያያዛ ህይወቷ ያላለፈበት መሆኑ ተነግራል፡፡     በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል
923
6
"አዲስ የባህር ፈንጂ የሚጥል ማንኛውም መርከብ ወዲያውኑ ይደመሰሳል" — ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላለፉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሆርሙዝ ሰርጥ ዓለም አቀፍ የባህ+1
"አዲስ የባህር ፈንጂ የሚጥል ማንኛውም መርከብ ወዲያውኑ ይደመሰሳል" — ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላለፉ   የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሆርሙዝ ሰርጥ ዓለም አቀፍ የባህር ክልል ውስጥ የተቀበሩ የባህር ፈንጂዎች (mines) በሙሉ በአሜሪካ የባህር ኃይል መወገዳቸውን እና መኮላሸታቸውን ገልጸዋል።   ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባስተላለፉት ጠንካራ መልእክት፣ ኢራን አዲስ የባህር ፈንጂዎችን ለማስቀመጥ የምትሞክር ከሆነ ማንኛውም መርከብ ወይም የውሃ ላይ ጀልባ ወዲያውኑ እና በተደራጀ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ እንደሚደመሰስ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷታል ብለዋል።   አሜሪካ በህዋ ኃይል (Space Force) አማካኝነት የሆርሙዝ ሰርጥን በእያንዳንዱ ኢንች በቅርበት እየተከታተለች መሆኑን የጠቀሱት ትራምፕ፣ የፒክአክስ ተራራን (Pickaxe Mountain) ጨምሮ ቀደም ሲል የወደሙትን ሶስት የኒውክሌር ጣቢያዎች በተመሳሳይ ሁኔታ እየተከታተሉ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።   አሜሪካ በሰርጡ ውስጥ ምንም ዓይነት አዲስ የባህር ፈንጂ የመቅበር እንቅስቃሴን በፍጹም የማትታገስ መሆኗን እና ይህ አቋሟ በአሁኑ ወቅት በሙሉ ጥንካሬ ወደ ተግባር መግባቱን አስምረውበታል። @Seledadotio @Seledadotio
1 190
7
በናይጄሪያ የ101 ዓመቷ አያት በአደንዛዥ ዕፅ ንግድ ታሰሩ ​በናይጄሪያ ደቡብ ምዕራብ ክፍል በምትገኘው ግዛት ነዋሪ የሆኑ የ101 ዓመቷ ኤስተር ኦጉንማቦ የተባሉ አረጋዊት ማሪዋና (ካናቢስ) ሲሸጡ
በናይጄሪያ የ101 ዓመቷ አያት በአደንዛዥ ዕፅ ንግድ ታሰሩ ​በናይጄሪያ ደቡብ ምዕራብ ክፍል በምትገኘው ግዛት ነዋሪ የሆኑ የ101 ዓመቷ ኤስተር ኦጉንማቦ የተባሉ አረጋዊት ማሪዋና (ካናቢስ) ሲሸጡ በመገኘታቸው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ​የናይጄሪያ የዕፅ ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ (NDLEA) እንዳስታወቀው፣ አያት ኤስተር በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች በትንሽ በትንሹ የታሸገ 'ስከንክ' የተባለ የማሪዋና አይነት ሲሸጡ ተደርሶባቸዋል። አረጋዊቷ ለፖሊስ በሰጡት ቃል፤ ቀደም ሲል የነበራቸው የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቃቸው በእሳት ከተቃጠለባቸው በኋላ ገቢ ለማግኘት ሲሉ ወደ እፅ ንግዱ መግባታቸውን ተናግረዋል። ​እንደ ኤጀንሲው ገለጻ፣ በሌጎስ የምትኖረው ሴት ልጃቸው በየአራት ቀኑ ዕፁን አዘጋጅታ የምታቀርብላቸው ሲሆን፣ እሷም ለምርመራ በቁጥጥር ስር ውላለች። ​የዕፅ ተቆጣጣሪ ኤጀንሲው ስራ አስፈፃሚ ሞሐመድ ማርዋ አረጋዊቷን በእድሜያቸው ምክንያት በዋስ እንዲፈቱና የምክር አገልግሎት እንዲሰጣቸው አዝዘዋል። ሆኖም በዋስ መፈታታቸው ከህጋዊ ተጠያቂነት እንደማያድናቸውና ክስ ሊመሰረትባቸው እንደሚችል ተገልጿል ሲል የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ሰሞኑ ዘግበዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 250
8
ኢራን የዶናልድ ትራምፕ ትንሹ ልጅን የሆነውን ባሮን ትራምፕን ለገደለ የ10 ሚሊዮን ዶላር እከፍላለው አለች ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትንሹ ልጅ የሆነውን ባሮን ትራምፕን ለመግደል የታለ
