ar
Feedback
Hasen Injamo

Hasen Injamo

الذهاب إلى القناة على Telegram

Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Hasen Injamo

تُعد قناة Hasen Injamo (@haseniye) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 927 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 110 في فئة الاقتصاد والمالية والمرتبة 2 266 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 927 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 35، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -9، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 23.68‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.68‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 536 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 042 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 31.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الاقتصاد والمالية.

14 927
المشتركون
-924 ساعات
-97 أيام
+3530 أيام
أرشيف المشاركات
ለመ-ገንዘብ ከፍላችሁ የስልክም ይሁን የአድራሻ መረጃ ልናገኝላችሁ ያልቻልን ሰዎች ይህንን እንዳነበባችሁ ብትልኩልን:: ABDUKERIM OMER FIKADU BEKELE HABIBA HAYRU NUREDDIN MOHAMMED ABDELA DEGELO ቴሌግራም 👇🏼

-> ሙዚቃ በጣም ምርጥ ነገር ነበር:: ግን በሰካ-ራምና ዝሙ-ተኛ እጅ ገባ:: ሙዚቃ የመላእክት ኸርዝ እና የአጋንንት ኸርዝ አለው:: የመላእክቶቹ ሙሉ ለሙሉ ሲያርቁት በአጋንንት ቁጥጥር ስር ዋለና ወደ ፍትወት የሚመራው ብቻ ቀረ:: -> የገንዘብ ሲስተም እጅግ በጣም ምርጥ ግኝት ነበር:: ኃይማኖታዊያን ዱንያ ብለው ናቁትና በገዳ^ይ, በሰካ^ራምና ዝሙ^ተኛ እጅ ወድቆ ኃይማኖትና ክብር ሳይቀር ያስገብር ያዘ:: -> Ai እጅግ በጣም ድንቅ ግኝት ነው:: ግን አሁንም በተመሳሳይ ሰዎች እጅ ነው ያለው:: ለመልካም ከተጠቀምንበት የፋይናንስ ሲስተሙን ሰንሰለት ሊበጥስልን ይችላል:: ገንዘብ ወደማያስፈልግበት ሥርዓት ይወስደናል:: ምርት በAi እና ሮቦት የሚመረት ከሆነ የካፒታሊስት የፋይናንስ ሥርዓት ይቋረጣል:: ይህ የገባኝ የንግድ ባንኮችን ዲጂታል መገበያያ እና የብሔራዊ ባንኮች ዲጂታል መገበያያን ልዩነት ስጎረጉር ነው:: (መ-ገንዘብ ላይ በስሱ አለ)

በሶሻል ሚዲያ የተለየ ሥራ ወይም የወደፊት ዓላማ የሌላችሁ ምእመና ጠዋት እንደተነሳችሁ በፍጹም Scroll ባታደርጉ ይመከራል:: ከዚህ ዓመል ውጹ:: አንድ ሰው ከእንቅልፉ እንደተነሳ መሥራት ያለበት ትልቅ የአዕምሮና የሰውነት ጉልበት የሚጠይቁ ሥራዎችን ነው:: እኔንም ጮምሮ ፖሳቾች እራሱ ረፈድ ማድረግ ይኖርብናል:: ቀን ያረጁ ሴሎች ሌሊት ይታደሳሉ, ይቀየራሉ ብሎኛል ዶፍተር ጀማል:: በአዲስ ሴል አዳዲስ ሥራዎችን መሥራት C ገባን ቅንጭላታችንን በአሮጌ እና ትርካ ምርኪ ጀንክ መሙላታችን ያዛዝናል:: Me too.

