Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
Channel Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 795 subscribers, ranking 1 541 in the Medicine category and 2 158 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 795 subscribers.
According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 324 over the last 30 days and by 13 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.13%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.56% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 863 views. Within the first day, a publication typically gains 1 352 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center.
For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Medicine category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 03 September | 0 | |||
| 02 September | +14 | |||
| 01 September | +4 |
| 2 | No text... | 360 |
| 3 | No text... | 332 |
| 4 | HDSS Network, Health Sector Officials and Academic Institutions Sign MoU
-----------------------------------------------------
A Memorandum of Understanding (MoU) has been signed between the Health and Demographic Surveillance System (HDSS) Network and health sector officials and representatives of academic institutions to improve coordination in generating and using population ƀased health and demographic data for health planning and decision-making.
Organized by the Impact HDSS Ethiopia Project, the high-level event brought together leadership from the Ministry of Health (MoH), Ethiopian Public Health Institute (EPHI) and HDSS host academic institutions, to ratify governance frameworks, formalize data-sharing agreements, and advance evidence-informed health policy.
Dr. Mesay Hailu, Director General EPHI, delivered the opening speech, emphasizing the importance of a coordinated and standardized health surveillance system in supporting Ethiopia’s national health priorities.
Highlighting the scale of the network, Dr. Mesay noted that it brings together 14 public universities, one college and 15 surveillance sites, covering nearly 1.4 million people across more than 256,000 households. He emphasized the role of the network in generating long-term health and demographic evidence at the population level.
He also underscored the need to integrate the surveillance sites through standardized digital and technological platforms, which would help connect local-level data with national health policies, strengthen cause-of-death reporting, and improve disease surveillance and outbreak response. He acknowledged the support of partners, including the Gates Foundation and Vital Strategies, for the initiative.
