Hasen Injamo
前往频道在 Telegram
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye
显示更多📈 Telegram 频道 Hasen Injamo 的分析概览
频道 Hasen Injamo (@haseniye) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 890 名订阅者,在 经济与金融 类别中位列第 8 340,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 280 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 890 名订阅者。
根据 29 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 81,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.15%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.62% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 748 次浏览,首日通常累积 2 030 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 36。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው::
https://telega.io/c/Haseniye”
凭借高频更新(最新数据采集于 30 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 经济与金融 类别中的关键影响点。
14 890
订阅者
无数据24 小时
+207 天
+8130 天
帖子存档
14 890
በ $1 ዶላርና በኢትዮጵያ ብር መካከል ያለው ልዩነት 170 ብር ነው ካልክ የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ላይ ነህ::
99 ዜሮዎች ያሉት ዱዎህትራይጂንቲሊዮን የኢትዮጵያ ብር ምንዛሪው ዜሮ ዶላር ነው::
14 890
መንግሥት እራሱ ብር እያተመ ለምን መልሶ ታክስ ስጡኝ ይላል?
-> ሕዝቡ መንግሥትም ይቸግረዋል ብሎ እንዲያስብ
-> ታክስ የሚከፈለው መንግሥት ባተመው ብር ስለሆነ ያንን ለማግኘት ምእመኑ እንዲለፋ
-> እንዳያምጽ አቅሙን ለማሳጣት
-> የንግድ ሥራ ላይ ያልሆኑ ወታደሮች ውት^ድርናውን ትተው ወደ ንግድ እንዳይሄዱ
እያየሁ እጨምራለሁ
14 890
መ-ገንዘብ መጽሓፍ ቅድመ ሕትመት ዋጋ
- የታዳጊዎች 825 ብር
- የአዋቂዎች 900 ብር
- ሁለቱን የምትፈልጉ 1,725 ብር
ዋጋው በመላ ኢትዮጵያ በፖስታ ቤት ማድረሻን ይጨምራል::
CBE
1000632718245
IZZELISLAM ABDULKADIR
ስክሪንሹት, ስም, ስልክ, አድራሻ (ለምሳሌ ቡታጅራ, ሰመራ, እንጅባራ, ሳሪስ, ጨርቆስ)
ቴሌግራሙ ውስጥ ከዚህ ውጭ ምንም ዓይነት መልእክትም ይሁን ጥያቄ ባለመጠየቅ አግዙን::
https://t.me/MeGenzeb
14 890
ለባንክ ብድር የምትጠይቁ ምእመናን ሁሉ:- የሠራተኞች ጡረታ ውዝፉ 5 ብር ቢሆን እንኳ ከፍላችሁ ሳትጨርሱ ክሊራንስ ላታገኙ ትችላላችሁ:: ማጣሪያው ወደሗላ 10 ዓመት ማለትም እስከ 2007 ድረስ ሊሄድ ይችላል:: ስለዚህ ይህንን ከግምት ያስገባ እንቅስቃሴ አድርጉ::
14 890
+2
መ-ገንዘብ 3 ለታዳጊዎች በከለር ነው የተዘጋጀው:: የአዋቂዎች ላልገባችሁ ወይም አይገባንም ብላችሁ ለሰጋችሁ ጥሩ ይመስለኛል::
መ-ገንዘብ መጽሓፍ ቅድመ ሕትመት ዋጋ
- የታዳጊዎች 825 ብር
- የአዋቂዎች 900 ብር
- ሁለቱን የምትፈልጉ 1,725 ብር
ዋጋው በመላ ኢትዮጵያ በፖስታ ቤት ማድረሻን ይጨምራል::
CBE
1000632718245
IZZELISLAM ABDULKADIR
ስክሪንሹት, ስም, ስልክ, አድራሻ (ለምሳሌ ቡታጅራ, ሰመራ, እንጅባራ, ሳሪስ, ጨርቆስ)
ቴሌግራሙ ውስጥ ከዚህ ውጭ ምንም ዓይነት መልእክትም ይሁን ጥያቄ ባለመጠየቅ አግዙን::
https://t.me/MeGenzeb
14 890
ማሳሰቢያ
1) መ-ገንዘብ 2 መጽሓፍ ባለፈው ላመለጣቸው (4ኛ እትም) ነው::
2) መ-ገንዘብ 3 ደግሞ ለታዳጊዎች ሲሆን መ-ገንዘብ 2 ቀለል ተደርጎ ተዘጋጅቶ ነው::
3) ከየትኛውም ክፍለሃገር ማዘዝ ይቻላል::
4) በአቅራቢያችሁ ባለ ቅርንጫፍ ፖስታ ቤት በኩል ይደርሳችሗል:: ለቅልጥፍና ኢትዮጵያ ፖስታ!
