fa
Feedback
Hasen Injamo

Hasen Injamo

رفتن به کانال در Telegram

Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Hasen Injamo

کانال Hasen Injamo (@haseniye) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 751 مشترک است و جایگاه 8 514 را در دسته اقتصاد و امور مالی و رتبه 2 292 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 751 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 38 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 27.29% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.88% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 026 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 048 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 35 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اقتصاد و امور مالی تبدیل کرده‌اند.

14 751
مشترکین
+224 ساعت
+197 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
ያኛው ይቆረ^ጣል ቢባል ቶሎ እንዲደርቅልኝ አ(ስ)ቀድሙኝ የሚል ይበዛ ነበር::
ያኛው ይቆረ^ጣል ቢባል ቶሎ እንዲደርቅልኝ አ(ስ)ቀድሙኝ የሚል ይበዛ ነበር::

ስለኮንትሮባንድ አዋጅ ዝም አልክ ላላችህኝ ... ኮንት^ሮባንድ ማለት ለእኔ:- - ጤናን ሊጎዱ የሚችሉ ማናቸውም ነገሮች ያለበቂ ፈቃድ መሸጥ, መደለል, መላክ, ማስመጣት - የጦር መሳሪያ ዝውውርም ይሁን ምርት - የገንዘብ ኖት ሕትመትም ይሁን ዝውውር ናቸው:: ሦስቱ ነገሮች በግለሰቦች እጅ የገቡ ወቅት ሁላችሁም እራሳችሁን ጠብቁ:: ማንም አይጠብቃችሁም:: መንግሥት ለግለሰቦች የሰጠ ወቅት መንግሥትነቱን ያጣና አስፈጻሚ ፖሊስ ይሆናል:: መድኃኒት እና የጦ^ር መሳሪያ ለግለሰብ ከተለቀቀ ፋብሪካ የከፈቱ ሰዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ የግድ ጦ^ርነት መክፈትና በሽታ መፍጠር ይኖርባቸዋል:: ካልሆነ ፋብሪካዎቹ ይዘጋሉ:: ገንዘብም ለግል ባንኮች የተፈቀደ ወቅት ኮርፖሬቶክራሲ ይወለዳል:: በመሆኑም ከ100 ሺህ ብር በላይ በግል መያዝም ይሁን ማዘዋወር አይቻልም ከተባለ naturally የግል ባንኮችንም ይመለከታቸዋል:: የግል ባንክ ማለት በብሔራዊ ባንክ ስር የተ70-ሰቡ ግለሰቦች ማለት ነው:: ለግል ትርፍ ነው የሚሮጡት:: ዲቪደንዱ ወደ ግለሰቦች ይገባል:: አይግባ ሳይሆን የባንክ ድርሻ የሌላቸው ሰዎችም ነጻነት ይጠበቅ:: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲነካ አይስማማኝም:: ምክንያቱም ሲያተርፍ ትርፉ ወደ መንግሥት ካዝና ይገባና በኢንፍራስትራክቸር በኩል እናገኘዋለን:: ዓለምን በጦ^ርነትና ሰቆቃ ጀሃ^ነም ያስመሰላት ሦስቱ ነገሮች በግለሰቦች እጅ ገብተው ነው:: እንጂ ኬላ ወጥረህ 20 ካልሲ, አራት ሞባይል ስልክ, 80 ደብተር ተዘዋወረ ብሎ መውረስ ልክ ሰውነት ላይ የደም ዝውውርን እንደማቆም ስለሆነ ኢኮኖሚው በራሱ ጊዜ ስትሮክ ይመታዋል:: ካልሲ ስትቆጥር ሙስናው ይቆጣጠርሃል:: በዚህ ስታፍነው በዚያ ይቀደዳል:: ሰዎች ተዘዋውረው መሥራት አለባቸው:: ለሥራ በተንቀሳቀሱና በሥራ በተጠመዱ ቁጥር ወንጀል ይቀንሳል:: ጤና ይስተካከላል:: ተፈጥሯዊ የገንዘብ ሕትመት ማለትም ምርት ይጨምራል:: ምርት ሲጨምር ግሽበት መቀንሱ አውቶማቲክ ነው:: የሆነ ጊዜ የጦ^ር መሳሪያ ምርት የአዋጭነት ጥናት ጀምረን ዓለም ላይ የት የት ልንሸጠው እንደምንችል, እነማንን ማጋጨት እንዳለብን, ከእኛ ስንት ሰው እንደሚሰዋ ሁላ ሠርተነው በጣም ያዋጣል:: ከኛ ከኢንቨስተሮቹ በኩል የሚሰዋ ሰው "Human cost” ብለን እንደ ማንኛውም ወጪ ይዘነዋል:: ማካካሻው ኢንሹራንስ ነው:: አሪፍ ቢዝነስ ነው:: በጣም የቆየ ጥናት ስለሆነ update ይደረግልኝ የሚል ሰው ኮሜንት ላይ ሲዖል እንገናኝ ብሎ ይጻፍ:: ሲዖል የሰሜን ኮሪያ ዋና ከተማ ነው ደግሞ::

