es
Feedback
Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ir al canal en Telegram

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

El canal Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 526 suscriptores, ocupando la posición 1 729 en la categoría Medicina y el puesto 2 329 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 526 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 168, y en las últimas 24 horas de 6, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 14.92%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 8.36% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 166 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 214 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Medicina.

14 526
Suscriptores
+624 horas
+267 días
+16830 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+70
en 0 canales
mayo '26
+248
en 1 canales
Get PRO
abril '26
+187
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+104
en 1 canales
Get PRO
febrero '26
+51
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+125
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+286
en 3 canales
Get PRO
noviembre '25
+706
en 3 canales
Get PRO
octubre '25
+113
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+89
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+136
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+140
en 1 canales
Get PRO
junio '25
+465
en 1 canales
Get PRO
mayo '25
+327
en 5 canales
Get PRO
abril '25
+147
en 1 canales
Get PRO
marzo '25
+159
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+125
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+262
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+513
en 1 canales
Get PRO
noviembre '24
+619
en 2 canales
Get PRO
octubre '24
+592
en 1 canales
Get PRO
septiembre '24
+309
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+578
en 1 canales
Get PRO
julio '24
+375
en 1 canales
Get PRO
junio '24
+312
en 1 canales
Get PRO
mayo '24
+308
en 1 canales
Get PRO
abril '24
+361
en 1 canales
Get PRO
marzo '24
+327
en 1 canales
Get PRO
febrero '24
+372
en 2 canales
Get PRO
enero '24
+531
en 1 canales
Get PRO
diciembre '23
+462
en 2 canales
Get PRO
noviembre '23
+129
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+190
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+106
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+85
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+73
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+73
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+52
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+50
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+84
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+53
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+64
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+95
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+86
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+57
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+67
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+72
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+60
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+107
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+105
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+101
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+72
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+38
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+67
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+99
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+30
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+112
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+133
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+106
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+107
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+113
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+76
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+243