4) የክፍያ መረጃ በቴሌግራም ከላካችሁ በሗላ ዝም በሉት:: በነካችሁት ቁጥር መሴጁ ወደቅርብ (Recent) ይሆናል:: ከሗላ ያሰልፋችሗል::
5) ከመጽሓፍ ክፍያና መረጃ መላክ ውጭ ምንም ዓይነት መረጃ ከይቅርታ ጋር አይስተናገድም:: ስለሚያምታታ ይደለታል::
ከመክፈላችሁ በፊት አካውንቱን ቼክ አድርጉ:: ከፍሎ የማይደርሰው የለም::
CBE
1000632718245
IZZELISLAM ABDULKADIR
https://t.me/MeGenzeb
14 890
መጀመሪያ ስለፋይናንስ ለሙስሊሞች ጻፍኩ:: ከዚያም ደገምኩ:: ሙስሊሞቹ ንባብና ሥራ ትተው ሙግትና ክርክር ውስጥ ገቡ:: ክርስቲያኖች ግን የሸሪዓውን ጭምር አንብበው መጠቀም ጀመሩ:: በእርግጥ በጣኣኣኣም አሞኝ የምሞት የሚመስለኝ ወቅት ስለነበር ለክርስቲያኖችም እጽፋለሁ የሚል ግምት ስላልነበረኝ እንደው አንድ ክርስቲያን እንኳ አንብቦ ከዚህ ከከፋ ድህነት ቢወጣ ብዬ እያንዳንዱን የዐረቢኛ ቃል በቅንፍ በአማርኛ ተርጉሜዋለሁ::
ከወራት በፊት አንዲት ክርስቲያን ልጅት ከሐዋሳ ደወለች:: ጴ^ንጤ መሰለችኝ:: ያነበበችው ለሙስሊሞች የተጻፈውን ፊያት መገበያያን ነው:: ገባሽ ወይ ስላት በደንብ አለችኝ:: ከራሷም አልፋ ባሏን እና ጓደኛዋ ላይ ለውጥ አመጣች:: ጓደኛዋ ብሬ ከሚጋሽብ ለምን አልጠቀምበትም ብላ በ150 ሺህ ብር ሶፋ ልትገዛ ስትወጣ "ሀጂ ወርቅ ግዙ:: ያተርፋል:: መቼም ቢሆን ዋጋው አይቀንስም:: ሰርቶ ለወጪ ከሆነ መሻሻል የለም ብለዋል" ብዬ አስነበብኳትና ይኸው ተግብራው ወርቅ ባንዴ ተተኩስ በጣም አተረፋት እያለች ብዙ አጫወተችኝ:: እንዲህ ያሉ መኣት አሉ::
የመ-ገንዘብ 2 ዋነኛ ከፋይና ገዢ ክርስቲያኖች ናቸው:: የታዳጊዎች ላይ ስለሺ ቀድሞ 50 አዘዘ:: ሳባ 10 አዘዘች:: በእርግጥ ሙስሊሞችም ደህና እየገባቸው ነው:: አንዳንዴ እኩል እኩል ይመጣሉ:: እስካሁን አይ^ሁድ ነኝ ያለኝ የለም:: እዚህ ቤት ግን በሰዎች መካከል አድልዎ የለም:: ብቻ የሰው ልጅ ድህነት አይቅጣው::
14 890
ወደድንም ጠላንም ዓለም የምትመራው በሰ^ካራም, ሽ^ፍታ, ዱር^ዬ, ሕጻናትን ደ ^ፋሪና ገ ^ዳይ በመሳሰሉት ስብ^ስቦች እንጂ በአላህ ነቢያት አይደለም:: ንግሥና በእነዚህ እጅ ከገባ ቆይቷል:: አያስነኩህም:: ኢብሊስ ተቆጣጥሮታል:: አንተ የምትነግሥበት ብቸኛ ቦታ አባወራነትህ ላይ ነው:: በትዳር Kingdom ውስጥ ንግሥትን አክብረህ ልጆችን ወልደህ ንጹሕ ትውልድ እየተካህ ትሄዳለህ:: በሒደት ይህንን የዱ^ርዬ ንግሥና መገርሰ^ስ ትችላለህ:: እንደው ባትችል እንኳ Termህን በክብር አጠናቀህ በወዳጅ በዘመድ በእድር በክብር ትሸኛለህ:: እያንዳንዱ አባወራ በአማካይ ካለው 60 ዓመት ውስጥ 40 የንግሥና ዓመታት አሉት:: የዚህን ያህል ጃንሆይ እንኳ አልነገሡም:: የውጪው የዙሪያህ ትር^ምስ ብቸኛ መሸሻ የተከበረ ቤት ነው:: እሱ ከተበላ^ሸብህ እዚህ ምድር ላይ ምንም አትሠራም:: You must go. You must step down to ቀbirr. ስለዚህ Kingደማችሁን ተንከባከቡ:: ከጥቃትና ወረራ ጠብቁ::