በዚህ ዘመን ሥራ ስትሠሩም ይሁን ብር ስትይዙ ጩኸት ባታበዙ አሪፍ ይመስለኛል:: ክ^ፉ ሰው እና ክ^ፉ መናፍስት ትስባላችሁ:: የትልቅ ግብር ከፋይ ፕሮግራምም ላይ ባትገኙ, ከተገኛችሁም በተወካይ ቢሆን:: ታዳሚው ሁላ ጤ^ነኛ እንዳይመስላችሁ:: በየት በኩል ስንት ልፍለጠው? በምን ላስወንጅለው የሚል አይ^ጥ ሞልቷል:: በየሚዲያው ቫይራል እወጣለሁ ብለህ ቫይረስ አትሰብ-ስብ:: ገና በቲቪ ወይም በሆነ ቻነጭ ምስል ሲያዩ "ምን ይመስላል? ምን ትመስላለች? ..." እያሉ የሚያሽሟጥጡ ሰዎች አልገጠሟችሁም? ገና እንዳዩ ነው እኮ:: በምንም ሳያውቁዋቸው ዝም ብለው የሚጠሉ ሰዎች አሉ:: እስቲ የት እንደሚደርስ እናየዋለን ብሎ ውድቀትህን የሚጠባበቅ ሀ-ሲድ በሽ ነው:: ለማክሸፊያ ምጽዋትና ጸሎት አብዙ:: እና ሲጠቃለል ብር ጩኸት ቢወድ ኖሮ ባንክ ቤት ውስጥ ሙዚቃ ይከፈት ነበር:: ኢትዮጵያ ውስጥ አንድም ቀን በቲቪ አይታችሗቸው የማታውቁዋቸው ቢሊየነሮች በብዛት አሉ:: ወይ በለቅሶ ወይ በሰርግ አጋጣሚ ነው የምታውቋቸው:: ዶሮ ለአንድ ሕጻን የማይበቃ እንቁላል ለመጣል በማስካካት መንዱሩን ሁላ ትበጠብጣለች:: ለመንደር ሁላ የሚበቃ ወተት የምትሰጥ ላም ግን ድምጿ አይሰማም ይባላል:: ሁለቱም እንደየአፈጣጠርና ጥቅማቸው ቢሆኑም ቅሉ ... አፋ^ኝና አዳኝ በበዛበት በዚህ ወቅት ሰተር ማለት ሸጋdha.

ዋልያ ዘመን ዋልያ መጻሕፍት "ዋልያ ዘመን" በሚል አዲስ እና ቀጣይነት ባለው ዝግጅት የሀገር ባለ ውለታ የሆኑ በሥራቸው ብዙ አበርክቶ ያለቸውን እንግዶችን ይዞላችሁ ይቀርባል:: በዚህ ዝግጅት የሚጋበ
ዋልያ ዘመን ዋልያ መጻሕፍት "ዋልያ ዘመን" በሚል አዲስ እና ቀጣይነት ባለው ዝግጅት  የሀገር ባለ ውለታ የሆኑ በሥራቸው ብዙ አበርክቶ ያለቸውን እንግዶችን ይዞላችሁ ይቀርባል:: በዚህ ዝግጅት የሚጋበዙ እንግዶቻችን የተለያየ ልምዶቻቸውን የሚያሰቀስሙን፣ ከተሞክሯቸው ትይዩ ደግሞ እውቀት የሚያስጨቡጡን ይኾናል።  እርስዎም ቅዳሜ ከሰዓትዎን ከኛ ጋር ቢያሳልፉ አብዘተው ከሚያተርፉት ይሆናሉ። የዕለቱ ተጋባዥ እንግዳ:- 👉 ደራሲ ፍቅረማርቆስ ደስታ ቦታ፦ 4ኪሎ ኢክላስ ሕንጻ ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ ቀን እና ሰዓት፦ ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 8:30 ጀምሮ                            ዋልያ መጻሕፍት

ዲናሬ ዳታቤዝ ላይ ብዙ ጅምር ኢሜይሎች አሉ:: ለሙከራ ይሁን ለምር ባይታወቅም ኢሜይል verify ካደረጋችሁ በሗላ ነው ወደ ምትፈልጉት አገልግሎት የምትገቡት:: ምናልባትም Spam ፎልደራችሁ ውስጥ
ዲናሬ ዳታቤዝ ላይ ብዙ ጅምር ኢሜይሎች አሉ:: ለሙከራ ይሁን ለምር ባይታወቅም ኢሜይል verify ካደረጋችሁ በሗላ ነው ወደ ምትፈልጉት አገልግሎት የምትገቡት:: ምናልባትም Spam ፎልደራችሁ ውስጥ ገብቶም ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ ኢሜላችሁ ውስጥ ገብታችሁ Verify በሉት:: ብርቅ እና የተለየ ሳይንስ እየነገርኳችሁ ሳይሆን አገልግሎቱን ከስር ከስር ለመመለስ ነው:: ጸ^ብ ማለቴ ጠ^ብ እርግፍ አድርጌ ለማገልገል ነው:: Portal sign in የሚለው ለኢምፖርት ጭነት የሚያገለግለው ቲሆን Book consultation የሚለው የምክር እና ስልጠና ምድብ ነው::

