es
Feedback
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page

Ir al canal en Telegram

AACABOF PUBLIC PAGE

Mostrar más
3 094
Suscriptores
+724 horas
+27 días
+3630 días

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '26
+11
en 0 canales
agosto '26
+192
en 0 canales
Get PRO
julio '26
+110
en 0 canales
Get PRO
junio '26
+95
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+61
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+57
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+57
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+222
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+120
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+258
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+62
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+180
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+44
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+89
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+62
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+45
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+92
en 0 canales
Get PRO
abril '25
+80
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+346
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+532
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+219
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+432
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+193
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+178
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+43
en 1 canales
Get PRO
agosto '24
+73
en 1 canales
Get PRO
julio '24
+58
en 1 canales
Get PRO
junio '24
+37
en 2 canales
Get PRO
mayo '24
+34
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+36
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+10
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+17
en 1 canales
Get PRO
enero '24
+11
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+144
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+11
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+299
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
02 septiembre+9
01 septiembre+2
Publicaciones del Canal
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው። ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና የከተማ አስተዳደሩ ለሕፃናት እድገት እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት በተለይም በ"የአዲስ አበባ የወደፊት ተስፋ የቅድመ ልጅነት እድገት ተነሳሽነት" የተሰጠ እውቅና ነው። ኢኒሼቲቩ ቀዳማይ ልጅነትን በመንግሥታት ፖሊሲዎች እና በዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት አጀንዳ ማዕከል ላይ ለማስቀመጥ በትኩረት ይሰራል። ይህ እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን ፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው። እውቅናው አዲስ አበባን በአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት እድገት የከተማ አመራር ተምሳሌት ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ይታመናል።

2
+6
Sin texto...
114
3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግዢና የጨረታ ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ እያደረገ መሆኑ ተገለፀ። ################################################ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት (e-GP) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል:: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቢሮዎች፣ ክፍለ ከተሞችና ተቋማት የበጀት ዓመቱን የግብይትና የጨረታ ሂደቶች በኤሌክትሮኒክ ግዥ (e-GP) ሥርዓት በኩል ማከናወን ጀምረዋል። በከተማዋ ያሉ አቅራቢዎችና ኮንትራክተሮች በፖርታሉ ላይ በመመዝገብ የጨረታ ሰነዶችን በኦንላይን መግዛት፣ ማመልከትና ውጤት መከታተል የሚያስችላቸው አሠራር ተዘርግቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በመጀመሪያው ምዕራፍ በምዝገባ፣ በዕቅድ (Registration & Planning) እና በግዢ (Purchasing) ስልጠና ወስደው ወደ ትግበራ የገቡትን የ48ቱን ተቋማት ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች የተሟላ ዕውቀት ይዘው እንዲተገብሩ የጨረታ ሂደትና የውል አስተዳደር (Tendering & Contract Management) ሞጁሎች እንዲሁም አዲሱን የመንግስት ግዥ አዋጅ 92/2018 እና መመሪያ በማዘጋጀት አቅማቸውን እየገነባ እንደሚገኝ በፋይናንስ ቢሮ የመንግሥት ኤሌክትሮኒክ ግዢ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጴጥሮስ ሥዩም ገልፀዋል፡፡ የአሠራር ሽግግሩ ውጤታማ እንዲሆን ለከተማ አስተዳደሩ የግዥ ባለሙያዎችና ለአቅራቢዎች ተደጋጋሚ የስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ ፕሮግራሞች እየተሰጡ ይገኛሉ። ይህ አሠራር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይናንስ ሥርዓቱን ዘመናዊ፣ ግልጽና ወጪ ቆጣቢ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት በእጅጉ እያገዘው እንደሚገኝ አቶ ጴጥሮስ ገልፀዋል፡፡ ቢሮው የመንግሥት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ (e-GP) ሲስተም ትግበራን ወደ 60 ተቋማት ያሰፋፋ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ምዕራፍ በምዝገባ፣ በዕቅድና በግዥ ስልጠና ወስደው ወደ ትግበራ የገቡ 48 ተቋማት ባለሙያዎች የሲስተሙን አሠራር ቅደም-ተከተል ከመተግበራቸው ባሻገር፣ የባለሙያዎችን የሙያ ብቃት ደረጃ (Professionalism) የሚያሳድግና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (Certifications) የሚያስገኝ እንደሆነ ገልፀዋል። ቢሮው ሂደቱን በተግባር የሚደግፉ እውቀትና ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች በተቋማት በመመደብ የቅርብ እገዛ እያደረገ ይገኛል። የግዢና የጨረታ ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን በብቃት፣ በጥራትና በዘመናዊ ሲስተም እንዲመራ በማድረግ በከተማ አስተዳደሩ ግልጽነትና ፍትሃዊነት የሰፈነበት አሠራር ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አቶ ጴጥሮስ አመላክተዋል፡፡ ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !! ዌብሳይት:- aabof.com.et ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
332
4
Sin texto...