Representing the Ministry of Health, Dr. Muluken Argaw, Strategic Lead Executive Office Director, underscored the importance of reliable population data in shaping health policy, strategic planning and targeted interventions.
Dr. Muluken highlighted the role of the HDSS network in generating evidence from communities and making that information available to support national health priorities. He emphasized that institutionalizing the network would strengthen the link between population-level evidence and decisions made at the national level.
He also noted the importance of sustained collaboration among the Ministry of Health, EPHI and the academic institutions hosting HDSS sites. Such collaboration, he emphasized, would support the continued generation and use of high-quality health and demographic data for planning and decision-making.
Technical presentations on the sustainability of the HDSS Network and the Management of Data Access and sharing, were featured on the program.
May be an image of dais and text. May be an image of one or more people, dais and newsroom. May be an image of text. May be an image of one or more people. May be an image of one or more people and dais | 963 |
| 5 | No text... | 865 |
| 6 | የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዳይሬክተሮች የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና የኢንስቲትዩትን የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማስተባበሪያ ማዕከል (PHEOC)፣ የቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (VHF) ላቦራቶሪ፣ የጂኖሚክስ ላቦራቶሪ እና የስነ ምግብ ላቦራቶሪዎችን የቴክኒክ ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝቱ ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎችን በእውነተኛ ጊዜ ለማስተባበር፣ ከፍተኛ ስጋት ያላቸውን በሽታ አምጪ ተህዋስያን ለመመርመር፣ የጂኖም ክትትልና ትንተና ለማካሄድ እንዲሁም በስነ ምግብ ዘርፍ የላብራቶሪ ምርመራና ሳይንሳዊ ድጋፍ ለመስጠት ያለውን አቅም ለተሳታፊዎቹ እንዲያውቁ አስችሏል። | 1 521 |
| 7 | No text... | 1 520 |
| 8 | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ክልሎች የሕብረተሰብ ጤና ምርምርን እንዲያጠናክሩ የዲጂታል መሠረተ ልማት መሳሪያዎች ድጋፍ አደረገ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአውሮፓ ሕብረት ድጋፍ የተገዙ ሰርቨሮችን ለአራት ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች የመረጃ ቋትን፣ ዲጂታላይዜሽን እና የምርምር አቅምን እንዲያጠናክሩ የዲጂታል መሠረተ ልማት መገልገያዎች ድጋፍ አድርጓል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢንስቲትዩቱ የ2019 ዓ.ም ዓመታዊው የግምገማ ጉባኤ ጎን ለጎን ክልሎች እራሳቸውን እንዲያጠናክሩና የቴክኖሎጅ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ይህ ድጋፍ እንደተደረገላቸው በመግለፅ፣ ክልሎች መረጃዎቻቸውን በአግባቡ እንዲያከማቹ፣ እንዲተነትኑ እና ለምርምርና ውሳኔ ሰጪ ሥራዎች እንዲያውሉ እንዲሁም በአገር ደረጃ የመረጃ ልውውጥን እንዲያሳልጡ እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ በበኩላቸው ድጋፉ አፋር፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ምርምር እንዲያካሂዱና የጤና ሥርዓቱን እንዲያጠናክሩ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።