ልጄ የዌብሳይ+ፖርታል ከሠራልኝ በሗላ መርቅኛለሁ:: ፖርታሉ ብዙ ዳታ ስለሚሸከም መግባት የሚቻለው በ TIN ነው:: ምክንያቱም የምንሠራው ከትላልቅ ኩባንያዎች ጋር በመሆኑና ሁሉም TIN እና ኢሜይል የግድ ስለሚኖረው ሥርዓት ያለው አካሄድ የግድ ነው:: ከየትም ሀገር ሆነው ጭነታቸውን መከታተል ይችላሉ:: - ንግድ ፈቃድ ጋር ባለሙያ አለ:: - ገቢዎች ጋር ባለሙያ አለ:: - ትራንዚት ባለሙያ አለ:: - የባንክ ጉዳይ ባለሙያ አለ:: - ቻይና ሶርሲንግ ባለሙያ ከእነ ቢሮ እና መጋዘን ጭምር አለ:: -> መርከብ የግድ ይለናል:: ለአሰብ መዝመት አሁን ነው:: ልጆች የቅድሙ ቁርስ ሰላጣ አልነበረም እንዴ? የሆነ ሌላ ድሮ የማውቀው ዓይነት ጣዕም ነበረው:: እግረ መንገዴን ሻሸመኔን ልያት ብዬ ወርጄ ሰላጣ ብበላ ጉድ ሳልሆን አይቀርም:: ሕዳሴ ነሽ የሚል መርከብ ይታየኛል:: ለማንኛውም ምክር የምትፈልጉ ኢሜይልና ስልክ ብቻ በቂ ነው:: ጭነትና ምክር ለየብቻ ናቾ:: የዌብሳይት ሊንክ በኮሜንት! ዲናሬ https://dinaret.com

መንግሥት ግብር እና ታክስ እንደማያሳድግ እየገባው ይመስለኛል:: ሰሞኑን አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን እያየሁ ነው:: የግብርና ማሽነሪና ግብአት ከቀረጥ ነጻ ሊደረጉ እንደሆነ ይሰማል:: ጥሩ ነው:: ነዳጅ በፍራንኮ ቫሉታ ሊገባ መሆኑን ሳነብ ቆሜ አጨብጭቤያለሁ:: ነዳጅ ላይ የብር ድጎማ ቢነሳ//ባይነሳ የሚያመጣው ለውጥ የለም:: ከድንበር ውጭ በዶላር የሚመጣ ነዳጅ ላይ የኢትዮጵያን ብር ብትቆልል በነጻ ብታድል ውጤቱ እምብዛም ነው:: ዋጋው የግሽበት መለኪያነት ከማገልገል ውጭ ኢኮኖሚው ላይ ጠብ የሚል አይኖረውም:: ብር ከድንበር አይወጣማ!! ማትስ ነው ጨዋታው ስልህ! ውጪ ያለ ዶላር ወደ አገር ውስጥ ሲገባ ተመዝግቦና ቻርጅ ተከፍሎበት ነው:: አገር ውስጥ ቢገባም ለመገበያያነት አይውልም:: ተመልሶ ቻርጅ ተከፍሎበት ይወጣል:: በመሃል ሙስና ሁላ ይታከልበታል:: So ይህንን ደርሶ መልስ ሳይንከራተት ፊያት ዶላሩን እዚያው ኩዌት ወይም ኳታር ወርውሮ ነዳጁን ይዞ መምጣት:: መ-ገንዘብ 2 ላይ ስለ ሆላንድ በሽታ ያነበባችሁ ይገባችሗል:: በዚህ የኢኮኖሚ በሽታ ዋነኛ ተጠቂ ኩዌት ነች ብያችሗለሁ:: ኩዌት ላይ ዶላሩ ተከምሮ ተከምሮ ኢንቨስትመንት ዜሮ! ነዳጅ በፍራንኮ ከገባ ብዙ ነገር ያቃልላል:: ማትስ መሥራት አለብን:: በማ^ፊያ እና በበደል በሚተዳደር ዓለም ላይ መላእክት መላእክት መጫወት አያዋጣም:: በድህነት ቢዘፍቀን እንጂ:: Already በባ^ርነት ስር ነን ያለነው:: ሱፍ በክራባት ሁላ አያምርብንም:: ባሪ^ያ ሲኮራ ማጭድ ይታጠቃል ዓይነት ነገር ነን:: ኤለን መስክ ጋር የተከራከሩበትን ጉዳይ በድምጽ ብገባ ሁላ ደስ ይለኛል::

