የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
Channel የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 823 subscribers, ranking 7 553 in the Religion & Spirituality category and 2 849 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 823 subscribers.
According to the latest data from 01 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 223 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.71% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 552 views. Within the first day, a publication typically gains 1 030 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።
"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 02 September | +2 | |||
| 01 September | 0 |
| 2 | ኢየሱስ ይመጣል በሚል መሪ ቃል በሻኪሶ ከተማ የጀማ ወንጌል ስብከት ተካሄደ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ምሥራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ስር የምትገኘው የሻኪሶ አጥቢያ በሻኪሶ ከተማ ምዕመናን ያሳተፈ ከተማ አቀፍ የጀማ ወንጌል ስብከት አካሄደች።
ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢየሱስ_ይመጣል" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ታላቅ የጀማ ወንጌል ሥርጭት የመንግሥቱ ወንጌል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሲሰበክ ብዙዎች ወንጌል ሰምተዋል፤ ንስሐ የገቡም መኖራቸው ተገልጿል።
ይህ ከተማ አቀፍ የወንጌል ስብከት አጥቢያዋ ከነሐሴ 18-22/2018 ዓ.ም አንድ ለአንድ ያካሄደችው የወንጌል ምስክርነት ሳምንት መዝጊያ ፕሮግራም ነው።
"እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።" ራእይ 22፥12
መረጃዉ፦ የመሰረተ ክርቶስ ቤተክርስቲያን ነዉ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለዜና ሽፋን መልአክት ለመላክ
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል | 1 366 |
| 3 | ሆሊስቲክ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ በ4ኛው ዙር 200 ተማሪዎችን በታላቅ ድምቀት አስመረቀ
ሆሊስቲክ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ ከዲፕሎማ እስከ ማስተርስ ፕሮግራም በቲዎሎጂ ትምህርት ሲያሰለጥናቸው የነበሩትን 200 ተማሪዎች ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሚሽን እና የቲዎሎጂ መምሪያ ኃላፊ ፓስተር ይልማ ዋቄ በበኩላቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በመስተላለፊ ስለ ካውንስሉ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ ተመራቂዎች የተጣለባቸውን አደራ በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል።
የኮሌጁፕሬዚዳንት ዶ/ር አንዷለም ጌታቸው ባደረጉት ንግግር፤ ለተመራቂዎች፣ ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመቀጠልም ተመራቂዎቹ በኮሌጁ ቆይታቸው የተሰጣቸውን አደራ በጥንቃቄ እንዲጠብቁና በተግባር እንዲኖሩት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ቄስ ዶክተር ጎፈሬ አዲሾ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ “በአዲሱ ምዕራፍ ምን ታደርጋላችሁ?” በሚል ርዕስ በጥልቀት የእግዚአብሔርን ቃል ለተመራቂዎች አካፍለዋል።
በምረቃ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሚሽን እና የቲዎሎጂ መምሪያ ኃላፊ ፓስተር ይልማ ዋቄ፣የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ቀጠና ዋና ጸሐፊ መጋቢ በለጠ አጀሮ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል። | 1 888 |
| 4 | ፈጣሪ ሃይማኖት መራጭ አይደለም ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ
https://youtu.be/HRgsm4hhdcM?si=SSKxme0U1qcorc6r | 849 |
| 5 | መስጅድ ውስጥ ልሳን ተናገርኩ ወንጌላዊ ሁሴን መሀመድ
ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ሙሉ ቪዲዮውን ይመልከቱ
https://youtu.be/HRgsm4hhdcM | 1 |
| 6 | 🇪🇹 ምስጋና ለሁሉም!
