en
Feedback
Hasen Injamo

Hasen Injamo

Open in Telegram

Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Hasen Injamo

Channel Hasen Injamo (@haseniye) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 838 subscribers, ranking 8 214 in the Economy & Finance category and 2 277 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 838 subscribers.

According to the latest data from 07 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 97 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.47%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.98% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 779 views. Within the first day, a publication typically gains 2 074 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 43.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Economy & Finance category.

14 838
Subscribers
-324 hours
+137 days
+9730 days
Posts Archive
በትምህርት ብቻ የምታገኛቸው ብዙ ነገሮች እንዳሉ ግልጥ ነው:: ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር (PLC) አብላጫ ድምጽ 50 ሲደመር አንድ ወይም 51% ነው:: በአክሲዮን ማኅበር (S.C.) ግን የዚህ ግልባጭ ነው:: የአክሲዮን ማኅበር አብላጫ ድምጽ ከ20% እስከ 30% ቲሆን 70 እና 80 ፐርሰንት ግን አናሳ ድምጽ ነው:: በዓረብኛ ግራመር ብዙ ቁጥር ሴቴ ጾታ ነው ያለው:: <<ኩለ ጀምዒን ሙአነሱ>> እንደማለት:: ከአክሲዮን አባላቱ ውስጥ 20% የሚግባቡ አባላት ካሉ እንዳሻቸው ማሾር ይችላሉ:: 80% አይስማማም:: ለመስማማት ቢሞክር እንኳ አስተባባሪዎቹ ይጠለፋሉ:: በብዛት ቢሆን ኖሮ የዓለም አጧዥ ቻይኖችና ሕንዶች ይሆኑ ነበር:: ጥንጥዬ አይ^ሁድ ቋጥረው ይፈቱታል:: አምላክም አንድ ስለሆነ ያወዛግባል እንጂ አይወዛገብም:: ትንሽ የሚገ^ድል ሰው ወንጀለኛ ተብሎ ይታሠራል:: ብዙ ሲገ^ድል ግን ፕሬዝዳንት ይሆናል:: ኢትዮጵያ ውስጥ ቢዝነስም በግል ወጥሩ:: የመን^ጋ ፋራ ቁጠባ አለላችሁ:: ሕንጻ ካላችሁ ለባንክ ብራንች አከራዩት:: የምእመኑ ኪስ እናተ ፎቅ ስር ነው:: የሕንጻውን ደህንነት ባንኩና መንግሥት ይጠብቁታል:: በዚህ ምክር ብዙ ወንድሞች ተጠቅመዋል::

ከአክሲዮን ገበያ ሼር እንግዛ ወይ? ================= ያው የባንኮች አክሲዮን ነው ያለው:: ኮርፖሬት ቢዝነስ ላይ ገና ነን:: አሁን ላይ የአክሲዮን ጉሊት ስለመጣ እጃችሁ ላይ ያለውን ሼር በቀላሉ መሸጥ ትችሉ ይሆናል:: ትንሽዬ መሻሻል አለ:: ድሮ the most illiquid asset ወይም ወደ ገንዘብ ለመከርበት የሚሸግር ንብረት ቢኖር ሼር ነበር:: አሁንም ቢሆን በትርፍ ብር ብቻ ነው መጫወት ያለባችሁ:: ትርፍ ብር ከየት መጥቶ ትሉ ይሆናል:: ያው አክሲዮን የኳድራንት four 4️⃣ ኢንቨስተሮች ጨዋታ ነች:: በፊትም አዲስ አክሲዮን ላይ ካልገባን ብላችሁ ስትንገበገቡ .. አይዟችሁ, አትቸኩሉ, አምስት ዓመት ጠብቁዋቸው ያልኳችሁን አስታውሱ:: ያኔ ያመልጠኛል ብላችሁ የተንገበገባችሁ ለመቆጨት ወራትም አልፈጀባችሁ:: የዛሬ ስምንት ዓመት መቋቋም የጀመሩ ባንኮች እስከዛሬም ዲቪደንድ መክፈል አልጀመሩም:: የሚያመሰግኑኝ ይኖራሉ:: ያንን ብር ብትሸቅሉበት ኖሮ ከአክሲዮኑ ምንም አያመልጣችሁም ነበር:: አሁን ደረሳችሁበት:: << ፕሪሚየማቸው ከፍተኛ የሆኑና አስተማማኝ የሚባሉት እንኳ ልዩነቱ ማለትም ለፕሪሚየም የከፈላችሁትን ለማካካስ እስከ አራትና አምስ ዓመት ይወስድባችሗል:: ዝቅተኛ ፕሪሚየም ኖሮኣቸው "ምንም አይልም" የሚል ዲቪደንድ ያላቸው የተሻሉ የሚሆንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉዋቸው:: አንዱ Divided Yield ይባላል>>:: ይህንን ከዕለታት ባንዱ ምሽት በሰፊው አብራራላችሗለሁ:: ለአሁን በአጭሩ ለማስረዳት ዋጋው 10 ሚሊዮን ብር የሆነ ቤት ወርሃዊ ኪራዩ 25 ሺህ ብር ሆኖ የ20 ሚሊዮን ብር ቤት ደግሞ ወርሃዊ ኪራዩ 35 ሺህ ብር ቢሆን የቱን ትመርጡ ነበር? ያለ ጥርጥር የመጀመሪያውን ነው:: በ20 ሚሊዮን ብር ሁለት ቤት ገዝታችሁ 50 ሺህ ማከራየት ትችላላችሁ:: ላለማወሳሰብ ሌላ ሴናሪዮ አላካተትኩም:: አሁንም ቢሆን ጀማሪ አክሲዮን ላይ በፍጹም እንዳትሞክሩ:: ቢዝነሱን በደንብ የምታውቁት ብትሆኑ እንኳ በግላችሁ ከባንክ ጋር ሥሩ:: በእርግጥ አዲሶቹንም ኢንቨስትመንት ባንክ ይዞኣቸው ስለሚመጣ ለሀብታሞች ድንገተኛ ትርፍ ሊያስገኙ ይችሉ ይሆናል:: የቆዩና ጥሩ ትርፍ ያላቸው ሆነው በአክሲዮን ገበያ ላይ ለመሸጥ ቢመዘገቡም ባይመዘገቡም ትርፍ ብር ካላችሁ በስሱ ተሳተፉ:: በአክሲዮን ገበያ ላይ ለመሸጥ ሳይመዘገቡ ጥሩ የሆኑ ይኖራሉ:: በ OTC (Over the counter) ማለት ነው:: እንደ ነጋዴ ምላጭ ሁኑ:: ሲጠቃ-ለል አክሲዮን ላይ ኢንቨስት ሲደረግ profit ተኮር ሳይሆን wealth ተኮር ነው:: ሁለቱም ከተገኙ ዴግ!