ተጽፎ እጃችሁ እስኪደርስ ያለውን ፈተና ልቀንጭብ ============== 👉🏼 ሳይንስ ዘርፍ ላይ መጽሓፍ ማዘጋጀት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ የጻፈ ያውቀዋል:: 👉🏼 ከዚያም ለድፍን ሀገር በነጻ ነው የማሰራጨው:: ዱዲ አምስት ሳንቲም ለሥርጭት አልተቀበልኩም:: ይልቅስ እከፍላለሁ ሁላ:: 👉🏼 ምክንያቱም ጽፌ ሳልጨርስ, ማተሚያ ቤት ሳላስገባ ጨርሶ ለሚከፍለኝ ሰው ብችል በየቤቱ እራሴ ባደርስ ለኔ ክብር ነው:: ለዚህ ሥራ ብር ብቻ ሳይሆን በትክክል መረጃ የሞሉልኝ በጣም ረድተውኛል:: 👉🏼 ወይኔ በላቸው ወይኔ በላቸው!! ከሌላ ባንክ እና ከቴሌብር ገንዘብ ብቻ የላኩ ሰዎችን መረጃ ማሟላት የቻልኩት ኦዲተር እና የሒሳብ ሰነድ አጣሪ ሆኜ ስለሠራሁ ይመስለኛል የተወጣሁት:: ከየት በማን አማካኝነት ለምን እንደገባ ከማይታወቅ የብር ተመሳሳይ ቁጥሮች ተነስተህ የሰውየው ማንነት ጋር ለመድረስ ያለው መከራ ለማውራት አይመችም:: 900 ብር ሲል ለምን? Really የመጽሓፍ ነው? ከቴሌብር እና Other Bank የመጣው ምንም Clues የለውም:: 👉🏼 ፌስቡክ ኮሜንት ላይ ማንነቱ በማይታወቅ የተቆለመመ ፕሮፋይል አልደረሰኝም ይልሃል:: መረጃ አሞላል በጽሑፍም በቪዲዮም ልከህለት የማይሰማ ብዛቱ:: ከቴሌብር ወይም ሌላ ባንክ ብር የላከ ሀብታሙ ወይም ኢሊያስ የሚባል ሰው ስምና አድራሻ ለመገመት Habtamu Habitamu Habetamu ሀብታሙ ሃብታሙ ሐብታሙ ሓብታሙ ኀብታሙ ኃብታሙ ኻብታሙ ሁላ ተጠቅመን ቻት ውስጥ አመላካች መረጃ እንፈልጋለን:: ከዚያ የሆነ ግሩፕ እንከተዋለን:: Elias Elyas Eliyas Ilias Iliyas ኢሊያስ ኤሊያስ እያልን መከራ ነው የምንበላው:: በተባለው ትእዛዝ መሠረት ቢሞላ የሰከንድ ሥራ ነው:: በዓብዱ የሚጀምርማ ተውት:: ገና ስናየው ይደክመናል:: 👉🏼 ኮሜንት ላይ ግጥጥጥም አድርጎ ጽፎ ሄዶ መረጃ ልኬያለሁ የሚል ብዛቱ:: 👉🏼 በፖስታ ቤት ካደረግነው በሗላ በፍጹም መጭበርበር የለም:: ስህተት ቢያጋጥም እንኳ የተሳሳትናቸውን ለማስተካከል so easy. እንዲሁም ከፍሎ የማይደርሰው አንድም ሰው አይኖርም:: የብር አታችመንት ቦታ የመጠጥ ኮዳ ፎቶ የላከ ሰው ሁላ አለ:: ቢሆንም ቢሆንም ከፍለህ አሳትመህ በየመጻሕፍት ቤቱ በዱቤ በትነህ በአምስት ዓመት ከመለቃቀም በጣኣኣኣኣኣም ይሻላል::

እንደዚህ የሚሉ መረጃ ያልደረሳችሁ መረጃችሁ በተለያዩ ምክንያቶች አልደረሳችሁም ማለት ነው:: በተያያዘው ቴሌግራም ላኩልን:: በፎቶው ላይ ያለውን መልዕክት የደረሳችሁና መሴጅ ያልደረሳችሁ ግን Onli
+1
እንደዚህ የሚሉ መረጃ ያልደረሳችሁ መረጃችሁ በተለያዩ ምክንያቶች አልደረሳችሁም ማለት ነው:: በተያያዘው ቴሌግራም ላኩልን:: በፎቶው ላይ ያለውን መልዕክት የደረሳችሁና መሴጅ ያልደረሳችሁ ግን Online ማየቻ RD ET ቁጥር ይላክላችሗል:: ፖስታ ቤት ተሸኝቷል ይሚል ቁጥር ያልደረሳችሁ በዚህ ስም, ስልክ, አድራሻና የከፈላችሁበት ላኩ ፕሊስስስስስ! https://t.me/MeGenzeb