306
5
+2
Sin texto...
1
6
የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን” ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን” ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን” ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን” ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን” ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን” ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን” ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን” ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
961
7
ዛሬ 33ኛውን ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ “ብሩህ ነገን በዛሬ አዕምሮዎች” በሚል መሪ ቃል አስጀምረናል። ይህ ጉባኤ በየዓመቱ የምናካሂደው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን ጤናማ እና ውጤታማ ለማድረግ፣ በዘርፉ የተሰሩትን ጠንካራ ስራዎች ልምድ የምንቀምርበት፣ የሚታረሙትንም ለይቶ በጋራ መፍትሄ የምንሰጥበትና በጋራ እቅጣጫ የምንይዝበት ጉባኤ ነው ። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በከተማ አስተዳደራችን በልዩ ትኩረት ሰርተን የተማሪዎች ውጤት እየተሻሻለ መጥቷል። ዛሬ በከተማችን የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤት ወደ 33 በመቶ መሻሻል አሳይቷል። ነገር ግን አሁንም ከፍ ያለ ውጤት እንጠብቃለን፤ ገና ብዙ መሥራት ይጠበቅብናል። መምህራን፤ ባለድረሻ አካላት በእልህ ሰርተን መፍጠር የሚችሉ፣ ችግር የሚፈቱ፣ በሥነ ምግባር የታነፁ፣ እውቀት የታጠቁ ተማሪዎችን በብዛት ለመፍጠር መረባረብ ይጠበቅብናል። ከተማ አስተዳደራችን ዋናውን ኢንቨስትመንት ትምህርት ላይ እናውል ብለን፣ ትልቁን በጀት ለትምህርት ዘርፍ እንዲሆን አድርገናል። ትውልድ ላይ ከመሰረቱ መስራት ወሳኝ በመሆኑ፣ ዋና የእዕምሮ እድገት በጨቅላ ህፃንነት ወቅት በመሆኑ ቀዳማይ ልጅነት ላይ እየሰራን እንገኛለን። በዚህ አግባብ ከመሰረቱ ጀምረን እየሰራን በአንደኛ ደረጃ እንዲሁም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ውጤት እና በዲሲፕሊን የታነፀ ትውልድ እንጠብቃለን። እስካሁን በተገኘው ውጤት ሁላችሁንም ከልብ እያመሰገንኩ፤ በቀጣይም በእውቀት የበለፀጉ፣ በስነምግባር የታነፁ፣ አልቀው የሚሰሩ ተማሪዎች ለመፍጠር ከልብ፣ ዋጋ ከፍለን ተባብረን እንድንሰራ አደራ እላለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ
554
8
+9
Sin texto...