አደገኛ ታክሶች -> መጥፎ የትዳር አጋር:- የሕይወት ዘመን አደገኛ ታክስ ብቻ ሳይሆን ሕይወትህን እኝክ አድርጎ በልቶ አሟሟትህንም ሊያበላሽ ይችላል:: ከማግባትህ በፊት እጅግ በጣም ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅብሃል:: እንደ ጨው ተቀምሶ ስለማይታይ ከገባህም በሗላ በጥንቃቄ ተከታተለው:: የማስተካከያ እርምጃ ውሰድ:: -> ፕሮካስትኔሽን:- ጊዜያዊ ምቾት መምረጥ, ፍጹም የሆነ ውጤት በመጠበቅ ወደ ትግበራ አለመግባት እና አክብዶ ማየትን ይይዛል:: የዘርፉ ሰዎች ቢያብራሩት እመርጣለሁ:: -> መጥፎ አስተዳደር:- በግለሰብ ደረጃ የማይሠሩ ነገሮችን እንዲያስተዳድር የተሰጠው አካል ከቆለፈህ ቆለፈህ ነው:: ዓይንህ እያየ ሕይወትህ ይበላል:: መታወቂያ እጅግ በጣም ርካሽ ግን እጅግ በጣም ውድ ዋጋ የሚያስከፍል ነው:: ፓስፖርት ተመሳሳይ ነው:: አንድን ጀግና ሊያከስሙ የሚችሉ በካሽ ሳይሆን ከሕይወት ላይ የሚከፈሉ ታክሶች ናቸው:: ሦስቱም በአንዴ ከያዙህ ካንተ በላይ ግብር የሚከፍል የለም::