photo content
+1

ስዑድ አረቢያ የዓለም አቀፍ የውሾችን መውሊድ እያከበረች ነው:: ሰው የሚመጥነውን ያውቃል::
ስዑድ አረቢያ የዓለም አቀፍ የውሾችን መውሊድ እያከበረች ነው:: ሰው የሚመጥነውን ያውቃል::

የምኖረው በጉራጌ ባሕል ነው:: መሆን የምፈልገው ከአባቴ ወይም ከአያቴ አሕመድ 1/10ኛ ጸባይ ለመያዝ እንጂ ማንንም ሮል ሞዴል አላደርግም:: ያላየሁትና ያልተኗኗርኩትን ሰው ሞዴል ባደርግ መበጣጠስ እንጂ አልሆነውም:: ለእኔም አይሆኑም:: 11 ልጆችን ለፍተው አሳድገው ሲሞቱ ዱዲ ዕዳ የሌለባቸው, ለቅሶ የማያመልጣቸው, አራስ እና ሕመምተኛ የሚጠይቁ, የተሰበረ ላም ሳይቀር የሚያክሙ, ጅብን የሚያናግሩና ቃልኪዳን (Treaty) የሚዋዋሉ, ሶላት የማያመልጣቸው, ረመዷንን ቆጮ በጎመን በልተው ጹመው ውለው ሌሊቱን የሚሰግዱ, የሰው ሐቅ በፍጹም የማይነኩ ብቻ ሳይሆን ወደ ሗላ ሰባት ትውልድ ኦዲት የሚያደርጉ ሰዎችን 1/10ኛ ባገኝ በምን ዕድሌ!! ድሮ ገጠር ላም ገደል ከገባ, ወይም ገንዘብ ከጠፋን ቀጥታ ወደ ኦዲት ነው የሚገባው:: ላሚቷ ላይ የሰው ሐቅ አለባት ወይ? ነው የሚባለው:: ቤት በሰውም ይሁን በመብረቅ ከተቃጠለ መጀመሪያ ስህተት ኦዲት ይደረጋል:: ከቤቱ ጋር ሊቃጠሉ ይችሉ ይሆናል በሚል የእንሽላሊት, የጉንዳን ሐቅ ለደሃ, ለቆ^ማጣ ወይም ከፍተኛ ችግር ላለበት ሰው ይሰጣል:: ከኤኮሲስተሙ ጋር ያላቸው መግባባት አጃዒብ ነው:: ዛሬ ከእህቴ ጋር ኦዲት እያደረግን ነበር:: ኦዲቱ በአባትም በእናትም በኩል ነው የሚሠራው:: በርቸ ማለቅ አለበት:: በርቸ ማለት Karma ማለት ነው:: ወላጅ ቁሳዊም መንፈሳዊም ውርስ ያወርሳል:: ቁሳዊም ላይ ዕዳ ካለ ይከፈላል:: መንፈሳዊም ላይ ዕዳ ካለ ይወራረዳል:: የቁሳዊውን ከፍለህ የመንፈሳዊው ከቀረ ይበላብሃል:: ውርሱን የሚያሸጥ ዕዳ ይመጣብሃል:: የአባትህን ስም በመልካም እንዳታስጠራ ነገሮች ይሰነካከሉብሃል:: የዲኤንኤ ኦዲትና ኤዲት የግድ ይላል:: ልጆችህ በፍጹም ሀራም መብላት የለባቸውም:: ይመ^ረዛሉ:: ዕዳ በሌለበት ሰው ቅኑ:: ሰላም ውሎ ያድራል:: ሰላም ኖሮ ይሞ^ታል:: መክፈል ላትችሉ ትችላላችሁ:: ጻፉትና ለወራሽ ስጡ:: ዕዳ እያለበት የሞተ ነፍሱ ትንጠለጠላለች:: አታርፍም:: የሞቱ ወላጆቻችሁ ካለባቸው አሳርፉዋቸው:: በሞት ተቆርጠን እናበቃለን ብለን እንዳንሸወድ:: በአፈጣጠር ሞት ከሕይወት ይቀድማል:: እናቱ ማኅጸን ያለ ልጅ ስለፈረስና መኪና, ስለ ፀሐይና ጨረቃ ብትነግረው እንደ እብድ ሊያይህ ይችላል:: ዓለሙ የእናቱ ሆድ ነበር:: በስንጥቕ በኩል ይወጣል:: ልክ እንደዚሁ የሞተን ሰው በስንጥቅ አፈር ወደ ቀብር ስንልከው ጠባብ ዓለም ይመስለናል:: ከውልደት አልተማርንም:: የዚያኛው ዓለም sophistication እንዲህ ቀላል አይደለም:: ላንተ ብስባሽ አጥንት የሚታይህ ሳታይ እንድታምን ብቻ ነው እንጂ ጉዱ ሌላ ነው:: ሳይንሱን ሌላ ጊዜ እናወራዋለን:: ሮል ሞዴሎቻችንን ወላጆቻችን እናድርግ:: ለሞዴልነት በፍጹም ላንተ ክፉ የማይሆን እጅግ ርኅሩህ የሆኑት ወላጆችህ ይሻሉሃል ወይስ ባንተ ቢዝነስ የሚሠራ ሴሌብሪቲ?

