ch
Feedback
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

前往频道在 Telegram

AACABOF PUBLIC PAGE

显示更多
3 086
订阅者
-224 小时
-57
+12630
吸引订阅者
九月 '26
九月 '260
在0个频道中
八月 '26
+192
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+110
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+95
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+61
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+57
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+57
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+222
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+120
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+258
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+62
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+180
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+44
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+89
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+62
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+45
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+92
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+80
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+346
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+532
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+219
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+432
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+193
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+178
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+43
在1个频道中
Get PRO
八月 '24
+73
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+58
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+37
在2个频道中
Get PRO
五月 '24
+34
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+36
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+10
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+17
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+11
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+144
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+11
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+299
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
01 九月0
频道帖子
"መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት ነው" አቶ ዘላለም ሀብቴ #################################### ነሐሴ26/ 2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዱ ሰራተኛና አመራር ግላዊና ሙያዊ ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ሀብቴ ገለጹ። ዳይሬክተሩ በተቋሙ የስነ-ምግባር፣ የመልካም አስተዳደርና የፀረ-ሙስና አሰራሮችን አስመልክተው ለኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በሰጡት ቃለ-መጠይቅ፣ የስነ-ምግባር መከበር የህዝብን እምነት ለመገንባት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለማረጋገጥ እና የተቋሙን መልካም ስም ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። አቶ ዘላለም በመግለጫቸው እንደጠቆሙት፣ ስነ-ምግባር ማለት አንድ ግለሰብ ወይም ተቋም በስራና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው የሚከተላቸው የሞራል መርሆዎችና የአሰራር ደንቦች ስብስብ ነው። ታማኝነት፣ ቅንነት፣ ፍትሃዊነትና ኃላፊነት የአንድን አካል ትክክለኛ ውሳኔ የመወሰን አቅም እንደሚገነቡ ያብራሩት ዳይሬክተሩ፤ መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን እንደ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ የህግ የበላይነት፣ ህዝባዊ ተሳትፎና ውጤታማነት ያሉ መሰረታዊ መርሆዎችን አጠናክሮ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል። በሌላ በኩል መልካም አስተዳደርን የሚያደናቅፉ እንደ ተቋማዊ ድክመት፣ የበቂ ግልጽነትና ተጠያቂነት ማነስ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት፣ ቢሮክራሲያዊ መጓተትና ደካማ የቁጥጥር ስርዓት ያሉ ተግዳሮቶችን የመፍትሔ አቅጣጫዎች አመላክተዋል። እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ግልጽ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት፣ ተከታታይ ስልጠናዎችን መስጠት፣ የቅሬታ አቀራረብ ስርዓትን ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ እና ተጠያቂነት ያለው አመራር መገንባት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በመጨረሻም ዳይሬክተሩ ሙስናና ብልሹ አሰራርን በጋራ መከላከል እንደሚገባ አሳስበው፣ ሙሉ ሰራተኞችና አመራሮች ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና ታማኝነትን በዕለት ተዕለት ስራቸው ውስጥ በመተግበር የተሻለና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህዝቡ ማበርከት እንደሚገባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

2
没有文字...
126
3
በመዲናዋ 20 ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ - ከንቲባ አዳነች በተያዘው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ 20 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል። ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት ÷ በምርጫ ለሕዝብ የገባነውን ቃል ለመፈጸም 24/7 በትጋት በመስራት አዲስ አበባን ተምሳሌታዊ ከተማ እናደርጋታለን ብለዋል። ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የመዲናዋ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከሀገራዊ ርዕይ፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንጻር የተቃኘ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ጠንካራ የተቋም ግንባታ፣ የተቀናጀ ጥራት ያለውና ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ አይበገሬ አረንጓዴ ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ይደረጋል ነው ያሉት፡፡ አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ 11 የመሶብ ማዕከላት መኖራቸውን ጠቁመው ÷ በ2019 በጀት ዓመት ተጨማሪ 20 ማዕከላት እንደሚከፈቱ ተናግረዋል፡፡ ማዕከላቱ የሚከፈቱት ወረዳዎችን በክላስተር በማደራጀት እንደሆነና በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 66 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላትን ለመክፈት መታቀዱን አመልክተዋል። በሁሉም ዘርፍ የተሳለጠ እና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ከንቲባዋ አረጋግጠዋል፡፡
116
4
+6
没有文字...
