uk
Feedback
Hasen Injamo

Hasen Injamo

Відкрити в Telegram

Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Hasen Injamo

Канал Hasen Injamo (@haseniye) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 922 підписників, посідаючи 8 152 місце в категорії Економіка та фінанси та 2 286 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 922 підписників.

За останніми даними від 02 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 25, а за останні 24 години на 2, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.18%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 13.38% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 757 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 997 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 44.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Економіка та фінанси.

14 922
Підписники
+224 години
-227 днів
+2530 днів
Архів дописів
Tofik Hessian የምትባል ምእመን ለመ-ገንዘብ ብር ልከህ አድራሻ አልሞላህም:: ባስቀመጥከው ስልክ ስንደውልም "አይደለሁም ተሳስተሃል" ብለኸናል:: በ TrueCaller እየው:: የዱቤ ስልክ አይደለም::

ለመ-ገንዘብ መጽሐፍ ከፍለው የሪል ኢስቴት ጉዳይ የምንጠቀምበት ቴሌግራም ውስጥ የላኩ አሉ ወላሂ:: ሀጂ መጽሓፌን ይለኛል:: ዛሬ የሪል ኢስቴቱን ቴሌግራም ጎብኘት ሳደርግ እዚያ ልከዋል:: የሪል ኢስቴቱ እኮ ለብቻው ተዋቅሮ በራሱ ሠራተኞች እየሄደ ሲሆን የመጽሓፍ ጉዳይ አይመለከታቸውም:: ግን ፖስቱን ወደ ሗላ ሄዳችሁ ስትፈልጉ እንዴት የመ-ገንዘብን ቴሌግራም ሊንክ አላገኛችሁም? ብቻ ያም ሆነ ይህ ከፍሎ መረጃ ልኮ ፖስታ ቤት ያልተላከለት አንድም ሰው የለም:: እዚህ መጥተህ አልደረሰኝም ከማለትህ በፊት ስም, ስልክ, አድራሻ አድርሰን:: በተለይ ከ Other bank ወደ ኢት ንግድ ባንክ የከፈላችሁ ሰዎች አይደለም አድራሻ ቀርቶ ስማችሁን አንድ ፊደል እንኳ ማግኘት በፍጹም አይቻልም:: በባንኩ ብራንች ደረጃ እንኳ ማግኘት አይቻልም:: ስለዚህ ብራችሁን ነው ቋጥረን የምናስቀምጠው::