ነጋዴዎች ከቻይና ለምን ፌክ ወይም ጥራቱ ዝቅ ያለ ዕቃ ያመጣሉ ብላችሁ ተበሳጭታችሁ አታውቁም? በተለይ ወዲያው ወዲያው ሲበላሽባችሁ:: አትበሳጩ:: ጥራት ያለው ዕቃ አስመጥታችሁ ሞክሩት:: ማን ከለከላችሁ? ገበያ የሚወሰነው በአቅርቦት እና ፍላጎት ነው:: መንግሥት የፈለገ መመሪያና ማጥበቂያ ቢያወጣ አቅርቦትና ፍላጎት ጆሮው ጥጥ ነው:: ነጋዴው ገዢ ካገኘ ከፌክ ዕቃ ጋር ምን አጋተተው? ገዢዎች አቅም የላቸውም:: ብልጭልጭ ወዳጆች አሉላችሁ:: ውዱን የማይገዙ:: ጥራት ያለው ዕቃ ብታመጡ ከአንድ ዙር አታልፉም:: ትልቁ አስወዳጅ ጉምሩክ ነው:: በ40 ብር የገዛኸው ዕቃ 500 ብር ነው የገዛኸው ብሎ ይቀርጥሃል:: እዚህ ጋር ያለውን ካልኩለስና ማትሪክስ እንተወው:: በትምህርትና ስልጠና አታገኙትም:: አራት አምስቴ አስመጥታችሁ ነው ማስተር የምታደርጉት:: የሆነ ዘርፍ ላይ ገዢ አጥቼ ጥራት ያላቸው ዕቃዎችን በሙሉ መጨረሻ ላይ እራሴ ነኝ ለቤቴ የወሰድኳቸው:: ምክንያቱም መደብሩ ውድ ነው አስብለው ደንበኛ ያባርራሉ:: ሁሉም ባይሆኑም ግን ውድ ዕቃ የሚገዙ ሰዎች እራሳቸው ማምጣትና ማስመጣት የሚችሉ ዓይነት ናቸው:: ስለዚህ ገቢው ለመንቀሳቀስም ለማመጽም የማያበቃው ምእመን የግድ ለለት መወጣጫ ዕቃ ይመጣለታል:: ነጋዴው የሚጭነው የገበያውን ምላሽ (response) እያየ ነው:: ጥራቱን የጠበቀ ዕቃ ብታመጡ ተወዳዳሪዎችና አሳላጮች "እሱ 2ኛው ነው" ያስብሉባችሗል:: ትርፍ ከሁለት ነገር ነው የሚገኘው:: አንደኛው ገቢዎችና ጉምሩክን በመሹሎክ ሲሆን ሁለተኛው ገበያ ውስጥ የብዙኃን ዕቃ አስገብቶ ሳይመቱ በማለፍ ነው:: ኒች እና ከስተማይዝድ ማርኬት ገና ነን:: ሕዝባችን middle class የለውም:: ጥቂት ሀብታም እና ነፍ ድሃ የተዋቀረ ስለሆነ:: ጥራት ያለው ዕቃ ግዙ አልልም:: ገቢያችሁ ነው የሚገዛላችሁ:: በነጋዴው ከማሳበብ በገቢያችን ብናሳብብ ባይ ነኝ::

