en
Feedback
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

Open in Telegram

AACABOF PUBLIC PAGE

Show more
3 088
Subscribers
+224 hours
+47 days
+12830 days
Posts Archive
ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስናካሂድ የነበረውን የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዝርዝር እቅድ ውይይት አጠናቀናል። በውይይታችንም እቅዶቹን ይበልጥ ተጨባጭ በማድረግ በቀጣይ አምስት ዓመታትም አልቀን በመፈፀም፣ የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት ሳንሸራርፍ ለመፈፀም፣ የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እጅግ ጠቃሚ እና ገንቢ ተግባቦት እና ዝግጁነት ፈጥረናል። ከሀገራዊ ፖሊሲና ስትራቴጂያችን በመነሳት ህዝባችንም በድጋሚ ሲመርጠን “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌታዊ ሀገር” ብለን የገባነውን ቃል ለመፈፀም እንደ አዲስ አበባ “አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት” ለማድረግ የጀመርነውን ጉዞ ዋና ርዕያችን አድርገናል። ለእቅዳችን ስኬት መሰረቶች የሆኑት ባለፋት አምስት ዓመታት አቅደን አልቀን ያስመዘገብነው ውጤት፣ የህዝብና መንግሥት ከደህነት የመውጣት ፍላጎት፣ በከተማችን የተፈጠረው የስራ ትጋት፣ በታማኝነት ማገልገል፣ በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ በፍጥነትና በጥራት የመፈፀም ልምድ፣ በጀትን በመቆጠብ መጠቀም ትልቅ ስንቅ ናቸው። በቀጣይ ትኩረታችንም ተቋማዊ ብቃትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ በአሰራር፣ በአደረጃጀት፣ የዘመነ ቴክኖሎጂ በሚጠቀም የላቀ አገልግሎት መስጠት፣ የተቀናጀ ጥራት ያለው ሰፊ መሰረት ልማት በፍጥነት መገንባት፣ አዲስ መሰረተ ልማት መገንባት ብቻ ሳይሆን ነባሮቹን በሚገባ ማስተዳደር፣ የንፁህ መጠጥ ውኃና የቤት አቅርቦት ማሳደግ፣ የማህበራዊ ዘርፍ (ጤና፣ ትምህርት …) ተደራሽነትና ጥራት እንዲሁም ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ አልቀን መፈፀም፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ ያሟላ የጤና አገልግሎት መስጠት፣ የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን፣ የከተማችንን የቱሪዝም መዳረሻ ከተማነት ማረጋገጥ፣ አዲስ አበባን ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ አፍሪካዊት ከተማ ማድረግ፣ ለወጣቶች ተጠቃሚነት፣ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲሁም በኢኮኖሚና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን ባህል በማድረግ ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማትን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ አምራችነትን ማሳደግ፣ ተረጂነትን መቀነስ፣ የስራ እድልን በሰፊው መፍጠር፣ የከተማ ግብርና፣ የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን፣ ፅዳትና የቆሻሻ አወጋገድን ባህል ማድረግ … ወዘተ፤ በአጠቃላይ ከተማችንን ጽዱ፣ ውብ እና ለሁሉም የምትመች ከተማ ማድረግ የእቅዳችን ትኩረቶች ናቸው። የእቅዳችን ቅኝትም ስትራቴጂክ እይታ ያለው፤ ራዕያችንን ለማሳካት አቅዶ መተግበር፤ የተለጠጠ፣ አካታች፣ ፍትሃዊ እንዲሁም አሳታፊ እንዲሆን ማድረግ ነው። ይህ የእቅድ ውይይት አመራራችን በዋናነት እቅዱን በተሟላ ሁኔታ የተረዳ፣ ስትራቴጂክ አመራር የሚሰጥ፣ በአስተሳሰብ አንድነት የሚቆም፣ ከተለያየ የጥቅም ትስስር ነፃ የሆነ፣ የይቻላል መንፈስን የተላበሰ፣ በአፈፃፀም ተቀራራቢ የሆነ፣ ትጋት እና የአመራር ዲሲፒሊን ያለው፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት እያሰፈንን ህዝቡ የከተማችንን ራዕይና ግብ የተጋራ እንዲሆን በተለየ መንገድ የሄድንበት የውይይት መድረክ ነው። ልማትን በመንግስት ብቻ ማሳካት እይቻልም። በመሆኑም መላው የከተማችን ነዋሪዎች፣ ግለሰቦችና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ፣ የግሉን ዘርፍ ማበረታታት፣ በጊዜ የለንም መንፈስ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ አሳድገን በከተማችን ለማሳካት የተወጠነውን ትልቅ ራዕይ ለመፈፀም በላቀ እንተጋለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል። የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው። እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን። በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደገ ነው AMN- ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ሙስና እና ብልሹ አሰራር በጊዜ እንዲገታ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ገልጸዋል፡፡ ከኤ ኤም ኤን ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን፤ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ ለመከላከል በሰፊው እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ ግንጸኝነትን እና አሳታፊነትን ተግባራዊ በማድረግ የማህበረሰብ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑንም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት በተሰራው ሥራ ውጤት ተገኝቷል ያሉት አቶ አብዱልቃድር፤ ግልጸኝነትን እና አሳታፊነትን እንዲሁም ተጠያቂነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገለፀዋል፡፡ ብልሹ አሰራር በዜጎች መካከል ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዳይኖር በማድረግ የሃገርን ኢኮኖሚ ጭምር ወደ ኋላ የሚጎትት ነው፡፡ መንግስትም ሙስናን ሃገራዊ ችግር አድርጎ በመውሰድ በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የተቋማት አቅም አለመዳበር እና የህዝብ ግንዛቤ በሚፈለገው ልክ አለመጎልበቱ የጸረ ሙስና ትግሉ የሚፈለገውን ውጤት እንዳያመጣ እንቅፋት እንደሆነ በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱና አገልግሎቶች ከሙስና በጸዳ አግባብ እንዲሰጡ በትኩረት እየሰራ ሲሆን፤ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡ በየሻምበል ምህረት

