en
Feedback
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

Open in Telegram

Every one comment us about the informations that we are uploading. you are also very wellcommed to give us nominations which helps us to improve our capability with regard to the concerns of the organization.

Show more
1 488
Subscribers
+124 hours
-47 days
+1430 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
July '26
July '26
+25
in 0 channels
June '26
+51
in 0 channels
Get PRO
May '26
+38
in 0 channels
Get PRO
April '26
+33
in 0 channels
Get PRO
March '26
+37
in 0 channels
Get PRO
February '26
+30
in 0 channels
Get PRO
January '26
+37
in 0 channels
Get PRO
December '25
+42
in 0 channels
Get PRO
November '25
+64
in 0 channels
Get PRO
October '25
+52
in 0 channels
Get PRO
September '25
+44
in 0 channels
Get PRO
August '25
+47
in 0 channels
Get PRO
July '25
+47
in 0 channels
Get PRO
June '25
+37
in 0 channels
Get PRO
May '25
+31
in 0 channels
Get PRO
April '25
+50
in 0 channels
Get PRO
March '25
+52
in 0 channels
Get PRO
February '25
+51
in 0 channels
Get PRO
January '25
+79
in 0 channels
Get PRO
December '24
+134
in 0 channels
Get PRO
November '24
+98
in 0 channels
Get PRO
October '24
+95
in 0 channels
Get PRO
September '24
+74
in 0 channels
Get PRO
August '24
+111
in 0 channels
Get PRO
July '24
+32
in 0 channels
Get PRO
June '24
+32
in 0 channels
Get PRO
May '24
+51
in 0 channels
Get PRO
April '24
+177
in 0 channels
Get PRO
March '24
+555
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
18 July+1
17 July+1
16 July0
15 July+3
14 July+1
13 July0
12 July+1
11 July+2
10 July+1
09 July+5
08 July+4
07 July0
06 July0
05 July+2
04 July+1
03 July0
02 July+1
01 July+2
Channel Posts
የመዲናዋ የዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ አፈጻጸም እስከአሁን 79% መድረሱ ተገለፀ። በዚህ 2018/19 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሁሉም ክፍለ ከተሞች የተለያዩ የችግ
+1
የመዲናዋ የዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ አፈጻጸም እስከአሁን 79% መድረሱ ተገለፀ። በዚህ 2018/19 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሁሉም ክፍለ ከተሞች የተለያዩ የችግኝ ዓይነቶችን በየአካባቢያቸው በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን ለማሳረፍ በታቀደው የክረምት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ዕቅድ መሠረት እስካሁን ባለው ጊዜ ከፍተኛ አፈጻጸም መመዝገቡ ተገለፀ። በከተማ አቀፍ በወጣው መረጃ መሠረት በክረምቱ የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በአጠቃላይ 6,000,807 ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን እስካሁን ባለው ጊዜ 4,759,435 ችግኞችን በመትከል ዕቅዱን በ79% ማሳካት ተችሏል። ከተተከሉት ችግኞች መካከል 2,268,991 የጥላ ዛፎች፣ 2,102,297 የውበት ዛፎች እንዲሁም 388,147 የፍራፍሬ ችግኞች መሆናቸው ተመልክቷል። በዚህ የታላቅ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የኅብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን በአጠቃላይ 756,575 ነዋሪዎች በተከላው ላይ ተሳትፈዋል። ከነዚህም መካከል 360,480 ወንዶች ሲሆኑ 396,095 ሴቶች በመሆን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የኅብረተሰብ ክፍል ድርሻ ይዘዋል። የችግኝ ተከላው ቀሪ ዕቅዶችን ሙሉ በሙሉ ለማሳካትና የተተከሉትንም የመንከባከብ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

2
በከተማዋ የሀይድሮ ሲዲንግ ሳር ተከላ ቴክኖሎጂን ገቢራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ሙከራ ግምገማ ተካሄደ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የከተማዋን የአረንጓዴ ልማት ስራ ለማዘመን የሚያስች+4
በከተማዋ የሀይድሮ ሲዲንግ ሳር ተከላ ቴክኖሎጂን ገቢራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ሙከራ ግምገማ ተካሄደ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የከተማዋን የአረንጓዴ ልማት ስራ ለማዘመን የሚያስችል የሀይድሮ ሲዲንግ  የሳር ተከላ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ለማድረግ የሙከራ ግምገማ አካሂዷል፡፡ ለዚህ ቴክኖሎጂ ተግባራዊነትም አዋጭነቱን ለማረጋገጥ የሙከራ ስራ ተሰርቶ የተገመገመ ሲሆን አበረታች ዉጤት በማስገኘቱ በቀጣይነት የከተማዋን የአረንጓዴ መሰረተ ልማት በዚህ መንገድ ለማዘመን እንደ አንድ አማራጭ ተቀምጧል፡፡
181
3
#ችግኝ እንዴት ይተከላል?