ከተክሎ-ሎጂ ጋር መግባባት ከbad ነው:: የመጽሓፍ መከታተያ RD ቁጽር እና የፖስታ ቤት tracking ፖርታል ስርሰጣቸው ✔️ የማይደረግበት ቦታ ላይ ራይት አድርገው ሲፈልጉ እንዲህ የሚባል ትዕዛዝ
ከተክሎ-ሎጂ ጋር መግባባት ከbad ነው:: የመጽሓፍ መከታተያ RD ቁጽር እና የፖስታ ቤት tracking ፖርታል ስርሰጣቸው ✔️ የማይደረግበት ቦታ ላይ ራይት አድርገው ሲፈልጉ እንዲህ የሚባል ትዕዛዝ የለም ይላቸዋል:: ከዚያ የሌለ ነገር የሰጠሗቸው የሚመስላቸው አይጠፉም:: ለምሳሌ ስም የሚለው ቦታ ላይ ስማችሁን በትክክል ጻፉ:: ለምሳሌ Tamrat Geleta Iticha ብዬ ምሳሌ demonstrate ሳደርግ ብዙ ምእመን ስም ላይ Tamrat Geleta Iticha ብለው ይሞላሉ:: አድራሻ ምሳሌ Afar Logia ብዬ ሳስረዳ እራሱኑ ገልብጠው የሚሞሉ ገጥመውኛል:: በኮሜንት ይመጡና ሀጂ ዝም አሉን የሚሉ አሉ:: አሁንም ፖርታሉ ላይ ያልሆነ ትእዛዝ ሲያዙት እናቶትን ባይልም ግን የለም ሲላቸው በስጫ ይላቸዋል:: ዋናው አምናችሁ ስለከፈላችሁ እኛም ይህንን ለማረጋገጥ እየጣርን ነው:: በነገራችን ራስጌና ግርጌ GBO የሚል አድራሻ ካገኛችሁ ዋናው ፖስታ ቤት ጥቁር አንበሳ መጥታችሁ ውሰዱ እንደማለት ነው:: አድራሻ በደፈናው አዲስ አበባ ላሉት ነው:: ለቡ, ጀሞ, KFC (ኮዬ ፈጬ) ብለው ሞልተው ዋናው ፖስታ ቤት የተደረገባቸው አንዳንድ ምእመናን አሉ:: እያየን እየተነጋገርን እያስተካከልን ነው::

መ-ገንዘብ 1ኛ ዙር ላይ ወደ ፖስታ ቤት የተላከ የሚለው ደርሷችሁ መጽሓፍ ግን ያልደረሳችሁ ምእመናን ቁጥሩን እንልክላችሁና በፖስታ ቤት tracking portal መከታተል ትችላላችሁ:: ሊንኩ ከስር አለ:: https://domestictrack.ethio.post/PostGlobal/WebTrack/Track.aspx

