Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
El canal Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 795 suscriptores, ocupando la posición 1 678 en la categoría Medicina y el puesto 2 281 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 795 suscriptores.
Según los últimos datos del 04 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 301, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.81%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.37% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 634 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 386 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center.
For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Medicina.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 05 julio | +2 | |||
| 04 julio | +6 | |||
| 03 julio | +22 | |||
| 02 julio | +11 | |||
| 01 julio | +13 |
| 2 | የኢንስቲትዩቱ የብሄራዊ የጤና መረጃ አሰተዳደር ቅመራና ማእከል የሕብረተሰብ ጤና ፖሊሲ ሞዴሊንግ ዉድድርን አስጀመረ
EPHI’s Data Management Opens Public Health Policy Modelling Hackathon in Addis Ababa
---------------------------------
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል የሕብረተሰብ ጤና ፖሊሲ ሞዴሊንግ ሃካቶን (ውድድር) 2026 በአዲስ አበባ ያስጀመረ ሲሆን ይህ ከሰኔ 24 እስከ 29/2018 ዓ.ም ለስድስት ቀናት የሚቆየው ይህ ሃካቶን (ውድድር) “ሞዴሊንግን እና ፖሊሲን በማስተሳሰር የሕዝብ ጤና ተግዳሮቶችን መፍታት” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ መርሐ-ግብሩን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፤ ይህ የሃካቶን (የፈጠራ ውድድር) በኢንስቲትዩቱ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን ገልጸው፣ በሕብረተሰብ ጤና ዘርፍ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ አሰጣጥን ለማጠናከር ረገድ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቅሰዋል። ሞዴሊንግ ከቴክኒካዊ ትንተና ባለፈ መሄድና ለፕሮግራም ዕቅድ ዝግጅት፣ ለሀብት ክፍፍል፣ ለአገልግሎት አሰጣጥ እና ለፖሊሲ ውሳኔዎች ድጋፍ ለመስጠት መዋል እንዳለበትም አክለው ገልጸዋል። የሕዝብ ጤና ውሳኔዎች ብዙውን ጊዜ ውስን በሆኑ ሀብቶች፣ ያልተሟሉ መረጃዎች እና እርስ በርስ በሚፎካከሩ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የሚወሰኑ በመሆናቸው፤ ሞዴሊንግ እና የመረጃ ትንተና (ዳታ አናሊቲክስ) አማራጮችን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ፣ ምርጫዎችን ለማነጻጸር እና ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ ለመገመት እንደሚረዱ ዶ/ር መሳይ ገልጸዋል። በዚህ ረገድ ዋነኛው ጥያቄ ሊሆን የሚገባው “ምን ዓይነት ሞዴል መገንባት እንችላለን?” የሚለው ሳይሆን፣ “ለየትኛው የፕሮግራም ወይም የፖሊሲ ውሳኔ ነው በማስረጃ የተደገፈ እገዛ ማድረግ የምንፈልገው?” የሚለው ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ይህ የሃካቶን መድረክ መረጃን ከማስረጃ፣ ማስረጃን ከውሳኔ አሰጣጥ፣ ውሳኔ አሰጣጥን ደግሞ በተግባር ከሚገለጥ የሕብረተሰብ ጤና ዕርምጃ ጋር ለማገናኘት የሚረዳ ተግባራዊ መድረክ እንደሚፈጥርም አክለው ገልጸዋል።
የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል (NDMC) ዳይሬክተር ዶ/ር ትግስት ሹመት በበኩላቸው የማዕከሉ አንዱ ተግባርና ኃላፊነት የጤና ፕሮግራሞችን እና የፖሊሲ ውሳኔዎችን ለማገዝ የሚያስችሉ የመረጃ አያያዝ፣ የትንተና እና የሞዴሊንግ ሥራዎችን ማከናወን መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሃካቶንም በ ጌትስ ፋውንዴሽን በሚደገፈው የሞዴሊንግ አቅምን ለማጠናከር እየተተገበረ ያለዉ የፕሮጀክት አካል መሆኑን ገልጸዋል።
በመጀመሪያው የሥራ ቀን የመረጃ ትንተና፣ ሞዴሊንግ እና ቪዥዋላይዜሽን ዲቪዥን ኃላፊ በሆኑት በአቶ ሙሉጌታ ገረመው የሃካቶኑን ዓላማዎች፣ የሥራ ሂደቶች፣ የሚጠበቁ ውጤቶች እና የዳኝነት ሂደቶችን በተመለከተ ማጠቃለያ ቀርቧል። በብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና ማዕከል ዳታ ሳይንቲስት የሆኑት ዶ/ር መስፍን ለተሳታፊዎቹ ስለ ትብብር ደንቦች፣ ስለ ቡድን ምስረታ እና ስለ ውድድሩ ተግዳሮት መስኮች ገለጻ አድርገዋል። በተጨማሪም በፕሮጀክት ሆፕ (Project HOPE) የከፍተኛ የትግበራ ምርምር አማካሪ ፕሮፌሰር ጋሻው፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በሥነ ተዋልዶ፣ በእናቶች፣ በአራስ ሕፃናት፣ በሕፃናት ጤና እና በሥነ ምግብ ውጤቶች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ባለብዙ ገፅታ ተጋላጭነቶችን የሚያብራራውን "Pathways for Ethiopia" ጥናት አቅርበዋል።
ውድድሩ በቁልፍ አራት የተግዳሮት ዘርፎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ በወረዳ ደረጃ ያልተከተቡ (ዜሮ-ዶዝ) ሕፃናት መጠን (ጫና)፣ የወባ መከላከያ መድኃኒቶች ፍላጎት ትንበያና ስርጭት፣ የኩፍኝ በሽታ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ ደንቦች እና የኩፍኝ በሽታ ስርጭት ሞዴሊንግ ናቸው። ቡድኖቹ በመጨረሻው ቀን ለፕሮግራም መሪዎች፣ ለዳኞች እና ለአጋር ድርጅት ተወካዮች የሚቀርቡ ፕሮቶታይፖችን ወይም የመረጃ ሰሌዳዎችን (dashboards) በማዘጋጀት ላይ ይገኛሉ። ------------------------------------
EPHI’s Data Management Opens Public Health Policy Modelling Hackathon in Addis Ababa
The Ethiopian Public Health Institute’s (EPHI) National Data Management and Analytics Center for Health (NDMC) has opened the NDMC Public Health Policy Modelling Hackathon 2026 in Addis Ababa. The six-day event, running from July 1–6, 2026, is being held under the theme “Bridging Modelling and Policy to Solve Public Health Challenges.”
Director General of EPHI, Dr Mesay Hailu, in his opening speech described the hackathon as the first initiative of its kind at the institute and said it marks an important step toward strengthening evidence-informed decision-making in public health. He said modelling should move beyond technical analysis and be used to support programme planning, resource allocation, service delivery and policy decisions. With public-health decisions often made amid limited resources, incomplete information and competing priorities, Dr. Mesay said modelling and data analytics can help clarify choices, compare options and anticipate risks. The central question, he noted, should not be “What model can we build?” but “Which programme or policy decision do we want to support with evidence?” The hackathon, he added, offers a practical platform to connect data with evidence, evidence with decision-making, and decision-making with public-health action.