ደስስስስስ የሚል ቀን ይሁንላችሁ::
14 890
የማንም ሰው ቴሌግራም መልዕክት አልተከፈተም:: ከላካችሁ በሗላ ጠብቁ:: ብዙ ሰው ስለሆነ የባንክ ስቴትመንት ጋር እያመሳከርን መልስ እንሰጣለን:: ከዚያ መጽሓፉን እንልካለን::
14 890
+1
ሁለት መጻሕፍት ባንዴ
አንዱ ለታዳጊ አንዱ ለአዋቂ
=================
ሁለተኛው ዙር የመ-ገንዘብ መጻሕፍት ቅድመ ክፍያ እና ሕትመት ተዠምሯል:: ከናንተ የሚጠበቀው ታክሎ ይታተምልኝ ብሎ ማዘዝና የክፍያ ስክሪንሹቱን, ስም, ስልክ, አድራሻና ለየትኛው እንደከፈላችሁ በቴሌግራም ልኮ መጠባበቅ ነው:: Yes 👍 እኔ ደግሞ ባጭር ታጥቄ እንዳከበራችሁኝ ማስተናገድ በደስታ:: የመጽሓፎቹን ትንታኔ በቪዲዮ ለመሥራት ከልጆቼ ጋር ተግባብተናል:: ምክንያቱም የታዳጊዎቹን መ-ገንዘብ 3 ከእነርሱ ጋር መስመር በመስመር ነው የተናበብነው:: በ PhD ደረጃ የሚወራ እጅግ ሰፊ ርዕስ ለታዳጊዎች እንዲገባ ማድረግ ምን ያህል ፈታኝ እንደሆነ እራሴንም ፈትኜበታለሁ::
______
መ-ገንዘብ መጽሓፍ ቅድመ ሕትመት ዋጋ
- የታዳጊዎች 825 ብር
- የአዋቂዎች 900 ብር
- ሁለቱን የምትፈልጉ 1,725 ብር
ዋጋው በመላ ኢትዮጵያ በፖስታ ቤት ማድረሻን ይጨምራል::
CBE
1000632718245
IZZELISLAM ABDULKADIR
ስክሪንሹት, ስም, ስልክ, አድራሻ (ለምሳሌ ቡታጅራ, ሰመራ, እንጅባራ, ሳሪስ, ጨርቆስ)
ቴሌግራሙ ውስጥ ከዚህ ውጭ ምንም ዓይነት መልእክትም ይሁን ጥያቄ ባለመጠየቅ አግዙን::
https://t.me/MeGenzeb
14 890
የመጽሓፍ ብር ከከፈላችሁ እና እኔ ጋር ከደረሰ ለመጽሓፉ ምንም እንዳታስቡ:: ኢንሻአላህ:: ብቻ ትክክለኛ ስልክና አድራሻ ቴሌግራም ላይ መላካችሁን አትርሱ:: ክፍያ እንደቆመ ቴሌግራሙን ከፍተን ምላሽ እንሰጣለን::
-> ብር ስትልኩ Izzelislam Abdulkadir የሚል ስም ከመጣላችሁ ይደርሳል::
14 890