ቁርአን 114 ምእራፎች አሉት:: አንቀጽ እና ፊደሎቹ ሳይቀር ቁጥራቸው ይታወቃል:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم በጽሑፍም በሒፍዝም ያስተላለፉት ብቸኛ መጽሓፍ ይህ ነው:: ሌላ የለም:: እ
ቁርአን 114 ምእራፎች አሉት:: አንቀጽ እና ፊደሎቹ ሳይቀር ቁጥራቸው ይታወቃል:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم በጽሑፍም በሒፍዝም ያስተላለፉት ብቸኛ መጽሓፍ ይህ ነው:: ሌላ የለም:: እዚህ ቁርአን ውስጥ መውሊድ ስለማክበርና መደሰት በግልጽ አንቀጾች ሰፍሯል:: ዒደልፊጥርና ዒደል አድሃ ግን በግልጽ አልሰፈሩም:: በቁርኣን የመውሊድ መረጃ ከሁለቱ ዒዶች መረጃ በላይ ጠንካራ ነው:: ቢድዓ እያሉ የሚንጫጩ ሰዎች ይህንን እንኳ አያውቁም:: ሶላት እንኳ ስንት ረካዓ እንደሚሰገድ የመውሊድ ያህል በቁርኣን አልተብራራም:: ዙህር አራት ይሰገድ ሁለት ቁርኣን ውስጥ የለም:: እነዚህን የምናገኘው ሀዲሶች ውስጥ ነው:: ሀዲሶቹ የነቢያችን صلى الله عليه وسلم ቢሆኑም ቅሉ ሰብሳቢዎቹ አብዛኞቹ ከ200 ዓመታት በሗላ በግል ተነሳሽነት የሰበሰቡዋቸው ናቸው:: አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው:: ይህንን ያህል ክፍለዘመን ለምን ሳይሰበሰቡ ቆዩ? ለሚለው ሀዲሶችን መሰብሰብ ቢድዓ (ፈጠራ) ነው ብለው ያምኑ ስለነበር ነው:: ነቢያችን صلى الله عليه وسلم እንዳይሰበሰብ ከልክለው ስለነበር ሶሃቦችን ከዚያ በሗላ የመጡትም ፈሩ:: በመረጃ መዛባት በሙስሊሞች መካከል ከባድ ትርምስ ተፈጥሮ ብዙ ምእመን እርስበእርስ ተጋድ^ሏል:: ለዚህ መፍትሔ ቢሰጥ በሚል አፈታሪኩን (ሀዲሱን) ወደ ጽሑፍ ቀየሩት:: የሀዲሶች አንዳንድ መረጃዎች የጭቅጭቅ መንስዔ ሲሆኑ ጊዜ "ወትሮም ነቢያችን صلى الله عليه وسلم ያልሰበሰቡት ነገር ነው እያበጣበጠን ያለው የሚሉ በርካታ ድምጾች ያሉት ለዚህ ነው:: ሀዲስን መጣልም መፍትሔ አይደለም:: ከቁርኣን ማስቀደም ደግሞ የባሰ ፈተና ነው:: መፍትሔው በማያውቁት ነገር አለመዘባረቅ እና የሙስሊሞችን ክብር አለመንካት ነው::

ድርብ መውሊድ ነው ዛሬ በነቢ ሙሐመድ صلى الله عليه وآله وسلم መውሊድ ተደስተን ውለን ማምሻው ደግሞ በማትሪክ የተይሲር ዐብዱልቃዲር መውሊድ ሆነ:: አልሃምዱሊላህ:: ፊቅሕ መዝሃበ-ሻፍዒያ ሊያጠናቅቅ ደርሷል:: ተሰውፍ ጦሪቃ ወስዷል:: ማትሪክ መትርኳል:: መውሊዱ ተራዝሟል::