"ዓድዋ ናይት ፋይት" በአዲስ አበባ ሰማይ ስር የተጻፈ አዲስ የስፖርት ታሪክ! ​በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም የተደረገው ታላቁ "ዓድዋ ናይት ፋይት" (Adwa Night Fight) የሚክስድ ማርሻል አርት (MMA) ውድድር በታላቅ ስኬት፣ በደመቀ ድባብ እና በሰላም ተጠናቋል! ​ይህ ታሪካዊ ምሽት የከተማችንን ሁለገብ አቅም፣ የስፖርታዊ ውድድሮች አዲስ እይታን፣ እንዲሁም መዲናችን አዲስ አበባ አለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ታላላቅ የስፖርት ዝግጅቶች የማስተናገድ ብቃቷ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ዳግም ያረጋገጠበት ነበር። ዋና ዋና የስኬት ኩነቶች፦ 1. ​ስማርት እና ዘመናዊ አዲስ አበባ :-የኢትዮጵያዊነት እና የፅናት ምልክት በሆነው በዓድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው ይህ ውድድር፤ የከተማችንን ዘመናዊነት (Smart City) እና ለትላልቅ አለም አቀፍ ኹነቶች ያላትን ዝግጁነት በግልጽ እና በተግባር አሳይቷል። 2. ​የተወዳዳሪዎች ድንቅ ብቃት:-ተወዳዳሪዎቻችን ያሳዩት ከፍተኛ የቴክኒክ፣ የፅናት እና የስፖርታዊ ጨዋነት ብቃት የምሽቱን ሳቢነት እና አዛኝነቱን በእጅጉ ጨምሮታል። 3. ​የስፖርቱ አዲስ ምዕራፍ:- እንደ Mixed Martial Arts (MMA) ያሉ አዳዲስ እና አሳታፊ የስፖርት አይነቶች በሀገራችን እያደጉ መምጣታቸውን እና የወጣቶቻችንን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ አዳዲስ አሰራሮች እየተተገበሩ መሆናቸውን ማሳያ ነው። 4. ​የህዝቡ ደማቅ አቀባበል፦ የስፖርት አፍቃሪው ህዝባችን ያሳየው ደማቅ ድጋፍ እና ፍቅር ውድድሩ ልዩ ቀለም እንዲላበስ አድርጎታል። ​ይህ ታላቅ ዝግጅት በስኬት እና በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ተወዳዳሪዎች፣ አዘጋጆች፣ የስፖርት አፍቃሪዎች እና ለከተማችን ነዋሪዎች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ​አዲስ አበባ፣ የአለም አቀፍ ስፖርታዊ ኹነቶች እና የታላላቅ ህልሞች መድረክ!