Dr. Tigist Shumet Director of NDMC on her behalf said that NDMC’s mandate includes data management, analytics and modelling to inform health programmes and policy decisions. She noted that the hackathon is part of EPHI’s broader effort to strengthen national capacity in public-health modelling and evidence use through a Gates Foundation-supported project. | 926 |
| 3 | Sin texto... | 814 |
| 4 | ለበሽታ ተጋላጭ ማህበረሰብን ያማካለ የተቀናጀ የIPC/WASH አገልግሎት ፍኖተ ካርታ ማጠናቀቂያ አውደ ጥናት ተካሂዷል
--------------------
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ምላሽና መልሶ ማገገም ዳይሬክቶሬት ከጤና ሚኒስቴርና ከሪዞልቭ ቱ ሴቭ ላይቭስ (Resolve To Save Lives) ጋር በመተባበር ለበሽታ ተጋላጭ ማህበረሰብን ያማካለ የተቀናጀ የIPC/WASH ፍኖተ ካርታ ማጠናቀቂያ አውደ ጥናት ተካሄደ።
በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ምላሽና መልሶ ማገገም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አ/ቶ መድሃንዮ ሀብተፂሆን እንደገለጹት፣ ሰነዱ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ልዩ ድጋፍ ለሚሹና ለወረርሽኝ ተጋላጭ በሆኑ ቦታዎች ላይ፣ ሰዎች በብዛት በሚሰበሰቡበት ቦታዎች ላይ እንዲሁም የመግቢያና መውጫ ኬላዎች ላይ እየታየ ያለውን የበሽታ መከላከያና ቁጥጥር (Infection Prevention and Control/IPC) አንዲሁም የግልና የአካባቢ ንፅህና ላይ ያለውን ክፍተት በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል ሥርዓት ለመገንባትና ለመዘርጋት ያለመ ነው በማለት ገልጸዋል።
በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት የሕብረተሰብ-ጤና አደጋ የበሽታ መከላል እና መቆጣጠር፣ የግልና የአካባቢ ንፅህና አንዲሁም የጅምላ አደጋ ምላሽና መልሶ ማገገም ዲቪዥን አስተባባሪ የሆኑት ወ/ት ሃና መኮንን እንደተናገሩት ሰነዱ በውስጡ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን ያካተተ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በቂ የሆነ የበሽታ መከላከያ እና መቆጣጠሪያ (IPC) አንዲሁም የግልና የአካባቢ ንፅህና አገልግሎት፣ ጠንካራ የቅድመ ማስጠንቀቂያና የቅኝት ስርዓትን መዘርጋትና የህብረተሱን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚረዱ የአሰራር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚረዱ ናቸው በማለት አብራርተው ለሰነዱ ትግበራም የሚያስፈልገው የሀብት ማሰባሰቢያ መንገዶችም አብረው እንደተቀመጡ ተናግረዋል። በአውደ ጥናቱ የኢንስቲትዩቱ፣ የጤና ሚኒስቴር፣ የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች፣ የሃይማኖት ጉባኤ ተወካይ፣ እንዲሁም የተለያዩ አጋር ድርጅቶች በአውደ ጥናቱ ተሳትፈዋል። | 1 036 |
| 5 | Sin texto... | 1 006 |
| 6 | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል በዛሬው ዕለት በብሔራዊ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ላይ ከክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች፣ ከአለም አቀፍ ተቋማት፣ ከአጋር አካላት፣ ከክልል ጤና ቢሮዎች እና ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ጥሪ ከተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር ስብሰባ አካሄደ፡፡
ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ስብሰባውን በንግግር በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት ሀገራችን ኢትዮጵያ እያጋጠሟት ያሉ የተለያዩ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን በተገቢው ሁኔታ ምላሽ ለመስጠት ይቻል ዘንድ የተጠናከረ የዝግጁነት ምላሽ ስርዓት እንዲኖራት ማድረግ ወቅታዊና ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በአጽንኦት አስረድተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል ብሔራዊ ስትራቴጂክ ዕቅድ መተግበር የሀገሪቱን የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የአደጋ ጊዜ ምላሽ አቅምን ለማሻሻል፤ የተቋማትን ቅንጅት ለማጠናከር እና የሕብረተሰቡን ጤና ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ስተዋጽኦ እንዳለው አስገንዝበዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ በበኩላቸው የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን በብቃት ለመቆጣጠር እና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት በሁሉም ደረጃዎች ያለ ትብብርና ቅንጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ስትራቴጂክ ዕቅዱ በብሔራዊ እና በክልል ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ በሚከሰትበት ጊዜ ምላሽ የሚሰጡ ተቋማትን በማጠናከሩ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚደርግ አብራርተዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታም በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ እና በእንግሊዝ መንግስት የጤና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር ተቋማቱ ከዚህ ቀደም ሲያደርጉት እንደነበረው ሁሉ አሁንም ለኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ሰርቪላንሰ ዳይሬክቶሬት የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ ወ/ት ኤቢሴ ኦቦሴ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማስተባበርያ አሰሳ ወጤት በማቅረብ፤ በቀጣይ የስትራቴጅክ እቅድ አፈጻጸምን የሚከታተል የተክኒካል ቡድን በፌደራልና በክልል ደረጃ አስፈላጊነቱን በማስገንዘብ በቀጣይም ሁሉም በዕቅዳቸዉ ውስጥ በማካተት የታለመዉን የልሕቀት ማዕከል ዕወን በማደረግ የበኩላቸዉን ድርሸ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ | 1 546 |
| 7 | Sin texto... | 1 452 |
| 8 | Sin texto... | 2 038 |
| 9 | EPHI hosts LINDA-FAMILIA Work Package 2 Workshop to digitalize Maternal and Child Health Services
---------------------------------
The Ethiopian Public Health Institute (EPHI) hosted LINDA-FAMILIA Work Package 2 (WP2) Implementation Planning Workshop in Addis Ababa, bringing together consortium partners from Ethiopia, Rwanda, Tanzania, Uganda, the Ministry of Health, and other partner institutions to strengthen coordination for the implementation of electronic health registries (eRegistries) across the four east African participating countries.