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ46 ቀናት ሲያከናውነው የቆየው የምክክር መድረክ በሰላም በመጠናቀቁ ደስታችንንና ምስጋናችንን እንገልጻለን።
በዚህ ረጅምና አስፈላጊ የምክክር ሂደት በኃላፊነት፣ በትዕግሥትና በመከባበር ለተሳተፉ ተሳታፊዎች፣ ለኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች፣ ውይይቱን በትጋት ሲያስተባብሩ ለነበሩ ባለሙያዎችና ሠራተኞች ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በተጨማሪም ተሳታፊዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡና መድረኩ በሰላም እንዲካሄድ፣ ከፈጣሪ ጥበቃ በታች ቀንና ሌሊት የደኅንነትና የሰላም ጥበቃ ሲያደርጉ ለነበሩ ሁሉ ልዩ ምስጋናችን ይድረስ።
ለመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይህንን የምክክርና የሰላም ጉዞ በጋራ እንድንደግፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ልዩነቶቻችንን በውይይት እያቀራረብን፣ የሚያግባቡንን የጋራ እሴቶች እያጠናከርን፣ ለትውልድ ሰላማዊ፣ የተረጋጋችና የበለጸገች ኢትዮጵያን በጋራ እንገንባ።
ሰላም የሁላችንም ነው፤ ለሰላም መሥራትም የሁላችንም ኃላፊነት ነው! 🇪🇹
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለዜና ሽፋን መልአክት ለመላክ
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል | 3 277 |
| 7 | https://youtu.be/WjTj9yLfTIk?si=VTWTlzvQLqGLvPiE | 2 842 |
| 8 | የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሏን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠች
የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ያከናወነችውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት የሚዘክር የ70ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥታለች።
በዓሉ በ1ኛ ሳሙኤል 7፥12 “አቤንኤዘር” እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን፥ በበዓሉ ላይ በርካታ የምስጋና፣ የጸሎት ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
ይህ ታላቅ ክብረ በዓል ከነሐሴ 3 ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።
በ1948 ዓ.ም.“መሠረተ ሕይወት” በሚል ስያሜ ጉዞዋን የጀመረችው ይህች ታሪካዊት ቤተክርስቲያን፥ ባለፉት ዓመታት ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ለማድረስ ባደረገችው ጥረት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች ከ60 በላይ አዳዲስ አጥቢያዎችን በመትከል ረገድ ታላቅ ታሪክ መሥራቷ ተጠቅሷል።
ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ ጎን ለጎን ማኅበረሰቡን የሚጠቅሙ በርካታ ማኅበራዊ ሥራዎችን ስታከናውን የቆየች ሲሆን ከምሥረታዋ ጋር ተያይዞ የተቋቋመው የመጀመሪያው የመሠረተ ሕይወት ቤተክርስቲያን መሠረተ ትምህርት ቤት አሁንም ድረስ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በሥነ-ምግባር የታነጸ ዜጋ በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
የቤተክርስቲያኗ መሪዎች እንደተናገሩት፤ ነሐሴ 23 በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ወንጌላውያን አማኞች በሙሉ የሚሳተፉበት ታላቅ የምስጋና እና ራዕይ የማጋራት መርሃ ግብር ይካሄዳል ብለዋል።
በተጨማሪም ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. የዝማሬ እና ወንጌል ማወጅ የእግር ጉዞ መርሃ ግብር ይከናወናል። ይህ ጉዞ ከቤተክርስቲያኑ ግቢ ተነስቶ በሞላ ማሩ እና በአብነት በበላ | 3 577 |
| 9 | የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት በማለት ተናገሩ።
ነሐሴ8 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛ የካውንስል ስብሰባ አካሄዷል። በስብሰባዉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌትነት ለማ መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን በመልክታቸዉም የመካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በረጅም የአገልግሎት ዘመኗ በአገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳረፉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የታወቀች አንጋፋ ቤተ እምነት ናት። ለዛሬው ሁለንተናዊ እድገት የቀደሙ መሪዎች ያበረከቱት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነበር። ያሉት ጠቅላይ ፀሐፊዉ ዛሬም ቢሆን ከትውልድ፣ ከአገርና ከሁሉ በላይ ከእግዚአብሔር የተሰጣትን ታላቅ መለኮታዊ አደራ በታማኝነት መወጣት ይጠበቅባታል። ብለዋል የዛሬዎቹ መሪዎች ትላንትን በማስታወስ፣ ዛሬን በታማኝነት በማገልገል እና ነገን መሠረት በሚጥል ራዕይ በመመልከት ዋናውን ነገር ዋና አድርገው መቀጠል አለባቸውም በማለት አክለዋል።