ሥራ ጀማሪ ከሆናችሁ ምክር መጠየቅ ያለባችሁ:- ኮንትሮ^ባንድ የሠራ, ሱቅ ታሽጎበት survive ያደረገ, ከስሮ የተነሳ ሰው ጠይቁ:: The hardest way ነው የተማረው:: አቅልሎ ይነግራችሗል:: ድፍረት እስከ ቱቲ ያስታጥቃችሗል:: የትላልቅ ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ ወይም በግሉ ድርጅት ከፍቶ ያልሠራ ተቀጣሪ የሆነን ሰው አትጠይቁ ባይባልም ግን ስሙት:: ሰምታችሁ ዋጥ አድርጉት:: ሌላ ሰው ባደራጀው ድርጅት ውስጥ ስኬታማ ሥራ አስኪያጅ ቢሆን እንኳ በግሉ ቆሞ አልሄደም:: ከቦዪንግ ሥራ አስኪያጅ የሊስትሮ ሳጥን ሥራ አስኪያጅ ምክር ይሻላችሗል:: በኮንፊደንስ ሁለቱ አይገናኙ:: የቦዪንጉ ለብቻህ ወጥተህ ሥራ ብትሉት ሊቸገር ይችላል:: ምክር ብትጠይቁት መነሻ ወጪ ያንርባችሗል:: ከንግድ ፈቃድ ያስጀምራችሗል:: እዚህ ጋር የጠቀስኩላችሁ ሁለት ነጥቦች ወሳኝ ናቸው:: በከፍተኛ መነሻ ወጪ ከጀመራችሁ ሥራውን ሳታውቁት መነሻ ላይ ትመታላችሁ:: ሥራችሁ ፈቃድ እየከፈቱ መዝጋት ይሆናል:: ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ ከንግድ ፈቃድ ከጀመራችሁ ስደት ያምራችሗል:: ሥራው ሳይገባችሁ ንግድ ፈቃድ ስታወጡ ገቢዎች ሚኒስቴር ሥሩ አትሥሩ አያውቅላችሁም:: ገቢዎች ጥፋት አለበት ብዬ አልወስድም:: ምክንያቱም ሥራው ገብቶኛል, ልነግድ ብላችሁ ፈቃድ አውጥታችሗላ!!! ያስገባላችሗል:: አናፍጦ ያስተምራችሗል:: ተናፍጣችሁ ካለፋችሁት ጀግና ናችሁ:: ኢትዮጵያ ውስጥ ጭንቅላቱን 7% ሊጠቀም የሚችለው ነጋዴ ይመስለኛል:: ፐርሰንቱ በጥናት የተደገፈ ባይሆን ተባብረን እንደግፈው:: ከዚያ ውጭ ያለው ለኮፊያና ለጥምጣም ነው የሚጠቀምበት:: ከነጋዴ በተሻለ የሚጠቀመው ጫካ የገባ ሽ^ፍታ ነው:: ነጋዴ ማለት ከሕግ ይልቅ የሕግ ክፍተቶችን ልቅም አድርጎ የሚያውቅ ማለት ነው:: መንግሥት የፈለገውን ዐይነት ሕግ ቢያወጣ ነጋዴ ክፍተቱን ያውቀዋል:: ጦ^ርነት ሁላ አይፈራም:: ተቀጣሪ ከሆነ ሰላም እስኪወርድ ቁጭ ብሎ ይጠብቃል:: ቻይኖችን ብታዩ ከኢትዮጵያውያን በላይ የሕግ ክፍተቶችን ጥንቅቅ አድርገው ያውቃሉ:: አሁንማ ሕግ አስወጪ ሁላ ሆነዋል:: መንግሥታቸው ለኢትዮጵያ እንጢቅ ብድር አበድሯል:: ከ$51 ቢሊዮን ዶላር ብድር ውስጥ ግማሹ የእነርሱ ነው:: ሲጠቃ-ለል በራሱ ቀጥ ብሎ የቆመ ሰው ምክር የተሻለ ነው::

አላገባሁም:: የሆነ ብር ነበረኝ:: መኪና ላስቀድም ወይስ ቤት ልሥራበት? እንደየሰው እና አካባቢው ቢለያይም እኔ ግን መኪና ነው የማስቀድመው:: ወንድ ልጅ እግር እንጂ አገር የለውም እንደሚባለው ወንድ የትም ቢሄድ ጠፉን ሁላ እያቀና ሀገር ማድረግ ይችላል:: እግርህ ይቅደም:: በዚህ ዘመን ሞባይል የሌለው ጆሮ እንደሌለው ሁሉ ... መኪናም የሌለው እግር አለው ማለት አያስደፍርም:: እንደውም ልበጭርቅበትና ቅድሚያ የሚሸማተረው ሦስተኛው እግርህ ነው:: ቤት ተቀዳሚ ነገር መሆኑ አያጠያይቅም:: ለዚህኛው የኢኮኖሚ ሲስተም ቤት መሠረታዊ ነገር እንደሆነ ደጋግመን አንስተነዋል:: ሆኖም ግን ያለ እግር ቤቱም ሴቱም አይሰሉም:: እግር (መኪና) የግድ ነው:: ዘንድሮ በመኪና እንኳ መፈጸም ያልተቻለ ሀጃ በቸርኬ ከባድ ነው:: ቴሌኮሙ ቢዘምንም የመኪና ሚና ገና ነው:: መኪና ማለት መለስተኛ ቢሮ ነው:: ስለዚህ መኪና ግዛ:: ተሯሯጥ:: አስሩጠው:: መኪናውን ለተፈጠረለት ዓላማ አውለው:: ንዳው:: አልኩህ እኮ ንዳው:: ፀሓይ የለ ውርጭ, ዝናብ የለ ጭጋግ, ሰርግ ይምጣ ለቅሶ, ምጥ ይምጣ ፍልጥ ... አያሳስብም:: ሩቅ የሚባል ሰፈር የለም:: ታዲያ መኪናህን የሴት መኪና እንዳታደርገው:: ስታጥብ እንዳትውል:: ገና ቤት አልገዛህም እኮ:: ሩጫ ላይ መኳኳል አለ እንዴ? ሩጥ ተባል:: ጎን ለጎን ሴት አታሯሩጥ:: በትእግስት ሠርተህ በመኪናው ላይ ቤቱ የመጣ ወቅት ሴቱ ያሳድዱሃል:: ናማ! ሴቶቹን አስተውለሃቸዋል? እንዴት እንደበለጡህ? ወጥረው ሠሩ:: ንብረት ያዙ:: ያንንም በጀነት ሰንጢ የተሠራ ነገር ያዙ:: የቀራቸው ፍቅር እና አፍቃሪ ባል ነው:: ካንተ ሌላ አይፈልጉም:: አንተም ወጥረህ ሥራ:: ወጥራ የሠራች እና የተማረችዋ ጋር ተወዳጅ:: የምትለዋወጡት ፍቅር ብቻ ነው:: መቼም አትሰለቻቹም:: መቼም አትዘጋጉም:: መሃል ሰፋሪዋን ግን አደራ:: ወይ ጥንቅቅ አድርጋ የተማረች:: ወይ በጣቷ የምትፈርም ትሁን:: ሳታገባ ኪሎሜትር የቆጠረችም ከbad ነች:: ስትጃጃል ያለፋትን ሁሉ ካንተ ትፈልጋለች:: እና መኪና የዝነጣ ግዛ አሉህ ደግሞ:: የሥራ ነው የተባልከው:: ቢዝነሱ በዝነጣ የሚመጣም ከሆነ መብትህ ነው:: ድሮ መኪና ብርቅ በነበረ ዘመን ጫማ ነበር የሚታየው:: ብድር ለማግኘት ወይም እቃ ለመሸጥ ጫማ ወሳኝ ነበር ነበር:: አሁን መኪና ነው:: ካንተ ጋር ቢዝነስ የሚሠራ ሰው መኪናህን እንጂ ቤትህን አያውቅም:: ቤትህን የሚያውቁት ባንኮች ናቸው:: ቤትህን ለባንክ ... መኪናህን ለማርኬቲንግ ዓላማ ብለህ ነው የምትገዛው::