ጋብሮቮው ቤቱን ሊከፍት ቁልፍ አውጥቶ ከእጁ ላይ ይወድቅበታል:: ከዚያ የመንገድ መብራቱ ጋር ወጥቶ ሲፈልግ ያገኘው ጓደኛው አብሮ እያፋለገው "... በትክክል እዚህ ጋር ነበር የወደቀብህ?" ብሎ ሲጠይቀው ... የወደቀውማ ጭለማው ጋር ነበር ግን እዚያ መብራት የለም አለው ይባላል:: የብዙ ችግሮቻችን መፍትሔ ፍለጋ እንደዚህ ነው:: ሳር ሳሩን እየረገጡ መሄድ, መብራት እና ጊዜያዊ ምቾት ያለበት ቦታ ብቻ ሄዶ መብለጭለጭ, ዘላቂ መፍትሔ ለሚያመጣ ትግል አለመዘጋጀት ነው:: ይህ የመንግሥትም የፋይናንስ ተቋማትም ዋነኛ ችግር ነው:: አንድ ሕንጻ ላይ አራት ባንክ ታገኛለህ:: ጸጉር ቤት እንኳ በዚህ ልክ የለም:: ደቡብ ኮሪያ ልሄድባችሁ ነው:: በጦ^ርነት ደቃ ማገገም አቃታት:: የካፒታሊዝም ምኞት ሊያሳድጋት አልቻለም:: ባንኮቿ ከተማ መሃል ችምችም ብለው ገጠሩን የሚያየው ጠፋ:: የምክር ቤት አባላትም የመረጣቸውን ሕዝብ ትተው መብራት ጋር ውለው ያድራሉ:: ስለዚህ መንግሥት የግል ኮርፖሬት ድርጅቶችን አከሰመና ወረሳቸው:: በመንግሥት ባንኮች በኩል ከወለድ ነጻ ብድር እና በልማት ባንኮች በኩል ማሽነሪዎችን ከጥሬ ዕቃ ጋር አቀረበ:: ቴክኒክና ሙያ ግዳጅ ሆነ:: ገጠር ለሚገቡ ለመንግሥት ባንኮች ወታደርና ፖሊስ ተመደበ:: ክተት ወደ ኢንደስትሪነት አወጀ:: ዛሬ እነዚያ ኢንደስትሪዎች ዓለምን ጉድ አሰኙት:: የአይፎን ሙሉ ግብዓት ሳምሰንግ ነው የሚያመርተው:: አይፎንም ያዝክ ሳምሰንግ አምራቹ አንድ ነው:: ልዩነቱ ሎጎ እና ጥራት:: በስ! ኢትዮጵያ ውስጥ በዚህ አያያዛችን እናሳዝናለን:: መንግሥት እራሱ በነጻ መፍጠር በሚችለውን ባዶ ቁጥር በታክስ መልክ ሰብስቦት የሚያድግ መስሎት ይሯሯጣል:: ባዶ ቁጥሩን ተውት ብንል እንኳ ኢኮኖሚክስ ተምሬያለሁ የሚሉ ሁሉ በምዕራብ አለቆች መጽሓፍ ደንዝዟል:: አሜሪካ ባደገችበት ባ^ሪያዎችም የሚያድጉ ይመስላቸዋል:: መቶ ብር ውስጥ ያለው ብልጭልጭ ስትራይፕ ወርቅ ይመስለው የነበረ ማስተርስ የያዘ ሰው ገጥሞኛል:: መንግሥት አራት አትሌቶች ሊሠሩት የሚችሉትን ሪዞርት በመገንባት እራሱን ፋንታሳይዝ ያደርጋል:: የግል ባንኮች ገጠር ሊገቡና ከዋነኛ አምራች ጋር ሊሠሩ ቀርቶ ወታደር እንኳ ደፍሮ የማይገባባቸው በርካታ ቦታዎች አሉን:: ባንኩም የመንግሥት ኃላፊውም እዚሁ መብራት ስር ሽር ብትን ይላሉ:: የግል ባንክ ገጠር ግባ ብትለው ሰኪዩሪቲ አይሰማውም:: ቢገባ ደግሞ ፎርማቱ Commercial ስለሆነ ገጠር ብታስገባው ግሽበት ይዞብህ ይገባል:: ወላሂ መታሰር ያለባቸው እኮ ብዙ ኃላፊዎች አሉን:: ትንሽ ቀዳዳ ባገኝ የማስራቸው ኃላፊዎችና ፕሮፌሰሮች ብዛታቸው:: ለፍርድ አላቀርባቸውም:: ለጊዜው ዳኛው እራሴው ነበርኩ የምሆነው:: እያንዳንዱን ፕሮፌሰርና ዶክተር የእስር ጊዜውን እራሱ ነው የሚወስነው:: በተማረበት ፊልድ መፍትሔ እንዲያመጣ ትቆልፍበታለህ:: ውለድ ነው የምትለው:: ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተምሮ የቤቱን ኤሌክትሪክ እንኳ የማይዘረጋ ሰው ስለ EV ሊሠራልህ አይችልም:: ይህ በኤሌክትሪክ ሽቦ መገ^ረፍ ነው ያለበት:: በዶክትሬት ተመርቆ ርቦኛል ይላል:: ቂ^ጡን በመርፌ ሳይሆን በመድፌ እየወጋህ ዚምባብዌ መሸኘት ነበር::

መ-ገንዘብ 3 ለታዳጊዎች coming soon 🔜 ወይ ሞባይል ጌም ወይ ሰኞ ማክሰኞ ላልተጫወተ ሰው ሊከብድ ይችላል:: ሰኞ ማክሰኞ ጨዋታ ደንበኛ ፊውዶ ካፒታሊዝም ሥርዓት ነው:: አንድ ጎበዝ ተጫዋች
መ-ገንዘብ 3 ለታዳጊዎች coming soon 🔜 ወይ ሞባይል ጌም ወይ ሰኞ ማክሰኞ ላልተጫወተ ሰው ሊከብድ ይችላል:: ሰኞ ማክሰኞ ጨዋታ ደንበኛ ፊውዶ ካፒታሊዝም ሥርዓት ነው:: አንድ ጎበዝ ተጫዋች ብዙ ቤት ከገዛ ሌሎች ተጫዋቾች አይችሉትም:: ስለዚህ ጨዋታው ይፈርሳል ማለትም ሲስተሙ ይወድቃል:: ስለዚህ ጎበዙ ተጫዋች ቤት ያከራያል:: ክፍያ እንደየሰፈሩ በኩር^ኩም, በእዝዝሎሽ ወይም በቆርኪ ይሆናል:: ከዚያ ፍልሚያው ይቀጥላል:: ይህንን ምሳሌ አድርጋችሁ ፔፐር መሥራት ትችላላችሁ:: Coming soon 🔜