ትላልቅ ማለትም ኮርፖሬት ድርጅቶችን ተቀጥረው የሚመሩ ወይም ከመሩ ሰዎች ይልቅ የሊስትሮ ሳጥን የመሩ ሰዎች የተሻለ በራስ መተማመን አላቸው:: ኢትዮ ቴሌኮምም በለው ንግድ ባንክን ወይም ሌላ ትልቅ ድርጅት የሚመሩ ሰዎች የማሽን አንድ ክፍል ወይም ስፔር ናቸው:: ለምን ክራንክሻፍት አይሆኑም:: በማንኛውም ተመሳሳይ ስፔር ይቀየራሉ:: ድንገት ቢባረሩ በራሳቸው ችለው ለመቆም ረጅም ስብራት እና ዝገት ማስተናገድ አለባቸው:: ጭንቅላታቸው ውስጥ ቅጥር ነው ያለው:: ወሬያቸው ደግሞ በጣም ገራሚ ቢሆንም በራስህ ችለህ ድርጅት አቋቁም ብትሉዋቸው ይነስራቸዋል:: አንድ ምሳሌ ልጨምርላችሁ:: ከሦስቱ ብ^ሔሮች ውጭ ያለን ብሔ^ር ሀገር ምራ ብትለው አልቻልኩም ብሎ ጥሎ ይወጣል:: ከእነዚህ ውስጥ አንደኛውን ብንወስድ ይህንን ስነልቦና ለማዳበር ብዙ ማገዶ ፈጅቷል:: ግንሳ? ከአስር ዓመት በፊት የነበረውና አሁን ያለው ስነልቦናው አንድ አይደለም:: Part of ስትሆን እና whole ስትሆን ስነልቦናህ ይለያያል:: ከበሮ በሰው እና በራስ እጅ እንደሚለያየው ማለት ነው:: እያንዳንዱን የቤት ሥራ በቤት ውስጥ "አጋዥ ሠራተኛ" ያደገ ልጅ እና በ Hardship ውስጥ ወይም ተጋግዞ ሲሠራ ያደገ ልጅ እኩል ኃላፊነት አይሸከሙም:: ሞልቃቃዎቹ በወላጅ ውርስ ሲካሰሱ ይኖራሉ:: ሲበታተኑ ከአንድ ማኅጸን የወጡ አይመስሉም:: በእርግጥ ወላጅም ቀድሞ ማከፋፈል አለበት:: ልክ እንደዚሁ ተቀጥረው ትላልቅ ድርጅቶችን የመሩ ሰዎች ከወሬ የዘለለ ቁምነገር አታገኙባቸውም:: ምክንያቱም ቢዝነስ ከ scratch ተነስቶ እንዴት እንደሚያድግ አያውቁም:: ለሚስቶቻችን እንደ አባቷ የማንሆነው ... ወልደውና አሳድገው ትልቅዬ ከሆነች በሗላ ነው የምናውቃት:: እስቲ ሚስትህን ልብ በላት:: አባቷ ምን ያህል እንደለፉባት አስበኸው ታውቃለህ? ያ ሁሉ ልፋት አንተ አቅፈሃት እንድትተኛ ነው እንዴ? አባቷን ካባትህ ነጥለህ ማየት እንደሌለብህ ካወቅህ አንተ ተቀጣሪ ባል ሳትሆን አባት ነህ:: ካልሆነሳ? ሴት ልጅ ወልደህ አሳድገህ ለትዳር እስክታደርስ አይገባህም:: ቢዝነስም ላይ የሆነ ድርጅት ተቀጥሮ የኖረ ሰው ባል ነው እንጂ አባት አይደለም:: ወሬው ባላዊ እንጂ አባታዊ ሊሆን አይችልም:: የተቀጣሪነት እንጂ የአሳዳጊነት ስነልቦና experience አላደረገም:: ባል ሚስቱ ጋር ከተደባበሩ እመጭ ብሎ ፍንጥር ይላል:: ትእግስት የለውም:: አባት ግን ልጄ ደበረኝ ደበረችኝ ሊል አይችልም:: ገርፎም ቢሆን ያስተካክላል:: በግሉ ትንሽም ይሁን ድርጅትን ከስክራች አንስቶ ይዞ የሚሄድ ሰው ወሬ አያበዛም:: ተጣማሪ አጋዥ አይፈልግም:: የተግባር ሰው ነው:: የማሽን ጥርስ ወይም ስፔር ሳይሆን ሙሉ ማሽኑ ነው:: ለመንቀሳቀስ ነዳጅ ወይም ኤሌክትሪክ ብቻ ነው የሚፈልገው:: ተቀጣሪ የነበረው ግን ምን የማይፈልገው ነገር አለ?

በተለይ በአሁን ወቅት አንድ ደሃ ድንገት ተነስቶ ሀብታም ሊሆን አይችልም:: በምርቃናም በጠንካራ ሠራተኝነትም የሚደረስበት አልሆነም:: መመርቀን (ሞቲቬት መሆን) ጥሩ ነው:: ጠንካራ ሠራተኝነትም መጥ
+1
በተለይ በአሁን ወቅት አንድ ደሃ ድንገት ተነስቶ ሀብታም ሊሆን አይችልም:: በምርቃናም በጠንካራ ሠራተኝነትም የሚደረስበት አልሆነም:: መመርቀን (ሞቲቬት መሆን) ጥሩ ነው:: ጠንካራ ሠራተኝነትም መጥፎ ሆኖ አያውቅም:: ግን በጥበብ መሆን አለበት:: አንድ ኢትዮጵያዊ ደሃ በ10 ዓመት እንዴት ወደ ፋይናንስ ነጻነት ሊሻገር ይችላል? የሚል ፍኖተ ካርታ ነው:: የመጀመሪያው ዓመታት ላይ ብሩን ልቆጥብህ ቢልም የማይሆን ስለሆነ በራሱ ላይ ቢቆጥበው ማለትም ቢበላበትና ቢቅምበት ይሻላል ማለት ሳይሆን አጫጭር የሙያ ስልጠናዎችን ቢወስድበት በሚል ተነሳሁ:: ኤሌክትሪክ, ቀለም, ሜካኒክ, ሹፍርና, የጸጉር ሙያ, IT, Ai, ወዘተ ስልጠናዎችን ወሰደ ማለት ወጥቶ ባይሠራበት እንኳ ቤት ውስጥ ለራሱ ቢሠራ ወጪ ቀነሰ ማለት ነው:: ስቶቭ በተበላሸ ቁጥር አዳዲስ አይገዛም:: ምን የኤሌክትሪክ ዝርጋታ እንደሚያስፈልግ ያውቃል:: እንዲሁም ሙያ ካለው በየትኛውም circumstances ተቋቁሞ መውጣት ይችላል:: የተለያዩ ሙያዎች ካሉህ ሁሌ ሥራ ላይ ነህ:: ስትሠራ ወጪ ማውጫ ጊዜ የለህም:: ይልቅስ ገቢ ላይ ነህ:: ስለዚህ ይህንን የበዛ ገቢ ወደ ጊዜያዊ ቁጠባ ብትወስደው ግሽበት ብዙም አያጠቃውም:: በቅርብ ርቀት ወደ ንብረት ትቀይረዋለህ:: ዝርዝሩን ከመጽሓፎቹ!