አንዳንድ መንግሥት ... መንግሥት የሆነ የሚመስለው ቁጥጥርን ማጠንከር ተፈሪ የሚሆን ይመስለዋል:: ቁጥጥር ሊያስፈልግ የሚችለው ፍላጎትና አቅርቦት ሲቀራረቡ ነው:: ማለትም ቢያንስ መሠረታዊ ፍላጎት መቀራረብ አለበት:: ሕዝባችን ጠዋትና ማታ የሚኳትነው መሠረታዊ ፍላጎት ለማሟላት ነው:: ምርትህ ከሚያድገው የሕዝብ ቁጥር ጋር እየተጣጣመ ሳይሄድልህ የቁጥጥር አዋጅ ብትደረድር አዋጅ አውጪውና አ(ስ)ፈጻሚው ቀድመው ያፈርሱታል:: ምግብ, ልብስ, መጠለያ ከተሟላ በሗላ ሌ^ብነት ከመጣ እጅ ስለመ^ቁረጥ እናወራለን:: የቤት ኪራይ የሚያጣድፈው ኃላፊ ላይሰርቅ አይችልም:: መሬት የመንግሥትና የሕዝብ የተባለ ቢሆንም ግን የካድሬ ሆነ:: ምእመኑ መሬት ሳይኖረው ቤት ሥራ ተባለ:: ምን ላይ ይሥራ? እኮ ምን ላይ? መሬት ቢኖረው እንኳ የጭቃ ቤት እንዲሠራ አይፈቀድለትም:: የግንብ ቤት ደግሞ እየተሠራ አይደለም:: ግለሰቦች ከሺህ ግለሰቦች ቀብድ ሰብሰበው እየሞከሩ ቢሆንም ከስር ከሚመጣው ተወላጅ ጋር በፍጹም አይጣጣምም:: መንግሥት ደግሞ ኃይሌን ገ/ሥላሤ ሊሠራው በሚችለው ሪዞርትና ሎጅ ላይ ቢዚ ሆነ:: ወንዱ ምእመን ሚስቱን ሪዞርት ወስዶ ሊያስረግዛት ይችል ይሆናል:: የተረገዘ መወለዱ አይቀርም:: ለኦፕራሲዮን 400K ከፍሎ ይወለድ:: ጥሩ:: ያው ልጅ መግዛት በሉት:: ግን እሺ ልጁ የት ይደግ? ሪዞርቱ ማሳደጊያ አለው ወይ? የጅል ጥያቄ ጠየቅሁ አይደል? ይቅርታ:: ሺህ የውጭ ኩባንያ ብናስገባ ሁለት ነገር ነው ይዘው የሚመጡት:: ተጨማሪ ሰው እና ዶላር:: ዶላሩ ኢትዮጵያ ገብቶ ምንም አይሠራም:: ተመ-ልሶ ይወጣል:: የሚመጡ ሰዎች ሊመጠምጡ እንጂ ሊኖሩ አይደለም:: አጥንተው የሚመ-ጡት የተነባበረ የቁጥጥር ሕግና መመሪያ ክፍተቶችን ከባለሥልጣናት ጋር ተጠቅሞ መሰወር ነው:: ስለዚህ አስቻይ የሥራ ምሕዳር ፈጥሮ ምእመኑን በሥራ ማሯሯጥ ነው:: በነገራችን ግርጌ ሰሞኑን ገቢዎች እየሄድኩ ነበር:: ኧረ ዛሬም ሄጃለሁ:: ግንቦት ስለሆነ ነው ወይስ ምን ተፈጥሮ ነው ጸጥ ረጭ ያለው:: መታወቂያ አስይዛችሁና ተመዝግባችሁ በባጅ ነው የምትገቡት:: Almost ወረፋ የለም:: ሐምሌና ጥቅምት እንደዚያ ይሆን ይሆን? እንጃእ:: ከሆነ ልናድግ መንገድ ጀምረናል ማለት ነው::