"ሸቀጣዊ ገንዘብ" የሚለው ቃል Commodity Money ለሚለው ቃል ትርጉም ሆኖ በመ-ገንዘብ 2 ጥቅም ላይ የዋለ ነው:: በባለፉት ሦስቱ መጽሐፎቼ የእንግሊዝኛውን Commodity Money ቀለል ባለ አማርኛ ቃል ወይም ሐረግ ለመተካት ብዙ ተቸግሬ ነበር:: ይህኛው ገላጭ ሆኖ አግኝቼ ተጠቀሜዋለሁ::

ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ አለ:: አልተነካም:: ወጣት ሠራተኛም ሞልቷል:: ግን የሚያሠራ ሥርዓት አለ ማለት አይቻልም:: ችግሩ ሥራም ሠራተኛም ሳይሆን ሥራ አስኪያጅ ይመስለኛል:: ቅጣት, መዋጮ እና ግብር
ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ አለ:: አልተነካም:: ወጣት ሠራተኛም ሞልቷል:: ግን የሚያሠራ ሥርዓት አለ ማለት አይቻልም:: ችግሩ ሥራም ሠራተኛም ሳይሆን ሥራ አስኪያጅ ይመስለኛል:: ቅጣት, መዋጮ እና ግብር ሲበዛ ሥራው አስኪያጁ ጉ^ቦ ይሆናል:: ፎቅ የሠራ ሰው ለንብረቱ ዋስትና እየሰጋ ባለበት ወቅት ወጣቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆኖ ስለመሻሻል አያስብም:: በ5,200 ብር ምክንያት የባንክ አካውንት የታገደበት ሰው አለ:: በአስር ሺህ ብር እና በሀያ ሺህ ብር የግብር ተመን እና ክፈል/አልከፍልም ምክንያት ሠራተኛ ሁለት ዓመት ሥራ ይፈታል:: በሥራ መጥመድ የነበረብንን ወጣት በ10 ሺህ ብር የመዋጮ ወይም ግብር ተመን ሥራ ሲፈታ በሚፈጥረው ወን^ጀል ምክንያት በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ሥራ ያስፈታል:: ያንን ወጣት ማሰር, ፍርድ ቤት ማመላለስ, እስር ቤት ውስጥ መቀለብ, የሥራ ዓመታት መባከን ወዘተ:: ለእኔ ትልቁ ግብር ከፋይነት በሥራ ቢዚ ተኹኖ ያለወንጀል መኖር እና ፖሊስ አለመፈለግ ነው:: የሆኑ ፍሬንዶች ፎቅ መሥራት ፈልገው ኢትዮጵያ ውስጥ ይሻላል ወይስ ኢሚሬትስ በሚለው ተወዛግበው እኔ ጋር መጡ:: ኢሚሬት ላይ ሥሩትና እንደ አክሱም ሐውልት ቆራ^ርጠን ጭነን እናመጣዋለን አልኳቸው:: ይህንን ስል ኢትዮጵያ ውስጥ ዲቪ ካልሞሉ ሰዎች አንዱ ነኝ:: የምሳፈረው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው:: ET ከሌለ ብቻ ነው በሌላ የምሳፈረው:: የውጭ ሀገር አብዛኛው ቆይታዬ 10 ቀናት ቢበዛም ወር ነው:: Rare case ነው የምቆየው:: ከመሆኑም ጋር ኢትዮጵያ ላይ የሚያሠራ environment ነው የታጣው::

