ch
Feedback
Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

前往频道在 Telegram

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 的分析概览

频道 Ethiopian Public Health Institute | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (@ethphi) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 515 名订阅者,在 医学 类别中位列第 1 729,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 329

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 515 名订阅者。

根据 10 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 168,过去 24 小时变化为 6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 14.92%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.36% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 166 次浏览,首日通常累积 1 214 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through ephieoc@gmail.com

凭借高频更新(最新数据采集于 11 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 医学 类别中的关键影响点。

14 515
订阅者
+624 小时
+267
+16830

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+59
在0个频道中
五月 '26
+248
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+187
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+104
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+51
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+125
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+286
在3个频道中
Get PRO
十一月 '25
+706
在3个频道中
Get PRO
十月 '25
+113
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+89
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+136
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+140
在1个频道中
Get PRO
六月 '25
+465
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+327
在5个频道中
Get PRO
四月 '25
+147
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+159
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+125
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+262
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+513
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+619
在2个频道中
Get PRO
十月 '24
+592
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+309
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+578
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+375
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+312
在1个频道中
Get PRO
五月 '24
+308
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+361
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+327
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+372
在2个频道中
Get PRO
一月 '24
+531
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+462
在2个频道中
Get PRO
十一月 '23
+129
在1个频道中
Get PRO
十月 '23
+190
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+106
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+85
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+73
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+73
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+52
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+84
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+53
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+64
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+95
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+86
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+57
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+67
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+72
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+60
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+107
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+105
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+101
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+72
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+38
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+67
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+99
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+30
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+112
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+133
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+106
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+107
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+113
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+76
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+243
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+319
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+149
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+3 714
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+4 494
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
10 六月+12
09 六月+3
08 六月0
07 六月+6
06 六月+14
05 六月+2
04 六月+5
03 六月+4
02 六月0
01 六月+13
频道帖子
የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዣን ካሴያ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ጎበኙ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዣን ካሴያ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፣ መንግሥት የሕብረተሰቡን ጤና ለማሻሻል የጤና ባለሙያዎችን አቅም በመገንባት፣ የጤና መረጃዎችን ዲጂታላይዝ በማድረግ እና የድንገተኛ ጤና አደጋዎችን ለመቆጣጠር የተለያዩ የዝግጁነት ሥራዎችን እያከናወነ ነው። በተለይም የኢቦላ ወረርሽኝን ለመከላከል የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልን በማጠናከር በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሃይሉ በበኩላቸው፣ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ ከ100 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው ተቋም ሲሆን በምርምር፣ በብሔራዊ የላቦራቶሪ አገልግሎት እና በሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ በበኩላቸው የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል። ዶ/ር ዣን ካሴያ በበኩላቸው በጉብኝቱ ወቅት የተመለከቷቸው የኢንስቲትዩቱ አገልግሎቶችና አቅሞች ውጤታማ መሆናቸውን መመልከታቸውን እና መደነቃቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም በአፍሪካ ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና ሥርዓቶችን ለማጠናከር ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ እንደሚያጠናክሩ አስታውቀዋል።

