BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page
Open in Telegram
3 098
Subscribers
+424 hours
+97 days
+4130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+18
in 0 channels
August '26
+192
in 0 channels
Get PRO
July '26
+110
in 0 channels
Get PRO
June '26
+95
in 0 channels
Get PRO
May '26
+61
in 0 channels
Get PRO
April '26
+57
in 0 channels
Get PRO
March '26
+57
in 0 channels
Get PRO
February '26
+222
in 0 channels
Get PRO
January '26
+120
in 1 channels
Get PRO
December '25
+258
in 0 channels
Get PRO
November '25
+62
in 0 channels
Get PRO
October '25
+180
in 0 channels
Get PRO
September '25
+44
in 0 channels
Get PRO
August '25
+89
in 1 channels
Get PRO
July '25
+62
in 0 channels
Get PRO
June '25
+45
in 0 channels
Get PRO
May '25
+92
in 0 channels
Get PRO
April '25
+80
in 0 channels
Get PRO
March '25
+346
in 0 channels
Get PRO
February '25
+532
in 0 channels
Get PRO
January '25
+219
in 1 channels
Get PRO
December '24
+432
in 0 channels
Get PRO
November '24
+193
in 0 channels
Get PRO
October '24
+178
in 0 channels
Get PRO
September '24
+43
in 1 channels
Get PRO
August '24
+73
in 1 channels
Get PRO
July '24
+58
in 1 channels
Get PRO
June '24
+37
in 2 channels
Get PRO
May '24
+34
in 0 channels
Get PRO
April '24
+36
in 0 channels
Get PRO
March '24
+10
in 0 channels
Get PRO
February '24
+17
in 1 channels
Get PRO
January '24
+11
in 0 channels
Get PRO
December '23
+144
in 0 channels
Get PRO
November '23
+11
in 0 channels
Get PRO
October '23
+299
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 04 September | +3 | |||
| 03 September | +4 | |||
| 02 September | +9 | |||
| 01 September | +2 |
Channel Posts
የፋይናንስ ቢሮ የተቀናጀ የዲጂታል መንግሥታዊ ክፍያ ሥርዓት ትግበራ ማዕቀፍን ወደ ሥራ ሊያሰገባ መሆኑ ተገለፀ፡
##########################################
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የመንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን፣ የፋይናንስ ግልጽነትን ለማስፈንና የህዝብ አገልግሎት ክፍያዎችን ለማቀላጠፍ ያለመ "የተቀናጀ የዲጂታል መንግሥታዊ ክፍያዎች ትግበራ ማዕቀፍ" በፋይናንስ ቢሮ ደረጃ ወደ ሥራ ሊገባ መሆኑን ተገለፀ፡፡
ይህ ትግበራ የሀገሪቱን ብሔራዊ የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ የሕዝብ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን ትስስር በማጠናከር በቢሮው የሚሰጡ ማናቸውንም የመንግሥት አገልግሎት ክፍያዎች (P2G) እና የመንግሥት ወጪ ክፍያዎችን (G2P) በዲጂታል መንገድ በብቃትና በፍጥነት ለመፈጸም ያስችላል።
በዚህ አዲስ ማዕቀፍ አገልግሎት ፈላጊዎች ወደ ቢሮው በአካል ሳይመጡና ጥሬ ገንዘብ ሳይይዙ በማንኛውም የባንክና የዲጂታል ክፍያ አማራጭ ክፍያቸውን መፈጸም እንደሚያስችላቸው በቀረበው ሰነድ ተመላክቷል፡፡
የቢሮውን የገንዘብ እንቅስቃሴና የሂሳብ አያያዝ ሙሉ በሙሉ በዘመናዊ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ከተያያዘው የፋይናንስ ሥርዓት ጋር በማቀናጀት የፋይናንስ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ለአገልግሎት ፈላጊዎችም ሆነ ለቢሮው የሥራ እንቅስቃሴ ከፍተኛ የጊዜና ተጨማሪ ወጪ ቁጠባን እንደሚያደርግ ተገለፃል፡፡