👆🏾👆🏾👆🏾 ጽሑፉ ከላይ አለ
👆🏾👆🏾👆🏾 ጽሑፉ ከላይ አለ

ሕዝቡ በሁለት የኑሮ መደብ ማለትም በጥቂት ካፒታሊስት እና በነፍ ደሃ መሃል የሚከፍለው የፋይናንስ ሥርዓቱ ነው:: ሚሊዮኖች ይቆጥባሉ:: አስሮች ወስደው ይሠሩበታል:: መንግሥት ምንም ሊያደርግ አይችልም:: መካከለኛ ገቢ ያለው ሕዝብ ልፍጠር ካለ ከካፒታሊስት የፋይናንስ ሥርዓት መውጣት የግድ ይለዋል:: ገና ሳይጀምረው ሥልጣኑን ያጣል:: ስለዚህ ፈረንጆቹ በሚያሰምሩለት መስመር ይሄዳል:: ማናችሁም ሥልጣን ብታገኙ የተለየ አትሠሩም:: ወደ 1% ነዋሪ መግባት እና ወደ 99% አኗኗሪ ውስጥ መሆን የምትወስኑት እራሳችሁ ናችሁ:: ካላመናችሁኝ እንዴት ደሃ እንደምትሆኑ ላስረዳችሁ:- -> ዶክትሬት ዲግሪ ለመያዝ ሚሊዮን ብር እና ከ25 እስከ 40 ዓመት ወስዶባቹሗል:: ባንክ ብትወስዱት ግን የባጃጅ ሊብሬ ወይም የኩሽና ካርታ ያህል ዋጋ የለውም:: ስትሞቱም አብሮኣችሁ ይሞታል:: ለምስጦቹ ዋጋ ይኑረው አይኑረው የምስጦቹን DNA 🧬 ስካን አድርገን እንመረምረዋለን:: ከአንገት በላይ ቆ^ርጣችሁ ለልጆች ማውረስ አትችሉም:: የባሰ አለላችሁ:: ላስተምርበት ብትሉም ደመወዝ ነው:: 88% ይቆረጣል:: ላማክርበት ብትሉም የ30 ዓመት ወጪ እይያዝላችሁም:: በቀላል ምሳሌ በ90 ሺህ ብር ተመርቶ በመቶ ሺህ የተሸጠ እቃ ግብር የሚጠየቀው በአስር ሺህ ብር ብቻ ሲሆን ... ምሁሩ የመቶ ሺህ ብር ቢያማክር ወይም ቢያሰለጥን ግብር የሚጠየቀው በሙሉ ሒሳብ በመቶ ሺህ ብሩ ነው:: እናንተ የሆነ ኖርማል ኑሮ ኖራችሁ ክልት^ው ስትሉ ምንም ነገር ያልተያዘለት እከካ^ም ልጅ ጥላችሁ ትሄዳላችሁ:: ወደ ሲስተሙ ለመቀላቀል ስንት ዓመት እንደሚፈጅበት በራሳችሁ ኑሮ ገምቱት:: ይህንን እንዳነበባችሁ አቅጣጫ ወስኑ:: ተስፋ ላስቆርጣችሁ ሳይሆን what’s going on የሚለውን ለማመልከት ነው:: ምን ዓይነት ሚስት/ባል መምረጥ እንዳለባችሁ እና ጸሎት ማድረግ አለባችሁ ወይስ የለባችሁም የሚለውን በሌላ ወቅት እንነጋገራለን::

መንግሥት የማያልቅ ብር እጁ ላይ አለ ማለት እያፈሰ ቢደፋው ሀብታም እንሆናለን ብሎ የሚያስብ የዋሕ አይኖርም:: እድገት በባንክ ቦኖ አይደለም:: እድገት በምርት ነው:: አስር ሰዎች ኖረው 10 ብርጭቆ ሻይ ቢፈላላቸውና ለማከፋፈል አስርም ቦኖ ቢታተም አንድ ሺህ ቦኖ ቢታተም በሻዩ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም:: አንዱን ሻይ በአንድ ቦኖም ቢገዙት በመቶ ቦኖም ቢገዙት ያው ነው:: ግሽበት የሚፈጠረው ሌላ ሻይ ሳይፈላ የሰዎቹ ቁጥር ሲጨምር ነው:: ለዚህም ነው ብዙ ታክስ መሰብሰብ ገቢ አይሆንም:: ብዙ ብር ማተምም አለማተምም ምርት አይደለም የምለው:: አሁንስ ተግባባን?

መ-ገንዘብ 3 ለታዳጊዎች ምን ይዟል? የሆነ ትርፍ አግኝቶ ብሩ እስኪጠፋ የሚዝናና የዘንዶ ባሕሪይ ተጠናውቶታል::
መ-ገንዘብ 3 ለታዳጊዎች ምን ይዟል? የሆነ ትርፍ አግኝቶ ብሩ እስኪጠፋ የሚዝናና የዘንዶ ባሕሪይ ተጠናውቶታል::

ሴልሶችን አሠማርተው በገፍ ሲሸጡ የነበሩ ሪል ኢስቴት አልሚዎች ብር አጥብቆ ለጠየቃቸው እየመለሱ ናቸው:: ምክንያቱም ቤቱን ከመገንባት ብሩን መመለስ ያዋጣቸዋል:: ከወለድ ነጻ ሸቅለውበት, ቫት, ውል ማፍረሻ, የአስተዳደር ወጪዎች, ኮሚሽን ቆርጠው መመለስ የትም ያልተበላበት ቢዝነስ ነው:: ምእመኑም የ15 ሚሊዮን ብር ቤት በአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሊበላ ነበር:: ወንድሜ የትም የሆነ አጓጊ ትርፍ ካየህ ... ትልቅዬ ገደል አለ:: ላስፈራራ ሳይሆን ቀብድ ከመክፈላችሁ በፊት አረጋግጡ:: አሁን ላይ ትልቅ ለውጥ መጥቷል:: እንደ ድሮ ዘሎ መክፈል እየቀነሰ ነው::