ኢራን የዶናልድ ትራምፕ ትንሹ ልጅን የሆነውን ባሮን ትራምፕን ለገደለ የ10 ሚሊዮን ዶላር እከፍላለው አለች ​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትንሹ ልጅ የሆነውን ባሮን ትራምፕን ለመግደል የታለመ ሴራ የሚያሳይ ቪዲዮ በኢራን መንግስታዊ ቴሌቪዥን ከተሰራጨ በኋላ የአሜሪካ ሚስጥራዊ አገልግሎት (Secret Service) ጉዳዩን ማጣራት ጀምሯል። ​በቴሌቪዥን የተሰራጨው ባለ 3 ደቂቃ ቪዲዮ የ20 ዓመቱ ባሮን ትራምፕ እንቅስቃሴ በቅርብ እንደሚከታተል የገለፀ ሲሆን፣ እሱን ለገደለ ሰው የ10 ሚሊዮን ዶላር የጉርሻ ክፍያ እንደተዘጋጀ ገልጿል። የድርጅቱ ቃል አቀባይ ኔት ሄሪንግ እንደተናገሩት፣ ኤጀንሲው ስለ ቪዲዮው መኖር የሚያውቅ ሲሆን ከደህንነት ጥበቃ ጋር በተያያዘ ስጋት የሚፈጥሩ ማናቸውንም ነገሮች ይመረምራል። ​ይህ ማስፈራሪያ የመጣው አሜሪካ እና እስራኤል በየካቲት ወር በኢራን ላይ ጥቃት ካሰነዘሩ በኋላ ሁለቱ ሀገራት በጦርነት ውስጥ ባሉበት ወቅት ነው። የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻመኔይ በአሜሪካ ጥቃት ከተገደሉ ወዲህ የኢራን መገናኛ ብዙኃን በትራምፕ እና በቤተሰቦቻቸው ላይ ያተኮሩ የተለያዩ የማስፈራሪያ መልእክቶችን ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። @Addis_News @Addis_News
1 413
9
በደቡብ ሱዳን ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስቸኳይ ምርመራ ጠየቀ ትናንት ሰኞ ​በደቡብ ሱዳን በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ
በደቡብ ሱዳን ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስቸኳይ ምርመራ ጠየቀ ትናንት ሰኞ ​በደቡብ ሱዳን በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ። ሮይተርስ እንደዘገበው ​የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMISS) ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሰላም አስከባሪዎቹ መደበኛ የተሽከርካሪ ጥበቃ እና ቅኝት በማድረግ ላይ በነበሩበት ወቅት መሆኑን ገልጿል። በዚሁ ጥቃት አሰቃቂ ድርጊት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን የገለጸው ድርጅቱ፣ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት በፍጥነት ተለይተው ለሕግ እንዲቀርቡ እና አጣዳፊ ምርመራ እንዲደረግ ጥብቅ ጥሪ አቅርቧል። ​እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃ ከሆነ፣ በዚህ ዓመት (2026) ብቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የነበሩ ዘጠኝ የሰላም አስከባሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ​ደቡብ ሱዳን ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ምክንያት የሰላም አስከባሪዎች ለከፍተኛ አደጋ እየተጋለጡ ሲሆን፣ ድርጅቱ በአካባቢው ሰላምና ደኅንነት ለማስከበር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 467
10
በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ጢያ፣ ሱተን እና ኧሽከዲየ ቀበሌዎች የጸጥታ ችግር መከሰቱ ተገለጸ። በጢያ፣ ሱተን እና ኧሽከዲየ ቀበሌዎች የጸጥታ ችግር መከሰቱን፤ በዚህም ከባድ የጦር መሣሪያ ተኩስ እንደሚሰማና ነዋሪዎች ቀያቸውን ለቀው እየሸሹ መሆኑ ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የወረዳው የጸጥታ ኃይል በአጥቂዎቹ ጫና ወደ ቡኢ ከተማ ማፈግፈጉን እና አንዳንድ ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቀው ወደ ቡኢ ከተማ መግባታቸውን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ። በተለይ "አቅም-አጠር አረጋውያን፣ እናቶች፣ ሕፃናትና ሕሙማን በግጭቱ መካከል ቀርተዋል" የሚል መረጃ የተሰማ ሲሆን መረጃውም ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል። በክስተቱ እስካሁን ምን ያህል የሰው ሕይወት መጥፋቱ ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ሁኔታውን በተመለከተ በይፋ የወጣ መንግሥታዊ መረጃም የለም፡፡ ሆኖም የጸጥታ ችግሩ በፍጥነት እንዲቀረፍና በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐን ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ነዋሪዎች እየጠየቁ ነው፡፡ የፌዴራል መንግሥትና የክልሉ የጸጥታ ተቋማት እንዲሁም  የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅቶች በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐንን ለመጠበቅ ፈጣን እርምጃ ይውሰዱ የሚል ጥሪም ቀርቧል። በዚህ ቀጣና ቀደም ብሎም መሰል የጸጥታ ችግሮች ሲከሰቱ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ ችግሩ በተለያየ ጊዜና ቦታ መከሰቱን እንደቀጠለ ለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 833