አንድን ሌ^ባ እንዲይዙ አስር ሰዎችን ብትልኩ ሌ^ቦቹ 11 ይሆናል:: የሥራ እንቅስቃሴ ተገድቦ የመንግሥት ሥራ ሌ^ቦችን ማደን ከሆነ ኢኮኖሚው << ሌ^ብነት መር >> ኢኮኖሚ ይሆናል:: ሌ^ብነት እንደ ፕሮቶዞኣ ይባዛል:: እንደ ወረርሽኝ ተዛምቶ መንግሥትን ይገለብጣል:: ሌ^ብነቱ inner circle ውስጥ ይገባል:: ኢሕአዴግ ጉድ የሆነው እንደዚያ ነው:: የ 1997 ምርጫ ለኢሕአዴግ መውደቅ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል:: ኃላፊዎቹ "ለካ መውደቅም አለ" ብለው በተለይ በአደራ አስተዳደር ወቅት ከዘረ^ፋ ውጭ ሌላ ሥራ አልሠሩም:: ስለ ኢሕአዴግ ዲሞግቱና ሲያንቆለጳጵሱ ጣዖት እንዳይሆንባቸው ብለህ የምትሰጋላቸው ሰዎች ቢሮ ግን የግል ሥራ ነው የሚሠሩት:: ሀገር መምራት ትተው ኑሮኣቸውን መምራት ውስጥ ገቡ:: የተማረረው ሕዝብ ተንቤን ደርሶ ነው የተመለሰው:: ትግራዋይ የተጠቀመ ይመስል:: በስሙ ነገዱበት:: ጦሱ ዛሬም ድረስ አለ:: አሁንም ሌ^ባን ሊይዙ የምታሰማራቸው ሰዎች ከሌ^ባው የባሱ ባለ ሁለት ስለት ሌ^ቦች ናቸው:: ወዲህ ለኪሳቸው ነው የሚሮጡት:: የከፋው ስለት ደግሞ የመንግሥት inner መዋቅር ያውቃሉ:: ማን ባለሥልጣን የት እንደሚጠጣና እንደሚቅም .. ማን የማንን ሚስት እንደሚቾምስ ያውቃሉ:: (በጭረቅ የግድ ይላል):: እና ከተራው ሌ^ባ ይልቅ አደገ^ኞቹ አ(ስ)ፈጻሚዎቹ ናቸው:: ሌ^ባው ብር ሊዘር^ፍ ይችላል:: እነዚያ ግን አስተዳደሩን ነው የሚዘርፉት:: ከፖለቲካ ምሕዳር ይልቅ የሥራ ምሕዳር ከሰፋ ሌ^ብነት dramatically ይቀንሳል::

photo content

ዲናሬ የኢምፖርት ማሳለጥ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል:: ቻይኖች በሀገራችን ፋብሪካና በኮንስትራክሽን አካባቢ በውድድር አላስቀምስ ብለዋል:: አልቻልናቸውም:: በመንግሥታቸው እገዛ ደህና ይዘዋል:: ተቃውሞ
ዲናሬ የኢምፖርት ማሳለጥ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል:: ቻይኖች በሀገራችን ፋብሪካና በኮንስትራክሽን አካባቢ በውድድር አላስቀምስ ብለዋል:: አልቻልናቸውም:: በመንግሥታቸው እገዛ ደህና ይዘዋል:: ተቃውሞ የለኝም:: እኛም በምርትና በአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና መወዳደር የግድ ይላል:: አንድ ኢምፖርተር ጥያቄ ካቀረበበት ጀምሮ ዕቃውን ጭኖ አምጥቶ ሽጦ ገቢዎች ኦዲት ድረስ ፍኖተ ካርታው መስተካከል አለበት:: ከአራት ዓመት በሗላ ገቢዎች ጋር ከሚይያዝ ዛሬውኑ አስተካክሎ ቢጭን ሸጋ ነው:: ዛሬ በቃ ይጫን ይጫን ተብሎ ጉምሩክ ላይ በ Under invoice ቢያልፍ ነገ ገቢዎች ጋር በ capital injection ይያዛል:: ምክንያቱም የ ቀረጥ ልዩነት (Customs difference) ማጣፊያ ስለሚያጥር:: የኢምፖርት ሙሉ ጉዳያችሁን አንድ ዌብሳይት ፖርታል ላይ ብቻ ትጨርሳላችሁ:: የግድ ኢ-ሜይል ያስፈልጋችሗል:: እኛ ባናስገድዳችሁ Ethiopian Single Windows 🪟 (eSW) ያስገድዳችሗል:: So እኛም ጋር በኢሜይል አካውንት ትከፍቱና ሙሉ ፕሮሰሳችሁን ትከታተላላችሁ:: ሊንክ በኮሜንት

ትንንሽ ሳንቲሞች እና ብሮች መጥፋት ግሽበትን የሚያባብስ ኑሮን የሚያስወድድ የሚመስለው አለ:: ኑሮን ከፊያት ብር ማያያዝና የዩኒቨርሲቲ ትራዲሽናል ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ሰለባ የመሆን ችግር ነው:: እዚህ የምታገለው በዩኒቨርሲቲ ዲናቹራላይዝድ ሆኖ የወጣን ቴስታታ ለመመለለስ ነው:: አይደለም አንድና አምስት ብር ቀርቶ መቶ ብር ቢጠፋ ግሽበት ጋር ያለው ቁርኝት ብዙም አይደለም:: አመላካች ሊሆን ይችል ይሆናል:: መቶ ብር ማለት "100" የሚባል ቁጥር ማዘዋወሪያ ትሪ ሲሆን ስዕሎቹ ማጀቢያ ናቸው:: ያ አጀብ ወደ ሞባይል መጥቶ በፍራክሽን ደረጃ መክፈል አስችሎናል:: ቡና ስንጠጣ 35.03 መክፈል እንችላለን:: ስለዚህ ሦስት ሳንቲም አለ:: በብረት ላይ ተጨፍልቆና የሆነ የቆቅ ወይም ሚዳቆ ስእል ሲያጅበው ስላላየን ይሆናል:: የግሽበት ዋነኛ መንስዔ ለሥራ አለመንቀሳቀስ ነው:: ለሥራ እንቅስቃሴ የሚገድቡ መሥሪያ ቤቶችም ጭምር ግሽበት ፈጣሪ ናቸው:: የሆነ ልግመኛ ሚኒስትር ካለ በትብብር ሊቀነደብ የግድ ይላል:: (የውበት ሳሎን ውስጥ ነው ደግሞ):: ባለሥልጣናት ጭምር ሰብ-ስበን ማሰልጠን አለብን:: ግሽበት በምን እንደሚፈጠር ከነመፍትሔው በመ-ገንዘብ 2 ውስጥ አስፍሬያለሁ::