#ችግኝ እንዴት ይተከላል?
231
4
በከተማዋ የሀይድሮ ሲዲንግ ሳር ተከላ ቴክኖሎጂን ገቢራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ሙከራ ግምገማ ተካሄደ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የከተማዋን የአረንጓዴ ልማት ስራ ለማዘመን የሚያስች+3
በከተማዋ የሀይድሮ ሲዲንግ ሳር ተከላ ቴክኖሎጂን ገቢራዊ ለማድረግ የሚያስችል የቅድመ ሙከራ ግምገማ ተካሄደ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የከተማዋን የአረንጓዴ ልማት ስራ ለማዘመን የሚያስችል የሀይድሮ ሲዲንግ  የሳር ተከላ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ለማድረግ የሙከራ ግምገማ አካሂዷል፡፡ ለዚህ ቴክኖሎጂ ተግባራዊነትም አዋጭነቱን ለማረጋገጥ የሙከራ ስራ ተሰርቶ የተገመገመ ሲሆን አበረታች ዉጤት በማስገኘቱ በቀጣይነት የከተማዋን የአረንጓዴ መሰረተ ልማት በዚህ መንገድ ለማዘመን እንደ አንድ አማራጭ ተቀምጧል፡፡
137
5
#እኔ ተዘጋጅቻለሁ! እናንተስ?
#እኔ ተዘጋጅቻለሁ! እናንተስ?
460
6
በ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ መሰብሰብ ችለናል። የገቢ መሰረትን በማስፋትና የሚሰበሰብ ገቢ ፍትሀዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲሰበሰብ በማድረግ በሰፊው በመሰራቱ የ2ዐ18 ገቢ አሰ+4
በ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ መሰብሰብ ችለናል። የገቢ መሰረትን በማስፋትና የሚሰበሰብ ገቢ ፍትሀዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲሰበሰብ በማድረግ በሰፊው በመሰራቱ የ2ዐ18 ገቢ አሰባሰብ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃር በ 116.3 ቢሊዮን ብር ወይም 50 % እድገት አሳይቷል። ግብር ከፋዮቻችንን ከልብ እናመሰግናለን!! ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ
448
7
No text...
435
8
የተማሪዎች የክረምት ወራት አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ተሳተፎ ሀገራዊ ስሜትን በማጎልበት ረገድ ፋይዳዊ የጎላ ነው ። የክረምት ወራት ተማሪዎች ከክፍል ውስጥ ትምህርት ወጥተው በተግባራዊ እውቀት የሚበለፅጉበት ወርቃማ ወቅት ነው። በዚህ ወቅት ወጣቶችና ህጻናት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ በክፍል ውስጥ በንድፈ-ሀሳብ የተማሩትን የተፈጥሮ ሳይንስ የስነ-ምህዳር (ecosystem) እውቀትን ከአካባቢያቸው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በቀጥታ ለማስተሳሰር ይረዳቸዋል። ይህ አይነቱ የተግባር ትምህርት ከተራ የቃላት ሽምደዳ ባለፈ የተማሪዎችን አስተሳሰብ በሰፊው ያሳድጋል። ከተፈጥሮ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት መፍጠራቸው የአዕምሮንና የአካላዊ ስራን በአንድነት በማዋሃድ ሁለንተናዊ እድገታቸውን ያፋጥነዋል። የአካባቢ እንክብካቤ ግንዛቤ በልጅነት ጊዜ ሲቀረጽ ዘላቂና ጠንካራ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው። ተማሪዎች በልጅነታቸው አካባቢያቸውን፣ አፈራቸውንና እፅዋትን መንከባከብ ያለውን የላቀ ጠቀሜታ ተረድተው ሲያድጉ የነገው የአካባቢ ተቆርቋሪ ዜጋ ሆነው ይቆማሉ። ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ሂደት ውስጥ ተማሪዎች የስራን ክቡርነት በተግባር ይረዳሉ። ማንኛውም ስራ በተለይም ለአገርና ለተፈጥሮ የሚደረግ ጥረት ትልቅ ዋጋ እንዳለው ስለሚገነዘቡ ለስራ ያላቸው አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ ይቀረጻል። ይህ መርሃ-ግብር ከግል ጥንካሬ ባለፈ ማህበራዊ ክህሎትን ለማዳበር ትልቅ ድልድይ ነው። ተማሪዎች በጋራ ጉድጓድ ሲቆፍሩ፣ ችግኝ ሲያጓጉዙና ሲተክሉ ሌሎች ሰዎችን አክብረው በጋራ እንዴት ተባብረው መስራት እንደሚችሉ ይማራሉ። የቡድን ስራ (teamwork) ያለውን ኃይልና በጋራ የሚሰራ ስራ ውጤታማነቱ ቀጣይነት እንደሚኖረው በተግባር ይመሰክራሉ። በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ የተማሪዎችን ስነ-ልቦናዊ ጤንነት በማሳደግ ከዲጂታል ስክሪኖች ሱስ እንዲርቁና ንጹህ አየር እያገኙ ማህበራዊ ትስስራቸውን እንዲያጠናክሩ ትልቅ ድጋፍ ያደርጋል። በጣም አስደሳች የሚያደርገዉ ደግሞ ተማሪዎች የለፉበትና የሰሩት ነገር ፍሬ አፍርቶ፣ ችግኞቹ አድገው አካባቢውን ሲያስተካክሉ በተግባር ማየታቸው ነው። ይህ ውጤት በሀገራቸው ላይ ያላቸውን ተስፋ በእጅጉ ያሳድጋል። የሌሎችን እጅ ከመጠባበቅ ይልቅ በሀገራቸው በራሳቸው እጅ ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ እና ውብ ሀገር መፍጠር እንደሚቻል ትልቅ እምነት ያሳድርባቸዋል። በገዛ ጉልበታቸውና እውቀታቸው ያሸበረቀች አረንጓዴ አገርን ሲያዩ በሀገራቸው ይኮራሉ፤ የአገራዊ ማንነትና የበለጸገ ማንነት ስሜታቸውም ከፍ ይላል። ለማጠቃለል፣ የተማሪዎች የክረምት የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ የአንድ ወቅት ስራ ብቻ ሳይሆን የነገዋን የበለጸገች አገር የሚረከቡ ንቁ፣ አገር ወዳድ፣ ስራ አክባሪና ከተፈጥሮ ጋር የተስማሙ ትውልዶችን የማፍሪያ ታላቅ ብሄራዊ የዕዉቀት መድረክ ነዉ።
426
9
ኑ ፍሬ እናፍራ ***** የምንተጋለት ውጤት የጋራ ልማታችን ነው! በርትተን ከሰራን፣ ተባብረን ካለማን የሀገራችንን ጸጋ አሟጠን በመጠቀም የምግብ ዋስትናችንን ማረጋገጥና የጋራ ብልጽግናችንን ማብሰር
ኑ ፍሬ እናፍራ ***** የምንተጋለት ውጤት የጋራ ልማታችን ነው! በርትተን ከሰራን፣ ተባብረን ካለማን የሀገራችንን ጸጋ አሟጠን በመጠቀም የምግብ ዋስትናችንን ማረጋገጥና የጋራ ብልጽግናችንን ማብሰር እንችላለን። ምድር ፍሬ የምትሰጠው ለታታሪዋ፤ ሀገር የምትለማው በህብረት ነው። ዛሬ የምንተክለው፣ የምንጠብቀውና የምንከባከበው ፍሬ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ የብልጽግና መሰረት ነው። በጋራ እንስራ፤ ለራሳችንና ለሀገራችን ፍሬ እናፍራ! #ኑ_ፍሬ_እናፍራ #የጋራ_ልማት #ምግብ_ዋስትና
423
10
ኢትዮጵያ እየተከለች ነው! እርስዎስ? በክረምቱ አሻራዎን ያኑሩ። #Green Legacy
ኢትዮጵያ እየተከለች ነው! እርስዎስ? በክረምቱ አሻራዎን ያኑሩ። #Green Legacy
419
11
+3
No text...