የአንድ ሀገር መንግሥት በምንም ፎርሙላ የሀገሩን ገንዘብ ሊቸግረው አይችልም:: Never! በፍጹም:: መንግሥት ገንዘብ ከቸገረው እኔን ያናግረኝ:: ቀልድ ሊመስላችሁ ይችላል:: ሙሉ የገንዘብ ካዝና ፈርመህ የሰጠኸው ሰው ማደል ካልቻለ ንግሥና አልታደለም:: ገንዘብ unlimited resource ተደርጓል:: ብትዘግነው አያልቅም:: ብትሰበስበውም አይሰበሰብም:: ቢታተምም ባዶ ቁጥር:: ባይታተምም ባዶ ቁጥር:: መንግሥት ከሆንክ እኮ ገንዘብ ሁን ትለዋለህ:: ቢሊዮን, ትሪሊዮን በጀት ይሆናል:: ችግሩ ገንዘብ አይደለም:: አስተሳሰብ ነው:: ትሪሊዮን ብር ብታትም ዋጋው ትንሽዬ ትሪ አይሞላም:: ከሰው አካውንት ብትሰበስበው በሚዳቆ ቀንድ አይሰፈርም:: It is a claim ticket 🎟️ (ቦኖ ነው):: ሀገር በቦኖ ብዛት አያድግም:: ገንዘብ ብለን ቦታ የሰጠነው ነገር የአየር ያህል ቦታ አይዝም:: በኮምፒውተሮች ሰርቨሮች ውስጥ የሚደንስ ኤሌክትሮን ወይም ከዚያ በታች ነው:: ስለዚህ ትክክለኛ ገንዘብ ላብ ወይም እንቅስቃሴ በመሆኑ ሰዎችን እየገረፉም እያሰለጠኑም ለሥራ ማንቀሳቀስ የግድ ነው:: መንግሥት በገንዘብ ካሳበበ መቼም አያሳድግህም:: ተሰደድ::

ሾፌርም እግረኛም ሐኪም ቤትን ቢጎበኙ ============== አሁን አለርት ሆስፒታል ነበርኩ:: አንድ የቤተሰብ ሕጻን ልጅ ትናንትና እግሩን መኪና ገጭቶት እየታከመ ዛሬ ልጠይቅ ሄጄ ለቅሶው ሲረብሸኝ ወጣሁ:: ተመልሼ መሪ እይዛለሁ አላልኩም ነበር:: በእርግጥ ከ20 ዓመታት በላይ መኪና ይዤ አደጋ አድርሼም ደርሶብኝም አላውቅም:: መብራት ላይ ከሗላ ተራ ኩርኩሞች አይጠፉም:: እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ሆኜ እየነዳሁ እንቅልፍ ከተጫጫነኝ ዳገት ላይ ጥላ ቦታ ፈልጌ ናፕ አደርጋለሁ:: ቁልቁለት ጋር ከቆምኩ ፍሬን የጣለ እንዳይወጣብኝ ነው:: ኦሪጅናል ነፍስ ይዤ ጭራሽ ቤተሰብ የምጭንበትን መኪና ስፔር በፍጹም ሎካል አልጠቀምም:: ሹፍርና 360 ዲግሪ ነው:: በ50 እየነዳህ ፍጥነትህ በ300 እንደሆነ አትዘንጋ:: ምክንያቱም በስድስቱም አቅጣጫ አደጋ አምጭ ነገር ሊኖር ይችላል:: በ4 አቅጣጫ የሚመጣ በ50 አብዛው:: 200 ኪሎሜትር በሰዓት ይሆናል:: ከከፍታ ቦታ የሚወድቅ ወይም የሚንከባለል, ኩርባ ላይ የሚቀነጠስ ተሳቢ, ዳገት ላይ የሚንሸራተት ኮንቴይነር ወይም የአጠና ጭነት, ከስር የሚቆረጥ ድልድይ ወይም የሚንሸራተት ገደል ሊገጥም ይችላል:: ከተማ ውስጥ ሁሌ 300 ኪሜ/በሰዓት እንደሆነ ማሰብ የግድ ይላል:: ከከተማ ውጭ በፍጥነትህ አብዛው:: በ80 እየነዳህ ነው ማለት 500 ኪሎሜትር ላይ ነህ:: እና ገና አንድ ፍሬ ጩጬ ልጅ አጥንቶቹ ተሰብረው ስጋው ተቦጭቆ, ገና የአጥንት ሕክምና ላይ ሲሆን ገጪ እስር ቤት, ቤተሰቦቹና ቤተሰባችን ሐኪም ቤት:: ሕጻኑ በለቅሶ ዓይኑ አብጦ ሲያላውሰኝ ወጣሁ:: አለርት emergency 🚨 7 ቁጥር ላይ:: ሕክምና ምን ያህል ክቡር ሥራ እንደሆነ ሆስፒታል ሄዶ ማየት ነው:: ሐኪሞችን አመሰግናለሁ:: ይህንን የምታነቡ ሐኪሞች ሕጻን ሙሐመድ ሳላህን ተንከባከቡትማ!