የኢትዮጵያ ድህነት በዓል ብዛት የመጣ ነው የሚል ሰው ይኖራል:: የበዓል ብዛት ግን አሪፍ የኢኮኖሚ ማነቃቂያ ነው:: ሰው ሲያርፍ እንደ ላም ተኝቶ አያመሰኳም, አያመነዥግም:: ያለረፍት ያጠፋል:: ስለዚህ የሚጠፋ ነገር አምርቶ ማቅረብ ነው:: የምርት demand ሲፈጠር የአቅርቦት ዘርፉ ይበልጥ ይንቀሳቀሳል:: ቁጠባ ኢኮኖሚን ይገ^ድላል:: ማጠፋፋት ግን ሥራ ይፈጥራል:: በእርግጥ እኛ በበዓልም በአዘቦትም ገበታችን የብላኔ ነው:: ሳንፈራ እንብላ:: እናብላ:: ጤናችንን እንጠብቅ:: ብዙ ስለበላህ አትወፍርም:: የአብዛኛው ምእመን ውፍረት የጭንቀት እንጂ የምግብ አይደለም:: የአላህ ጸጋ አልተነካም:: ስንት ፕላኔት ላይ ስንትና ስንት ጸጋ ተከማችቶ ገና መሬት ላይ ነን::

photo content

እኔ ስለበዓል እና መውሊድ ከቁርኣን አንስቼ ለመግቢያ ሳነሳ አንዱ inbox መጥቶ አቡዳውድ ቲርሙዚይ ይለኛል:: ከ114 የቁርኣን ምእራፍ ውስጥ አቡዳውድም ቲርሙዚይም ቡኻሪይም የሉም:: አታደናግሩ:: አቡዳውድ የተወለዱት ነቢያችን صلى الله عليه وسلم ካለፉ ከ200 ዓመታት በሗላ ነው:: ሀዲሳቸውን የሰበሰቡት መቼ እንደሆነ ገምቱ:: ቁርኣን ውስጥ ዒደልፊጥርም ዒደል አድሃም በቃል ደረጃ ብትፈልጉ አታገኙም:: በመውሊድ አትከራከሩ ነው ነጥቡ:: እንደውም በቁርኣን ጠንካራ ማስረጃ ያለው መውሊድና ቁርኣን የወረደበት ቀን ነው:: በዚህ መደሰት ከሰበሰብይችሁት ሁሉ በላጭ ነው ይላል ሱረቱል ዩኑስ:57 ላይ:: የቁርኣኑን ስንጨርስ ወደ ተከበረው ሁለተኛ መረጃ ወደ ሀዲስ እንመጣለን:: ያኔ እነ አቡዳውድ ይወሳሉ::

በጾምና በስግደት እንኳ ይገኝ ይሆን? የሚያስብልን ውድ ዕቃ ማለትም ጀነት በመሰ^ዳደብ የሚፈልግ ሰው ድፍረት ይገርማል:: እርስበእርስ ይቅርና ከሌሎች ኃይማኖቶች ጋር ሳይቀር ጥንቃቄ ይጠይቃል:: ሙስሊሞች የክርስቲያኖችን ነገር በመስደ^ብ ሊያሰልሙ እንደማይችሉ ሁሉ አንዳንድ ክርስቲያኖችም ነቢ ሙሐመድን صلى الله عليه وسلم በመስ^ደብ ልንጠመቅ የሚጠብቁ አሉ:: እንደውም ይብስ እልህ ውስጥ ነው የሚከተው:: ስ^ድድብ ከዕውቀት ማነስ ነው የሚመነጨው::: አንድ ምሳሌ ላንሳ:- ክርስቲያኖች ታቦት ይሸከማሉ:: ጦ^ር ሜዳም ሳይቀር ይዘው የሚሄዱባቸው አጋጣሚዎች አሉ:: ይህንን የሚተች ሙስሊም አይጠፋም:: ነቢ ዳውድ عليه السلام እና ጧሉት (ሳዖል) ታቦት ተሸክመው ጃሉትን (ጎሊያድን) ሊገጥሙ የሄዱበት ታሪክ በቁርኣን አለ:: ክርስቲያኖች ከዚያ ጀምሮ ይዘውት የመጡት ተግባር ነው የሚሆነው:: በጊዜ ርዝመት መሠረቱ ይልቀቅ አይልቀቅ ለሌላ ጥናት ቢተውም ግን መነሻ አለው:: "ታቡት" የሚለው ቃል ቁርኣን ውስጥ አለ:: ለያውም መላኢካዎች ናቸው ተሸክመው ያመጡት:: ታቡቱ ውስጥ የነቢያት ቅርሶች ነበሩበት:: ያንን ያዩ ጊዜ ልባቸው ተረጋጋ:: ጃሉትን ገጠሙና በጠጠር ረቱት ይላል ቁርኣን:: ይህንን ያመጣሁት ማወቅ ያሉብን በርካታ ነገሮች አሉ:: ባወቅን ቁጥር ልባችን ይረጋጋል:: ከስ^ድድብ እንወጣለን::