ሀብታም ያልሆንኩት ሕሊናዬን አልሸጥም ብዬ ነው ይልሃል:: ሲጀመር መሸጫ ቦታውን ታውቀዋለህ? ዋጋስ ያወጣልሃል? ሕሊናህ ምን ይዟል? ንብረት አፍርቷል? ዝና አምጥቷል? ማን ባዶ ሕሊና ይገዛል? አንተ እራሱ ከ7 ዘ^ር የተዋረሰ እከክ ያለበትን ሕሊና ትገዛ ነበር? አዎ ሕሊናቸውን የማይሸጡ አሉ:: ግን ሀብታም ሆነው የማይኮሩና በምጽዋት የበረቱ, ትልቅ ሥልጣን ይዘው ኃላፊነት የሚሰማቸው, ታላቅ የኃይማኖት አባት ሆነው ከፈጣሪ ውጭ ማንንም የማይፈሩ ይኖራሉ:: ፀሓይን በቀኝ ጨረቃን በግራ ቢያኖሩላቸው ከዓላማቸው ፍንክች የማይሉ የታላቅ አዕምሮ ባለቤቶች አሉ:: ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ የሆነ ኑሮውን የሚቀይር አዕምሮ የሌለው ሰው ማንም አይገዛውም:: በቀላሉ ሲጠቃለል:- ሕሊናህን ገበያ ወስደህ አስገምተህ የሆነ አሪፍ ቢዝነስ ጋር ፊትለፊት ተጋፍጠህ ወይም ማንም በማያይህና በማይሰማህ ቦታ ላይ አሪፍ ዘ^ረፋ አግኝተህ "አይ አምላኬን እፈራለሁ" ብለህ ትተኸው አልፈሃል?

ለመ-ገንዘብ ከፍላችሁ የስልክም ይሁን የአድራሻ መረጃ ልናገኝላችሁ ያልቻልን ሰዎች ይህንን እንዳነበባችሁ ብትልኩልን:: ABDUKERIM OMER FIKADU BEKELE HABIBA HAYRU NUREDDIN MOHAMMED ABDELA DEGELO ቴሌግራም 👇🏼

-> ሙዚቃ በጣም ምርጥ ነገር ነበር:: ግን በሰካ-ራምና ዝሙ-ተኛ እጅ ገባ:: ሙዚቃ የመላእክት ኸርዝ እና የአጋንንት ኸርዝ አለው:: የመላእክቶቹ ሙሉ ለሙሉ ሲያርቁት በአጋንንት ቁጥጥር ስር ዋለና ወደ ፍትወት የሚመራው ብቻ ቀረ:: -> የገንዘብ ሲስተም እጅግ በጣም ምርጥ ግኝት ነበር:: ኃይማኖታዊያን ዱንያ ብለው ናቁትና በገዳ^ይ, በሰካ^ራምና ዝሙ^ተኛ እጅ ወድቆ ኃይማኖትና ክብር ሳይቀር ያስገብር ያዘ:: -> Ai እጅግ በጣም ድንቅ ግኝት ነው:: ግን አሁንም በተመሳሳይ ሰዎች እጅ ነው ያለው:: ለመልካም ከተጠቀምንበት የፋይናንስ ሲስተሙን ሰንሰለት ሊበጥስልን ይችላል:: ገንዘብ ወደማያስፈልግበት ሥርዓት ይወስደናል:: ምርት በAi እና ሮቦት የሚመረት ከሆነ የካፒታሊስት የፋይናንስ ሥርዓት ይቋረጣል:: ይህ የገባኝ የንግድ ባንኮችን ዲጂታል መገበያያ እና የብሔራዊ ባንኮች ዲጂታል መገበያያን ልዩነት ስጎረጉር ነው:: (መ-ገንዘብ ላይ በስሱ አለ)