The workshop is part of the LINDA-FAMILIA Project, a four-year initiative funded by the European Union under the Horizon Europe Program and led by University College Cork. The project aims to improve maternal, new-born, and child health by promoting sustainable digital health solutions and strengthening health information systems.
Work Package 2, jointly led by EPHI and the Norwegian Institute of Public Health is the project's largest component. It focuses on co-designing, adapting, and strengthening digital health systems and implementing electronic health registries to improve maternal, new-born, postnatal, and child vaccination services while enhancing data quality and use for decision-making.
Dr. Aderajew Mekonnen, Director of the Health System Research Directorate at EPHI and Principal Investigator of the LINDA-FAMILIA project in Ethiopia, welcomed participants and reaffirmed EPHI's commitment to advancing evidence-based digital health innovations that strengthen health systems and improve maternal, newborn, and child health outcomes.
Dr. Abas Hassen, Health Innovation and Quality Lead Executive Officer at the Ministry of Health of Ethiopia delivered keynote address. He emphasized that the LINDA-FAMILIA initiative will make a significant contribution to advancing Ethiopia's Digital Health 2030 agenda. He noted that strengthening digital health systems through collaborative partnerships is essential to improving the quality, accessibility, and efficiency of healthcare services across the countries.
Professor Ali Kashan of University College Cork, global coordinator of the LINDA-FAMILIA Project, presented the overall implementation framework for Work Package 2. He noted that the workshop will enable consortium members to refine implementation approaches, adjust support mechanisms based on country needs, clarify partner responsibilities, and establish realistic timelines for the remaining project period.
Dr. Mahima Venkateswaran of the Norwegian Institute of Public Health, also highlighted implementation status and challenges across Ethiopia, Rwanda, Tanzania, and Uganda.
Mr. Asfaw Kelbessa representative of the Digital Health Lead excusive of the Ministry of Health Ethiopia provided a detail presentation on the current Ethiopia’s Digital health implementation framework and challenges.
During the first day of the workshop, Principal Investigators from Ethiopia, Rwanda, Tanzania, and Uganda presented updates on their Work Package 2 activities, followed by discussions and a question-and-answer session. The two-day workshop will conclude on July 3, 2026 with agreed implementation plan of each country. | 1 821 |
| 10 |
The workshop concluded with a shared commitment among participating countries and partners to advance data harmonization, strengthen interoperability, and promote regional collaboration. The agreed roadmap is expected to enhance research quality, improve health information systems, and support more effective national and regional health policies, ultimately contributing to better maternal, newborn, and child health outcomes across the region. | 2 079 |
| 11 | EPHI Leads Regional Workshop to Advance Data Harmonization and Interoperability for Maternal and Child Health Systems
-----------------
The Ethiopian Public Health Institute (EPHI), through its Health System Research Directorate, successfully concluded a four-day Data Harmonization and Interoperability Systems Workshop under the Horizon Europe-funded LINDA-FAMILIA Project, reaffirming its commitment to strengthening digital health systems and evidence-based healthcare across Africa.
Held from June 28 to July 1, 2026, at the Capital Hotel and Spa in Addis Ababa, the workshop brought together experts and partners from Ethiopia, Rwanda, Uganda, Tanzania, to harmonize maternal, newborn, child health, and infectious disease data systems. The LINDA-FAMILIA project is being implemented across Ethiopia, Rwanda, Uganda, and Tanzania to improve health systems through interoperable digital platforms that enhance maternal, newborn, and child health services, disease surveillance, clinical decision-making, and the use of real-time health data.