ላይቭ ፕሮግራማችን ከግማሽ በሗላ አልሰማሁም ያለች እህት አለች:: የድምጽ ችግር እንዳይኖር በሌላ ቴሌግራም እያደመጥኩ ነበር:: ምናልባት በቀጣይ ስልክ አስቀምጣለሁ:: ፕሮግራሙ ክርክር ለሚወዱ ማይማ
ላይቭ ፕሮግራማችን ከግማሽ በሗላ አልሰማሁም ያለች እህት አለች:: የድምጽ ችግር እንዳይኖር በሌላ ቴሌግራም እያደመጥኩ ነበር:: ምናልባት በቀጣይ ስልክ አስቀምጣለሁ:: ፕሮግራሙ ክርክር ለሚወዱ ማይማን ማደናገር ነበር:: መውሊድ በመጣ ቁጥር "ቁርኣን ውስጥ የተጠቀሱት ሁለቱ ዒዶች ናቸው" እያሉ የሚያደርቁን አሉ:: ቁርኣን ውስጥ ዒደልፊጥርም ዒደል አድሃም በግልጽ አልተጠቀሱም:: በግልጽ "መደሰቻ በዓል - ዒድ" ተብሎ የተጠቀሰው የፋሲካ በዓልን ነው:: ቀጥሎ የተሻለ ግልጽነት ያለውና መደሰቻ ተብሎ የተወሳው መውሊድ ሲሆን ይህም በሱረቱል ዩኑስ 57 እና 58 ላይ እናገኘዋለን:: ዒደልፊጥርም ይሁን ዒደል አድሃ ሀዲስ ውስጥ ነው የምናገኛቸው:: Primary source የሆነው ቁርኣን ስለበዓል አጀንዳ ያላደረገው ያን ያህል መሠረታዊ ጉዳይ ስላልሆነ ነው:: ለማይማን ቁርኣን ውስጥ ይህንን በዓል አክብሩ ያንን አታክብሩ የተባለ የለም:: ካለም እላይ የተጠቀሰው የነቢ ዒሳ عليه السلام የማዕድ መውረድ በዓል ነው:: ፋሲካ ሊሆን ይችላል:: ይህም እራሳቸው ተዓምሩን እንይ:: ዕለቱን በዓል እናደርገዋለን ሲሉ ... አላህም ይህንን በዓል ብትተውት አይቀጡ ቅጣት እቀጣለሁ ብሎ ማሳሰቢያ አክሎበታል:: ትኩረቱ ቃልኪዳኑ ላይ ነበር::

ስለመውሊድ እና ዒድ ትንሽ እናወራለን::

መ-ጽሓፍ ስትገዙ Bot አሞላልም ይሁን ሌላ ጥያቄ ካላችሁ በቴሌግራም ግቡ:: ከፍሎ የማይደርሰው አየር ላይ የሚቀር አንድም ሰው አይኖርም:: ምክንያቱም ከባንክ ስቴትመንት ስለምንነሳ Spelling ሳይቀር የባንኩን ነው የምንጠቀመው:: የታዳጊ 825 ብር የአዋቂ 4ኛ እትም 900 ዋጋ ኢትዮጵያ ውስጥ የትም ከነማድረሻው ጭምር ነው CBE: 1000787104464 Mr Teyseer Abdulkadir Nureddin ቦቲ Bot 🤖 https://t.me/MEGENZEBDeliveryBot