በሶሻል ሚዲያ የተለየ ሥራ ወይም የወደፊት ዓላማ የሌላችሁ ምእመና ጠዋት እንደተነሳችሁ በፍጹም Scroll ባታደርጉ ይመከራል:: ከዚህ ዓመል ውጹ:: አንድ ሰው ከእንቅልፉ እንደተነሳ መሥራት ያለበት ትልቅ የአዕምሮና የሰውነት ጉልበት የሚጠይቁ ሥራዎችን ነው:: እኔንም ጮምሮ ፖሳቾች እራሱ ረፈድ ማድረግ ይኖርብናል:: ቀን ያረጁ ሴሎች ሌሊት ይታደሳሉ, ይቀየራሉ ብሎኛል ዶፍተር ጀማል:: በአዲስ ሴል አዳዲስ ሥራዎችን መሥራት C ገባን ቅንጭላታችንን በአሮጌ እና ትርካ ምርኪ ጀንክ መሙላታችን ያዛዝናል:: Me too.

ተጽፎ እጃችሁ እስኪደርስ ያለውን ፈተና ልቀንጭብ ============== 👉🏼 ሳይንስ ዘርፍ ላይ መጽሓፍ ማዘጋጀት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ የጻፈ ያውቀዋል:: 👉🏼 ከዚያም ለድፍን ሀገር በነጻ ነው የማሰራጨው:: ዱዲ አምስት ሳንቲም ለሥርጭት አልተቀበልኩም:: ይልቅስ እከፍላለሁ ሁላ:: 👉🏼 ምክንያቱም ጽፌ ሳልጨርስ, ማተሚያ ቤት ሳላስገባ ጨርሶ ለሚከፍለኝ ሰው ብችል በየቤቱ እራሴ ባደርስ ለኔ ክብር ነው:: ለዚህ ሥራ ብር ብቻ ሳይሆን በትክክል መረጃ የሞሉልኝ በጣም ረድተውኛል:: 👉🏼 ወይኔ በላቸው ወይኔ በላቸው!! ከሌላ ባንክ እና ከቴሌብር ገንዘብ ብቻ የላኩ ሰዎችን መረጃ ማሟላት የቻልኩት ኦዲተር እና የሒሳብ ሰነድ አጣሪ ሆኜ ስለሠራሁ ይመስለኛል የተወጣሁት:: ከየት በማን አማካኝነት ለምን እንደገባ ከማይታወቅ የብር ተመሳሳይ ቁጥሮች ተነስተህ የሰውየው ማንነት ጋር ለመድረስ ያለው መከራ ለማውራት አይመችም:: 900 ብር ሲል ለምን? Really የመጽሓፍ ነው? ከቴሌብር እና Other Bank የመጣው ምንም Clues የለውም:: 👉🏼 ፌስቡክ ኮሜንት ላይ ማንነቱ በማይታወቅ የተቆለመመ ፕሮፋይል አልደረሰኝም ይልሃል:: መረጃ አሞላል በጽሑፍም በቪዲዮም ልከህለት የማይሰማ ብዛቱ:: ከቴሌብር ወይም ሌላ ባንክ ብር የላከ ሀብታሙ ወይም ኢሊያስ የሚባል ሰው ስምና አድራሻ ለመገመት Habtamu Habitamu Habetamu ሀብታሙ ሃብታሙ ሐብታሙ ሓብታሙ ኀብታሙ ኃብታሙ ኻብታሙ ሁላ ተጠቅመን ቻት ውስጥ አመላካች መረጃ እንፈልጋለን:: ከዚያ የሆነ ግሩፕ እንከተዋለን:: Elias Elyas Eliyas Ilias Iliyas ኢሊያስ ኤሊያስ እያልን መከራ ነው የምንበላው:: በተባለው ትእዛዝ መሠረት ቢሞላ የሰከንድ ሥራ ነው:: በዓብዱ የሚጀምርማ ተውት:: ገና ስናየው ይደክመናል:: 👉🏼 ኮሜንት ላይ ግጥጥጥም አድርጎ ጽፎ ሄዶ መረጃ ልኬያለሁ የሚል ብዛቱ:: 👉🏼 በፖስታ ቤት ካደረግነው በሗላ በፍጹም መጭበርበር የለም:: ስህተት ቢያጋጥም እንኳ የተሳሳትናቸውን ለማስተካከል so easy. እንዲሁም ከፍሎ የማይደርሰው አንድም ሰው አይኖርም:: የብር አታችመንት ቦታ የመጠጥ ኮዳ ፎቶ የላከ ሰው ሁላ አለ:: ቢሆንም ቢሆንም ከፍለህ አሳትመህ በየመጻሕፍት ቤቱ በዱቤ በትነህ በአምስት ዓመት ከመለቃቀም በጣኣኣኣኣኣም ይሻላል::