Opening the workshop, Dr. Aderajew Mekonnen, Director of EPHI's Health System Research Directorate and Principal Investigator of the LINDA-FAMILIA Project in Ethiopia, emphasized that harmonized data standards are fundamental to improving data quality, strengthening evidence-based decision-making, and achieving better health outcomes.
He noted that the workshop would establish a shared understanding of existing maternal and child health data dictionaries, develop a standardized framework, and define a core set of harmonized variables aligned with World Health Organization recommendations while addressing country-specific priorities. Dr. Aderajew also underscored the importance of achieving technical interoperability, particularly through the integration of Electronic Medical Record (EMR) systems with District Health Information Software 2 (DHIS2), to enhance data exchange and support more efficient health information systems.
Dr. Aderajew acknowledged the technical leadership of Professor Ali Kashan of University College Cork, Ireland, and Dr. Mahima Venkateswar of the Norwegian Institute of Public Health, as well as the contributions of the Ministry of Health and other project partners. He encouraged participants to actively share experiences, identify common data elements and existing gaps, and jointly develop harmonized definitions and coding standards to strengthen maternal and child health information systems and disease surveillance across participating countries.
Throughout the workshop, participants reviewed existing national data dictionaries, mapped variables against World Health Organization recommendations, and discussed the development of standardized datasets to support interoperable digital health systems. The discussions focused on producing harmonized data definitions, standardized coding rules, and a practical implementation framework to improve data quality, reporting, and health service delivery.
Prof. AliAli Kashan facilitated technical sessions aimed at improving the comparability of maternal health data across participating countries. Participants assessed existing data collection tools using a structured 50-variable framework, examined the availability and quality of priority data elements, explored opportunities for federated research, identified implementation gaps, and developed country-specific policy briefs. The workshop also produced a joint regional roadmap outlining shared priorities, implementation timelines, and collaborative actions.
In parallel, Dr. Mahima Venkateswar led practical sessions on strengthening interoperability between health information systems, with particular emphasis on integrating EMR platforms with DHIS2. Through technical presentations and hands-on discussions, participants enhanced their understanding of system integration, data exchange mechanisms, and real-time reporting processes tailored to country-specific contexts. | 2 016 |
| 12 | Sin texto... | 1 780 |
| 13 | ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቫይራል ሎድ (VL) እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ (EID) ፕሮግራሞች የ2018 ዓ.ም. አገር አቀፍ የአፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከCU-ICAP ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የ2018 ዓ.ም. አገር አቀፍ የኤች አይ ቪ ቫይራል ሎድ (HIV Viral Load/VL testing) እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ (Early Infant Diagnosis/EID) የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ ከሰኔ 22-24/ 2018 ዓ.ም አካሂዷል።
በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ የክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች/የክልል ሪፈራል ላቦራቶሪዎች፣ የናሙና ማጓጓዣ አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ አጋር ድርጅቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ በበጀት ዓመቱ በዚህ ዘርፍ የተገኙ አበረታች ውጤቶች እና በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ መፍታት ያለባቸውን ተግዳሮቶች የዳሰሱ ሲሆን፣ አያይዘውም የኤች አይ ቪ ቫይራል ሎድ እና የጨቅላ ህጻናት የኤች አይ ቪ ምርመራ አገልግሎቶች የኤች አይ ቪ ህክምናን ውጤታማ ለማድረግ እና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የህክምና ውሳኔ ለመስጠት ያላቸውን ወሳኝ ሚና አጽንኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም ይህንን እና ሌሎች የጤና የላቦራቶሪ አገልግሎቶችን ጥራት፣ ተደራሽነትና ቀጣይነት ለማሻሻል የሰው ኃይል አቅምን፣ መሣሪያዎችንና ግብዓቶችን ለማጠናከር ኢንስቲትዩቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በጤና ሚኒስቴር የኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ አውደ-ጥናት በዋናነት የተዘጋጀበትን ዓላማ እና ከዚህ ዓመታዊ የስራ አፈጻጸም ግምገማ የሚገኙ ግኝቶችን በተግባር በመተግበር ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት ሁሉም አካላት በትብብርና በባለቤትነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። በበጀት ዓመቱ ለተገኙ ቁልፍ ውጤቶችም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት አመስግነዋል።
በአውደ-ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከክልሎች እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት አፈጻጸም በጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በዋናነትም በክፍተት የተገመገሙ እና መሻሻል ያለባቸው ሥራዎች ተለይተው የማሻሻያ ዕቅድ በማውጣት አውደ-ጥናቱ ተጠናቋል። | 1 938 |
| 14 | Sin texto... | 2 037 |
| 15 | Sin texto... | 3 191 |
| 16 | Sin texto... | 2 450 |
| 17 | የካውንት ዳውን 2030 ጉባኤ በአዲስ አበባ ተጀምሯል ----------------------
የዘላቂ ልማት ግቦችን (Sustainable Development Goals 2030 /SDG/) መነሻ በማድረግ በመላው አፍሪካ የሚገኙ የጤና መረጃዎችን፣ የእናቶች እና የህፃናት ጤና አፈጻጸምን ለመገምገም የተዘጋጀው “ካውንትዳውን 2030” (Countdown 2030) የተሰኘው አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ።
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከ36 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የጤና ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች እና የአለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ ኢትዮጵያ በእናቶችና ህፃናት ጤና ላይ ያስመዘገበችውን ፈጣን ለውጥ አብራርተዋል። ሚኒስትሯ እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ ባደረገችው የተቀናጀ ጥረት የእናቶች ሞት ምጣኔን በ100 ሺህ በህይወት ከሚወልዱ ህፃናት ውስጥ ወደ 141 ዝቅ ማድረግ የቻለች ሲሆን፣ ይህም በአህጉር ደረጃ ካሉ ምርጥ ተሞክሮዎች አንዱ ነው። አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ማዕከል (Africa-CDC) መቀመጫ መሆኗ፣ አህጉራዊ ድንበር ዘለል የጤና ስጋቶችንና ወረርሽኞችን በጋራ ለመከላከል ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አክለዋል።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ጥራት ያለው መረጃ በማመንጨትና እንደ ማርበርግ ቫይረስ በሽታ እና ኤምፖክስ ያሉ አደገኛ በሽታዎችን በፍጥነት በመለየት ረገድ የዳበረ አቅም እንዳለው ገልጸው ይህም አፍሪካውያን በራሳቸው አቅም ሀገር-በቀል የጤና መረጃ ባለቤትነት በመሸጋገር ላይ እንደሚገኙ ማሳያ መሆኑንና ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።
በተጨማሪም ዶ/ር መሳይ በሳምንቱ ውስጥ የሚከናወኑት የቴክኒክ ስራዎች በመረጃ ትንተና ላይ የዘመኑ መገልገያዎችን እና ዘዴዎችን በመጠቀም የቴክኒክ ክህሎትን ማሳደግ፣ ጥራት ያላቸው የትንታኔ ሪፖርቶችን ማውጣት፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን በመፈተሽና ተሞክሮዎችን በመካፈል በሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር እና መረጃዎች ከፖሊሲ ግብአትነት ወደ ተግባር መተርጎማቸውን ማረጋገጥ ከጉባኤው አላማዎች ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ በዝርዝር አብራርተዋል።
የ“ካውንትዳውን 2030” ዳይሬክተር ዶ/ር ቼኪህ ፋይ፣ ይህ ስብስብ የቴክኒክ ትንታኔን ከአመራር ቁርጠኝነት ጋር ያቀናጀ መሆኑን ገልጸው፣ ዋናው ዓላማው የተሻለ መረጃን ወደተሻለ የፖሊሲ ውሳኔና ውጤት መቀየር እንደሆነ አስገንዝበዋል።
ጉባኤው እስከ ሳምንቱ መጨረሻ የሚቀጥል ሲሆን፣ ሀገራት እስከ 2030 በቀሩት ጥቂት ዓመታት ውስጥ በጤናው ዘርፍ ሊያከናውኗቸው በሚገቡ ስልታዊ ኢንቨስትመንቶች ላይ የጋራ መግባባት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። | 2 821 |
| 18 | በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥ ለሕብረተሰብ ጤና ወሳኝ መሆ ኑ ተገልጿል::
በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥ (Evidence-Informed Decision-Making – EIDM) ጉባኤ በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ እየተካሄደ ሲሆን የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ማጠናከር የወቅቱ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተገለጸ።
በጉባኤው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ፣ ጉባኤው የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ለማጠናከር ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።
ዶክተር መሳይ አክለው እንዳሉት፣ ኢንስቲትዩቱ ከ1924ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የሕብረተሰብ ጤና ስራዎችን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው ኢንስቲትዩቱ የላቦራቶሪ አገልግሎቶችን በሀገር አቀፍ ደረጃ በማስፋፋት፣ በሥነ-ምግብ ጥናት፣ በሕብረተሰብ ጤና ክትትል፣ በድንገተኛ የጤና አደጋ ዝግጅትና ምላሽ ዘርፎች ጉልህ ሚና በመጫወት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ስርዓት ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ መቆየቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም በሀገር ደረጃ አንጋፋ ተቋም በመሆን በአፍሪካ ደረጃም የልህቀት ማእከል መሆኑን ገልጸዋል።
የዘንድሮው ጉባኤ ከኢንስቲትዩቱ ተልዕኮና ስትራቴጂያዊ እቅድ ጋር በቅርበት የተሳሰረ መሆኑን የገለጹት ዶክተር መሳይ፣ ኢንስቲትዩቱ ከተለያዩ ምንጮች የጤናና ከጤና ጋር ተያያዥ መረጃዎችን በመሰብሰብ ብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ቅመራ ትንተና ማዕከል የማቋቋምና የማስተዳደር ኃላፊነት እንደተሰጠው አስታውሰዋል።
በተጨማሪም ብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ቅመራ ትንተና ማዕከሉ የጤና መረጃዎችን በመሰብሰብ ብቻ ሳይሆን በማደራጀት፣ በደህንነት በመጠበቅ በማስተዳደርና ወደ ተግባራዊ ማስረጃ በመቀየር ለውሳኔ አሰጣጥ እንደሚያገለግል ገልጸዋል። በተለይም የሰው፣ የእንስሳትና የአካባቢ ጤናን በሚያስተሳስረው የ"አንድ ጤና" አቀራረብ ውስጥ የዲጂታል ማከማቻዎች የተለያዩ ማስረጃዎች የሚገናኙባቸው ወሳኝ ስፍራዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደርና ትንተና ማዕከል ዳይሬክተር ዶክተር ትዕግስት ሹመት በበኩላቸው፣ አውደ ጥናቱ መረጃን ለጤና ፖሊሲ ግብዓት፣ማስረጃ ተኮር ውሳኔ አሰጣጥ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ዶክተር ትዕግስት ማብራሪያ፣ ኢንስቲትዩቱ በአሁኑ ወቅት ከ600 በላይ የሚሆኑ የጤና እና ጤና ነክ መረጃዎችን በመሰብሰብ፣ በማደራጀትና በማከማቸት ለሀገራዊ የጤና ውሳኔዎች ግብዓት እያደረገ ይገኛል። እነዚህ መረጃዎች በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር፣ የጤና ፖሊሲዎችን ለመቅረጽ እና በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን ለማሳለጥ ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው።
ዶክተር ትግስት አክለውም፣ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጀምሮ የተደራጁ የጤና መረጃዎች የተለያዩ የጤና ስጋቶችን እና ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር በተደረጉ ትንተናዎች እና ምላሾች ውስጥ በቀጥታ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ ገልጸዋል።
የመረጃ ልውውጥና ትብብርን ለማጠናከር ከ195 በላይ የመንግሥት፣ የግል፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች በመረጃ አሰባሰብ ላይ እንዳሉና መረጃ ልውውጥ ዙሪያ የተቀናጀ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
ተናጋሪዎቹ በጋራ ያስተላለፉት መልዕክት፣ የተጣራና የተደራጀ መረጃን ወደ ተግባራዊ ማስረጃ በመቀየር በጤና ዘርፍ የሚሰጡ ውሳኔዎች በታማኝ መረጃ ላይ እንዲመሰረቱ ማድረግ የጤና ሥርዓቱን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ነው።
በጉባኤው ከጤና ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI)፣ ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ተቋም (AHRI)፣ ከጤና ሚኒስቴር ስር ካሉ ኤጀንሲዎች፣ ከፌዴራል ሆስፒታሎች፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከአጋር ተቋማት የተውጣጡ ተመራማሪዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎች፣ የፕሮግራም መሪዎችና ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
The 2026 Evidence-Informed Decision-Making (EIDM) Conference officially opened in Addis Ababa at the Adwa Victory Memorial Museum Hall, bringing together health leaders, policymakers, researchers, and stakeholders to strengthen the use of evidence in Ethiopia’s health system. The conference aims to promote data-driven decision-making and foster collaboration among institutions working to improve public health outcomes across the country.