የአፋር ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀመዶ አህመድ የተደረገው ድጋፍ የተቋማቸውን የመረጃ ማከማቻ ቋት እና የሕብረተሰብ ድንገተኛ አደጋ ቁጥጥር ማዕከልን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።
https://ephi.gov.et/ኢንስቲትዩቱ-ክልሎች-የሕብረተሰብ-ጤና-ም/
https://x.com/i/status/2095105686485024867
https://ephi.gov.et/ኢንስቲትዩቱ-ክልሎች-የሕብረተሰብ-ጤና-ም/
https://x.com/i/status/2095105686485024867
https://www.facebook.com/share/p/1DiLAhVzrp/ | 1 346 |
| 9 | No text... | 1 085 |
| 10 | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2019 በጀት ዓመት የሥራ እቅድ ውይይት ተደረገበት::
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2019 በጀት ዓመት የሥራ እቅድና ዋና ዋና የአፈጻጸም አመልካቾችን ይፋ አደረገ፤ እቅዱ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር፣ በላብራቶሪ አገልግሎት፣ በምርምርና በተቋማዊ አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በ215 ወረዳዎች የወረርሽኝ ዝግጁነትና ምላሽ ዕቅዶችን ማጠናቀቅ፣ 14 ሀገራዊ የሙከራ ልምምዶችን ማካሄድ እና የጤና አደጋ ምላሽ አቅም ማሳደግን ያካትታል።
ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር፣ ዕቅዱ በቀረበበት ወቅትና የኢንስቲትዩቱ ዓመታዊ የግምገማ ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢንስቲትዩቱ፣ የክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች፣ ከክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች የጋራ ቅንጅትና ጥረት ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልጸው በበጀት አመቱ የነበረውን አፈጻጸም በዝርዝር በመገምገሙ የነበሩ ጥንካሬዎችን ለማሳደግ እና ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት ታቅደው ለተያዙ የትኩረት አቅጣጫዎች በተሻለ ሁኔታ ለማዘጋጀት ማስቻሉን አብራርተዋል።
ዶ/ር መሳይ አያይዘውም በምርምርና መረጃ አያያዝ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን በማጠናከር፣ ሀገራዊ የህብረተሰብ ጤና ፖሊሲዎችንና ውሳኔዎችን በእውቀትና መረጃ ላይ የተመሰረቱ ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የላብራቶሪ መሠረተ ልማቶችን ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 3 (BSL-3) እንዲሁም ተንቀሳቃሽ የላብራቶሪ አገልግሎቶችን ማዘመን፣ ልኬቶችን ማስቀጠል እና የዲጂታል መረጃ ስርዓትን ማስፋፋት የሀገሪቱን የባዮ-ደህንነትና የመመርመር አቅም ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
የኢንስቲትዩቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሕይወት አበበ እቅዱን ሲያቀርቡ፣ የተቀመጡት ግቦች ከሀገራዊ የጤና ዘርፍ ቅድሚያ ሰጪ ጉዳዮች፣ ከክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች እና አጋር ድርጅቶች የትግበራ ስትራቴጂዎች ጋር የተናበቡ እና የተጣጣሙ በመሆናቸው የጋራ የሥራ ማዕቀፍ በመሆን ያገለግላሉ ብለዋል።
ወ/ሮ ሕይወት ስለ ዕቅዱ ሲያብራሩ፣ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ ዘርፍ፣ በ215 ወረዳዎች የወረርሽኝ ዝግጁነትና ምላሽ ዕቅዶችን ማጠናቀቅ እና 14 ሙሉ ሀገራዊ የሙከራ ልምምዶችን ማካሄድ ታቅዷል። የPHEM-DHIS2 መረጃ ኤክስፖርት ትክክለኛነትና ሙሉነትን ወደ 85 በመቶ እና የትራከር ሪፖርት ሽፋንና ሙሉነትን ወደ 90 በመቶ ለማሳደግም ግብ ተይዟል።
የሕብረተሰብ ጤና ስጋት ግምገማ ሪፖርቶችን በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ማቅረብ እና ለሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የሚሰጠውን ምላሽ ከ80 ወደ 85 በመቶ ማሳደግ፣ በላብራቶሪ አገልግሎት ዘርፍ 250 ደረጃ በደረጃ ላብራቶሪዎችን ለማሻሻል ወደ እውቅና ለመሄድ የሚደረግ ልዩ ልዩ ስራዎችን ለመደገፍ፣ 80 ላብራቶሪዎችን ለISO 15189:2022 ዕውቅና ለማብቃት እና 2,500 የሕብረተሰብ ጤናና ክሊኒካል ላብራቶሪዎችን ካርታ ለማዘጋጀት መታቀዱን ዕቅዱ ያመላክታል።