119
5
የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
194
6
ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስናካሂድ የነበረውን የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዝርዝር እቅድ ውይይት አጠናቀናል። በውይይታችንም እቅዶቹን ይበልጥ ተጨባጭ በማድረግ በቀጣይ አምስት ዓመታትም አልቀን በመፈፀም፣ የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት ሳንሸራርፍ ለመፈፀም፣ የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እጅግ ጠቃሚ እና ገንቢ ተግባቦት እና ዝግጁነት ፈጥረናል። ከሀገራዊ ፖሊሲና ስትራቴጂያችን በመነሳት ህዝባችንም በድጋሚ ሲመርጠን “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌታዊ ሀገር” ብለን የገባነውን ቃል ለመፈፀም እንደ አዲስ አበባ “አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት” ለማድረግ የጀመርነውን ጉዞ ዋና ርዕያችን አድርገናል። ለእቅዳችን ስኬት መሰረቶች የሆኑት ባለፋት አምስት ዓመታት አቅደን አልቀን ያስመዘገብነው ውጤት፣ የህዝብና መንግሥት ከደህነት የመውጣት ፍላጎት፣ በከተማችን የተፈጠረው የስራ ትጋት፣ በታማኝነት ማገልገል፣ በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ በፍጥነትና በጥራት የመፈፀም ልምድ፣ በጀትን በመቆጠብ መጠቀም ትልቅ ስንቅ ናቸው። በቀጣይ ትኩረታችንም ተቋማዊ ብቃትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ በአሰራር፣ በአደረጃጀት፣ የዘመነ ቴክኖሎጂ በሚጠቀም የላቀ አገልግሎት መስጠት፣ የተቀናጀ ጥራት ያለው ሰፊ መሰረት ልማት በፍጥነት መገንባት፣ አዲስ መሰረተ ልማት መገንባት ብቻ ሳይሆን ነባሮቹን በሚገባ ማስተዳደር፣ የንፁህ መጠጥ ውኃና የቤት አቅርቦት ማሳደግ፣ የማህበራዊ ዘርፍ (ጤና፣ ትምህርት …) ተደራሽነትና ጥራት እንዲሁም ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ አልቀን መፈፀም፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ ያሟላ የጤና አገልግሎት መስጠት፣ የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን፣ የከተማችንን የቱሪዝም መዳረሻ ከተማነት ማረጋገጥ፣ አዲስ አበባን ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ አፍሪካዊት ከተማ ማድረግ፣ ለወጣቶች ተጠቃሚነት፣ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲሁም በኢኮኖሚና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን ባህል በማድረግ ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማትን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ አምራችነትን ማሳደግ፣ ተረጂነትን መቀነስ፣ የስራ እድልን በሰፊው መፍጠር፣ የከተማ ግብርና፣ የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን፣ ፅዳትና የቆሻሻ አወጋገድን ባህል ማድረግ … ወዘተ፤ በአጠቃላይ ከተማችንን ጽዱ፣ ውብ እና ለሁሉም የምትመች ከተማ ማድረግ የእቅዳችን ትኩረቶች ናቸው። የእቅዳችን ቅኝትም ስትራቴጂክ እይታ ያለው፤ ራዕያችንን ለማሳካት አቅዶ መተግበር፤ የተለጠጠ፣ አካታች፣ ፍትሃዊ እንዲሁም አሳታፊ እንዲሆን ማድረግ ነው። ይህ የእቅድ ውይይት አመራራችን በዋናነት እቅዱን በተሟላ ሁኔታ የተረዳ፣ ስትራቴጂክ አመራር የሚሰጥ፣ በአስተሳሰብ አንድነት የሚቆም፣ ከተለያየ የጥቅም ትስስር ነፃ የሆነ፣ የይቻላል መንፈስን የተላበሰ፣ በአፈፃፀም ተቀራራቢ የሆነ፣ ትጋት እና የአመራር ዲሲፒሊን ያለው፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት እያሰፈንን ህዝቡ የከተማችንን ራዕይና ግብ የተጋራ እንዲሆን በተለየ መንገድ የሄድንበት የውይይት መድረክ ነው። ልማትን በመንግስት ብቻ ማሳካት እይቻልም። በመሆኑም መላው የከተማችን ነዋሪዎች፣ ግለሰቦችና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ፣ የግሉን ዘርፍ ማበረታታት፣ በጊዜ የለንም መንፈስ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ አሳድገን በከተማችን ለማሳካት የተወጠነውን ትልቅ ራዕይ ለመፈፀም በላቀ እንተጋለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
380
7
+9
没有文字...