471
12
በወንዝ ዳርቻ ልማት ቀጣይነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ጥናት ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከሳውዝ ጌት-አዴይ አበባ-ቦሌ ቪ አይ ፒ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ኮሪደር ልማትን አስመልክቶ የቀረበውን የአካባቢ ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ እና የመልሶ ማስፈር ዕቅድ ጥናታዊ ፅሁፍ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል። በጥናቱ ግምገማ ላይ የቢሮው ኃላፊ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉን ጨምሮ የቢሮው የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥናቱ አቅራቢ የባዮስፌር ኢንቫይሮመንታል ኮንሳልቲንግ አማካሪ ድርጅት ተወካዮች ተገኝተዋል። ይህ በ12 ኪሎ ሜትር ርዝመት ላይ የሚያርፈው ታላቅ የኮሪደር የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ከመጀመሩ በፊት እንዲህ ዓይነት ጥናት መደረጉ እጅግ አስፈላጊ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተገልጿል። ጥናቱ የፕሮጀክቱን አዎንታዊ ጎኖች አስቀድሞ ለመለየት እና ሊከሰቱ ለሚችሉ ተፈጥሯዊና ማህበራዊ ችግሮች አስቀድሞ ምላሽ ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ እጅግ ወቅታዊ ስራ መሆኑም ተነግሯል። በዕለቱም በአማካሪ ድርጅቱ በዝርዝር በቀረበው በዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ ላይ የፕሮጀክቱ ጠቀሜታዎች፣ ሊያስከትላቸው የሚችላቸው አሉታዊ ተፅዕኖዎች እና እነዚህን አሉታዊ ጎኖች ለመቀነስ የሚያስችሉ ተገቢ የመፍትሄ አቅጣጫዎች በቀጣይነት ተዳስሰዋል። ከተሳታፊ የቢሮው ባለሙያዎችም ጥናቱን ይበልጥ ሊያዳብሩ የሚችሉ የተለያዩ ሙያዊ ሃሳቦችና የማስተካከያ ግብዓቶች የቀረቡ ሲሆን፣ በአማካሪ ድርጅቱ ተወካዮች በኩልም ለተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። በማጠቃለያውም የቢሮው ኃላፊ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ በቀረበው ጥናት ላይ የተሰጡት ጠቃሚ የባለሙያ ግብዓቶች እንዲካተቱበት ያሳሰቡ ሲሆን አማካሪ ድርጅቱ ጥናቱን ይበልጥ ግልፅና አጠር ባለ መልኩ አሻሽሎ በቀጣይ እንዲያቀርብም የስራ መመሪያ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
347
13
No text...