ለኢቫንጀሊካል ዜና ሩት ዋቅጅራ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ | 2 945 |
| 10 | የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነኢየሱስ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ሰጠች #ኢቫ_ዜና
https://youtu.be/4W8SEdsfGm4 | 2 347 |
| 11 | ሁሉም ወንጌል አማኝ ሊያየው የሚገባ ድንቅ ፕሮግራም
ክርስትና ውርስ አይሆንም
በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ሚዲያ የቀረበ
በ Evangelical Media Council ዩቲዩብ ቻናል ላይ ያገኙታል
ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ https://youtu.be/YDH1EH4SnIY?si=8T3fqaIV_6xkF1mB | 3 211 |
| 12 | የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር በማኅበራዊ ሚዲያና ብሮድካስት አጠቃቀም ላይ ሥልጠና ሰጠ።
ይህ ሥልጠና የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሥርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም ከማኅበራዊ ሚዲያ እና ከብሮድካስት አገልግሎት ሥራዎች ጋር የተያያዘ ሲሆን፤ በካውንስሉ ሥር ለሚገኙ የወንጌል አማኞች ሚዲያዎች በሙሉ የተሰጠ ነው።
የፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ መብራቱ እንደገለጹት ሥልጠናው የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃዎች ከሕግ አንጻር የሚያስከትሏቸውን ችግሮች ለማየት እና ለዚህም የመፍትሔ ሐሳብ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች እንዴት መከላከል እንደሚቻል ለመመልከት የተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የሕግ ክፍል ኃላፊ ወይዘሪት መንበረ አንድነት በበኩላቸው የወንጌላዊያን ሚዲያዎች ከሕግ አንጻር ምን ያህል ያውቃሉ? በሕጉስ መሠረት እየሠሩ ነው? የሚለውን ለማስገንዘብ ጭምር ሥልጠናው መዘጋጀቱን አንስተዋል።አክለወም ካውንስሉ በተጨማሪም ከሕግ አንጻር የተለያዩ ሥልጠናዎችን በቀጣይነት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮ የሕግ ሥርጸትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት አካዳሚክ ዓቃቤ ሕግ አቶ ሙሴ ባዬ ሥልጠናውን የሰጡ ሲሆን፥ ከተሳታፊዎች ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት ሰልጣኞች በቆይታቸው እጅግ ጠቃሚ እና ጥሩ ጊዜ እንደነበራቸውም ገልጸዋል።ከዚህ ስልጠና የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በስራቸው ላይ በተግባር እንደሚያውሉትና ውጤታማ እንደሚሆኑ ሙሉ እምነት እንዳላቸው አስታውቀዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ | 3 421 |
| 13 | የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ነሐሴን በጾምና በጸሎት የመሻር አገር አቀፍ ጥሪ አስተላለፈ #ኢቫ_ዜና@EGBCC | 2 897 |
| 14 | ነሐሴን በጾምና በጸሎት እንሻገር!
የአንድ ዓመት ጉዞ ሲጠናቀቅ፣ አዲስ ዓመትም ሲጀምር፤ በምስጋና ያለፈውን እናስብ፣ በጸሎት የሚመጣውን እንቀበል።
ነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም — አገር አቀፍ የጾምና የጸሎት ወር!
ስለ ሀገራችን፣ ስለ ሕዝባችን፣ ስለ ትውልዳችንና ስለ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ልብ እንጹም፤ እንጸልይ።
📖 “ በቸርነትህ ዓመቱን ታቀዳጃለህ .......” — መዝሙር 65፥11 | 3 444 |
| 15 | ኦርቶቶሜኦ የእውነትን ቃል በትክክል መክፈል የተሰኘውና በመጋቢ ቤዛዓለም በላይ የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ።
በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት ፓስተር ጌታሁን ነሲቡ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን መጽሐፉ ለምእመናንና ለቤተክርስቲያን ያለውን ጠቀሜታ በመግለጽ የተሰማቸውን ታላቅ ደስታ አጋርተዋል።
በምረቃው ላይ የመጽሐፉን ይዘት አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡት የቋንቋ ጥናት ባለሙያው አቶ አሺኔ አስቴን በበኩላቸው መጽሐፉ የወቅቱን ፍላጎት ያገናዘበና እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሥራ መሆኑን መስክረዋል።
በማቀጠልም ወንጌላው ዙርያ ሱማ የመጽሐፉን ዳሰሳ አቅርበዋል።
የመጽሐፍ ጸሐፊ መጋቢ ቤዛ ዓለም እንደተናገሩት ኦርቶቶሜኦ" የግሪክ ቃል ሲሆን "ኦርቶ" ማለት "በትክክል" ማለት ሲሆን"ቶሚሆ" ማለት ደግሞ "መቁረጥ" ከሚለው የግሪክ ቃል የተወሰደ መሆኑ ገልጿል።በዚህ ዘመን ያሉ አገልጋዮች መጽሐፍ ቅዱስን በራሳችን አውድና ለእኛ እንደሚመቸን እያፈታን ስለሆነ ለዚያ መፍትሔ ታስቦ የተጻፈ መሆኑን አክለው ተናግራዋል።
ለኢቫንጄሊካል ዜና ቤተልሔም ደረጀ
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website | 2 739 |
| 16 | https://youtu.be/r3J4k0KmQrk | 1 |
| 17 | https://youtu.be/CpJW1WYe72M | 2 444 |
