en
Feedback
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Open in Telegram

ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC

Channel የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC (@egbcc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 934 subscribers, ranking 7 407 in the Religion & Spirituality category and 2 823 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 934 subscribers.

According to the latest data from 16 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 188 over the last 30 days and by 23 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.28%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.47% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 540 views. Within the first day, a publication typically gains 892 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው። "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

11 934
Subscribers
+2324 hours
+537 days
+18830 days
Posts Archive
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች ለአዲስ አመት ከ600,000 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለማህበረሰቡ የምግብ ድጋፍ አደረጉ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያ
+7
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች ለአዲስ አመት ከ600,000 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለማህበረሰቡ የምግብ ድጋፍ አደረጉ። በመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የሆለታ 44 አጥቢያ እና የሆለታ ጭሪ አጥቢያዎች አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ በአካባቢያቸው ለሚገኙ 432 የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ አድርገዋል። የሆለታ 44 አጥቢያ ለ226 አቅመ ደካሞችና ድሆች 295,500.00 ብር ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው 10 ኪ.ግ ዱቄትና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ ስታደርግ እንዲሁም የሆለታ ጭሪ አጥቢያ ለ206 ችግረኞች 307,193.00 ብር ወጪ በማድረግ ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጋለች። በተጨማሪም የሆለታ 44 አጥቢያ በኤጀሬ ማረሚያ ቤት ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ሦስት ኩንታል አልባሳት እና የበዓል መዋያ የሚሆን የ18,000 ብር ድጋፍ ስትሰጥ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተካሄደው የወንጌል ሥርጭት 10 የሕግ ታራሚዎች ጌታ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል። መረጃው የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲየን ነው

የአሜን ቲቪ ሥራ አስኪያጅና አገልጋይ ሰብሌ በቀለ ሰው ሁሉ ስለ ነገ ሲያስብና ሲጨነቅ ይፈራል እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ
የአሜን ቲቪ ሥራ አስኪያጅና አገልጋይ ሰብሌ በቀለ ሰው ሁሉ ስለ ነገ ሲያስብና ሲጨነቅ ይፈራል እግዚአብሔር ግን ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።(ትንቢተ ኤርምያስ 29:11) ይህን የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል በመጥቀስ እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁበማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል

Wisdom Intergration ከ Gaps International Ministry ጋር በመተባበር የአይምሮ ውስንነት ካላቸው ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ጋር የአዲስ አመት ልዩ የበዓል ዝግጅት በሳር ቤት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ያከናወነ ሲሆን በዕለቱም ከልጆቹ እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር የህብረት ፣ የጨዋታ እና ማዕድ በጋራ የመካፈል ጊዜ የነበረ ሲሆን ለአዲስ አመት በዓል የሚሆን የልጆች መጫወቻዎች ፣ ዘይትና ዱቄት፣ ህይወታቸውን እንዲመሩበት ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። የዕለቱን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የWisdom የቦርድ አባል እህት ማርታ ፈለቀ ሁሉም ሰው ከዊዝደም ኢንቲግሬሽን ጋር በመተባበር በሙያ፣ በገንዘብ እና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብረው እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ። የዊዝደም ኢንቲግሬሽን መስራች የሆኑት ወንድም ዳንኤል እና ባለቤታቸው የኔነሽ ለልጆቹ ፣ ለወላጆች እና በዕለቱ ለተገኙ ታዳሚዎች ሁሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እና ለዊዝደም ኢንቲግሬሽን አገልግሎት መመስረት ምክንያት ስለሆናቸው ስለ ልጃቸው ካሌብ ዳንኤል እና ባጋጠመው የዓይምሮ ውስንነት ምክንያት ይህ አገልግሎት ለመመስረት ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል። የዕለቱ ተጋባዥ ዘማሪት የነበረችው ዘማሪት ሩት እጅግ በሚያጽናኑ ዝማሬዎች ጉባኤውን አገልግላለች። የጋፕስ ዓለም አቀፍ አገልግሎት መስራች እና መሪ በሆኑት መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ከዮሐንስ 4 ጠቅሰው በአይሑድ ማህበረሰብ ስለተገለሉት ሳምራውያን እና በሳምራውያኑ ስለተገለለችው ሳምራዊቷ ሴት ፣ እሷን ስለቀረባት እና ስለተቀበላት እየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል አካፍለዋል።

የወጣቶች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ በሆሳዕና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች፣ በከተማዋ ጎዳናዎችና አደባባዮች የወንጌል ስርጭት
+8
የወጣቶች የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴ በሆሳዕና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች፣ በከተማዋ ጎዳናዎችና አደባባዮች የወንጌል ስርጭት አካሂደዋል። ወጣቶቹ ይህን የወንጌል ስርጭት ያካሄዱት ከክረምት የወጣቶች ሳምንት የስልጠናና የትምህርት መርሐ ግብር በኋላ ሲሆን፣ በስርጭቱም ከሆሳዕና ከተማና አካባቢዋ የተውጣጡ ወጣቶች፣ ልጆች፣ መሪዎች፣ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ተሳትፈዋል። በእንቅስቃሴውም የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ለተለያዩ ማኅበረሰብ ክፍሎች ተሰብኳል፤ በርካታ ሰዎችም የወንጌሉን መልዕክት እንዲሰሙ ዕድል ተፈጥሯል። የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ አዴሣም በወንጌል ስርጭቱ ተሳትፈው፣ በከተማዋ አደባባይ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል። ቄስ ወንድማገኝ በተጨማሪም ወጣቶቹ በወንጌል ስርጭት እያደረጉ ላሉት አገልግሎት አበረታተዋል፤ ወንጌልን በድፍረትና በትጋት መመስከራቸውን እንዲቀጥሉም አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ነሐሴ ወር የወንጌል ስርጭትና የምስክርነት ወር በመሆኑ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች በወንጌል ምስክርነት አገልግሎት በስፋት እየተሳተፉ ነው። የሆሳዕና ወጣቶች ያካሄዱት ይህ የወንጌል ስርጭት እንቅስቃሴም፣ የወጣቶችን ተሳትፎ በማጠናከር የክርስቶስን ወንጌል ለሕዝብ ለማድረስ የተደረገ አገልግሎት ሆኗል። EECMY Youth Ministry