ፋይናንሻል ሲስተሙ ጨካኝ ነው:: ይዞ የተገኘ እንዲድን ተደርጎ ተዋቅሯል:: ሀብታም ደብ^ዳቢ እና ደሃ ተደብ^ዳቢ ለፍርድ ቢቀርቡ ፍርዱ ግልጽ ነው:: ባልናገረውም ታውቁታላችሁ:: እግር ዘርግታችሁ ተቀምጣችሁ ከጠበቃችሁት ኃይማኖታዊ እምነታችሁ ወይም ባሕላዊ ማንነታችሁ አይቋቋመውም:: እያያችሁት ትፈርሳላችሁ:: ሒጃብና ጺም መስቀልና ማእተብ አያድናችሁም:: ለብር ብላ ሂጃቧን ላለማውለቅ ወይም ከእነመስቀሏ ላለመባለግ ትንሽ ቀናት ብትታገል ነው:: ብር የሚያመጣ ከሆነ ሳታወልቃቸው ልትሸጣቸው ትችላለች:: ጺሙን ላለመላጨት ትንሽ ጊዜ ቢታገል ነው:: ቁርኣን ቢሃፍዝ እንኳ አይችለውም:: ቁርኣኑን እያየው ከልቡ ውስጥ ትቶት እየወጣ አቅም አንሶት ያለቅስ ይሆናል:: ይህንን የምጽፍላችሁ ላስጨንቃችሁ ወይም አጉል መካሪ ለመሆን አይደለም:: እየኖርንበት ያለነው ሲስተም ምን ያህል ከባድ እንደሆነ እኔም ዘግይቼ ነው የገባኝ:: ከ40ና 50 ዓመታት በፊት የገባቸው ሰዎች ለልጆቻቸው ተዘጋጅተውላቸዋል:: ዘና ብለው ሲኖሩና የሆነ የሚያስብላቸው ሰው ወይም መንግሥት ያለ ይመስላቸው የነበሩ ሰዎች ግን በልጆቻቸው ዕድሜ ቀልደዋል:: ዛሬ እነዚያ ልጆች እየኖሩ ያሉት የሕይወት ትግል በቃላት ለመግለጽ አይመችም:: ሲስተሙ ማስያዣ ፈልጓል:: ቤት ያልያዝክለት ልጅ ከሲስተሙ በ50% አርቀኸዋል:: ከተመሳሳይ ቤት ካገባና ልጆች ከደራረበ አረንቋ ውስጥ ወድቋል:: ተሰዶ እንኳ ወደ ሲስተሙ መቀላቀል አይችልም:: ስለዚህ ቆም ብላችሁ አስቡ:: የሲስተሙ ሪኳየርመንት ካጠናችሁ በአስር ዓመት ልትቀላቀሉ ትችላላችሁ::

ኪሴ ባዶ:- ሲሆን ጸጉሬን ተከርክሜው የተንጨባረረ, አዲስ ጫማ አድርጌ የተንሻፈፈ, ጥሩ መኪና ይዤ እየገፋሁ የምሄድ ይመስለኛል:: ብር ሞላ ያለ ጊዜ ጸጉሬ ተንጨባሮ የተከረከመ, ሁለት የግራ አድርጌ ቢሆን እንኳ አዲስ ብራንድ ጫማ ያደረግሁ, ድክሞ መኪና ይዤ በትእዛዝ የተሰራ ኒች መኪና ይመስለኛል:: መኪና ያለኝ ወቅት ከኃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ቦሌ ድልድይ በእግሬ ሄጃለሁ:: ምንም አልደከመኝም:: መኪና የሌለኝ ወቅት ግን ለማኪያቶ ቅርብ ካፌ መሄድ እንኳ ይደክመኛል:: ዓለምን የሚቀይር ብልሃት የመጣልኝ ወቅት ኬሻ ላይ ቁጭ ብዬ እሠራለሁ:: ምግብ ትዝ አይለኝም:: እራሴን ለመቀየር ብልሃት የጠፋኝ ወቅት በቁርስና በምሳ መሃል መክሰስ መብላት ያምረኛል:: ይህንን ነገር ብዙ ሰዎች ላይ አየሁት:: ለመታየት መከራቸውን የሚበሉ, ውድ ውድ ነገሮችን የሚገዙ ሰዎች ውስጣቸው ላይ የሚታገላቸውና የሚያሯሩጣቸውን ነገር ለማሸነፍ የሚታገሉ እንደሆኑ ነው:: ውስጡ ያለው ረብሻ በዝነጣ ለመሸፈን ይታገላል:: መዘነጥ መልበስ ጥሩ ነው:: ከውስጡ ጋር ትግል የገጠመ ሰው ዝነጣና ታይታ ግን ያስታውቃል:: መሠረታዊ ፍላጎቶቻችንን ብናሟላ አስተሳሰባችን ሁላ ይቀየር ነበር:: ጸቦቻችን ሁሉ ማለት ይቻላል ከለት ጉርስና መሠረታዊ ፍላጎት ጋር የተያያዙ ናቸው:: መኖሪያ ቤት ማግኘት እንደ ሰማይ እያዩት የራቀ ጉዳይ ነው:: እድር እና በራስ ቤት መታወቂያ ማውጣት የሀገሪቷን ግሪን ካርድ እንደ መያዝ ነው:: ሀገር ውስጥ ሆኖ ሀገር የራቀው እልፍ አዕላፍ ምእመን አለ::