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+319
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+149
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+3 714
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+4 494
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
11 junio+11
10 junio+12
09 junio+3
08 junio0
07 junio+6
06 junio+14
05 junio+2
04 junio+5
03 junio+4
02 junio0
01 junio+13
Publicaciones del Canal
ለሀገራዊ የምግብ ደህንነት ጥናት አገልግሎት የሚውሉ ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮችና ፕሪንተሮች ለክልሎች ድጋፍ ተደረገ። በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን እና በኢትዮጵያ የግብርና ባለሥልጣን በትብብር እየተካሄደ ላለው ሀገራዊ የምግብ ደህንነት፣ ምግብን ከባእድ ነገር ጋር መቀላቀል እና የምግብ ንጽህና አጠባበቅ ልምምድ ጥናት አገልግሎት የሚውሉ ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮችና ፕሪንተሮችን የጣሊያን መንግሥት ለክልሎች አገልግሎት እንዲውል ለኢትዯጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስረክቧል ። ጥናቱ በጣሊያን መንግሥት የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ እየተተገበረ ያለ ሲሆን፣ በመላ ሀገሪቱ በ25 ከተሞች እየተካሄደ ነው። ለጥናቱ አፈጻጸም አስፈላጊ የሆኑት የመረጃ ቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ክቡር ሴም ፋብሪዚ አማካይነት ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በርክክቡ ላይ እንደገለጹት፣ ኢንስቲትዩቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ የምግብ ደህንነትን ለማጠናከርና የምግብ ንጽህናን ለማሻሻል የሚያግዙ በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ጥናቶችን በማካሄድ ለፖሊሲ አውጪዎችና ለውሳኔ ሰጪዎች ጠቃሚ ግብዓት እያቀረበ ይገኛል።ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም የጣሊያን መንግሥት በየጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ (AICS) በኩል ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። ይህ አጋርነት በምግብ ደህንነት ዘርፍ እየተካሄዱ ያሉ ጥረቶችን ከማጠናከር ባሻገር በሌሎች የሕብረተሰብ ጤና መስኮችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸውን ገልጸዋል። የጣሊያን አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በበኩላቸው የጣሊያን መንግሥት እንደዚህ ያሉ የሕብረተሰብ ጤናና የምግብ ደህንነት ፕሮጀክቶችን መደገፉን ገልጸው፣ እስካሁን በፕሮጀክቱ የተመዘገቡ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። አምባሳደሩ የጣሊያን መንግሥት የEPHI እና የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ስራዎችን በቀጣይነት እንደሚደግፍም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ነጋሽ ስሜ በበኩላቸው፣ የተደረገው ድጋፍ የጥናቱን ስኬታማ አፈጻጸም ከማገዝ ባሻገር የፌዴራልና የክልል የምግብ ቁጥጥር ተቋማትን አቅም ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የስርዓተ ምግብ፣ የአካባቢ ጤናና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ማሰረሻ ተሰማ በበኩላቸው ጥረናቱ በዘጠኝ ዋና ዋና የምግብ ምርቶች ላይ የምግብ መበረዝ አስመልክቶ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ገልጸው፣ በፍራፍሬና አትክልት፣ በወተት ፣ በዶሮ ስጋ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች እና በቄራዎች እንዲሁም ባለ አራት እና ከዚያ በላይ ኮከብ ባላቸው ሆቴሎች ለሚካሄደው ጥናት የተደረገው ድጋፍ እገዛ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አብራርተዋል። መርሃ ግብሩ ላይ የጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ (AICS) ኃላፊ ክቡር ሚካኤል ሞራን እና የኤምባሲው ልዑካን እንዲሁም የክልል ተወካዮችና የኢትዮጵያ የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ኃላፊዎች በኢንስቲትዩት ብሔራዊ ስልጠና ማዕከል ተገኝተዋል።

2
+4
Sin texto...
750
3
የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዣን ካሴያ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ጎበኙ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዣን ካሴያ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፣ መንግሥት የሕብረተሰቡን ጤና ለማሻሻል የጤና ባለሙያዎችን አቅም በመገንባት፣ የጤና መረጃዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ እና የድንገተኛ ጤና አደጋዎችን ለመቆጣጠር የተለያዩ የዝግጁነት ሥራዎችን እያከናወነ ነው። በተለይም የኢቦላ ወረርሽኝን ለመከላከል የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልን በማጠናከር በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሃይሉ በበኩላቸው፣ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ ከ100 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ተቋም ሲሆን በምርምር፣ በብሔራዊ የላቦራቶሪ አገልግሎት እና በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ በበኩላቸው የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል። ዶ/ር ዣን ካሴያ በበኩላቸው በጉብኝቱ ወቅት የተመለከቷቸው የኢንስቲትዩቱ አገልግሎቶችና አቅሞች ውጤታማ መሆናቸውን መመልከታቸውን እና መደነቃቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም በአፍሪካ ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ እንደሚያጠናክሩ አስታውቀዋል።
1 633
4
+6
Sin texto...