ዛሬ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማችን በመካሄድ ላይ ያለውን “የሜክሰድ ማርሻል አርት እና የንኪኪ ስፖርት በአንድ መድረክ የሚይዘው ዓድዋ ፋይት ናይት" ውድድር፣ በታሪካዊው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘት ወጣቶችን አበረታተዋል። ክብርት ከንቲባ በመልእክታቸው፥ ውድድሩ በአደጉና በበለፀጉ ሀገራት እጅግ ተወዳጅ ስፓርት ሲሆን፤ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፓር መሰረተ ልመቶችን የሚፈልግ በመሆኑ እስከአሁን በአገራችን ሲካሄድ አይስተዋልም፥ ዛሬ ግን በከተማችን በተሰሩ ዘርፈ ብዙ ምቹ የስፓርት መሰረተ-ልማቶች እውን በመሆናቸዉ አዳዲስ የፓርት አይነቶች እየተካሄዱ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል። በመቀጠልም፥ ውድድሩ ወጣቶች ልዩ ተሰጥኦና ችሎታቸዉን የሚዳብሩበት ፣ለስፖርት ቱሪዝም፥ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብር የሚጠናከርበት፣ የከተማችንን ገፅታ የሚቀይር እና ተወዳዳሪነታችን የሚጨምር ነው ብለዋል። በመጨረሻም እንዲህ አይነት ውድድሮች፥ ወጣቱን ታሳቢ ያደረጉ መሠረተ-ልማቶችን ይበልጥ አጠናክረን እንድንሰራ ያደርገናል፤ ወጣቱም አለማቀፍ የተወዳዳሪነት መንፈስ እንዲያሳድግ ዕድል ይሰጣል ሲሉ ገልፀዋል። ክብርት ከንቲባ በመልእክታቸው አዘጋጆችን “በርቱ” ያሉ ሲሆን፤ ለተወዳዳሪዎችም መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የአራዳ የበጎነት መንደር ግንባታ በታቀደለት ፍጥነትና ጥራት እየተከናወነ ይገኛል በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የተጀመረው የአራዳ በጎነት መንደር የግንባታ ፕሮጀክት በከፍተኛ ፍጥነት ላይ መሆኑ ተገለጸ። የአራዳ የበጎነት መንደር የአቅመ ደካሞችና የሀገር ባለውለታዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መጀመሩ ይታወሳል። ቀደም ሲል የደሳሳ ጎጆዎች መገኛና ለመኖር ምቹ ያልነበሩ አካባቢዎችን በመቀየር፣ በርካታ ዜጎችን ችግር ለመቅረፍ የታለመው ይህ ግዙፍ የበጎነት ተግባር በአጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ምዕራፍ ላይ መድረሱን አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ባደረገው ቅኝት ታዝቧል። የፕሮጀክቱ አማካሪ ድርጅት ተወካይ ኢንጂነር በሪሁን ደርቤ ፤ የፕሮጀክቱ ግንባታ ከተጀመረ 54 ቀናት ማስቆጠሩን አስታውቀዋል። ግንባታው በሁለት ዙሮች የተከፈለ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን፣ አንደኛው ዙር ከብሎክ 1 እስከ 3 ያሉ ብሎኮች ግንባታ የተጀመረበት ነው ብለዋል፡፡ ሁለተኛው ዙር ደግሞ ከብሎክ 4 እስከ 15 ያሉትን ብሎኮች አካቶ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአንደኛው ዙር ግንባታቸው የተጀመሩት ስትራክቸራል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን የብሎክ ዎርክ እና የልስን ሥራዎችም እስከ አምስተኛ ፎቅ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። የግንባታ ሂደቱ በ24/7 የስራ ባሕል በከፍተኛ ጥራት እና ፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር በሪሁን ፤ ይህ ስኬት እንዲመዘገብ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት እና ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ ሚና እንደተጫወተ ጠቁመዋል፡፡ በሌላ በኩል ስለግንባታው ሃሳብ የሰጡት ከአየሰና ባጫ ተቋራጭ ተወካይ ኃይለሚካኤል ዋቆሽ፣ የፊኒሺንግ፣ የቡሎኬት ግንባታ እና የልስን ስራዎችም በፍጥነት እየተከናወን መሆኑን ገልጸዋል። AMN