እንደዚህ የሚሉ መረጃ ያልደረሳችሁ መረጃችሁ በተለያዩ ምክንያቶች አልደረሳችሁም ማለት ነው:: በተያያዘው ቴሌግራም ላኩልን:: በፎቶው ላይ ያለውን መልዕክት የደረሳችሁና መሴጅ ያልደረሳችሁ ግን Onli
+1
እንደዚህ የሚሉ መረጃ ያልደረሳችሁ መረጃችሁ በተለያዩ ምክንያቶች አልደረሳችሁም ማለት ነው:: በተያያዘው ቴሌግራም ላኩልን:: በፎቶው ላይ ያለውን መልዕክት የደረሳችሁና መሴጅ ያልደረሳችሁ ግን Online ማየቻ RD ET ቁጥር ይላክላችሗል:: ፖስታ ቤት ተሸኝቷል ይሚል ቁጥር ያልደረሳችሁ በዚህ ስም, ስልክ, አድራሻና የከፈላችሁበት ላኩ ፕሊስስስስስ! https://t.me/MeGenzeb

photo content
+1

ስዑድ አረቢያ የዓለም አቀፍ የውሾችን መውሊድ እያከበረች ነው:: ሰው የሚመጥነውን ያውቃል::
ስዑድ አረቢያ የዓለም አቀፍ የውሾችን መውሊድ እያከበረች ነው:: ሰው የሚመጥነውን ያውቃል::

የምኖረው በጉራጌ ባሕል ነው:: መሆን የምፈልገው ከአባቴ ወይም ከአያቴ አሕመድ 1/10ኛ ጸባይ ለመያዝ እንጂ ማንንም ሮል ሞዴል አላደርግም:: ያላየሁትና ያልተኗኗርኩትን ሰው ሞዴል ባደርግ መበጣጠስ እንጂ አልሆነውም:: ለእኔም አይሆኑም:: 11 ልጆችን ለፍተው አሳድገው ሲሞቱ ዱዲ ዕዳ የሌለባቸው, ለቅሶ የማያመልጣቸው, አራስ እና ሕመምተኛ የሚጠይቁ, የተሰበረ ላም ሳይቀር የሚያክሙ, ጅብን የሚያናግሩና ቃልኪዳን (Treaty) የሚዋዋሉ, ሶላት የማያመልጣቸው, ረመዷንን ቆጮ በጎመን በልተው ጹመው ውለው ሌሊቱን የሚሰግዱ, የሰው ሐቅ በፍጹም የማይነኩ ብቻ ሳይሆን ወደ ሗላ ሰባት ትውልድ ኦዲት የሚያደርጉ ሰዎችን 1/10ኛ ባገኝ በምን ዕድሌ!! ድሮ ገጠር ላም ገደል ከገባ, ወይም ገንዘብ ከጠፋን ቀጥታ ወደ ኦዲት ነው የሚገባው:: ላሚቷ ላይ የሰው ሐቅ አለባት ወይ? ነው የሚባለው:: ቤት በሰውም ይሁን በመብረቅ ከተቃጠለ መጀመሪያ ስህተት ኦዲት ይደረጋል:: ከቤቱ ጋር ሊቃጠሉ ይችሉ ይሆናል በሚል የእንሽላሊት, የጉንዳን ሐቅ ለደሃ, ለቆ^ማጣ ወይም ከፍተኛ ችግር ላለበት ሰው ይሰጣል:: ከኤኮሲስተሙ ጋር ያላቸው መግባባት አጃዒብ ነው:: ዛሬ ከእህቴ ጋር ኦዲት እያደረግን ነበር:: ኦዲቱ በአባትም በእናትም በኩል ነው የሚሠራው:: በርቸ ማለቅ አለበት:: በርቸ ማለት Karma ማለት ነው:: ወላጅ ቁሳዊም መንፈሳዊም ውርስ ያወርሳል:: ቁሳዊም ላይ ዕዳ ካለ ይከፈላል:: መንፈሳዊም ላይ ዕዳ ካለ ይወራረዳል:: የቁሳዊውን ከፍለህ የመንፈሳዊው ከቀረ ይበላብሃል:: ውርሱን የሚያሸጥ ዕዳ ይመጣብሃል:: የአባትህን ስም በመልካም እንዳታስጠራ ነገሮች ይሰነካከሉብሃል:: የዲኤንኤ ኦዲትና ኤዲት የግድ ይላል:: ልጆችህ በፍጹም ሀራም መብላት የለባቸውም:: ይመ^ረዛሉ:: ዕዳ በሌለበት ሰው ቅኑ:: ሰላም ውሎ ያድራል:: ሰላም ኖሮ ይሞ^ታል:: መክፈል ላትችሉ ትችላላችሁ:: ጻፉትና ለወራሽ ስጡ:: ዕዳ እያለበት የሞተ ነፍሱ ትንጠለጠላለች:: አታርፍም:: የሞቱ ወላጆቻችሁ ካለባቸው አሳርፉዋቸው:: በሞት ተቆርጠን እናበቃለን ብለን እንዳንሸወድ:: በአፈጣጠር ሞት ከሕይወት ይቀድማል:: እናቱ ማኅጸን ያለ ልጅ ስለፈረስና መኪና, ስለ ፀሐይና ጨረቃ ብትነግረው እንደ እብድ ሊያይህ ይችላል:: ዓለሙ የእናቱ ሆድ ነበር:: በስንጥቕ በኩል ይወጣል:: ልክ እንደዚሁ የሞተን ሰው በስንጥቅ አፈር ወደ ቀብር ስንልከው ጠባብ ዓለም ይመስለናል:: ከውልደት አልተማርንም:: የዚያኛው ዓለም sophistication እንዲህ ቀላል አይደለም:: ላንተ ብስባሽ አጥንት የሚታይህ ሳታይ እንድታምን ብቻ ነው እንጂ ጉዱ ሌላ ነው:: ሳይንሱን ሌላ ጊዜ እናወራዋለን:: ሮል ሞዴሎቻችንን ወላጆቻችን እናድርግ:: ለሞዴልነት በፍጹም ላንተ ክፉ የማይሆን እጅግ ርኅሩህ የሆኑት ወላጆችህ ይሻሉሃል ወይስ ባንተ ቢዝነስ የሚሠራ ሴሌብሪቲ?