የፋይናንስ ቢሮው ይህንን የተቀናጀ አሠራር ለመተግበር የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ ዝግጅቶችን፣ የሰው ኃይል ሥልጠናዎችን በመስጠት ወደ ሥራ እንደሚገባ አስታውቋል።
በዚሁ የምክክርና ማስጀመሪያ መድረክ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ከኢቲስዊች (EthSwitch) የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎችና ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የፋይናንስ ቢሮ አመራሮች እንዲሁም የጠቅላላ ካውንስል አባላት ተገኝተዋል።
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
| 2 | No text... | 214 |
| 3 | "የበጀት ውጤታማነት በተግባር!" አቶ ሽመልስ ዘመዴ (የፋይናንስ ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ)
########################
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የእንጦጦ ቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ጉብኝት ከፋይናንስ አስተዳደር፣ ከካፒታል በጀት አመዳደብ እና ከረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ዕድገት አንጻር ያለው የከተማ አስተዳደሩ ከ70 ፐርሰንት በላይ የሚሆነውን በጀት ለዘላቂ ልማት እየዋለ መሆኑን ያሳያል። በ87.6 ሄክታር መሬት ላይ የተዘረጋው ይህ ፕሮጀክት፣ ሀብት በቁጠባና በውጤት ተኮር መንገድ ለህዝብ ጥቅም መዋሉን የሚያረጋግጥ የተግባር ማሳያ ነው።
ፕሮጀክቱ የመሠረተ-ልማት ግንባታ ብቻ ሳይሆን ራሱን የቻለ አዳዲስ የገቢ ምንጮችን የያዘ ማዕከል ነው። በውስጡ ያቀፋቸው 10 ካፌዎች፣ 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፣ የፓርኪንግ አገልግሎቶች እና የመዝናኛ ስፍራዎች ለአነስተኛና መካከለኛ ንግዶች የስራ እድል ከመፍጠራቸውም በላይ፣ ለከተማዋ ተጨማሪ ገቢ የሚያመነጩ ዘላቂ የፋይናንስ ምንጮች ናቸው።
በውሃና አፈር ጥበቃ ላይ የተሰሩት 16 አነስተኛ ግድቦች፣ የድጋፍ ግንቦች እና የጎርፍ ማስወገጃዎች ከተማዋ በጎርፍና በአካባቢ ውድመት ምክንያት ልታጣ የምትችለውን ከፍተኛ የፋይናንስ ወጪ ይቀንሳሉ። የአረንጓዴ ልማቱና ማህበራዊ አገልግሎቶቹ የከተማዋን ነዋሪዎች የህይወት ጥራት በመጨመር ረጅም ጊዜ የሚዘልቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴት ይፈጥራሉ።
የፋይናንስ ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽመልስ ዘመዴ ቢሮው የመንግሥት በጀት ለትምህርት፣ ለጤና፣ ለሰው ተኮር ድጋፎች እና ለአካባቢ ልማት በተመጣጣኝ ሁኔታ እንዲመደብ ማድረጉ፣ የፋይናንስ አስተዳደሩ አጠቃላይ የህብረተሰብ ዕድገትን ማዕከል ያደረገ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልፀዋል፡፡
ኃላፊው እንዳሉት ጉብኝቱ የመንግሥት ፋይናንስ ወደሚጨበጥ የህዝብ ሀብትና የከተማ ኢኮኖሚ ማነቃቂያነት መለወጡን ያረጋገጠ እና የበጀት ውጤታማነትን በተግባር የታየበት ምልከታ መሆኑን አመላተዋል፡፡
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu | 436 |
| 4 | No text... | 379 |
| 5 | በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።
በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።
ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 495 |
| 6 | No text... | 483 |
| 7 | የእንጦጦ ቀበና ወንዝ ዳርቻና ቀበና ድልድይ በውስጡ ያሟላቸው አስደናቂ መሰረተ ልማቶች
👉 87.6 ሄክታር የሚሸፍን መሬት፤
👉 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት፤
👉 1 ትልቅ ግድብ ፤
👉 16 አነስተኛ ግድብ፤
👉 3 ቼክ ዳም ፤
👉 1.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሃይኪንግ፤
👉 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ የድጋፍ ግድግዳ፤
👉 3 ማራኪ ፏፏቴዎች፤
👉 1 የውሃ ምንጭ ግንባታ፤
👉 36, 928 ኪሎ ሜትር የኮንሶ ጋቢዮንና የኮንሶ እርከን ስራ፤
👉 59.7 ሄክታር የሚሸፍን የአረንጓዴ ልማት፤
👉 50,330 የተለያዩ ዝርያ ያላቸው የዛፍ ተክል
👉 10.62 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ፤