1 521
5
በኢትዮጵያ የአዳዲስ ክትባቶች ትግበራ ግምገማ ዙሪያ የመረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና ተካሄደ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክትባት የሚከላከሉ በሽታዎች ዲቪዥን አስተባባሪነት፣ Integrated Post-Introduction Evaluation (PIE) in Ethiopia የመረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና ከሰኔ 1-5 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል። ስልጠናው በቅርቡ ወደ አገሪቱ የገቡ አዳዲስ ክትባቶችን አፈጻጸም በመገምገም የተገኙ ተሞክሮዎችንና ተግዳሮቶችን ለመለየት እና ለወደፊት የክትባት ፕሮግራሞች ማሻሻያ ግብዓት ለማግኘት ያለመ ነው። በመክፈቻው ላይ የተላላፊ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ገመቹ ታደሰ የክትባት በሽታዎች ምርምር የአምስት ዓመት ስትራቴጂ መዘጋጀቱን በመግለጽ፣ ይህ ጥናት ከስትራቴጂው ቅድሚያ ከተሰጣቸው ተግባራት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለማንኛውም ጥናት የመረጃ ጥራት ወሳኝ በመሆኑ መረጃ ሰብሳቢዎች በኃላፊነትና በጥንቃቄ እንዲሰሩ አሳስበዋል። የጤና ሚኒስቴር የክትባት አገልግሎት ሃላፊ አቶ መልካሙ አያሌው በበኩላቸው፣ ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ በቅርብ ጊዜ የገቡትን የሄፓታይተስ ቢ፣ የወባ እና የኩፍኝ ክትባቶች አፈጻጸም ለመገምገም የሚሰበሰበው መረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አስገንዝበዋል። የክትባት የሚከላከሉ በሽታዎች ምርምር ዲቪዥን ሃላፊ ዶ/ር ራጂሃ አቡበከር ደግሞ ተሳታፊዎች በስልጠናው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የመረጃ አሰባሰብ ሂደቱን በተገቢው ሁኔታ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኞቹ ለ15 ቀናት በተመረጡ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በመሰማራት የመስክ መረጃ ስብስብ ሥራ ያከናውናሉ።
1 830
6
+7
Sin texto...
1 599
7
የአንትራክስ የላቦራቶሪ ምርመራን ወደ ክልሎች ለማስፋፋት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከዚህ በፊት በማዕከል ደረጃ ብቻ ሲሰጥ የነበረውን የአንትራክስ ሞለኪውላር ላቦራቶሪ ምርመራ (Anthrax Molecular Laboratory) አገልግሎትን በሶስት የክልል ላቦራቶሪዎች ማለትም በአማራ የሕህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (ባህርዳር)፣ በትግራይ ጤና ምርምር ኢንስቲትዩት (መቀሌ)፣ በአርባምንጭ የሕብረተሰብ ጤና ላቦራቶሪ (አርባምንጭ) አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚረዳ የናሙና አሰባሰብ፤ የሞለኪውላር (PCR) ምርመራ ዘዴዎችን፣ እንዲሁም የምርመራ ጥራት ማረጋገጫ ሂደቶችን ያካተተ ሥልጠና ከሲዲሲ-ኢትዮጵያ እና ከOSU-GOHI ጋር በመተባበር ከግንቦት 26 እስከ 29/2018 ዓ.ም ሰጠ። የኢንስቲትዩቱ የላቦራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል መለሰ እንደገለጹት የዚህ ምርመራ መስፋፋት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን፤ በዋናነትም የሞለኪውላር ላቦራቶሪዎችን በሀገር ደረጃ ለማስፋፋት ከተያዙ አቅዶች ውስጥ አንዱ እንደሆነና በሀገር ደረጃ እየተሰፋፋ ያለውን የአንትራክስ (አባ ሰንጋ) በሽታ ፈጥኖ ለመለየት እና ለመከላከል የነዚህ ላቦራቶሪዎች በክልል ደረጃ መጀመር ትልቅ ፋይዳ ይኖራቸዋል፡፡ አቶ ዳንኤል አያይዘውም ሥልጠናው ልምድ ባካበቱ የኢንስቲትዩቱ ባለሙያዎች እና በበይነ መረብ ከCDC- Atlanta የተሰጠ ሲሆን ስልጣኞችም የንድፈ ሃሳባዊ ዕውቀት እንዲሁም የሞለኪውላር ላቦራቶሪ የተግባር ልምምድ አድርገዋል፡፡ የሲዲሲ-ኢትዮጵያና የOSU-GOHI ተወካዮች በበኩላቸው ባሰተላለፋት መልዕክትም በዚህ ዘርፍ ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚሰጡ መግለጻቸውን አቶ ዳንኤል ተናግረዋል።
1 858
8
+1
Sin texto...