| 18 | “ተስፋችን በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ ነው'' ቬኔዙዌላውያን
በቬኔዙዌላ ከ300 በላይ በሚሆኑ ከተሞች በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተሰብስበው ኢየሱስ ክርስቶስ በሀገራቸው ላይ ጌታ መሆኑን በይፋ ያወጁበት ታላቅ የጸሎትና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄዱ።
"ቬኔዙዌላ የጸጋ ምድር" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ ዝግጅት አማኞች አደባባዮችንና ጎዳናዎችን በአምልኮ፣ በምስጋናና በጸሎት በመሙላት ለሀገራቸው ሰላም፣ አንድነት፣ ተስፋና ዘላቂ ለውጥ ተመኝተዋል።
ሀገሪቱ በፈታኝና እርግጠኝነት በጎደላቸው የችግር ጊዜያት ማለፏ የሚታወስ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የመጨረሻ ተስፋቸው በሰው ኃይል ወይም በፖለቲካ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አውጀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል
Telegram | Facebook | Youtube | Tiktok | Website | 2 341 |
| 19 | የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ሥነ መለኮት መምሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት ማስተባበሪያ ያዘጋጀው የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቋማት መምህራንና የሥራ ተሳታፊዎች ስልጠና ተካሄደ፡፡
ሥልጠና ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሐዋሳ ሐይቅ ዳር ቃለ ሕይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል።
"ከሙያ አልባ መምህር ወደ መምህር አልባ ክፍል ወይስ የመምህርነት ሙያና የትምህርት ጥራት በኢትዮጵያ"በሚል ዋና ርዕስ በሚካሄደው ሥልጠና፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፣ በሥነ መለኮት ተቋማት የመምህራንና የአመራሮች ሚናን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሏል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ከሐዋርያትና ከነቢያት አገልግሎት ጋር ተያይዞ ሊኖር የሚገባውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አቋም በስፋት ውይይት እንደሚካሄድበት ታውቋል።
መረጃውን በቤተክርስቲኒቱ አገኘነው፡፡
የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል
የወንጌል አማኞች ድምፅ
የ Evangelical Media/Council የዩቲዩብ ቻናልን
ሰብስክራይብ ለማድረግ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ
• YouTube: https://youtube.com/@ethiopiancouncilgospelbeli4732
• TikTok: https://www.tiktok.com/@evangelical.media
• Telegram: https://t.me/EGBCC
• Website: ecgbc.org
የቤተሰባችን አባል ለመሆን Follow, Subscribe, Like እና Share በማድረግ አብረውን ይሁኑ!
ለሀሳብ አስተያየት ጥቆማ በቴሌግራም
t.me/evangelicalmedia
📞251 991827226 ላይ ያገኙናል | 2 546 |
| 20 | በአምበሪቾ AIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ
በአምበሪቾ ዓለም አቀፍ የጸሎትና የወንጌል አገልግሎት (AIPM) የሚገነባው የAIPM ግሎባል ሚሽን ዩኒቨርሲቲ (AIPM–GMU) የመሠረት ድንጋይ የማኖር ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በሥነ ሥርዓቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አረጋ እሸቱ፣ እንዲሁም የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክብርት ወይዘሮ ውባየሁ በቀለ ተገኝተው የመሠረት ድንጋዩን አኑረዋል።
በመድረኩ የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና ጨምሮ የተገኙ እንግዶች ንግግር አድርገዋል። ተናጋሪዎቹ ተቋሙ እስካሁን በወንጌል፣ በጸሎት እና በማኅበረሰብ አገልግሎት ያከናወናቸውን ሥራዎች በማድነቅ፣ በማኅበረሰቡ ላይ ያሳደሩትን በጎ ተፅዕኖ አመስግነዋል።
እንዲሁም ይህ ዩኒቨርሲቲ የAIPM ብቻ ሳይሆን የመላው የከምባታ ሕዝብ ፕሮጀክት መሆኑን በመግለጽ፣ ሁሉም በትብብር እንዲደግፉት ጥሪ አቅርበዋል፤ መንግሥትም ለፕሮጀክቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።
የAIPM መስራችና ዳይሬክተር ዶክተር ደስታ ላንገና በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ከሚሽን አገልግሎት ባሻገር በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽን፣ በሥነ ምግባር እና በሙያ ክህሎት የተበቁ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን ማፍራት ዋና ዓላማው መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በተቋሙ ውስጥ የእውቀት እና የሁለንተናዊ እድገት ትምህርት በትኩረት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
AIPM-Ambaricho International Prayer and Missions Movement | 1 568 |