አንድ ወንድም inbox ትንሽዬ አንድ ሚሊዮን አካባቢ የምትሆን ብር አለችኝ:: ትንሽ ጨማምሬ መኪና ገዝቼ ተፍ ተፍ ልበል ወይስ ዶላርና ወርቅ ልግዛበት? -> ምንም አይገናኙም:: ወርቅም ይሁን ዶላር የሚገዛው ሥራ ለመሥራት ጊዜ, ቦታና ሁኔታ ያልተመቸው ሰው ነው:: ወርቅ ማለት እንቅስቃሴ ነው:: ተፍ ተፍ ማለት ነው:: ልክ ብራችሁ የመኪና ደረጃ ሲደርስ ግዙበትና ሥሩ:: መኪናው ማስያዣ ሁላ ሊሆን ይችላል:: ትንሽ በት በት ትሉና ሁለት ታደርጉታላችሁ:: ያኔ ኮንዶሚኒየም ስቱዲዮ መግዣ ጋር ትደርሳላችሁ:: ሁለቱም የካፒታሊስት ግብኣቶች ተሟልተዋል:: ምንና ምን? በመኪናው ስትሠሩበት ንግድ ፈቃድ አላችሁ:: ቤት ስትጨምሩ ኮላተራል ተሟላ:: ከዚህ በሗላ ሲስተሙ መግቢያ ጋር ደርሳችሗል:: የምነግራችሁ ባዶ ማነቃቃት ወይም የማይሳካ አካሄድ አይደለም:: በጣም ጤናማና ሊተገበር የሚችል ነው:: በዚህ በነገርኳችሁ ወቅት ትቅሙም ከነበር ከጀማው ተለዩ:: ትጠጡም ከነበር ከጀማው ተለዩ:: ጮማ ቆርጣችሁ በሽርጥ የምትቅሙበት ወቅት እንዲመጣ ከፈለጋችሁ ለተወሰኑ ዓመታት ውጡ:: እንዴት እንደምትወጡ እመለስበት ይሆናል::

ደሃም ሆነህ ቅጥርም ጠልተህ አብረው አይሄዱም:: ወላጆችህ ድህነት አውርሰውህ ይሆናል:: ያው እነርሱም ወርሰው ወይም ችግሮች ተደራርበውባቸው ይሆናል:: ሀገሪቷም ድሃ ነች:: Well, ታዲያ አንተም ድህነትን ማውረስ አለብህ ወይ? ከተባለ ማንም አይፈልግም:: ጅል ጥያቄ ነው:: ድሃ ከሆንክ የመጀመሪያው step መቀጠር ነው:: ስትቀጠር ደመወዙን ታርጌት ካደረግህ ለመውጣት ጊዜ ይፈጅብሃል:: የቅጥር ትልቁ ጥቅም ልምድ መቅሰም ነው:: አንዳንድ ቦታማ ደመወዝ ቀንሰህም ልትቀጠር ትችላለህ:: ከልምድ ባሻገር ሰዎችን ትተዋወቅበታለህ:: በዚህ ወቅት ትምህርትም ጠልተን ቅጥርም ጠልተን ግን ሀብታምነት መመኘት የማይሆኑ ነገሮች ናቸው:: ፌሚኒዝምን በጣም የጠጡ ወይም በጎረቤቶቻቸው ባለትዳሮች ኑሮ ተበሳጭተው ትዳር እና ባል የሚባል ነገር ጠልተው ግን በልጅ ፍቅር የሚነድዱ ሴቶች እንደማለት ነው:: አንዴ ተሳሳትብኝ የሚሉ አይጠፉም:: ገንዘብ ደግሞ አይሳሳትም:: እንደ ገንዘብ ዘመዱን የሚወድ አይቼ አላውቅም:: ይኖራል ግን የገንዘብ ዘመድ አወዳደድ ግን ይለያል:: አንድ ገንዘብ ... ገንዘብ የሌለበት ቦታ አይሄድም:: ስለዚህ በበሩ በኩል ግባ:: ትምህርት, አጫጭር የሙያ ስልጠና ውሰድ:: ተቀጠር:: ሁሉንም የወጪ በር ዝጋና ቋጥር:: ከዚያ ወደ ሁለተኛው ኳድራንት ትሻገራለህ:: የሽግግሩ ጊዜ ነቅለህ ከቅጥር አትወጣም:: ቅዳሜና እሁድ, ንጋትና ማታ ላይ ትሞክራለህ:: ብልጥ የወንዝን ጥልቀት በሁለት እግሩ አይፈትሽም ይባላል::