531
9
"መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት ነው" አቶ ዘላለም ሀብቴ #################################### ነሐሴ26/ 2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ መልካም አስተዳደር የሚጀምረው ከእያንዳንዱ ሰራተኛና አመራር ግላዊና ሙያዊ ስነ-ምግባራዊ ኃላፊነት እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዘላለም ሀብቴ ገለጹ። ዳይሬክተሩ በተቋሙ የስነ-ምግባር፣ የመልካም አስተዳደርና የፀረ-ሙስና አሰራሮችን አስመልክተው ለኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በሰጡት ቃለ-መጠይቅ፣ የስነ-ምግባር መከበር የህዝብን እምነት ለመገንባት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለማረጋገጥ እና የተቋሙን መልካም ስም ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። አቶ ዘላለም በመግለጫቸው እንደጠቆሙት፣ ስነ-ምግባር ማለት አንድ ግለሰብ ወይም ተቋም በስራና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው የሚከተላቸው የሞራል መርሆዎችና የአሰራር ደንቦች ስብስብ ነው። ታማኝነት፣ ቅንነት፣ ፍትሃዊነትና ኃላፊነት የአንድን አካል ትክክለኛ ውሳኔ የመወሰን አቅም እንደሚገነቡ ያብራሩት ዳይሬክተሩ፤ መልካም አስተዳደርን በዘላቂነት ለማስፈን እንደ ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ የህግ የበላይነት፣ ህዝባዊ ተሳትፎና ውጤታማነት ያሉ መሰረታዊ መርሆዎችን አጠናክሮ መተግበር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል። በሌላ በኩል መልካም አስተዳደርን የሚያደናቅፉ እንደ ተቋማዊ ድክመት፣ የበቂ ግልጽነትና ተጠያቂነት ማነስ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት፣ ቢሮክራሲያዊ መጓተትና ደካማ የቁጥጥር ስርዓት ያሉ ተግዳሮቶችን የመፍትሔ አቅጣጫዎች አመላክተዋል። እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ግልጽ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት፣ ተከታታይ ስልጠናዎችን መስጠት፣ የቅሬታ አቀራረብ ስርዓትን ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ እና ተጠያቂነት ያለው አመራር መገንባት እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል። በመጨረሻም ዳይሬክተሩ ሙስናና ብልሹ አሰራርን በጋራ መከላከል እንደሚገባ አሳስበው፣ ሙሉ ሰራተኞችና አመራሮች ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና ታማኝነትን በዕለት ተዕለት ስራቸው ውስጥ በመተግበር የተሻለና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህዝቡ ማበርከት እንደሚገባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
485
10
Sin texto...
379
11
በመዲናዋ 20 ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ - ከንቲባ አዳነች በተያዘው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ 20 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል። ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት ÷ በምርጫ ለሕዝብ የገባነውን ቃል ለመፈጸም 24/7 በትጋት በመስራት አዲስ አበባን ተምሳሌታዊ ከተማ እናደርጋታለን ብለዋል። ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የመዲናዋ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከሀገራዊ ርዕይ፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንጻር የተቃኘ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም ጠንካራ የተቋም ግንባታ፣ የተቀናጀ ጥራት ያለውና ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ አይበገሬ አረንጓዴ ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ይደረጋል ነው ያሉት፡፡ አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ 11 የመሶብ ማዕከላት መኖራቸውን ጠቁመው ÷ በ2019 በጀት ዓመት ተጨማሪ 20 ማዕከላት እንደሚከፈቱ ተናግረዋል፡፡ ማዕከላቱ የሚከፈቱት ወረዳዎችን በክላስተር በማደራጀት እንደሆነና በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 66 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላትን ለመክፈት መታቀዱን አመልክተዋል። በሁሉም ዘርፍ የተሳለጠ እና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ከንቲባዋ አረጋግጠዋል፡፡
356
12
+6
Sin texto...
399
13
የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
412
14
ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስናካሂድ የነበረውን የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዝርዝር እቅድ ውይይት አጠናቀናል። በውይይታችንም እቅዶቹን ይበልጥ ተጨባጭ በማድረግ በቀጣይ አምስት ዓመታትም አልቀን በመፈፀም፣ የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት ሳንሸራርፍ ለመፈፀም፣ የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እጅግ ጠቃሚ እና ገንቢ ተግባቦት እና ዝግጁነት ፈጥረናል። ከሀገራዊ ፖሊሲና ስትራቴጂያችን በመነሳት ህዝባችንም በድጋሚ ሲመርጠን “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌታዊ ሀገር” ብለን የገባነውን ቃል ለመፈፀም እንደ አዲስ አበባ “አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት” ለማድረግ የጀመርነውን ጉዞ ዋና ርዕያችን አድርገናል። ለእቅዳችን ስኬት መሰረቶች የሆኑት ባለፋት አምስት ዓመታት አቅደን አልቀን ያስመዘገብነው