ነጋዴዎች ከቻይና ለምን ፌክ ወይም ጥራቱ ዝቅ ያለ ዕቃ ያመጣሉ ብላችሁ ተበሳጭታችሁ አታውቁም? በተለይ ወዲያው ወዲያው ሲበላሽባችሁ:: አትበሳጩ:: ጥራት ያለው ዕቃ አስመጥታችሁ ሞክሩት:: ማን ከለከላችሁ? ገበያ የሚወሰነው በአቅርቦት እና ፍላጎት ነው:: መንግሥት የፈለገ መመሪያና ማጥበቂያ ቢያወጣ አቅርቦትና ፍላጎት ጆሮው ጥጥ ነው:: ነጋዴው ገዢ ካገኘ ከፌክ ዕቃ ጋር ምን አጋተተው? ገዢዎች አቅም የላቸውም:: ብልጭልጭ ወዳጆች አሉላችሁ:: ውዱን የማይገዙ:: ጥራት ያለው ዕቃ ብታመጡ ከአንድ ዙር አታልፉም:: ትልቁ አስወዳጅ ጉምሩክ ነው:: በ40 ብር የገዛኸው ዕቃ 500 ብር ነው የገዛኸው ብሎ ይቀርጥሃል:: እዚህ ጋር ያለውን ካልኩለስና ማትሪክስ እንተወው:: በትምህርትና ስልጠና አታገኙትም:: አራት አምስቴ አስመጥታችሁ ነው ማስተር የምታደርጉት:: የሆነ ዘርፍ ላይ ገዢ አጥቼ ጥራት ያላቸው ዕቃዎችን በሙሉ መጨረሻ ላይ እራሴ ነኝ ለቤቴ የወሰድኳቸው:: ምክንያቱም መደብሩ ውድ ነው አስብለው ደንበኛ ያባርራሉ:: ሁሉም ባይሆኑም ግን ውድ ዕቃ የሚገዙ ሰዎች እራሳቸው ማምጣትና ማስመጣት የሚችሉ ዓይነት ናቸው:: ስለዚህ ገቢው ለመንቀሳቀስም ለማመጽም የማያበቃው ምእመን የግድ ለለት መወጣጫ ዕቃ ይመጣለታል:: ነጋዴው የሚጭነው የገበያውን ምላሽ (response) እያየ ነው:: ጥራቱን የጠበቀ ዕቃ ብታመጡ ተወዳዳሪዎችና አሳላጮች "እሱ 2ኛው ነው" ያስብሉባችሗል:: ትርፍ ከሁለት ነገር ነው የሚገኘው:: አንደኛው ገቢዎችና ጉምሩክን በመሹሎክ ሲሆን ሁለተኛው ገበያ ውስጥ የብዙኃን ዕቃ አስገብቶ ሳይመቱ በማለፍ ነው:: ኒች እና ከስተማይዝድ ማርኬት ገና ነን:: ሕዝባችን middle class የለውም:: ጥቂት ሀብታም እና ነፍ ድሃ የተዋቀረ ስለሆነ:: ጥራት ያለው ዕቃ ግዙ አልልም:: ገቢያችሁ ነው የሚገዛላችሁ:: በነጋዴው ከማሳበብ በገቢያችን ብናሳብብ ባይ ነኝ::