347
8
+9
没有文字...
334
9
ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል። የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው። እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን። በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ
551
10
+6
没有文字...
490
11
ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደገ ነው AMN- ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ሙስና እና ብልሹ አሰራር በጊዜ እንዲገታ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ገልጸዋል፡፡ ከኤ ኤም ኤን ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን፤ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ ለመከላከል በሰፊው እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ ግንጸኝነትን እና አሳታፊነትን ተግባራዊ በማድረግ የማህበረሰብ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑንም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት በተሰራው ሥራ ውጤት ተገኝቷል ያሉት አቶ አብዱልቃድር፤ ግልጸኝነትን እና አሳታፊነትን እንዲሁም ተጠያቂነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገለፀዋል፡፡ ብልሹ አሰራር በዜጎች መካከል ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዳይኖር በማድረግ የሃገርን ኢኮኖሚ ጭምር ወደ ኋላ የሚጎትት ነው፡፡ መንግስትም ሙስናን ሃገራዊ ችግር አድርጎ በመውሰድ በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የተቋማት አቅም አለመዳበር እና የህዝብ ግንዛቤ በሚፈለገው ልክ አለመጎልበቱ የጸረ ሙስና ትግሉ የሚፈለገውን ውጤት እንዳያመጣ እንቅፋት እንደሆነ በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱና አገልግሎቶች ከሙስና በጸዳ አግባብ እንዲሰጡ በትኩረት እየሰራ ሲሆን፤ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡ በየሻምበል ምህረት
524
12
+2
没有文字...
501
13
"ዓድዋ ናይት ፋይት" በአዲስ አበባ ሰማይ ስር የተጻፈ አዲስ የስፖርት ታሪክ! ​በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም የተደረገው ታላቁ "ዓድዋ ናይት ፋይት" (Adwa Night Fight) የሚክስድ ማርሻል አርት (MMA) ውድድር በታላቅ ስኬት፣ በደመቀ ድባብ እና በሰላም ተጠናቋል! ​ይህ ታሪካዊ ምሽት የከተማችንን ሁለገብ አቅም፣ የስፖርታዊ ውድድሮች አዲስ እይታን፣ እንዲሁም መዲናችን አዲስ አበባ አለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ታላላቅ የስፖርት ዝግጅቶች የማስተናገድ ብቃቷ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ዳግም ያረጋገጠበት ነበር። ዋና ዋና የስኬት ኩነቶች፦ 1. ​ስማርት እና ዘመናዊ አዲስ አበባ :-የኢትዮጵያዊነት እና የፅናት ምልክት በሆነው በዓድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው ይህ ውድድር፤ የከተማችንን ዘመናዊነት (Smart City) እና ለትላልቅ አለም አቀፍ ኹነቶች ያላትን ዝግጁነት በግልጽ እና በተግባር አሳይቷል። 2. ​የተወዳዳሪዎች ድንቅ ብቃት:-ተወዳዳሪዎቻችን ያሳዩት ከፍተኛ የቴክኒክ፣ የፅናት እና የስፖርታዊ ጨዋነት ብቃት የምሽቱን ሳቢነት እና አዛኝነቱን በእጅጉ ጨምሮታል። 3. ​የስፖርቱ አዲስ ምዕራፍ:- እንደ Mixed Martial Arts (MMA) ያሉ አዳዲስ እና አሳታፊ የስፖርት አይነቶች በሀገራችን እያደጉ መምጣታቸውን እና የወጣቶቻችንን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ አዳዲስ አሰራሮች እየተተገበሩ መሆናቸውን ማሳያ ነው። 4. ​የህዝቡ ደማቅ አቀባበል፦ የስፖርት አፍቃሪው ህዝባችን ያሳየው ደማቅ ድጋፍ እና ፍቅር ውድድሩ ልዩ ቀለም እንዲላበስ አድርጎታል። ​ይህ ታላቅ ዝግጅት በስኬት እና በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ተወዳዳሪዎች፣ አዘጋጆች፣ የስፖርት አፍቃሪዎች እና ለከተማችን ነዋሪዎች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ​አዲስ አበባ፣ የአለም አቀፍ ስፖርታዊ ኹነቶች እና የታላላቅ ህልሞች መድረክ!