በዕቅዱ በምርምር ዘርፍ 95 የምርምር ፕሮጀክቶች፣ 38 የቴክኒክ ምርምር ሪፖርቶች፣ 45 የማስረጃ አጫጭር መግለጫዎች እና 117 የበሽታዎች ጫና ግምገማ ሪፖርቶችን ለማጠናቀቅ፣ ሰባት የሀገር አቀፍ የፖሊሲ አጫጭር መግለጫዎችንም ለማተም፣ የምርምር ትኩረቶቹም የእናቶችና ሕፃናት ጤና፣ የስነ-ተዋልዶ ጤና፣ ስነ ምግብ፣ ወባ እና ትኩረት የተነፈጋቸው የሐሩራማ በሽታዎች ተካተዋል።
የተቋሙን አቅም ለማጠናከርም 17,367 የጤና ባለሙያዎችን በአደጋ ቁጥጥር፣ በምርምርና በላብራቶሪ ዘርፎች ለማሰልጠን፣ 18 አዳዲስ የስልጠና ሞጁሎችን ለማዘጋጀት እና 18 አዳዲስ የስልጠና ፕሮግራሞችን ለመዘርጋት፣ ከአስራ አራት ሚሊዮን ብር በላይ የውስጥ ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዷል።
ዶ/ር መሳይ የዓመታዊ የግምገማ ስብሰባውን የመዝጊያ ንግግር በማድረግ የሥራ መመሪያ ካስተላለፉ በኋላ ተሳታፊዎች የኢንስቲትዩቱን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማእከል፣ ቪ ኤች ኤፍ ላብራቶሪ (VHF Laboratory)፣ ጄኖሚክስ ላብራቶሪ (Genomics Laboratory) እና የስነ ምግብ ላብራቶሪዎችን በመጎብኘት ስብሰባው ተጠናቋል። | 1 404 |
| 11 | No text... | 1 288 |
| 12 | የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች አፈጻጸም እያደገ መምጣቱ ተነገረ::
የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች በ2018 ዓ.ም የጤና አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ፣ የበሽታ ቅኝት፣ የላቦራቶሪ ምርመራና የምርምር አቅማቸውን በማጠናከር የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገባቸውን ገለጹ። ይህን ያስታወቁት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸማቸውን ሲያቀርቡ ነው።
የአማራ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ፣ ኢንስቲትዩቱ በ2018 ዓ.ም ካቀዳቸው ሥራዎች ከ95 በመቶ በላይ ማሳካቱን ገልጸዋል። ክልሉ በተለይም በዲጂታል የታገዙ የላቦራቶሪና የጤና አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ የአንድ ጤን አገልግሎት እና መሰል የሕብረተሰብ ጤና አቅሞችን ከማሳደግ ባለፈ የምርምር ሥራዎችን ማጠናከሩን ጠቁመዋል።
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ፣ ማርበርግን ጨምሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመመከትና ለመቆጣጠር የተቀናጀ የምላሽ ሥርዓት መጠናከሩን ገልጸዋል። በበሽታ ክትትልና ምርመራ፣ በግንኙነት ክትትል፣ በማኅበረሰብ ተሳትፎና በአደጋ ምላሽ አቅም ላይ የተገኙ ውጤቶች ለቀጣይ ጤና አደጋዎች ዝግጁነት ጠንካራ መሠረት መሆናቸውን አስረድተው፣ ኢንስቲትዩቱ በ2018 ዓ.ም ካቀዳቸው ሥራዎች 95 በመቶ በላይ ያህሉን ማሳካቱንም ገልጸዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾፌ፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት በተለይም በቅርቡ የተከሰተውን የማርበርግ ቫይረስ ለመቆጣጠር ውጤታማ ሥራ መሠራቱን ገልጸዋል። በክልሉ ተደጋጋሚ የጤና አደጋዎች መከሰታቸው የምላሽ አቅምን የበለጠ ማጠናከር እንዳስፈለገ ጠቁመው፣ ጠንካራ አመራርና ትብብር ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት ወሳኝ መሆኑን አስረድተው በ2018 ዓ.ም 87% በላይ አፈፃፀም እንዳመጡ ተናግረዋል።
የአፋር ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀመዶ አህመድ በበብኩላቸው፣ ክልሉ በሞቃታማና በረሃማ አካባቢ እንዲሁም ከሁለት አገራት ጋር በሚዋሰን ድንበር ላይ በመገኘቱ ሊከሰቱ ለሚችሉ የጤና አደጋዎች ዝግጁነቱን እያጠናከረ መሆኑን ገልጸዋል። በቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ በሕብረተሰብ ጤና ቅኝት፣ በላቦራቶሪ ምርመራና በአደጋ ምላሽ አቅም ላይ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዴንጉ ፌቨርና ኮሌራ ወረርሽኞች ላይ የተቀናጀ ምላሽ በመስጠት የወረርሽኝ ሞትን ወደ ዜሮ ማድረስ መቻሉን እና በአጠቃላይ በበጀት አመቱ ከ84.2% በላይ የስራ አፈፃፀም እንዳለው አስታውቀዋል።
የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶቹ ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከክልል አመራሮችና ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት በበሽታ ቅኝትና ምላሽ፣ በላቦራቶሪ፣ በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽንና በጤና አደጋ ዝግጁነት የተገኙ ውጤቶችን ለማጠናከር በቀጣይም በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። | 1 789 |
| 13 | No text... | 1 492 |
| 14 | No text... | 1 549 |
| 15 | በድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ፣ በላቦራቶሪና በምርምር አቅም ጉልህ እድገት ማስመዝገቡን የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ገለጸ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፈው በጀት ዓመት በብሔራዊ የጤና ድንገተኛ ምላሽ፣ በዲጂታል የበሽታ ክትትል፣ በላቦራቶሪ ምርመራ እና በጥናትና ምርምር አቅም ማስፋፋት ጉልህ እድገት ማስመዝገቡን አስታወቀ።
ተቋሙ ይህን ያስታወቀው በዓመታዊ የግምገማ ስብሰባው ላይ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ የሕብረተሰብ ጤናን ለማረጋገጥ የቅድመ-ማስጠንቀቂያና ዝግጁነት ሥራዎችን፣ የክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችን አቅም ማጠናከርን እና የጤና ዲፕሎማሲን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የአደጋ ቅድመ-ማስጠንቀቂያና ዝግጁነት ሥራዎችም በአፋር፣ ሶማሌ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያና ሲዳማ ክልሎች ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዶ/ር መልካሙ አብቴ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው፣ ኤምፖክስ፣ ኮሌራና ኩፍኝን ጨምሮ የተለያዩ የጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቢከሰቱም፣ ኢንስቲትዩቱ በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች የተመሠረተ ምላሽ መስጠቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የድንገተኛ አደጋ ቅንጅት ማዕከላት (EOCs) ከክልል ደረጃ ወደ ንዑስ ክልልና ዞን ደረጃ እየተስፋፉ መሆኑን ጠቁመዋል። በድንበር መግቢያና መውጫ ነጥቦችም ከ7.8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በዲጂታል የጤና ክትትል ምርመራ አግኝተዋል። በዲጂታል የበሽታ ክትትል በኩል፣ የDHIS2 ሽፋን ከ2024 ዓ.ም. 7 በመቶ ወደ 52 በመቶ አድጎ በአሁኑ ወቅት ከ81–85 በመቶ መድረሱ ተገልጿል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ እንደገለጹት፣ የሪፈራል ላቦራቶሪ ምርመራዎች ከ113 ሺህ ወደ 217 ሺህ ናሙናዎች አድገዋል። ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪዎችን ወደ ወረርሽኝ ቦታዎች በመላክም ናሙናዎችን ወደ አዲስ አበባ ሳያጓጉዙ በቦታው በ48 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በተከሰተበት ወቅትም ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪ ወደ ጂንካ መላኩን እንደምሳሌ ጠቅሰዋል።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የምርምር ሥራዎች ከመንግሥት ፖሊሲ፣ ከአገራዊ የጤና ቅድሚያዎችና ከሕብረተሰቡ የጤና ችግሮች ጋር እንዲጣጣሙ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል። ተቋሙም ከክልል የምርምር ተቋማትና ከአካዳሚክ ማዕከላት ጋር የአቅም ግንባታና የልምድ ልውውጥ እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
በቀጣይ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የክልል ላቦራቶሪዎችንና የምርምር ተቋማትን አቅም ማጠናከር፣ ብሔራዊ ባዮባንክ ማቋቋም፣ የላቦራቶሪ ጥራት ማረጋገጫን ማጠናከር እና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና መካከል ያለውን የአንድ ጤና (One Health) ቅንጅት ማሳደግ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ኃላፊዎችም በሰጡት አስተያየት፣ ኢንስቲትዩቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለው ለውጥ የሚበረታታ እና ፈለጉን ለመከተል ምሳሌ መሆን የሚችል እንደሆነ ገልጸዋል። | 1 344 |
| 16 | No text... | 1 399 |