288
14
የአዲስ አበባ ሞዴል የከተማ ብሎኮች … በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተጀምሮ ወደ ክልል ከተሞች የተስፋፋው የኮሪደር ልማት የከተሞችን ገፅታ በከፍተኛ ደረጃ እየቀየረው ይገኛል። ከዚህ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ ጎን ለጎን ደግሞ ወደ ውስጥ ያሉ የመኖሪያ መንደሮችን ደረጃ ለማሻሻል የተጀመረው የተቀናጁ ሞዴል የከተማ ብሎኮች ግንባታ አዲስና ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ከፍቷል። ይህ አዲስ የከተማ ፕላን አቀራረብ መዲናዋን ዘመናዊ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ከማድረግ ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ዘላቂ አንደምታዎችን ይዟል። በተለምዶ የከተማ ማደስ ስራዎች ሲነሱ የነባር ነዋሪዎች መፈናቀል እና የማህበረሰብ ስነ-ልቦናዊ መበተን ቀዳሚው ስጋት ነበር። የሞዴል የከተማ ብሎኮች ልማት ግን ይህንን አካሄድ የቀየረ ነው። ነዋሪዎች ከአካባቢያቸው ሳይነሱ፣ ባሉበት መንደር ውስጥ ያሉትን መኖሪያ ቤቶች፣ የጋራ መገልገያዎችን እና የውስጥ መንገዶችን በጋራ በማልማት ላይ ያተኩራል። ይህም ማህበረሰቡ ለዘመናት ያካበተው ማህበራዊ እሴት ሳይቋረጥ የኑሮ ደረጃው እንዲያሻሽል ያስችለዋል። ይህ የልማት ሞዴል የመኖሪያ እና የንግድ ቦታዎችን በአንድ ላይ አጣምሮ የያዘ ነው። አብዛኛዎቹ የከተማዋ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ነዋሪዎች ህይወታቸው የተመሰረተው በአነስተኛ ንግድ እና በቤት ውስጥ ስራዎች ላይ ነው። ብሎኮቹ የንግድ ሱቆችን፣ የአነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ቦታዎችን እና የገበያ ማዕከላትን በውስጣቸው ስለሚያካትቱ፣ ነዋሪዎች የተሻሻለ የመኖሪያ ቤት ማግኘታቸው ብቻ ሳይሆን የገቢ ምንጫቸውም ተጠብቆ እንዲቀጥል ያደርጋል። ይህ ደግሞ በከተማዋ ያለውን ድህነት ለመቀነስ ትልቅ አስተዋፅዖ ያበረክታል። የሞዴል ብሎኮች ግንባታ የነዋሪዎችን የዕለት ተዕለት የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽሉ በርካታ መሠረተ ልማቶችን ያካትታል። ብሎኮቹ ለህፃናት መጫወቻ፣ ለአረጋውያን ማረፊያ እና ለስፖርት ማዘውተሪያ የሚሆኑ ስፍራዎችን ያካትታሉ። ደረጃቸውን የጠበቁ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት እና የኮብልስቶን መንገዶች፣ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች እና ወጥ የቆሻሻ አያያዝ ስርዓቶችም አሉት። በተጨማሪም የማኅበረሰብ አቀፍ ፖሊስና የጥበቃ ማዕከላትን በማካተት የአካባቢውን ሰላም አስተማማኝ እያደረገው ነው። ሌላው የዚህ ሞዴል ትልቁ አንደምታ ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ላይ ማስተናገዱ ነው። በብሎኮቹ ውስጥ የሚገነቡት ህንጻዎች እና የንግድ ቦታዎች የሚያስገኙት ገቢ፣ የዝቅተኛ ገቢ ማህበረሰብ ክፍሎችን የመኖሪያ ቤት ግንባታ እና የመሠረተ ልማት ወጪን ለማቃለል ይውላል። ይህ አካሄድ የከተማዋን የቤት አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እና ፍትሃዊ የከተማ ልማትን ለማረጋገጥ ትልቅ የፖሊሲ መፍትሄ እየሆነ ነው። የእነዚህ ብሎኮች ስኬት በዋናነት የመንግስት፣ የባለሀብቶች እና የነዋሪዎች የተቀናጀ ተሳትፎ ውጤት ነው። በብሎኮቹ ህብረተሰቡ በጉልበቱ፣ በገንዘቡ እና በሃሳቡ ልማቱን በባለቤትነት እንዲመራው እየተደረገ ይገኛል፡፡ ይህ ሂደት በማህበረሰቡ ውስጥ የባለቤትነት ስሜትን ከመፍጠሩም በላይ፣ የጋራ ችግሮችን በጋራ የመፍታትና የበጎ ፈቃድ ባህልን በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ነው፡፡ በአጠቃላይ፣ የአዲስ አበባ ሞዴል የከተማ ብሎኮች ልማት መዲናዋን ወደ ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ከማሸጋገር ባለፈ፣ የነዋሪዎቿን ማህበራዊ ህይወት እና የኢኮኖሚ አቅም ባገናዘበ መልኩ የሚተገበር ፍትሃዊ የከተማ ማደስ ስራም ነው። ሥራው በስፋት ወደ ሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ሲሰፉ፣ የኢትዮጵያን የከተማ ልማት ጉዞ ወደ አዲስ ከፍታ እንደሚያሸጋግረው አያጠራጥርም፡፡
338
15
No text...