1 599
9
የዓለም የምግብ ደህንነት ቀን በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተከብሮ ውሏል። ​በኢንስቲትዩቱ የስነ-ምግብ፣ አካባቢ ጤና እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዳይሬክቶሬት ስር የሚገኘው የምግብ ደህንነት ምርምር ዲቪዥን፣ የዓለም የምግብ ደህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከ70 በላይ ለሚሆኑ የኢንስቲትዩቱ ካፌቴሪያና ኬተሪንግ አገልግሎት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። ስልጠናው በምግብ ደህንነት መርሆዎች፣ በግል ንፅህና፣ በደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ አያያዝ እና በምግብ ወለድ በሽታዎች መከላከል ዙሪያ ያተኮረ ነበር። ​በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት የምግብ ደህንነት ምርምር ዲቪዥን ኃላፊ አቶ ዋቅቶላ ጎበና ፣ የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ የሁሉም የጋራ ኃላፊነት መሆኑንና ሳይንስን መሰረት ያደረገ አሰራርን በመከተል በምግብ አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችን መከላከል እንደሚቻል ገልጸዋል። ​ከፍተኛ ተመራማሪው ዶ/ር ተስፋዬ ለገሰ በበኩላቸው፣ ትክክለኛ የእጅ ንፅህና፣ ዘመናዊ የምግብ ማከማቻ እና ጥንቃቄ የተሞላበት አያያዝ ልምዶች አብዛኞቹን በምግብ የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመግታት ወሳኝ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። ​የኢንስቲትዩቱ የካፍቴሪያ እና ኬተሪንግ አገጋግሎት ሀላፊ አቶ ያረድ ፋንታው በበኩላቸው ሰራተኞች በስልጠናው ያገኟቸውን ሳይንሳዊ እውቀቶች በዕለት ተዕለት ስራቸው ላይ በተግባር ማዋል እንዳለባቸው ተናግረው በስልጠና የተገኘውን እውቀት በተግባር እንደሚያውሉት ተናግረዋል።
1 844
10
+3
Sin texto...
1 681
11
+9
Sin texto...
1 899
12
የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች የኢቦላ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችል በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተግባር ልምምድ (Simulation exercise) አካሄዱ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከል በተጓዦችና ድንበር ጤና ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት የተከሰተውን የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ዝግጁነት ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር የመግቢያና መውጫ የጤና ቁጥጥር ባለሙያዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የጤና ልየታ፣ የቁጥጥር፣የቅኝት ስራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ተግባራዊ ልምምድ አካሄዱ፡፡ የተግባር ልምምዱ (Simulation exercise) ዋና ዓላማ የግብዓትና የሰው ኃይል ዝግጁነት ክፍተት በመለየት በሽታው ወደ አገር እንዳይገባ የመከላከል እንዲሁም በሽታው ቢከሰት እንኳን የመከላከል እና የምላሽ ስራዎች በምን ያህል ደረጃ ውጤታማ ይሆናሉ፣ ምን ጠንካራ ጎኖች አሉ፣ ክፍተቶችስ ምን ይመስላሉ የሚሉትን በመለየት በቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን በማስተካከል ጠንካራ ዝግጁነትን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር በተግባር ልምምዱ የማጠቃለያ ግምገማ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ከተገለጸበት ጊዜ አንስቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ሲሰራ መቆየቱን እና የተግባር ልምምድ መካሄዱ ትልቅ ተግባር መሆኑን አድንቀው፣ ከዚህ በፊት የነበሩትን ልምዶችና አሁን የተገኘውን እውቀት መሰረት በማድረግ በቀጣይ እስከ ታችኛው የጤና ተቋምና የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች በማውረድ ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ አገራችንን፣ ቤተሰባችንን፣ ሕብረተሰባችንን ከማንኛውም የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ችግሮች በመጠበቅና በመታደግ ለትውልድ የሚሻገር ስራ በመስራት ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተግኝተው በተግባር ልምምዱ ወቅት እንደገለጹት ኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልን ጥብቅ የሆነ የቅኝትና የልየታ ስራ እንዲሰራ የተደረገ መሆኑን፣ በኢትዮጵያ ባሉ በአየርም ሆነ በየብስ በሚገኙ የመግቢያና መውጫ በሮች በኩል በሽታው ከተከሰተባቸው አገራት የሚመጡ ተጓዦችን የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥርና ቅኝት ስራዎችን ተጠናክረው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ማንኛውንም የተላላፊ ወረርሽኝ በሽታ ናሙናዎች ለመመርመር የሚያስችል የሪፈረንስ እና የሪፈራል የላቦራቶሪ ዝግጁነት መጠናቀቁን አብራርተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም በኢትዮጵያ የኢቦላ ቫይረስ ተጠርጣሪ የሌለና በሽታውም ወደ ሀገር ያልገባ መሆኑን አረጋግጠው፣ በሽታው ሊከሰት ቢችል እንኳን ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙዎች የተግባር ልምምድ በማድረግ የክህሎት እና የብቃት ደረጃቸውን ያሳደጉ በመሆኑ በበሽታው የተጠረጠረ ሰው ቢገኝ ወደ ሌሎች ሰዎች በሽታውን ሳያስተላልፍ በተዘጋጁ የለይቶ ማቆያ ቦታዎች በመውሰድ አስፈላጊውን ህክምና የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ሕብረተሰቡ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚሰጡ መልዕክቶችን በሚገባ በመከታተል ተግባራዊ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር መልካሙ አብቴ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ለመከላከልና ዝግጅትን ከማጠናከር አንጻር ወረርሽኙ ከተከሰተባቸው አገራት አውሮፕላን ወደ አገራችን በረራ ከማድረጉ አስቀድሞ እያንዳንዱ ተሳፈሪ የጤና መረጃ ከመሙላት (e-THDF) አንስቶ እስከ መጨረሻው መደረግ የሚገባቸውን የቅኝት፣ የልየታ እና ክትትል ስራዎች በሚገባ እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የተካሄደው የጤና ባለሙያዎች የተግባር ልምምድ ወረርሽኙን በመከላከል ደረጃ ያሉትን ጠንካራ ጎኖች ለማስቀጠል፣ ክፍቶችን ደግሞ በማረምና በማስተካከል በዝግጁነት በኩል ያሉ ተግባራት አስተማማኝ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የተከናወነ መሆኑን ሰፊ ገለጻ አድርገዋል፡፡ አቶ ተመስገን ለሚ የኢንስቲትዩቱ የተጓዦችና ድንበር ጤና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኢቦላ ቫይረስ ምንነት ሲያስረዱ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት በ DRC እና Uganda አገራት የተከሰተው የኢቦላ በሽታ Bundibugyo Ebola Virus አማካኝነት የሚመጣ እጅግ ከባድና ለህልፈተ ህይወት የሚዳርግ ተላላፊ በሽታ ሲሆን በሽታው ፈጣን ህክምና ካላገኘ የሞት ምጣኔው እስከ 90% ሊደርስ የሚችል በጣም አደገኛ ወረርሽኝ መሆኑን፣ ምልክቶቹም ድንገተኛ ትኩሳት፣ ከፍተኛ የጡንቻና የራስ ምታት፣ የጉሮሮ መቁሰል፣ ማስመለስ፣ ተቅማጥ እና ከውስጥና ከውጭ አካላት የሚወጣ የደም መፍሰስ (Hemorrhage) የመሳሰሉት ምልክቶች መሆናቸውን ጠቁመው በሽታው ወደ አገር እንዳይገባ በሁሉም የዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች እና የየብስ መግቢና መውጫ በሮች ላይ በተለይም በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከፍተኛ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ሁሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ከበበው በቀለ በአትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት የቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ዳይሬክተር የሕረተሰቡን ጤንነት ከማስጠበቅ አንጻር አየር መንገዱ እየሰራ ያለውን በተመለከተ ሲገልጹ የአደጋ ጊዜ የምላሽ ዝግጁነት ተግባራትን አንዱ የስራችን ክፍል በማድረግ እቅድ ወጥቶ፣ አፈጻጸሙንም