Opening the event, Ethiopian Public Health Institute (EPHI) Director General Dr. Mesay Hailu said the conference reflects a shared commitment to advancing health systems through knowledge, innovation, evidence, and partnership. He noted that EPHI has grown into a nationally respected institution and a continental center of excellence, making significant contributions in vaccine production, laboratory services, nutrition research, public health surveillance, and emergency preparedness. Dr. Mesay added that the conference aligns with EPHI’s mandate to manage the National Health Data Management and Analytics Center, which transforms health data into actionable evidence for policymaking and planning.
National Health Data Management and Analytics Center Director Dr. Tigist Shumete said the conference focuses on leveraging data to support health policy development, knowledge management, and evidence-informed decisions. She highlighted that the Institute currently manages health-related data from more than 600 institutions and sources, helping to guide disease prevention, policy formulation, and national health planning. Dr. Tigist called for stronger collaboration among over 195 public institutions, private organizations, NGOs, and universities, while participants emphasized that converting high-quality data into actionable evidence is essential for building a more responsive and resilient health system in Ethiopia. | 3 565 |
| 19 | Sin texto... | 2 762 |
| 20 | ለድንገተኛ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ዓመታዊ የመድኃኒት ፈላጐትና አቅርቦትን የተመለከተ ዓውደ ጥናት በመካሄድ ላይ ይገኛል
----------------
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ብሔራዊ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቢከሰቱ ሊኖር የሚችለውን የመድኃኒት ፍላጐትና አቅርቦት በመተንበይ (National Public Health Emergency Supply Forecasting Annual Exercise) ከኢንስቲትዩቱ፣ ከተለያዩ ተቋማት እና ከአጋር ድርጅት ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን ዓመታዊ የልምምድ አውደ ጥናት በቢሾፍቱ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
አዉደ ጥናቱ ጠንካራ የሆነ የግብአት አቀርቦት ከብሔራዊ እስከ ወረዳ ድረስ ማንኛውም ሊከሰቱ ለሚችሉ የተፈጥሮና ሰዉ ሰራሽ አደጋዎች (natural disaster, humanitarian crisis, infectious disease outbreak) ያልተቆራረጠ የመድኃኒት አቅርቦትና ፈጣን የሆነ ምላሽ መስጠት ለማስቻል ያለመ መሆኑን ከመድረኩ ተመላክቷል።
የኢንስቲትዩቱ የቅድመ ዝግጁነትና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ነዒማ ዘይኑ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ለመስራት ከታቀዱ ተግባራት መካከል አንዱ ይህ ዓመታዊ የግብአት ፍላጎት ትንቢያ ሲሆን ወቅቱም የሚቀጥለዉን በጀት ዓመት ዕቅድ የሚታቀድበት እንደመሆኑ በመገባደድ ላይ ያለውን እንዲሁም ወቅታዊ የበሽታዎች ወረርሽኝ ስርጭት መረጃዎችን በመጠቀም ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለዉ ለሚገመቱ ወረርሽኞች የሚዉሉ ግብአቶችን ለማቀድ የተዘጋጀ መድረክ ነው፡፡
ወ/ሮ ነዒማ አያይዘውም የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከርና ቀጣይነት ያለዉ ምላሽ ለመስጠት የሚጠቅም በመሆኑ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን እየተሰራ ያለ ስራ ሲሆን ይህ ስራ በየአመቱ አቅም የመጨመርና የቅድመ ዝግጁነት አቅምን ለማጎልበትም እንደሚረዳ አስረድተዋል፡፡ | 3 273 |
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