በባሕር ወደ ስዑዲ በሚደረጉ ጉዞዎች የሚያልቀው ወጣት ቁጥር ከምናስበው በላይ ነው:: መስመሩ የአደንዛ^ዥ እጽ ማስገቢያ እየሆነ ከመጣ ወዲህ በተለይ ኢትዮጵያውያን በዚህ አቋራጭ ጥቅም ተታለው ውድ ሕይወታቸውን እያስቋረጡ ናቸው:: ብዙዎቹ ከገጠር የሚመለመሉ ወጣቶች ስለሆኑ በቂ የመንገድ ዕውቀት የላቸውም:: የባሕሩን አዞ ካለፉት በሗላ ሌላ የእጽ ዐዛ እየያዛቸው ነው:: "ይህንን እጣን ይዘህ ሂድ:: እንትን ጋር ስትደርስ 5 ሺህ ሪያል 10 ሺህ ሪያል ተቀብለህ አስረክብ" ሲባሉ በገንዘቡ ይደነግጣሉ:: ዕውነትም እጣን መስሏቸው ይዘው እየሄዱ ሲያዙ ቀጥታ ወደ እርምጃ ነው:: አንዳንድ ድንገት ያሳለፉ ልጆችን ወሬ ሰምተው ብዙዎች ጉድ እየሆኑ ስለሆነ መታቀቡ ይበጃል ብላኛለች እህት ፈውዚያ ከመካ ከተማ::
14 890
ምርትና አገልግሎት በፌስቡክ ኮሜንት ማስተዋወቅ የሚፈልግ የሚከተለውን ጠቅ ያድርግ 👇🏼👇🏼
https://www.facebook.com/share/199sJSmMb6/?mibextid=wwXIfr
14 890
የሁለቱም መጻሕፍት የመጀመሪያው ዙር ክፍያ 24 ሰዓት ሳይሞላ ሞልቷል:: የሕትመት ሒደት ተጀምሯል:: አሁን የስርጭት ቅልጥፍና ላይ ነው የምንሠራው::
ክፍያዎች ለጥቂት ቀናት ይቀጥሉ ተብሏል:: ቀኑ ሲበዛም ለማኔጅመንት ስለሚያስቸግር ይቆማል::
መ-ገንዘብ መጽሓፍ ቅድመ ሕትመት ዋጋ
- የታዳጊዎች 825 ብር
- የአዋቂዎች 900 ብር
- ሁለቱን የምትፈልጉ 1,725 ብር
ዋጋው በመላ ኢትዮጵያ በፖስታ ቤት ማድረሻን ይጨምራል::
CBE
1000632718245
IZZELISLAM ABDULKADIR
ስክሪንሹት, ስም, ስልክ, አድራሻ (ለምሳሌ ቡታጅራ, ሰመራ, እንጅባራ, ሳሪስ, ጨርቆስ)
ቴሌግራሙ ውስጥ ከዚህ ውጭ ምንም ዓይነት መልእክትም ይሁን ጥያቄ ባለመጠየቅ አግዙን::
https://t.me/MeGenzeb
14 890
ትምህርት ሥራን የሚቀሉ, ልፋትን የሚቀንሱ ፈጣን ቴክኖሎጂዎችን አመነጨ:: ትምህርት ቤቶች ግን እነዚህ ቴክኖሎጂዎች እንዴት እንደማንጠቀም ነው የሚያስተምሩት:: Aiን ሳትጠቀም የመልፋት ጥበብ, ጎግልን ሳትጠቀም የመድከብ ችሎታ ተመዝነህ ታልፋለህ::
እሺ ምን ይሁን?
ኮምፒውተርን ያላገኙ የነበሩ የጥንት ሰዎች ኮምፒውተርን ለማግኘት የሚያደርጉትን ልፋት ደግመን እየለፋን ነው:: መማር ማለት መልፋት, መድከም, የሚጠቅም ነገር አጠገብ እያለ አለመጠቀም ነው:: የማያልቅ መሬትን መጠቀም ሕገ ወጥነት ይሆንና አለመጠቀም ወይም በአንድ ቤት መታፈግ ግን ሕጋዊነትና ጨዋነት ነው:: መግባባት ከበደን::
14 890
አንድ ውኃ ፋፍሪካ ያለው ሰው በሌ^ባ ሠራተኞች ስለተቸገርኩ የማያፈናፍን ሲስተም ሥራልኝ:: አራት መኪና ጭኖ ከወጣ የአንዱ ውኃ ብር አይገባም አለኝ:: መኪናውስ ተመልሶ ይገባል ወይ? ስለው አዎ አለኝ::