592
14
+1
没有文字...
546
15
+9
没有文字...
541
16
ዛሬ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማችን በመካሄድ ላይ ያለውን “የሜክሰድ ማርሻል አርት እና የንኪኪ ስፖርት በአንድ መድረክ የሚይዘው ዓድዋ ፋይት ናይት" ውድድር፣ በታሪካዊው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘት ወጣቶችን አበረታተዋል። ክብርት ከንቲባ በመልእክታቸው፥ ውድድሩ በአደጉና በበለፀጉ ሀገራት እጅግ ተወዳጅ ስፓርት ሲሆን፤ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፓር መሰረተ ልመቶችን የሚፈልግ በመሆኑ እስከአሁን በአገራችን ሲካሄድ አይስተዋልም፥ ዛሬ ግን በከተማችን በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ምቹ የስፓርት መሰረተ-ልማቶች እውን በመሆናቸዉ አዳዲስ የፓርት አይነቶች እየተካሄዱ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል። በመቀጠልም፥ ውድድሩ ወጣቶች ልዩ ተሰጥኦና ችሎታቸዉን የሚዳብሩበት ፣ለስፖርት ቱሪዝም፥ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብር የሚጠናከርበት፣ የከተማችንን ገፅታ የሚቀይር እና ተወዳዳሪነታችን የሚጨምር ነው ብለዋል። በመጨረሻም እንዲህ አይነት ውድድሮች፥ ወጣቱን ታሳቢ ያደረጉ መሠረተ-ልማቶችን ይበልጥ አጠናክረን እንድንሰራ ያደርገናል፤ ወጣቱም አለማቀፍ የተወዳዳሪነት መንፈስ እንዲያሳድግ ዕድል ይሰጣል ሲሉ ገልፀዋል። ክብርት ከንቲባ በመልእክታቸው አዘጋጆችን “በርቱ” ያሉ ሲሆን፤ ለተወዳዳሪዎችም መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
597
17
+7
没有文字...
568
18
የአራዳ የበጎነት መንደር ግንባታ በታቀደለት ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ይገኛል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው የአራዳ በጎነት መንደር የግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት ላይ መሆኑ ተገለጸ። የአራዳ የበጎነት መንደር የአቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጀመሩ ይታወሳል። ቀደም ሲል የደሳሳ ጎጆዎች መገኛና ለመኖር ምቹ ያልነበሩ አካባቢዎችን በመቀየር፣ በርካታ ዜጎችን ችግር ለመቅረፍ የታለመው ይህ ግዙፍ የበጎነት ተግባር በአጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ምዕራፍ ላይ መድረሱን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ባደረገው ቅኝት ታዝቧል። የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ተወካይ ኢንጂነር በሪሁን ደርቤ ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከተጀመረ 54 ቀናት ማስቆጠሩን አስታውቀዋል። ግንባታው በሁለት ዙሮች የተከፈለ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን፣ አንደኛው ዙር ከብሎክ 1 እስከ 3 ያሉ ብሎኮች ግንባታ የተጀመረበት ነው ብለዋል፡፡ ሁለተኛው ዙር ደግሞ ከብሎክ 4 እስከ 15 ያሉትን ብሎኮች አካቶ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአንደኛው ዙር ግንባታቸው የተጀመሩት ስትራክቸራል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን የብሎክ ዎርክ እና የልስን ሥራዎችም እስከ አምስተኛ ፎቅ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱ በ24/7 የስራ ባሕል በከፍተኛ ጥራት እና ፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን ፤ ይህ ስኬት እንዲመዘገብ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት እና ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ሚና እንደተጫወተ ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ስለግንባታው ሃሳብ የሰጡት ከአየሰና ባጫ ተቋራጭ ተወካይ ኃይለሚካኤል ዋቆሽ፣ የፊኒሺንግ፣ የቡሎኬት ግንባታ እና የልስን ስራዎችም በፍጥነት እየተከናወን መሆኑን ገልጸዋል። AMN
552
19
+4
没有文字...
563
20
በአዲስ አበባ ከተማ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደረገ ይገኛል። https://www.facebook.com/share/p/18ojLabZnW/
571