በዚህ ዘመን ስለአምላክም ስለጣዖትም በቀላሉ ለማስረዳት ከገንዘብ የተሻለ ምሳሌ ማግኘት ይከብዳል:: ፈጣሪ አይታይም, አይዳሰስም, አይቀመስም ግን ሁሉንም ነገር ይገዛል:: የኃይማኖት መሪዎች የተለያዩ ምስሎች ቀርጸው ያመልኩታል:: በኪሳቸው ይዘውት ይዞራሉ:: ገንዘብም አይታይም, አይዳሰስም, አይቀመስም:: ግን ሁሉንም ነገር ይገዛል:: የሀገር መሪዎች የተለያዩ ስዕሎች እየሳሉ ለሕዝቡ ሰጥተው በኪሳቸው ይዘውት ይዞራሉ:: ይንከባከቡታል:: በዚህ ዘመን ትልቅዬ ጣዖት የቤንጃሚን ፍራንክሊን ፎቶ ነው:: ፈጣሪን በትክክል define ካላደረግህ የባከነ ሕይወት እንደ ምትመራው ሁሉ ገንዘብንም በትክክል define ካላደረግህ የባከነ ሕይወት ትኖራለህ:: ይህንን በትክክል define ካላደረገ ሰው ጋር መቼም አትግባባም::

ትምህርት ቤት ጎበዝ ተማሪ ሥራና ሕይወት ላይ የማይሳካለት ትምህርት ቤት ውስጥ አይኮርጅም:: አያስኮርጅም:: ክልክል ነው:: ሥራና ሕይወት ላይ ግን ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በመኮረጅና በማስኮረጅ ነው የምትኖረው:: ኩረጃ በትምህርት ቤት chea^ting ሲባል ሕይወት ላይ ግን cooperation ነው:: ጎበዝ ተማሪ ሆኖ ወጥቶ ሳለ መጠየቅ ያፍራል:: አታውቅም የሚባል ይመስለዋል:: ለዚያም ነው በንግድም በሌላ ሥራም የሚወድቀው:: ስለዚህ ዩኒቨርሲቲ ደሴት ውስጥ ሳትኮርጁ በአሪፍ ውጤት የተመረቃችሁ Welcome to the land of the masses of ኩረጃ!

ቻይና ለመጓዝ ቪዛ የምትጠይቁ ሚመናን በኢ ^ቦላ ምክንያት የአፍሪካ ቪዛዎች ያዝ እየተደረጉ ናቸው:: ፕሮግራማችሁ ላይ ይህንን ከግምት አስገቡ:: ከመደበኛው 10 ቀን እየቆየ ነው:: መልካም ጉዞ!

አሜሪካ ሙ^ስሊሙን ነው በቦ^ምብ የምት^ፈጀው:: ያው ትምህርት ሀራም ነው ብለህ ምርምርን ትተህ ዝም ሊሉህ ነው? የተማረ ማይምን ሁሌ ይወቅጣል:: ያለና የሚኖር ነው:: ወቀጣው ሙስሊም ስለሆንክ አይደለም:: ማይም ስለሆንክ ብቻ ነው:: ምክንያቱም የዕውቀት ደረጃህ ወቀጣውን የመከላከል አቅም የለውም:: በቀላል ምሳሌ:- አልአሙዲ ዳሽን ባንክን ሲከፍት ሙስሊሙ ሆዬ አልአሙዲ የነካውን ነገር ሁሉ ውሻ የነካው አድርጎ ገጀረ:: ፍልውሐ መስጂድን በሸራተን ጥራት ልሥራው ሲል "አትነጅሰን" ተባለ:: በሗላ ግን ለመጅሊስ ግልበጣ የት ተመረጠ? ሸራተን:: ፍልውሐና ሌሎች መስጂዶችም ጭምር የሚሠራው ማን ሆነ? አልአሙዲ:: ምንድነው ልዩነቱ ካልክ ምእመኑን ድህነት ወቅጦ አሳምኖት ነው:: ድህነት ያሳምናል:: የጌሙ ፕሮግራመር ካልሆንክ የነጻ ርካሽ ጌም ፍለጋ ትባዝናለህ:: አንዳንዱ ስለወለድ እኔን ሊያስጠነቅቅ ሲመጣ እስቅና እቦልከዋለሁ:: ምንም የሚያውቀው ነገር ስለሌለው ችግር እስኪያሳውቀው ትተወዋለህ:: ዞሮ መጥቶ በተማሪ አደብ "ሀጂ እስቲ አስረዳኝ" ይላል:: አንዳንድ ኃይማኖተኛ ባይ የባንክ ብድር-ተራ ማን አድርሶት? ባንኮች ለደሃ አያበድሩም እኮ:: በፍጹም:: አበድሩኝ ስትላቸው እስቲ የንግድህን ትርፍና ቤትህን አሳየን ይሉሃል:: በቃ ትጠፋለህ:: ሲስተሙን ሲዘረጉት ሸሽተህ እና እግርህን ዘርግተህ በቦ^ምብ ሲፈጁህ "ዋ ኢስላማ" ትላለህ:: እዚህ ጋር የምጽፈውን ነገር በታላቅ ስነሥርዓት አንብብ:: ተወያይ:: ጻፍ:: አሠራጭ:: ንቃ:: አንቃ::