11
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፡- ✅ከጠዋቱ 11፡00-11፡00 👉ኢዮ ጠቢብ ሆስፒታል፣ አበበ ቢቂላ ስታድየም፣ መድሀኒዓለም ት/ቤት ጀርባ፣ መድሀኒዓለም ኮንዶሚኔም፣ ቦናት እና አካባቢው፣                                                                                                  👉ሸጎሌ ቴሌ፣ ሩፋኤል ፊናንስ፣  አንበሳ ጋራጅ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል ጀርባ፣ ውሃ ጋኑ አካባቢ ( ጎማ አደባባይ) እና አካባቢው፣ ✅ከጠዋቱ 3፡30-10፡30 👉ሱሉልታ መሀል ከተማ ፣ኢንዱስትሪ መንደር ፣ ወሌ ፣ ጎሮ አርባ፣ አቢሲኒያ ባንክ፣ ዳሽን ባንክ፣ ሱሉልታ መዘጋጃ፣ ኪዳነ ምህረት መውጫ ፣ ሱሉልታ ቄራ ፣ ሱሉልታ ስላሴ፣ አለሙ ማደያ እና አካባቢው፣ ✅ ከጠዋቱ 2፡00-9፡30 👉 ብሄረ ጽጌ፣ ሳሪስ ነጋ ቦንገር ፣ ስላሴ ቤተክርስቲያን፣ቀይ አፈር፣ ቡራዩ ፣ አኔ ዲማ፣ ወታቤቻ ፣ ሀሙስ ገበያ እና አካባቢው፣ ✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00 👉 መካኒሳ አርሴማ ቤተክርስቲያን፣ ጀርመን አደባባይ ፣ ጀሞ ሚካኤል፣ አፍሪካ ህንጻ ፣ ዱላ ማርያም ፣ 👉 ጭሮ ቤካ፣ ኮራ፣ ኮሞና፣ ጮሮራ፣አንጫር፣ ቦሮዳ፣ ድንድር ፣ ሲዳማ ክልል ይርጋለም፣ ለኩ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ @Freshmerejaet @Freshmerejaet
1 987
12
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል። ውጤት ለማየት ፦ 👉 በድረ ገጽ ፡ https://r+1
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል። ውጤት ለማየት ፦ 👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et 👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram 👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል። @Addis_News @Addis_News
2 122
13
ሁለት የኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪዎች በደቡብ ሱዳን በደረሰባቸው የደፈጣ ጥቃት ተገደሉ   ግዛት ትናንት ሰኞ በደረሰ የደፈጣ ጥቃት፤ ሁለት የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች ሰባት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የተባበሩት መንግሥታት አስታወቀ። ይህም በተያዘው የአውሮፓውያኑ ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ በሥራ ላይ እያሉ የተገደሉትን የሰላም አስከባሪዎች ቁጥር ወደ ዘጠኝ አድርሶታል።   ከተጎዱት መካከል ሦስቱ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪዎች፣ ሁለቱ የደቡብ ሱዳን ፖሊሶች እና ሁለቱ የሲቪል ሰራተኞች እንደሚገኙበት የድርጅቱ ዋና ጸኃፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።   ጥቃቱ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የተፈጸመ መሆኑን እና ፓትሮሉ ወይም የክትትል ቡድኑ ሆን ተብሎ የተላመደ ይመስላል ብለዋል።   “እነዚህ ድርጅቱ በአካባቢው ያለውን ዘላቂ የጸጥታ ችግር ለመፍታት ከሚያደርጋቸው መደበኛ የክትትል ሥራዎች አካል ናቸው” ብለዋል ቃልአቀባዩ።   የተባበሩት መንግስታት የሚመለከታቸው አካላት ጥፋተኞችን ለፍርድ ለማቅረብ አጣዳፊ እና አጠቃላይ ምርመራ እንዲያደርጉ መጠየቁን ዱጃሪች ገልጸዋል። አክለውም “በድርጅቱ የሰላም አስከባሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የጦር ወንጀል ሊሆኑ ይችላሉ” ሲሉ አጽንኦት መስጠታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።   