👉 33.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት የእግረኛ መንገድ ፤
👉 33.2 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የመንገድ መብራት ፤
👉 19.13 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ እና የጐርፍ ማስወገጃ መስመር ዝርጋታ፤
👉 23 መጸዳጃ ቤቶች፤
👉 21 የእግረኛ ድልድዮች፤
👉 3 ተንጠልጣይ ድልድይ፤
👉 6 የእግረኛ የብረት ድልድይ፤
👉 1 ሰርኩላር ድልድይ፤
👉 1 የኮንክሪት ድልድይ፤
👉 9 የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች፤
👉 በአንድ ጊዜ 695 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችሉ 7 የተሽከርካሪ ማቆሚያ ፓርኪንጎች፤
👉 4 የመሰብሰቢያ ስፍራዎች ፤
👉 7 ፕላዛ ፤
👉 4 ፓቪሊዮን፤
👉 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፤
👉 2 አንፊ ቲያትር፤
👉 10 ካፍቴሪያዎች፤
👉 7 የልጆች መጫወቻ፤
👉 2 አነስተኛ የሕዝብ ቤተ መጽሀፍት አሟልቷል፡፡ | 1 |
| 8 | ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።
ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና የከተማ አስተዳደሩ ለሕፃናት እድገት እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት በተለይም በ"የአዲስ አበባ የወደፊት ተስፋ የቅድመ ልጅነት እድገት ተነሳሽነት" የተሰጠ እውቅና ነው።
ኢኒሼቲቩ ቀዳማይ ልጅነትን በመንግሥታት ፖሊሲዎች እና በዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት አጀንዳ ማዕከል ላይ ለማስቀመጥ በትኩረት ይሰራል።
ይህ እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን ፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው።
እውቅናው አዲስ አበባን በአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት እድገት የከተማ አመራር ተምሳሌት ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ይታመናል። | 480 |
| 9 | No text... | 479 |
| 10 | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግዢና የጨረታ ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ እያደረገ መሆኑ ተገለፀ።
################################################
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት (e-GP) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቢሮዎች፣ ክፍለ ከተሞችና ተቋማት የበጀት ዓመቱን የግብይትና የጨረታ ሂደቶች በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ሥርዓት በኩል ማከናወን ጀምረዋል። በከተማዋ ያሉ አቅራቢዎችና ኮንትራክተሮች በፖርታሉ ላይ በመመዝገብ የጨረታ ሰነዶችን በኦንላይን መግዛት፣ ማመልከትና ውጤት መከታተል የሚያስችላቸው አሠራር ተዘርግቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በመጀመሪያው ምዕራፍ በምዝገባ፣ በዕቅድ (Registration & Planning) እና በግዢ (Purchasing) ስልጠና ወስደው ወደ ትግበራ የገቡትን የ48ቱን ተቋማት ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የተሟላ ዕውቀት ይዘው እንዲተገብሩ የጨረታ ሂደትና የውል አስተዳደር (Tendering & Contract Management) ሞጁሎች እንዲሁም አዲሱን የመንግስት ግዥ አዋጅ 92/2018 እና መመሪያ በማዘጋጀት አቅማቸውን እየገነባ እንደሚገኝ በፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዢ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ሥዩም ገልፀዋል፡፡
የአሠራር ሽግግሩ ውጤታማ እንዲሆን ለከተማ አስተዳደሩ የግዥ ባለሙያዎችና ለአቅራቢዎች ተደጋጋሚ የስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ ፕሮግራሞች እየተሰጡ ይገኛሉ። ይህ አሠራር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይናንስ ሥርዓቱን ዘመናዊ፣ ግልጽና ወጪ ቆጣቢ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት በእጅጉ እያገዘው እንደሚገኝ አቶ ጴጥሮስ ገልፀዋል፡፡