334
16
+4
No text...
373
17
የመዲናዋ አዲሱ የውበት ማዕከል፤ የቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት+9
የመዲናዋ አዲሱ የውበት ማዕከል፤ የቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት
324
18
በአዲስ አበባ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎና በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው፡፡ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ስራ በተገቢውና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ ይገኛል። ለተከላው ስራ የሚሆኑ ዘርፈ ብዙና ለተለያዩ ጠቀሜታዎች የሚውሉ የችግኝ ዝርያዎች በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅተዋል። እስካሁን በተከናወኑ ተመሳሳይ ስራዎች የተገኙ ጠቃሚ ተሞክሮዎችንና ልምዶችን መሰረት በማድረግ፣ የመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ በመሆኑ ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞች የመጽደቅ እድላቸው ከፍተኛ እንዲሆን ተደርጎ መዘጋጀቱ ታውቋል። ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ ሰፊው የመዲናዋ ህብረተሰብ በንቃትና በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተሳተፈበት ይገኛል። ከተማችን አዲስ አበባም ለጉዳዩ ትልቅ ቦታ በመስጠት የሚጠበቅባትን ድርሻ በብቃት እየተወጣች ትገኛለች። ይህ ንቅናቄ ቆንጆ፣ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ፣ የችግኝ ተከላንና እንክብካቤን በህብረተሰቡ ዘንድ ወደ ዘላቂ ባህል የመቀየር ትልቅ ምዕራፍ ላይ መደረሱን በተግባር እያሳየ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ህዝቡ በተግባርና በመንፈስ እርስ በእርሱ እንዲቀራረብና አንድነቱን እንዲያጠናክር ከፍተኛ ድርሻ እያበረከተ ነው። በማንኛውም ሀገር ላይ ዘላቂ ለውጥ ሊመጣ የሚችለው ህዝቦች በሀገራቸው ጉዳይና በልማት ስራዎች ላይ በባለቤትነት ስሜት ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆን ሲችሉ ብቻ እንደሆነ በተጨባጭ እየታየበት ያለ ሂደት ነው። ይህ የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ አዲሱ ትውልድ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ንቁ፣ ተቆርቋሪና ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው። ወጣቱ ትውልድ ዛሬ በሚያኖረው አረንጓዴ አሻራ የነገዋን ውብና ለኑሮ ምቹ ሀገር የመገንባት ታሪካዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
349
19
No text...
308
20
በመዲናዋ የተጀመረዉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንደቀጠለ ነዉ፡፡ በከተማችን አዲስ አበባ የተጀመረዉ የ2018/19 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሁሉም ክ/ከተሞች+3
በመዲናዋ የተጀመረዉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንደቀጠለ ነዉ፡፡ በከተማችን አዲስ አበባ የተጀመረዉ የ2018/19 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሁሉም ክ/ከተሞች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደ ሀገር “ተስፋን እንትከል” በሚል መርህ ቃል በክቡር ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ ከተበሰረ በኋላ መዲናችን አዲስ አበባም የክረምት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን የተለያዩ የመዲናዋ የህብረተሰብ ክፍሎችን በንቅናቄ መልክ አስተባብራ በማሳተፍ እየተገበረች ትገኛለች፡፡ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ የሆኑ ችግኞች የመዲናዋን የአየር ንብረት ሁኔታ ግምት ዉስጥ ባስገባ መልኩ እየተተከሉ ሲሆን በተለይም ለሀገር በቀል ዛፎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የችግኞቹ ስብጥር የጥላ፤ለምግብነት የሚዉሉ የፍራፍሬ፤ የዉበት፤ለመድኃኒትነትና ለቅመማ ቅመም አገልግሎት የሚዉሉ የችግኝ ዓይነቶች ታሳቢ ተደርገዋል፡፡ መዲናዋ የአለም አቀፍ የአረንጓዴ ሽፋን ስታንዳርድ ላይ ለመድረስ እየተቃረበች የምትገኝ ሲሆን በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት አሁን ካለችበት 24 በመቶ ወደ 30 በመቶ የአረንጓዴ ሽፋን ግቧ ለመድረስ ደፋ ቀና እያለች ትገኛለች፡፡
493