ሲስተምህ ምርጥ ነው:: አትነካካው:: 75% ስኬት መንግሥት እንኳ መች ቻለው? ሠራተኞችህም ፈጣሪን የሚፈሩ, በኃይማኖት ተኮትኩተው ያደጉ ናቸው:: ከአራት መኪና ውኃ ሦስት መች አነሰህ? ሲስተሙ ጥብቅብቅ ካለ ውኃም መኪናም ጭራሽ አይወጣም:: ሠራተኞችም አይመጡም:: ሁሌ ሠራተኛ ስትቀይር, ስታሰለጥን ነው የምትኖረው:: እንደውም የማይሰረ^ቅ ከሆነ ብታስመረምር ጥሩ ነው:: ሲስተም ባጠበቅህ ቁጥር አደገኛ ሌ^ባ ነው የምትጠራው:: መንግሥት አንድን ያልታጠቀ ነጋዴ ሰር^ቋል ብሎ አስቦ 10 የታጠቁ ፖሊሶችን ሲልክ ጊዜ ከትጥቅ ጋር 11 ሆነው እንደተቸገረው ትቸገራለህ ብዬው ያማከርኩበትና ያሳረፍኩበትን ብር ኮሚሽን የስኳር መጠኑ በቀነሰ ልክ በሺህ አባዝቶ እንዲከፍለኝ ተስማማን:: 50K ልኳል:: ብዙ ይቀራል::
ምግብ ቤት ስትከፍት ሽንኩርት, ሥጋ ምናምን ከፈትፈት ማድረግ ያስፈልጋል:: ወይም በጋራ እንሥራ ብለህ ነው የምታመጣቸው:: የትም ቦታ ላይ ሥራ ስትጀምሩ እንዳትሠረቁ ከፈለጋችሁ በጋራ ሥሩ:: የሚሠ^ርቁትን ያህል መጠን በኮሚሽን አድርጉት:: የማድግበት ቦታ ነው ብለው ካመኑ የባለቤትነት ስሜት ያድርባቸዋል::
14 890
ባለፈው መንግሥት ለምን ያትማል? መበደር እየቻለ ያልኳችሁን አስታወሳችሁት? እሱ ማለት ነው:: አህመድ ሺዴ ለእዮብ የ1 ቢሊዮን ብር ጨው ስለሚያስፈልገኝ ብድር ሥራልኝ ይለዋል:: የብሔራዊ ባንኩ እዮብ የብድር ሰነድ ያዘጋጅና ለአቤ ሳኖ ይሰጠዋል:: የንግድ ባንኩ አቤ ሳኖ ሰነዱን (ቦንዱን) ትርፍ ብር ላላቸው አልአሙዲዎች ይሸጠዋል:: ከዚያ የገቢዎች ዓይናለም ንጉሤ ከአጣሙዲዎች (ገባሪዎች) ትሰበስብና ለአህመድ ሺዴ ትሰጠዋለች:: አሕመድ ሺዴ ጨው የገዛበት በጀቱን ከነወለዱ በእዮብ በኩል ለአቤ ሳኖ ደንበኞች (አልአሙዲዎች) ይከፍላል:: ብር ሳይታተም ብር እየተበደሩ then አጣሙዲዎች የሚገብሩበት ሥርዓት ማለት ነው:: ይህ የሕትመት ወጪን ይቀንሳል:: የተሻለ መንገድ እንደሆነ ብዙ ጊዜ ገልጫለሁ:: እንደውም ከዚም የቀጠነ መንገድ አለ:: እሱን ለመተግበር የግድ የድሮን ቃታ መያዝ አለብኝ::
ይልቅስ ጭሰኞች ከዚህ የገባርነት ሲስተም ቶሎ ባይወጡ እንኳ ልጆቻቸው እንዲወጡላቸው የግድ መ-ገንዘብን Manበብ አለባቸው:: ታክስን ሳያጭበረብሩ በእነርሱ ጎን ያሰልፉታል:: "Am tax payer” ማለት ጭሰኛ ነኝ እንደማለት ነው:: ከዚህ የምትወጣው በራስህ ብር ንብረት ትይዝና በሞኝ ብር ስትሸቅል ታክስ የመክፈል እድልህ በብዙ ወይም ሙሉ ለሙሉ ትቀንሳለህ:: ኢምፖርት ላይ ሰማያዊ መስመር የሚባል አለ:: የጉምሩክ ፈታሽ ኮንቴይነሩን ዘወር ብሎ እንኳ አያየውም ማለት ይቻላል:: የዚህ መስመር ተጠቃሚዎች ኮንቴይነር ሲያልፍ ባለሥልጣን ሲያልፍ መንገድ እንደምትለቀው ዓይነት ነገር::
14 890
ከወለድ ነጻ ማለት አረንጓዴ ብጫ ቀይ ባንድራ ላይ የሆነ ምልክት ስላደረግህበት አረንጓዴ ብጫ ቀይነቱን ይሰርዘዋል ብሎ እንደማሰብ ጋር ይመሳሰላል::