| 17 | ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች በመሰረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና እውቅና ተሰጣቸው
------------------------
ከአዲስ አበባ የተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ 37 የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ከኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከል ጋር በመሆን የሰጠውን የመሰረታዊ የፊልድ ኢፒዲሞሎጂ ስልጠና (Frontline Field Epidemiology Training Program) አጠናቀው ተመርቀዋል።
አቶ ዳንኤል ዳምጠው የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር እንዲሁም የምርምር ዳይሬክተር አሁን ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ባለሙያዎች የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ላይ ያላቸውን አቅም ይበልጥ የገነቡ ሲሆን ይህንንም አቅም በስራቸው በመተግበር ለሕብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ጥራት እንደሚያጎለብተው ገልጸው በቀጣይም እውቅና ካገኙት ባለሙያዎች መካከል አብላጫ ውጤት ያመጡት ቀጣዩን የመካከለኛ (Intermediate) ከዛም በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍተኛ (Advanced) FETP ስልጠናዎችን የመሰልጠን እድል እንደሚመቻችላቸው ገልጸዋል።
በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር በዝግጁነት ዳይሬክቶሬት የፈጣን ምላሽ ቡድን አስተዳድር ዲቪዥን ሃላፊ ዶ/ር መልካሙ አስራት ስልጠናው የተሰጠው በጽንሰ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን ተግባርንም ያካተተ በመሆኑ ባለሙያዎቹ በስራቸው ላይ ያላቸውን የጤና አደጋዎችን የመለየት፣ የመከላከል እና የመቆጣጠር አቅማቸውን የሚያዳብር መሆኑን የገለጹ ሲሆን ወ/ሮ እናኑ ሁነኛው የኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከል ተጠባባቂ ዳይሬክተር በበኩላቸው የስልጠናው የስልጠና መመሪያዎች (training manuals) ከወቅቱ ጋር እንዲስተጋበሩ በቅርቡም ተሻሽለው እንደሚቀርቡ ተናግረዋል።
የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት ባለሙያና የስልጠናው አስተባባሪ አቶ አወል ዳውድ እንዳስረዱት ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር አቅምን ለማሳደግ ስልጠናውን ተደራሽ በማድረግ ላይ ሲሆን የአሁኖቹን ተመራቂዎች ጨምሮ ከ235 በላይ ከአዲስ አባባ የመጡ ባለሙያዎች ስልጠናውን ወስደዋል። ስልጠናው የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቀድሞ የመለየት የመከላከልና ምላሽ የመስጠት ግንዛቤ እንዲሁም መሰረታዊ የኮምፒውተር ሞያዎች ጨምሮ ለባለሙያዎች በስፋት መሰጠቱን ተናግረዋል። | 1 831 |
| 18 | No text... | 1 669 |
| 19 | No text... | 1 700 |
| 20 | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 ዓ.ም. የተከናወኑ አበይት ውጤቶቹን ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) በ2018 በጀት ዓመት በሕብረተሰብ ጤና ደኅንነት፣ በበሽታ ቅኝትና ምላሽ፣ በላብራቶሪ፣ በምርምር፣ በዲጂታላይዜሽንና በጤና ስጋት ዝግጁነት ያስመዘገባቸውን ስትራቴጂያዊ ውጤቶች የሚገመግምበትንና የ2019 ዓ.ም. የተቋማዊ ግቦች ትውውቅ የሚያደርግበትን ዓመታዊ ጉባኤ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተሮች ፣የማኔጅመንት አባላት እና የክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተሮች እና ተወካዮች በተገኙበት ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የሀገሪቱን የሕብረተሰብ ጤና እና የጤና ደኅንነት ማዕቀፍ በጥንካሬ ለማስቀጠል የተቀረጹ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በመከተል ተጨባጭና ውጤቶች መምጣታቸውን አረጋግጠዋል።
ኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ቀድሞ የመለየት፣ የመከላከልና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ሀገራዊ አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ አጠናክሯል። በዚህም በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያና በዋና ዋና የየብስ ድንበር መግቢያዎች ላይ የሚደረገውን የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ቅኝት አጠናክሮ ማስቀጠሉን ዶ/ር መሳይ ጠቁመዋል።