ቢሮው የመንግሥት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ (e-GP) ሲስተም ትግበራን ወደ 60 ተቋማት ያሰፋፋ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ምዕራፍ በምዝገባ፣ በዕቅድና በግዥ ስልጠና ወስደው ወደ ትግበራ የገቡ 48 ተቋማት ባለሙያዎች የሲስተሙን አሠራር ቅደም-ተከተል ከመተግበራቸው ባሻገር፣ የባለሙያዎችን የሙያ ብቃት ደረጃ (Professionalism) የሚያሳድግና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (Certifications) የሚያስገኝ እንደሆነ ገልፀዋል።
ቢሮው ሂደቱን በተግባር የሚደግፉ እውቀትና ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች በተቋማት በመመደብ የቅርብ እገዛ እያደረገ ይገኛል። የግዢና የጨረታ ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን በብቃት፣ በጥራትና በዘመናዊ ሲስተም እንዲመራ በማድረግ በከተማ አስተዳደሩ ግልጽነትና ፍትሃዊነት የሰፈነበት አሠራር ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አቶ ጴጥሮስ አመላክተዋል፡፡
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu | 530 |
| 11 | No text... | 502 |
| 12 | No text... | 1 |
| 13 | የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች
ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”
ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”
ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”
ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”
ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን” | 1 358 |
| 14 | ዛሬ 33ኛውን ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ “ብሩህ ነገን በዛሬ አዕምሮዎች” በሚል መሪ ቃል አስጀምረናል።
ይህ ጉባኤ በየዓመቱ የምናካሂደው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን ጤናማ እና ውጤታማ ለማድረግ፣ በዘርፉ የተሰሩትን ጠንካራ ስራዎች ልምድ የምንቀምርበት፣ የሚታረሙትንም ለይቶ በጋራ መፍትሄ የምንሰጥበትና በጋራ እቅጣጫ የምንይዝበት ጉባኤ ነው ።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በከተማ አስተዳደራችን በልዩ ትኩረት ሰርተን የተማሪዎች ውጤት እየተሻሻለ መጥቷል። ዛሬ በከተማችን የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤት ወደ 33 በመቶ መሻሻል አሳይቷል። ነገር ግን አሁንም ከፍ ያለ ውጤት እንጠብቃለን፤ ገና ብዙ መሥራት ይጠበቅብናል።
መምህራን፤ ባለድረሻ አካላት በእልህ ሰርተን መፍጠር የሚችሉ፣ ችግር የሚፈቱ፣ በሥነ ምግባር የታነፁ፣ እውቀት የታጠቁ ተማሪዎችን በብዛት ለመፍጠር መረባረብ ይጠበቅብናል።
ከተማ አስተዳደራችን ዋናውን ኢንቨስትመንት ትምህርት ላይ እናውል ብለን፣ ትልቁን በጀት ለትምህርት ዘርፍ እንዲሆን አድርገናል። ትውልድ ላይ ከመሰረቱ መስራት ወሳኝ በመሆኑ፣ ዋና የእዕምሮ እድገት በጨቅላ ህፃንነት ወቅት በመሆኑ ቀዳማይ ልጅነት ላይ እየሰራን እንገኛለን። በዚህ አግባብ ከመሰረቱ ጀምረን እየሰራን በአንደኛ ደረጃ እንዲሁም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ውጤት እና በዲሲፕሊን የታነፀ ትውልድ እንጠብቃለን።
እስካሁን በተገኘው ውጤት ሁላችሁንም ከልብ እያመሰገንኩ፤ በቀጣይም በእውቀት የበለፀጉ፣ በስነምግባር የታነፁ፣ አልቀው የሚሰሩ ተማሪዎች ለመፍጠር ከልብ፣ ዋጋ ከፍለን ተባብረን እንድንሰራ አደራ እላለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 623 |
| 15 | No text... | 621 |
| 16 | "መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት ነው" አቶ ዘላለም ሀብቴ
####################################
ነሐሴ26/ 2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዱ ሰራተኛና አመራር ግላዊና ሙያዊ ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ሀብቴ ገለጹ።