በየጊዜው እየተገመገመ መሆኑንና የህብረተሰቡን ጤና ችግር የሚፈጥሩ ተላላፊ በሽታዎችንም ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንጻር ከኢትዮጰያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በቅንጅት አስፈላጊውን ስራ ሁሉ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ምናባዊ የሆነ የኢቦላ ተጠርጣሪ ሰው በማዘጋጀት በሽታው ከተከሰተባቸው አገራት ጀምሮ መረጃዎችን በማዘጋጀት እስከ ለይቶ ማቆያ ድረስ መደረግ ያለባቸውን አስፈላጊ ተግባራት ሁሉ ያካተተ የተግባር ልምምድ ያካሄዱ ሲሆን በልምምዱ ወቅት የነበሩ ጠንካራ ጎኖች እና ክፍተቶችን ተለይተው የማስተካከያ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል፡፡ የቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ባለድርሻ አካላት የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፥ NISS, Immigration, Customs, Federal Police, እንዲሁም አጋር ድርጅቶች፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)፣ የአሜሪካ በሽታዎች መከላከል ማዕከል (US CDC) ፣ የዓለም የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ፥ UK HSA እና ሌሎችም የተግባር ልምመዱ ላይ በአካል በመገኘት የገንዘብ ፥የእውቀት እና የክህሎት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
2 064
13
+3
Sin texto...
2 013
14
+9
Sin texto...
2 191
15
ለሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ለማስጣት አስፈላጊ የሆኑ የግብዓቶች ዝርዝር መመሪያ ማጠናቀቂያ አውደ ጥናት ታካሄደ ኢትዮጵያ ውስጥ ማንኛውም ዓይነት የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ በሚከሰትበት ጊዜ ፈጣን፣ የተቃነጀ እንዲሁም ሕይወት አድን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች የግብአቶች ዝርዝር መመሪያ ለማጠናቀቂያ አውደ ጥናት (ወርክሾፕ) ከግንቦት 18 - 22, 2018 ዓ.ም ተካሂዷል። በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት አስተዳደር ዲቪዥን አስተባባሪ አቶ ቢቂላ ዲሪባ እንደገለጹት፤ አሁን ላይ እየተዘጋጀ ያለው የግብአት ዝርዝር መመሪያ ድንገተኛ አደጋዎች ከመከሰቱ በፊት የሚደረግ የቅድመ ዝግጁነት ስራ አካል ነው። ዋናው ዓላማው አደጋ ከመከሰቱ በፊት ለእያንዳንዱ የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ምን ዓይነት ግብአቶች እንደሚያስፈልጉ አስቀድሞ መለየት፣ ሀገር አቀፍ ደረጃ ያለው ወጥ መመሪያ ማውጣት እንዲሁም የአቅርቦት ሰንሰለት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። አስተባባሪው አክለውም፥ ይህ ወጥ የሆነ አሰራር መዘርጋቱ ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ምላሽ መስጠ የሚያስችል ጠንካራ፣ ተቋማዊ እና ዘላቂ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት ሥርዓት መገንባት ነው። አውደ ጥናቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት ሥርዓትን ለማዘመን፣ የግብአት ድግግሞሽ እና ብክነትን ለመቀነስ፣ ወጥ የሆነ የምላሽ ሂደት እንዲኖር ለማድረግ እንደሚረዳ ተሳታፊዎች አጽንኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም መመሪያው ተቋማት አንድ አይነት የምላሽ አሰጣጥ እንዲከተሉ በማድረግ ቅንጅታዊ አሠራር ለመፍጠር እንደሚረዳ ተመላክቷል። በአውደ ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት፣ ከኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን፣ WHO፣ Project Hope፣ JSI፣ UKHSA፣ CHAI፣ ከክልሎች እና ከሆስፒታሎች የተውጣጡ፣ በቀጥታ የስራው ባለድርሻ የሆኑ አካላት ተሳትፈዋል። ይህ መመሪያ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች ዝግጁነትን የሥራ ባህል ለማድረግ መሠረታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
3 792
16
+7
Sin texto...