ይህ የቅርብ ጊዜ ድርጊት “ከዚህ ዓመት ጥር 1 ጀምሮ በጥፋት ድርጊቶች የተገደሉትን የሰላም አስከባሪዎች ቁጥር ወደ ዘጠኝ ያደርሰዋል” ብለዋል።   በደቡብ ሱዳን በመንግስታቱ ድርጅት ሠራተኞች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ቢሆንም፣ ከዚህ በፊት ያልተከሰቱ አይደሉም፤ በተለይም የድርጅቱ ተንቀሳቃሽ ቡድኖች በማህበረሰቦች መካከል በሚደረጉ ግጭቶች፣ በታጠቁ ወጣቶች እንቅስቃሴ እና ከወታደራዊ ኃይሎች ጋር በሚደረጉ ግጭቶች በተጎዱ አካባቢዎች ይንቀሳቀሳሉ።   በሰኔ ወር የድርጅቱ የደኀንነት ምክር ቤት፣ እየጨመረ በመጣው የኃይል ድርጊት እና ዝቅተኛ የህግ ተጠያቂነት አፈጻጸም ምክንያት፣ በተመድ የሰላም አስከባሪዎች ላይ ለሚፈጸሙ ጥቃቶች ተጠያቂነትን ለማጠናከር የሚያስችል የውሳኔ ሃሳብ አጽድቆ ነበር።   ይህ የተከናወነው በሠራተኞቹ ላይ ከተፈጸሙ ተከታታይ አደጋዎች በኋላ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በነሐሴ ወር መጀመሪያ ላይ፣ የእስራኤል እና የሂዝቦላህ አዲስ ግጭት ወቅት በሊባኖስ የድርጅቱ ጊዜያዊ ኃይል ውስጥ ያገለግሉ የነበሩ ሦስት የሰላም አስከባሪዎች መገደል ይገኝበታል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
2 052
14
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የ
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች  ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል። ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- - በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et - ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram - አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms @Seledadotio @Seledadotio
2 005
15
የድሮን ጥቃት ተፈፀመ በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት
የድሮን ጥቃት ተፈፀመ በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት ነሐሴ 18 ከለሊቱ 7:30 አካባቢ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። ጥቃቱ የተፈፀመው በሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ሲሆን በካምፑ ውስጥ የጦር መሳሪያ ክምችት መኖሩ ተዘግቧል። ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም @Addis_Reporter @Addis_Reporter
2 001
16
3ኛው የአፍሪካ ስታር ዋይድ አዋርድ በመስከረም ወር ይካሄዳል! “ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ፤ መመሰጋገን ባሕላችን እናድርግ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው 3ኛው ዙር የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በመጪው መስከረም ወር እንደሚካሄድ አዘጋጁ ከለር ፉል ኢቨንት ኦርጋናይዘር በዛሬዉ እለት በአምባሳደር ሆቴል በሰጠዉ መግለጫ አስታዉቋል። በዝግጅቱ ላይ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከአፍሪካ ህብረት (Aሀ) የተወጣጡ ተወካዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የውጭ ሀገራት እንግዶች እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንደሚታደሙ ተጠቅሷል። የዘንድሮው ዝግጅት ከአምናው በበለጠ አድማሱን በማስፋት አህጉራዊ ተደራሽነት ያለው እንዲሆን መደረጉ ተገልፆ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ምሁራንና ባለሙያዎች በዳኝነትና በኮሚቴነት መካተታቸዉም ነዉ የተገለፀዉ። ሽልማቱ በተለያዩ 11 ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የአመራር አባልና ኢንቨስትመንት ዘርፍ፣ የኮንስትራክሽንና ሪል እስቴት ዘርፍ፣አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባንክ፣ አቪየሽንና