ከተክሎ-ሎጂ ጋር መግባባት ከbad ነው:: የመጽሓፍ መከታተያ RD ቁጽር እና የፖስታ ቤት tracking ፖርታል ስርሰጣቸው ✔️ የማይደረግበት ቦታ ላይ ራይት አድርገው ሲፈልጉ እንዲህ የሚባል ትዕዛዝ
ከተክሎ-ሎጂ ጋር መግባባት ከbad ነው:: የመጽሓፍ መከታተያ RD ቁጽር እና የፖስታ ቤት tracking ፖርታል ስርሰጣቸው ✔️ የማይደረግበት ቦታ ላይ ራይት አድርገው ሲፈልጉ እንዲህ የሚባል ትዕዛዝ የለም ይላቸዋል:: ከዚያ የሌለ ነገር የሰጠሗቸው የሚመስላቸው አይጠፉም:: ለምሳሌ ስም የሚለው ቦታ ላይ ስማችሁን በትክክል ጻፉ:: ለምሳሌ Tamrat Geleta Iticha ብዬ ምሳሌ demonstrate ሳደርግ ብዙ ምእመን ስም ላይ Tamrat Geleta Iticha ብለው ይሞላሉ:: አድራሻ ምሳሌ Afar Logia ብዬ ሳስረዳ እራሱኑ ገልብጠው የሚሞሉ ገጥመውኛል:: በኮሜንት ይመጡና ሀጂ ዝም አሉን የሚሉ አሉ:: አሁንም ፖርታሉ ላይ ያልሆነ ትእዛዝ ሲያዙት እናቶትን ባይልም ግን የለም ሲላቸው በስጫ ይላቸዋል:: ዋናው አምናችሁ ስለከፈላችሁ እኛም ይህንን ለማረጋገጥ እየጣርን ነው:: በነገራችን ራስጌና ግርጌ GBO የሚል አድራሻ ካገኛችሁ ዋናው ፖስታ ቤት ጥቁር አንበሳ መጥታችሁ ውሰዱ እንደማለት ነው:: አድራሻ በደፈናው አዲስ አበባ ላሉት ነው:: ለቡ, ጀሞ, KFC (ኮዬ ፈጬ) ብለው ሞልተው ዋናው ፖስታ ቤት የተደረገባቸው አንዳንድ ምእመናን አሉ:: እያየን እየተነጋገርን እያስተካከልን ነው::

መ-ገንዘብ 1ኛ ዙር ላይ ወደ ፖስታ ቤት የተላከ የሚለው ደርሷችሁ መጽሓፍ ግን ያልደረሳችሁ ምእመናን ቁጥሩን እንልክላችሁና በፖስታ ቤት tracking portal መከታተል ትችላላችሁ:: ሊንኩ ከስር አለ:: https://domestictrack.ethio.post/PostGlobal/WebTrack/Track.aspx