የጭነት (Shipment), የአገር ውስጥ የስልጠናም ይሁን የምክር ቀጠሮ ማስያዣ ዌብሳይት ጨርሰን ሙከራ ላይ ነን:: ከሰሞኑ Link እልካለሁ:: ምክር ስትፈልጉ እዚያው ላይ ቀጠሮ መያዝ, ጭነት ከsourcing ጀምሮ እያንዳንዱን ክፍያ ክትትል እና ኮንቴይነር የት እንዳለ ጭምር ትከታተላላችሁ:: ከየሺፒንግ ሳይቶች በተለየ ነው:: ዋናው ጉዳይ ግን ምሥጢር መጠበቅ ላይ ድርድር የለም:: አብረውኝ ቻይና ከሚሄዱት ጋር ፎቶ እንኳ አልነሳም:: አንድ ጊዜ ብቻ የማይፖሰት ብዬ የግሩፕ ፎቶ ተነስተን ግን ከስልኬ ላይ ሁላ አጥፍቸዋለሁ:: እ ... ደግሞ ይህንን ያህል ብር አለኝ ምን ልጫን? የሚሉኝ በርካታ ሰዎች አሉ:: ይህንን ጥያቄ በፍጹም አላስተናግድም:: ምክንያቱም ሌላ ደንበኛ የለፋበትን አዋጪ ሥራ ልሰጣቸው ነዋ! ቻይናዎቹ ጋር ችግር አለ:: "እገሌ ይህንን እቃ ጭኖታል, አትፍራ" ብለው የአማርኛ ጽሑፍ ያለበትን ሳምፕል ሁላ ያሳያሉ:: ፎቶ አውጥተው ያሳያሉ::

ኢምፖርት ላይ ትልቁ ሀጃ ያለው ሀገር ውስጥ ነው:: ውጭ አይደለም:: የውጪው ቀላል ነው እያልኩ አይደለም:: ግን ዋናው ቻሌንጅ እዚሁ ነው:: አንደኛው ዕቃህን መሸጥ መቻል ወይም የት እንደ ምትሸጠው ማወቅ ሲሆን ሁለተኛው የገቢዎችን ኦዲት ማለፍ መቻል ናቸው:: ሽጠህ ብርህን ከነትርፉ መሰብሰብ is ከbad ካልኩለስ, ሰርከስ, ፊዚክስና ማትሪክስ ነው:: ከዚያ ያገር ውስጥ ገቢ ነፍስህነ ነው የሚያወጣው:: ስለዚህ pre-shipment ጥናት የግድ ነው:: Say የልጅህ ስም ሲወለድ ሆስፒታል ላይ ማሙሽ ካልከውና ሚኒስትሪ ላይ ካላስተካከልክ "አቶ ማሙሽ" ይሆናል:: ኢምፖርት ከዚህ ይብሳል:: ፕሮፎርማ ላይ ተሸውደህ ዕቃው ጉምሩክ ከደረሰ you are finished. ላስቦካህ ሳይሆን እያንዳንዱ ነገር ላይ ዘወትር ጠይቅ:: የምትጠይቀው አዲስ ስለሆንክ አይደለም:: ለነባርም ጭምር ነው:: ሌላ ሀገር ብዙም ችግር የለም:: መከራው እዚሁ እኛው ጋር ነው:: ከባንክ አመራረጥ ሳይቀር ጥንቃቄ ይጠይቃል:: ዶላር አለን አብሽር ብሎ ብር ካስገባህለት በሗላ ወንድሜ ማሳጅ የሚያደርጉህ መኣት ባንኮች አሉ:: ሁለት ዐመት ድረስ ክፍያህን ለሰፕላየር ያልላኩ ባንኮች ነበሩ:: ይህንን የሚነግርህ ውስጡ ያለ ሰው ነው::

ሰው ባልሄደበት ስለመሄድ ሁሉም ወላጅ ልጁን ትምህርት ቤት ሲልክ ሰፈር ውስጥ የቀረውን ሥራና ሥልጣን ትምህርት ቤት ያልሄዱ እና ከትምህርት የተባረሩት ተምነሸነሹበት:: የተማረ በኑሮ ሲማረር ያልተማረ ቀያይ ሴት እየቀያየረ ቀይ ምንጣፍ ያስነጥፍ ያዘ (ለጸይሞችና ለቡኒዎች ሌላ ጊዜ):: አሁን ምእመኑም ኢ-አማኒውም ትምህርትን የድህነት መንገድ አድርጎ ያይ ገባ:: ሀብት እና ክብር በመሰገጥ, በመገጀር እና በመደ^ደብ መሰለው:: ደ^ደቦችና ማይሞች የበዙበት ዓለም ምን እንደሚመስል መሳል አይቸግርም:: ስለዚህ ትምህርት ላይ ወጥሩ:: ሕክምናም በሉት ኢንጂነሪንግ በፓውዛ የማይገኙ ፊልዶች መሆናቸው አይቀርም:: አንድ ቀላል ነገር ብልጭ ላድርግላችሁ:: የእጅ ጽሑፍ እየጠፋ ነው:: ልጁም ወላጁም ኪይቦርድ እየወጋ በእጅ መጣፍ ሰነፈ:: ከሆነ ዓመት በሗላ ደብዳቤ የሚጽፍ ሊጠፋ ይችላል:: ይህ የኤሌክትሮኒክ ዐለም ምን ያህል እንደሚቆይ ለመገመት ቢያዳግትም ግን ከፊትለፊታችን ባለው ታላቁ ጦ^ርነት መጥፋቱ አይቀርም:: ስለዚህ ዋሻ የገባና ትምህርት ያለው ሰው ድጋሚ የሰውን ልጅ መርቶ የሚቀጥለው:: ሰው በጀማዓ ሲተው ቆም ብሎ ማሰብ, በጀማዓ ሲቆም ሄድ እያሉ ማሰብ ያስፈልጋል:: ምእመኑ በጀማዓ ጮማን ሲተው እኔ ወደ ጮማዬ ስመለስ ክብደቴን ቀነስኩ:: ቢያስቀዝንም ጮማ ቢገ^ድልህም ለስምህ እራሱ ጥሩ ነው:: ምቾትና ጮማ ተባብረው ገደ^ሉት ነው የምትባለው:: ቢያስቀዝንም ጮማ!