በአዲስ አበባ ከተማ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደረገ ይገኛል። https://www.facebook.com/share/p/18ojLabZnW/

ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች ዳግም «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ተኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል። እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ። ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq Words shape thought, and thought transforms the world. Speeches transcend the boundaries of time, serving as an enduring seal of a people's identity and a testament to an era, passed down from generation to generation. Viewed through the lens of leadership, a word is never merely a fleeting sound, it is a source of power that defines history, reshapes society, and builds a nation, allowing the public to discern a nation's hope and its leaders' vision through their executive rhetoric. Prepared by the Office of the Prime Minister of Ethiopia, the speeches and messages delivered by His Excellency Prime Minister Abiy Ahmed (PhD) from 2017 to 2018 E.C. have been officially released to readers in the 8th volume of the book entitled “Meskerem to Meskerem.” Delve into this volume to explore His Excellency the Prime Minister’s year long journey and multifaceted efforts to reconstruct and uplift the nation through his key speeches and strategic directives delivered over time. ↓ Discover the full journey, access the book here ↓ Link: https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq #PMOEthiopia

https://www.facebook.com/share/v/18712fBvUG/ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ተርሚናልና የንግድ ማዕከል እና ፕላዛ ምርቃት ሥነ-ስርዓት ያስተላፍኩት መልዕክት ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የዘመነ መሰረተ ልማት፤ የዘመነ አገልግሎት ለዘመናዊ ከተማ! ዛሬ በከተማችን አራት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ተርሚናሎችና ገበያ ማዕከላት (በጎተራ፥ ቦሌ፣ የካ እና ቀበና) መርቀን አገልግሎት አስጀምረናል። እነዚህ መሰረተ ልማቶች የትራፊክ መጨናነቅን የሚያቃልሉ፣ የትራንስፖርት ሥርዓትን የሚያሻሽሉ፣ ህዝባችንን ከዝናብና ፀሐይ እንግልት የሚከላከሉ፣ በርካታ የስራ እድሎችን የሚፈጥሩ ምቹ ፣ ንፁህ እና የሰውን ክብር የሚመጥኑ የዘመነ አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው። መሰረተ ልማቶቹ በአንድ ጊዜ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ ዓቅም ያላቸው ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ የታክሲ እና የአውቶቡስ ተርሚናሎች፣ የአየር ብክለትን የሚከላከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያዎች፣ ሰፊ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች፣ የንግድ ሱቆች፣ ካፍቴሪያና ሬስቶራንቶች፣ የልጆች መጫወቻና ማረፊያ ስፍራዎች፣ ምቹ የተሳፋሪ መጠበቂያ ስፍራዎች፣ የአስተዳደር እና የትኬት መቁረጫ ቴክኖሎጂዎች፣ አሳንሰሮች እና ንፁህ መፀዳጃ ቤቶች እንዲሁም የደህንነትና የአደጋ ቅድመ መከላከል ሥርዓቶች የተሟሉላቸው የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎትን ለማሳለጥ ትልቅ አስተዋጽዖ የሚያበረክቱ ናቸው። ከለውጡ በፊት 3 ሺህ ብቻ የነበረውን የአንድ ጊዜ የተሽከርካሪ ማቆሚያ አቅም እና ምንም ያልነበረንን ተርሚናል በአሁኑ ጊዜ በጥራትና በፍጥነት የተገነቡ፣ ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችን እና ተርሚናሎችን ከ170 ሺህ በላይ ማድረስ ችለናል ። ለከተማችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በተጨባጭ ቃላችንን በተግባር ስራዎችን እየፈጸምን በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን። አዲስ አበባ ከዚህ በላይ ይገባታል ቀጣይም ከሰራነው በላይ እንተጋለን! የዛሬዎቹ ፕሮጀክቶች እውን እንዲሆኑ ለተጋችሁ፣ ላስተባበራችሁ የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የትራንስፖርት ቢሮ አመራሮች፣ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪዎች በዚህ ስራ የተሳተፋችሁትን ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ https://www.facebook.com/share/p/1CkPUgqAYu/

ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ! በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን ይዟል። የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ የቻለ ሲሆን የዚሁ ተምህርት ቤት ተማሪ የሆነው ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል። በከተማ አስተዳደራችንም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ ነች። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብም የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር ፣ የትምህርት አመራሮች ፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሰናስለው መስራት ፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራት እንዲሁም ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!