2 686
17
በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ደህንነትን ለማጠናከር የሚያስችል የአንድ ጤና የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ማነቃቂያ አውደጥናት ተካሄደ:: የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በብሔራዊ የአንድ ጤና (One Health) ሴክሬታሪያት አማካኝነት በኢትዮጵያን ያሉ የጤና ስጋቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የዝግጁነትና ምላሽ አቅም ለማጠናከር ያለመ የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች (TWGs) ማነቃቂያ ወርክሾፕ ከግንቦት 20–21 ቀን 2018 ዓ. ም አካሂዳል ። በአውደጥናቱ የመንግሥት ተቋማትን፣ የልማት አጋሮችን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በአንድ ጤና አቀራረብ በማሰባሰብ ከአስተዳደር፣ ከቅንጅት፣ ከተጠያቂነት እና ዘላቂነት ጋር የተያያዙ ችግሮች ላይ ተወያይቷል። በዝግጅቱ ላይ የብሔራዊ የአንድ ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር ፈይሳ ረጋሳ የሰው፣ የእንስሳት እና የአካባቢ ጤና ሥርዓቶችን በተቀናጀ መንገድ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። “ዋና ግባችን ለጊዜው ለሚከሰቱ የጤና ችግሮች መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ፣ ከወረርሽኞች ውጪም በየዕለቱ የሚሰራ እና ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ ጠንካራ የሥራ ሥርዓት መገንባት ነው” ብለዋል። የአውደ ጥናቱ ቁልፍ ውጤቶች የመመሪያ ሰነዶችን (Terms of Reference - TORs) በማሻሻል የሥራ ኃላፊነቶችንና የሪፖርት ማቅረቢያ መዋቅሮችን ግልጽ ማድረግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም ለቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ቋሚ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎችን በመሾም እና መደበኛ የመግባቢያ መድረኮችን በመፍጠር እንደገና ማነቃቃትን ያካትታሉ። በአውደ ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን እንዲሁም እንደ FAO፣ Resolve to Save Lives፣ UKHSA፣ JSI፣ Core Group Partners Project፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር እና Project HOPE ያሉ አለማቀፍ አጋሮች ተሳትፈውበታል:: ተሳታፊዎች በሰው፣ በእንስሳት እና በአካባቢ ጤና መስኮች መካከል የሚከሰቱ አዳዲስ የጤና ስጋቶችን ለመቋቋም በቅጽበት የመረጃ ልውውጥን ማሻሻል፣ ሀብት ማሰባሰብ እና የተቀናጀ ምላሽ መስጠትን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። ይህ የተሳካ አውደጥናት የአንድ ጤና አቀራረብን በኢትዮጵያ ውስጥ ተቋማዊ ለማድረግ እና የዘርፎች መካከል ትብብርን ለሰዎች፣ ለእንስሳት እና ለአካባቢው ጤና መደበኛ የሥራ ባህል ለማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታይቶበታል:: EPHI Concludes One Health TWGs Revitalization Workshop to Strengthen Ethiopia’s Health Security The Ethiopian Public Health Institute (EPHI), through the National One Health Secretariat, has successfully concluded a two-day Technical Working Groups (TWGs) Revitalization Workshop held from May 28–29, 2026, aimed at strengthening Ethiopia’s preparedness and response to interconnected health threats. The workshop brought together government institutions, development partners, and stakeholders to address challenges related to governance, coordination, accountability, and the sustainability of the One Health approach. Speaking at the event, Dr. Feyisa Regassa, Chairperson of the National One Health Secretariat, emphasized the need to integrate human, animal, and environmental health systems. “Our ultimate objective is to pivot away from temporary fixes and build a resilient, everyday operational mechanism that endures well beyond active outbreaks,” he said. Key achievements of the workshop included refining draft Terms of Reference (TORs) to clarify mandates and reporting structures, strengthening accountability mechanisms, and revitalizing Technical Working Groups through the appointment of dedicated chairs and co-chairs and the establishment of regular communication platforms. The workshop also reinforced collaboration among key stakeholders, including the Ministry of Health, Ministry of Agriculture, Environmental Protection Authority, Ethiopian Wildlife Conservation Authority, and international partners such as FAO, Resolve to Save Lives, UKHSA, JSI, core group partners project , Ethiopia Red Cross Society and Project HOPE. Participants committed to enhancing real-time information sharing, resource mobilization, and coordinated responses to emerging health threats at the human-animal-environment interface. The successful workshop marks an important step toward institutionalizing the One Health approach in Ethiopia, making cross-sector collaboration a routine practice for protecting the health of people, animals, and the environment.