ቁርአን 114 ምእራፎች አሉት:: አንቀጽ እና ፊደሎቹ ሳይቀር ቁጥራቸው ይታወቃል:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم በጽሑፍም በሒፍዝም ያስተላለፉት ብቸኛ መጽሓፍ ይህ ነው:: ሌላ የለም:: እ
ቁርአን 114 ምእራፎች አሉት:: አንቀጽ እና ፊደሎቹ ሳይቀር ቁጥራቸው ይታወቃል:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم በጽሑፍም በሒፍዝም ያስተላለፉት ብቸኛ መጽሓፍ ይህ ነው:: ሌላ የለም:: እዚህ ቁርአን ውስጥ መውሊድ ስለማክበርና መደሰት በግልጽ አንቀጾች ሰፍሯል:: ዒደልፊጥርና ዒደል አድሃ ግን በግልጽ አልሰፈሩም:: በቁርኣን የመውሊድ መረጃ ከሁለቱ ዒዶች መረጃ በላይ ጠንካራ ነው:: ቢድዓ እያሉ የሚንጫጩ ሰዎች ይህንን እንኳ አያውቁም:: ሶላት እንኳ ስንት ረካዓ እንደሚሰገድ የመውሊድ ያህል በቁርኣን አልተብራራም:: ዙህር አራት ይሰገድ ሁለት ቁርኣን ውስጥ የለም:: እነዚህን የምናገኘው ሀዲሶች ውስጥ ነው:: ሀዲሶቹ የነቢያችን صلى الله عليه وسلم ቢሆኑም ቅሉ ሰብሳቢዎቹ አብዛኞቹ ከ200 ዓመታት በሗላ በግል ተነሳሽነት የሰበሰቡዋቸው ናቸው:: አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው:: ይህንን ያህል ክፍለዘመን ለምን ሳይሰበሰቡ ቆዩ? ለሚለው ሀዲሶችን መሰብሰብ ቢድዓ (ፈጠራ) ነው ብለው ያምኑ ስለነበር ነው:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم እንዳይሰበሰብ ከልክለው ስለነበር ሶሃቦችን ከዚያ በሗላ የመጡትም ፈሩ:: በመረጃ መዛባት በሙስሊሞች መካከል ከባድ ትርምስ ተፈጥሮ ብዙ ምእመን እርስበእርስ ተጋድ^ሏል:: ለዚህ መፍትሔ ቢሰጥ በሚል አፈታሪኩን (ሀዲሱን) ወደ ጽሑፍ ቀየሩት:: የሀዲሶች አንዳንድ መረጃዎች የጭቅጭቅ መንስዔ ሲሆኑ ጊዜ "ወትሮም ነቢያችን صلى الله عليه وسلم ያልሰበሰቡት ነገር ነው እያበጣበጠን ያለው የሚሉ በርካታ ድምጾች ያሉት ለዚህ ነው:: ሀዲስን መጣልም መፍትሔ አይደለም:: ከቁርኣን ማስቀደም ደግሞ የባሰ ፈተና ነው:: መፍትሔው በማያውቁት ነገር አለመዘባረቅ እና የሙስሊሞችን ክብር አለመንካት ነው::

ድርብ መውሊድ ነው ዛሬ በነቢ ሙሐመድ صلى الله عليه وآله وسلم መውሊድ ተደስተን ውለን ማምሻው ደግሞ በማትሪክ የተይሲር ዐብዱልቃዲር መውሊድ ሆነ:: አልሃምዱሊላህ:: ፊቅሕ መዝሃበ-ሻፍዒያ ሊያጠናቅቅ ደርሷል:: ተሰውፍ ጦሪቃ ወስዷል:: ማትሪክ መትርኳል:: መውሊዱ ተራዝሟል::

የኢትዮጵያ ድህነት በዓል ብዛት የመጣ ነው የሚል ሰው ይኖራል:: የበዓል ብዛት ግን አሪፍ የኢኮኖሚ ማነቃቂያ ነው:: ሰው ሲያርፍ እንደ ላም ተኝቶ አያመሰኳም, አያመነዥግም:: ያለረፍት ያጠፋል:: ስለዚህ የሚጠፋ ነገር አምርቶ ማቅረብ ነው:: የምርት demand ሲፈጠር የአቅርቦት ዘርፉ ይበልጥ ይንቀሳቀሳል:: ቁጠባ ኢኮኖሚን ይገ^ድላል:: ማጠፋፋት ግን ሥራ ይፈጥራል:: በእርግጥ እኛ በበዓልም በአዘቦትም ገበታችን የብላኔ ነው:: ሳንፈራ እንብላ:: እናብላ:: ጤናችንን እንጠብቅ:: ብዙ ስለበላህ አትወፍርም:: የአብዛኛው ምእመን ውፍረት የጭንቀት እንጂ የምግብ አይደለም:: የአላህ ጸጋ አልተነካም:: ስንት ፕላኔት ላይ ስንትና ስንት ጸጋ ተከማችቶ ገና መሬት ላይ ነን::

photo content