አያይዘውም በኤምፖክስ (Mpox) እና በማርበርግ (Marburg) ወረርሽኞች ወቅት በተዘረጋ የተቀናጀ የምላሽ ሥርዓት በሽታዎቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ መደረጉን ገልጸዋል።
የማርበርግ ወረርሽኝ ምላሽ ወቅት ከ20 ሚሊዮን በላይ የቤት ለቤት ጉብኝት፣ የበሽታ አሰሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን፣ ከ4.3 ሚሊዮን በላይ ተጓዦች በበሮች ላይ የጤና ምርመራ አግኝተዋል። የኤምፖክስና ሌሎች ወረርሽኞች ምላሽ ወቅትም ከ4.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጤና ትምህርት የተሰጣቸው ሲሆን፤ በኮሌራ፣ በወባ፣ በዴንጊ፣ በማጅራት ገትርና በሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ላይ የተቀናጀ የምላሽ ሥራ ተከናውኖ ከ3.7 ሚሊዮን በላይ ሰዎችም የኮሌራ ክትባት እንዲያገኙ ተደርጓል።
ተቋሙን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች አስተዳደር የልቀት ማዕከል (PHEM-COE) ለማድረግ የተያዘው ዘመናዊ የዲጂታላይዜሽን ፕሮጀክት ከዝግጅት ምዕራፍ ወደ ሙሉ ትግበራ እንዳሸጋገረ የገለፁት ዳይሬክተሩ ከአጋር አካላት በተገኘ ድጋፍ 3,515 ዘመናዊ ኮምፒውተሮች ተገዝተው ለ12 ክልሎች፣ ለ2 የከተማ አስተዳደሮች፣ ለፌዴራል ፖሊስና ለመከላከያ የጤና መዋቅሮች ተሰራጭተዋል። በተጨማሪም የ830 ወረዳዎች የአደጋ ስጋት ልየታ መረጃ በSTAR ሞጁል አማካኝነት ወደ ePHEM ሥርዓት እንዲገባ ተደርጓል ብለዋል።
ዶ/ር መሳይ ኢንስቲትዩቱ በISO 15189:2022 ዓለም አቀፍ መስፈርት ላይ የተመሠረተ የጥራት አሠራርን ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን፣ በተደረገው የቴክኒክ ድጋፍና ክትትል 10 የጤና ላብራቶሪዎች ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና (Accreditation) ማግኘታቸውን ገልፀዋል። 125 ላብራቶሪዎች በSLIPTA ፕሮግራም ሥር ድጋፍና ክትትል ያገኙ እንደሆነ እና፣ የBLQMS ትግበራም በሀገር ደረጃ 86 በመቶ መድረሱን ጠቁመው በዓመቱ 683,320 የሪፈራል ናሙናዎች በመደበኛና በአማራጭ የትራንስፖርት መንገዶች በተገቢው ጥንቃቄ መጓጓዛቸውን ገልፀዋል።
በሳይንሳዊ ምርምር ዘርፍ አመርቂ ውጤት እየመጣ እንደሆነ እና ኢንስቲትዩቱ 127 የምርምር ውጤቶችን በታዋቂ ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ጆርናሎች ላይ ማሳተሙን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ለ49 የምርምር ጥናቶች ደግሞ ቴክኒካል ሪፖርት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ ጥናቶቹ በሥርዓተ ምግብ፣ በጤና ሥርዓት፣ በተላላፊና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ የምርምር ጥራታቸውና ተአማኒነታቸው በገለልተኛ አካላት በኩል ዓለም አቀፍ መስፈርቱን ማሟላታቸው ተረጋግጧል።
በተጨማሪም የEMIS 2025 ሰርቬይ በይፋ ተጀምሮ የመረጃ ሰብሳቢዎች ሥልጠና ተጠናቆ ወደ መስክ የተሰማሩ ሲሆን፣ የምርምር ሥነ-ምግባር ቦርድ (IRB) ፕሮፖዛሎችን በዲጂታል ሥርዓት መገምገም መጀመሩ የምርምር ሥነ-ምግባር ክትትል ሂደቱን አዝምኖታል።
ኢንስቲትዩቱ በብሔራዊ የጤና ደኅንነት የድርጊት መርሃ ግብር (NAPHS) እና በ«አንድ ጤና» (One Health) ማዕቀፍ አማካኝነት የብዝሃ-ዘርፍ ትብብርን ያጠናከረ ሲሆን፣ በበርካታ ዓለም አቀፍ የሕብረተሰብ ጤና መድረኮችና ከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶች በመሳተፍ የሁለትዮሽና የብዙ ወገን ስትራቴጂያዊ አጋርነቱን አጠናከረ ዶ/ር መሳይ በንግግራቸው አውስተዋል።
ዶ/ር መሳይ በመጨረሻም የ2018 ዓ.ም. ስኬቶች ኢንስቲትዩቱ ከምርምርና መረጃ ማመንጨት ጀምሮ እስከ ላብራቶሪ አቅም ማጠናከር፣ ወረርሽኝ መቆጣጠርና ፈጣን ምላሽ መስጠት ድረስ ያለውን ብሔራዊ መሪነት የሚያረጋግጡ ሲሆን በዚህ ጉባኤው በ2018 ዓ.ም. የተመዘገቡ አፈጻጸሞችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር በመገምገም፣ በ2019 ዓ.ም. የተቋሙን ተልዕኮ በበለጠ ውጤታማነት ለማሳካት የሚያስችሉ ሀገራዊ ዕቅዶችን በመወያየትና በማጽደቅ ይጠናቀቃል ብለዋል። | 1 649 |