ዳይሬክተሩ በተቋሙ የስነ-ምግባር፣ የመልካም አስተዳደርና የፀረ-ሙስና አሰራሮችን አስመልክተው ለኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በሰጡት ቃለ-መጠይቅ፣ የስነ-ምግባር መከበር የህዝብን እምነት ለመገንባት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለማረጋገጥ እና የተቋሙን መልካም ስም ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ዘላለም በመግለጫቸው እንደጠቆሙት፣ ስነ-ምግባር ማለት አንድ ግለሰብ ወይም ተቋም በስራና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው የሚከተላቸው የሞራል መርሆዎችና የአሰራር ደንቦች ስብስብ ነው። ታማኝነት፣ ቅንነት፣ ፍትሃዊነትና ኃላፊነት የአንድን አካል ትክክለኛ ውሳኔ የመወሰን አቅም እንደሚገነቡ ያብራሩት ዳይሬክተሩ፤ መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን እንደ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ የህግ የበላይነት፣ ህዝባዊ ተሳትፎና ውጤታማነት ያሉ መሰረታዊ መርሆዎችን አጠናክሮ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በሌላ በኩል መልካም አስተዳደርን የሚያደናቅፉ እንደ ተቋማዊ ድክመት፣ የበቂ ግልጽነትና ተጠያቂነት ማነስ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት፣ ቢሮክራሲያዊ መጓተትና ደካማ የቁጥጥር ስርዓት ያሉ ተግዳሮቶችን የመፍትሔ አቅጣጫዎች አመላክተዋል።
እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ግልጽ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት፣ ተከታታይ ስልጠናዎችን መስጠት፣ የቅሬታ አቀራረብ ስርዓትን ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ እና ተጠያቂነት ያለው አመራር መገንባት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።
በመጨረሻም ዳይሬክተሩ ሙስናና ብልሹ አሰራርን በጋራ መከላከል እንደሚገባ አሳስበው፣ ሙሉ ሰራተኞችና አመራሮች ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና ታማኝነትን በዕለት ተዕለት ስራቸው ውስጥ በመተግበር የተሻለና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህዝቡ ማበርከት እንደሚገባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። | 537 |
| 17 | No text... | 418 |
| 18 | በመዲናዋ 20 ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ - ከንቲባ አዳነች
በተያዘው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ 20 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል።
ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት ÷ በምርጫ ለሕዝብ የገባነውን ቃል ለመፈጸም 24/7 በትጋት በመስራት አዲስ አበባን ተምሳሌታዊ ከተማ እናደርጋታለን ብለዋል።
ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የመዲናዋ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከሀገራዊ ርዕይ፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንጻር የተቃኘ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም ጠንካራ የተቋም ግንባታ፣ የተቀናጀ ጥራት ያለውና ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ አይበገሬ አረንጓዴ ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ 11 የመሶብ ማዕከላት መኖራቸውን ጠቁመው ÷ በ2019 በጀት ዓመት ተጨማሪ 20 ማዕከላት እንደሚከፈቱ ተናግረዋል፡፡
ማዕከላቱ የሚከፈቱት ወረዳዎችን በክላስተር በማደራጀት እንደሆነና በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 66 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላትን ለመክፈት መታቀዱን አመልክተዋል።
በሁሉም ዘርፍ የተሳለጠ እና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ከንቲባዋ አረጋግጠዋል፡፡ | 426 |
| 19 | No text... | 455 |
| 20 | የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers | 449 |