2 840
18
+6
Sin texto...
2 973
19
የምርምር ስነምግባር፣ የጥናታዊ ፅሁፎች ቅድመ ምርምር ግምገማና እዉቅና አሰጣጥ ቦርድ አሰራር እና የ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጥናታዊ ፅሁፎች መቀበያ ደህረ ገፅ ትዉዉቅና ስልጠና ተሰጠ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት መከታተያ ጽ/ቤት ከግንቦት 20 አስከ 22/2018 ዓ.ም የምርምር ጽሁፍ ስነ ምግባርን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምርምር ጽሁፎች ጋር የተያያዙ የሥነ ምግባር ጉዳዮችን አንስቶ የተወያየ እንዲሁም አገልግሎቱን በማዘመንና ዲጂታላይዝ በማድረግ የግምገማ ሂደቱን የሚከወንበትን ድረ-ገጽንም አስተዋዉቋል። የኢንስቲትዩቱ የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤት ዳይሬክተር ዶ/ር ማህደር ሚሊዮን በመድረኩ ላይ ጽ/ቤታቸው የተለያዩ የምርምር ጽሑፎች ከኢንስቲትዩቱም ሆነ ከሌሎች አጋር ተቋማት የሚመጡን የምርምር ስነምግባር ፋቃድ ጥያቄ በመገምገም ወደ ሥራ የሚያስገባ ጽ/ቤት መሆኑን ጠቅሰዉ በክልሎች ለሚገኙ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችና ጤና ቢሮዎች ለሚገኙ ባለሙያዎች የምርምር ጽሁፍን ሥነ-ምግባር አስመልክቶ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል:: የስልጠናው አላማም ከጽህፈት ቤታቸው ጋር በጋራ የሚሰራ ቦርድ (IRB) ፕሮፖዛሎችን የሚገመግምና አጽድቆ ምርምሮችን ወደ ሥራ እንዲገቡ የሚያደርግ ቦርድ ያላቸው ተቋማት ለሌሎች ልምድ የሚያካፍሉበት እና የሌላቸው ደግሞ የሚያቋቁሙበትን ሁኔታ መነሻ እውቀት እንዲቀስሙ ለማስቻል ሲሆን በመድረኩ ተቋማዊ የምርምር ጽሁፎች የግምገማ ቦርድ (Institutional Review Board) የሌላቸው የክልል የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የምርምር ስነምግባር መክታተያ ቦርዱ ማቋቋም የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይም ምክክር ተካሂዷል:: በምክክር መድረኩ አዳዲስ ከሥነ ምግባር የተያያዙ ጉዳዮችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የምርምር ፍቃድ ጽሑፎችንና ጥያቄ የሚላኩትም ድህረ ገፅ የሚተዋውቅበት መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል። የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በመስኩ በሙያ ልምዳቸው እና እውቀታቸው ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች የተሰጠ ሲሆን የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ተመራማሪ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታልየኢንስቲትዩቱ የምርምርሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤቱ ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ የምርምር ፁሑፎችን ገምግሞ ፍቃድ የሰጠና የአለም አቀፍ የምርምር ግምገማና ፍቃድ አሰጣጥ ስርዓትን በመከተል ከStratgic initiative for Developing Capacity in Ethical Review ( SIDCER) በ 2023 እ.ኢ.አ እዉቅና የተሰጠዉ ተቋም መሆኑ ይታወሳል::
2 197
20
+1
Sin texto...
1 840