ውጤት፣ የህዝብና መንግሥት ከደህነት የመውጣት ፍላጎት፣ በከተማችን የተፈጠረው የስራ ትጋት፣ በታማኝነት ማገልገል፣ በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ በፍጥነትና በጥራት የመፈፀም ልምድ፣ በጀትን በመቆጠብ መጠቀም ትልቅ ስንቅ ናቸው። በቀጣይ ትኩረታችንም ተቋማዊ ብቃትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ በአሰራር፣ በአደረጃጀት፣ የዘመነ ቴክኖሎጂ በሚጠቀም የላቀ አገልግሎት መስጠት፣ የተቀናጀ ጥራት ያለው ሰፊ መሰረት ልማት በፍጥነት መገንባት፣ አዲስ መሰረተ ልማት መገንባት ብቻ ሳይሆን ነባሮቹን በሚገባ ማስተዳደር፣ የንፁህ መጠጥ ውኃና የቤት አቅርቦት ማሳደግ፣ የማህበራዊ ዘርፍ (ጤና፣ ትምህርት …) ተደራሽነትና ጥራት እንዲሁም ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ አልቀን መፈፀም፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ ያሟላ የጤና አገልግሎት መስጠት፣ የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን፣ የከተማችንን የቱሪዝም መዳረሻ ከተማነት ማረጋገጥ፣ አዲስ አበባን ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ አፍሪካዊት ከተማ ማድረግ፣ ለወጣቶች ተጠቃሚነት፣ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲሁም በኢኮኖሚና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን ባህል በማድረግ ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማትን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ አምራችነትን ማሳደግ፣ ተረጂነትን መቀነስ፣ የስራ እድልን በሰፊው መፍጠር፣ የከተማ ግብርና፣ የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን፣ ፅዳትና የቆሻሻ አወጋገድን ባህል ማድረግ … ወዘተ፤ በአጠቃላይ ከተማችንን ጽዱ፣ ውብ እና ለሁሉም የምትመች ከተማ ማድረግ የእቅዳችን ትኩረቶች ናቸው። የእቅዳችን ቅኝትም ስትራቴጂክ እይታ ያለው፤ ራዕያችንን ለማሳካት አቅዶ መተግበር፤ የተለጠጠ፣ አካታች፣ ፍትሃዊ እንዲሁም አሳታፊ እንዲሆን ማድረግ ነው። ይህ የእቅድ ውይይት አመራራችን በዋናነት እቅዱን በተሟላ ሁኔታ የተረዳ፣ ስትራቴጂክ አመራር የሚሰጥ፣ በአስተሳሰብ አንድነት የሚቆም፣ ከተለያየ የጥቅም ትስስር ነፃ የሆነ፣ የይቻላል መንፈስን የተላበሰ፣ በአፈፃፀም ተቀራራቢ የሆነ፣ ትጋት እና የአመራር ዲሲፒሊን ያለው፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት እያሰፈንን ህዝቡ የከተማችንን ራዕይና ግብ የተጋራ እንዲሆን በተለየ መንገድ የሄድንበት የውይይት መድረክ ነው። ልማትን በመንግስት ብቻ ማሳካት እይቻልም። በመሆኑም መላው የከተማችን ነዋሪዎች፣ ግለሰቦችና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ፣ የግሉን ዘርፍ ማበረታታት፣ በጊዜ የለንም መንፈስ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ አሳድገን በከተማችን ለማሳካት የተወጠነውን ትልቅ ራዕይ ለመፈፀም በላቀ እንተጋለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
496
15
+9
Sin texto...
528
16
+9
Sin texto...
474
17
ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል። ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል። የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው። እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን። በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ
610
18
+6
Sin texto...
539
19
ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደገ ነው AMN- ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ሙስና እና ብልሹ አሰራር በጊዜ እንዲገታ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን ገልጸዋል፡፡ ከኤ ኤም ኤን ጋር ቆይታ ያደረጉት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን፤ሙስና እና ብልሹ አሰራር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ ለመከላከል በሰፊው እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የኦዲት ፎረም ተቋቁሞ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እየተደረገ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ ግንጸኝነትን እና አሳታፊነትን ተግባራዊ በማድረግ የማህበረሰብ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየተደረገ መሆኑንም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለማስቀረት በተሰራው ሥራ ውጤት ተገኝቷል ያሉት አቶ አብዱልቃድር፤ ግልጸኝነትን እና አሳታፊነትን እንዲሁም ተጠያቂነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገለፀዋል፡፡ ብልሹ አሰራር በዜጎች መካከል ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዳይኖር በማድረግ የሃገርን ኢኮኖሚ ጭምር ወደ ኋላ የሚጎትት ነው፡፡ መንግስትም ሙስናን ሃገራዊ ችግር አድርጎ በመውሰድ በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የተቋማት አቅም አለመዳበር እና የህዝብ ግንዛቤ በሚፈለገው ልክ አለመጎልበቱ የጸረ ሙስና ትግሉ የሚፈለገውን ውጤት እንዳያመጣ እንቅፋት እንደሆነ በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱና አገልግሎቶች ከሙስና በጸዳ አግባብ እንዲሰጡ በትኩረት እየሰራ ሲሆን፤ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡ በየሻምበል ምህረት
629
20
+2
Sin texto...
628
BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @aacabofp