ቱሪዝም፣ሴትና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች፣ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች እንደሆኑ ተገልጿል። የአዋርዱ ዋነኛ አላማ በዘርፉ የለፉና የደከሙ ግለሰቦችንና ተቋማትን ፈልፍሎ በማዉጣት የሃገር ባለዉለታ ስለመሆናቸዉና በትዉልዱ ዘንድ ሊመሰገኑ ሊዘከሩ እንደሚገባና ትዉልዱም ከመልካም ሥራቸዉና ከዘወትር ትጋታቸዉ ልምድ እንዲቀስም እድሉን ለማመቻቸት ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ይህ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት አቅም ለውጭ ሀገር አልሚዎች ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ፣ አሸናፊዎችን በትክክል ለመለየት ከሙያተኞች ግምገማ በተጨማሪ ህዝቡ በድረገፅ አማካኝነት በስልክ፣ በአሜይል፣ በቴሌግራም እና በዋትስአፕ ጥቆማዎችን መስጠቱን እንዲቀጥል አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል። የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ ለሕዝብ እና ለአገር በጎ ነገር ያበረከቱ ግለሰቦችና ስኬታማ የኢኮኖሚ ጃግኖች፣ በትጋት በቅንነት እና በሀገር ፍቅር መስራት ተምሳሌት የሆኑ አመራሮች፣ ዉስጥ በመሳተፍ በሙያቸዉ አንቱ ለተባሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚያበረክት ነዉ።
2 129
17
የ12ኛ ክፍል ዉጤት ሲለቀቅ በፍጥነት መረጃ ምታገኙበት እንዲሁም ውጤታችሁን ያለሰርቨር መጨናነቅ እንድታዩ የሚያግዛችሁን ቻናል አሁኑኑ ይቀላቀሉ! 👇 https://t.me/addlist/dLx_2YaQlwFmNjQ8
2 047
18
የድሮን ጥቃት ተፈፀመ በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት
የድሮን ጥቃት ተፈፀመ በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት ነሐሴ 18 ከለሊቱ 7:30 አካባቢ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል። ጥቃቱ የተፈፀመው በሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ሲሆን በካምፑ ውስጥ የጦር መሳሪያ ክምችት መኖሩ ተዘግቧል። ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም @Seledadotio @Seledadotio
2 361
19
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል @Addis_News @Addis_News
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል @Addis_News @Addis_News
2 194
20
የቀድሞ የባልደራስ ፓርቲ ሊቀመንበር እና አሁን በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ውስጥ በአባልነት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ እስክንድር ነጋ ንቅናቄያቸው ከመላ አባላቱ እውቅና ውጪ ከሌሎች
የቀድሞ የባልደራስ ፓርቲ ሊቀመንበር እና አሁን በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ ውስጥ በአባልነት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የተናገሩት አቶ እስክንድር ነጋ ንቅናቄያቸው ከመላ አባላቱ እውቅና ውጪ ከሌሎች ኃይሎች ጋር ጥምረት ለመፍጠር መሞከሩ ተቀባይነት የለውም አሉ።  አቶ እስክንድር ነጋ ዛሬ ለዶቼ ቬለ በሰጡት ቃለ ምልልስ በአፋብን ውስጥ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ያልተቀበሉት በውስጥ እና ረዣዥም ባሏቸው የውጭ ኃይሎች ጫና ምክንያት ከአመራርነት በመገፋቴ ነው ብለዋል። ከመንግስት ወታደራዊ ኃይሎች እና ለጊዜው ስማቸውን መጥቀስ ከማይፈልጉ ታጣቂዎችተደጋጋሚ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው እንደነበር የተናገሩት አቶ እስክንድር ኢትዮጵያ ውስጥ ከሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ወደ ትጥቅ ትግል በመግባታቸው ግን እንደማይቆጩ ተናግረዋል ። አቶ እስክንድር ነጋ ከጋዜጠኝነት ፣ እስከ ሰላማዊ የፖለቲካ መሪነት የደረሱ ፣ በተደጋጋሚ ለእስራት የተዳረጉ በኋላም የትጥቅ ትግል ለማድረግ ጫካ መግባታቸውን ይናገራሉ ።  @Addis_News @Addis_News
2 334