2
+6
没有文字...
1 030
3
በኢትዮጵያ የአዳዲስ ክትባቶች ትግበራ ግምገማ ዙሪያ የመረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና ተካሄደ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክትባት የሚከላከሉ በሽታዎች ዲቪዥን አስተባባሪነት፣ Integrated Post-Introduction Evaluation (PIE) in Ethiopia የመረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና ከሰኔ 1-5 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል። ስልጠናው በቅርቡ ወደ አገሪቱ የገቡ አዳዲስ ክትባቶችን አፈጻጸም በመገምገም የተገኙ ተሞክሮዎችንና ተግዳሮቶችን ለመለየት እና ለወደፊት የክትባት ፕሮግራሞች ማሻሻያ ግብዓት ለማግኘት ያለመ ነው። በመክፈቻው ላይ የተላላፊ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ገመቹ ታደሰ የክትባት በሽታዎች ምርምር የአምስት ዓመት ስትራቴጂ መዘጋጀቱን በመግለጽ፣ ይህ ጥናት ከስትራቴጂው ቅድሚያ ከተሰጣቸው ተግባራት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል። ለማንኛውም ጥናት የመረጃ ጥራት ወሳኝ በመሆኑ መረጃ ሰብሳቢዎች በኃላፊነትና በጥንቃቄ እንዲሰሩ አሳስበዋል። የጤና ሚኒስቴር የክትባት አገልግሎት ሃላፊ አቶ መልካሙ አያሌው በበኩላቸው፣ ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የክትባት ሽፋንን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ በቅርብ ጊዜ የገቡትን የሄፓታይተስ ቢ፣ የወባ እና የኩፍኝ ክትባቶች አፈጻጸም ለመገምገም የሚሰበሰበው መረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አስገንዝበዋል። የክትባት የሚከላከሉ በሽታዎች ምርምር ዲቪዥን ሃላፊ ዶ/ር ራጂሃ አቡበከር ደግሞ ተሳታፊዎች በስልጠናው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የመረጃ አሰባሰብ ሂደቱን በተገቢው ሁኔታ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርበዋል። ከስልጠናው በኋላ ሰልጣኞቹ ለ15 ቀናት በተመረጡ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በመሰማራት የመስክ መረጃ ስብስብ ሥራ ያከናውናሉ።
1 646
4
+7
没有文字...
1 448
5
የአንትራክስ የላቦራቶሪ ምርመራን ወደ ክልሎች ለማስፋፋት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከዚህ በፊት በማዕከል ደረጃ ብቻ ሲሰጥ የነበረውን የአንትራክስ ሞለኪውላር ላቦራቶሪ ምርመራ (Anthrax Molecular Laboratory) አገልግሎትን በሶስት የክልል ላቦራቶሪዎች ማለትም በአማራ የሕህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (ባህርዳር)፣ በትግራይ ጤና ምርምር ኢንስቲትዩት (መቀሌ)፣ በአርባምንጭ የሕብረተሰብ ጤና ላቦራቶሪ (አርባምንጭ) አገልግሎቱን ለማስጀመር የሚረዳ የናሙና አሰባሰብ፤ የሞለኪውላር (PCR) ምርመራ ዘዴዎችን፣ እንዲሁም የምርመራ ጥራት ማረጋገጫ ሂደቶችን ያካተተ ሥልጠና ከሲዲሲ-ኢትዮጵያ እና ከOSU-GOHI ጋር በመተባበር ከግንቦት 26 እስከ 29/2018 ዓ.ም ሰጠ። የኢንስቲትዩቱ የላቦራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል መለሰ እንደገለጹት የዚህ ምርመራ መስፋፋት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን፤ በዋናነትም የሞለኪውላር ላቦራቶሪዎችን በሀገር ደረጃ ለማስፋፋት ከተያዙ አቅዶች ውስጥ አንዱ እንደሆነና በሀገር ደረጃ እየተሰፋፋ ያለውን የአንትራክስ (አባ ሰንጋ) በሽታ ፈጥኖ ለመለየት እና ለመከላከል የነዚህ ላቦራቶሪዎች በክልል ደረጃ መጀመር ትልቅ ፋይዳ ይኖራቸዋል፡፡ አቶ ዳንኤል አያይዘውም ሥልጠናው ልምድ ባካበቱ የኢንስቲትዩቱ ባለሙያዎች እና በበይነ መረብ ከCDC- Atlanta የተሰጠ ሲሆን ስልጣኞችም የንድፈ ሃሳባዊ ዕውቀት እንዲሁም የሞለኪውላር ላቦራቶሪ የተግባር ልምምድ አድርገዋል፡፡ የሲዲሲ-ኢትዮጵያና የOSU-GOHI ተወካዮች በበኩላቸው ባሰተላለፋት መልዕክትም በዚህ ዘርፍ ቀጣይነት ያለው የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚሰጡ መግለጻቸውን አቶ ዳንኤል ተናግረዋል።
1 777
6
+1
没有文字...
1 530
7
የዓለም የምግብ ደህንነት ቀን በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተከብሮ ውሏል። ​በኢንስቲትዩቱ የስነ-ምግብ፣ አካባቢ ጤና እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዳይሬክቶሬት ስር የሚገኘው የምግብ ደህንነት ምርምር ዲቪዥን፣ የዓለም የምግብ ደህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ ከ70 በላይ ለሚሆኑ የኢንስቲትዩቱ ካፌቴሪያና ኬተሪንግ አገልግሎት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። ስልጠናው በምግብ ደህንነት መርሆዎች፣ በግል ንፅህና፣ በደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ አያያዝ እና በምግብ ወለድ በሽታዎች መከላከል ዙሪያ ያተኮረ ነበር። ​በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት የምግብ ደህንነት ምርምር ዲቪዥን ኃላፊ አቶ ዋቅቶላ ጎበና ፣ የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ የሁሉም የጋራ ኃላፊነት መሆኑንና ሳይንስን መሰረት ያደረገ አሰራርን በመከተል በምግብ አማካኝነት የሚመጡ በሽታዎችን መከላከል እንደሚቻል ገልጸዋል። ​ከፍተኛ ተመራማሪው ዶ/ር ተስፋዬ ለገሰ በበኩላቸው፣ ትክክለኛ የእጅ ንፅህና፣ ዘመናዊ የምግብ ማከማቻ እና ጥንቃቄ የተሞላበት አያያዝ ልምዶች አብዛኞቹን በምግብ የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመግታት ወሳኝ መሆናቸውን አስገንዝበዋል። ​የኢንስቲትዩቱ የካፍቴሪያ እና ኬተሪንግ አገጋግሎት ሀላፊ አቶ ያረድ ፋንታው በበኩላቸው ሰራተኞች በስልጠናው ያገኟቸውን ሳይንሳዊ እውቀቶች በዕለት ተዕለት ስራቸው ላይ በተግባር ማዋል እንዳለባቸው ተናግረው በስልጠና የተገኘውን እውቀት በተግባር እንደሚያውሉት ተናግረዋል።
1 692
8
+3
没有文字...
1 544
9
+9
没有文字...
1 727
10
የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች የኢቦላ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችል በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተግባር ልምምድ (Simulation exercise) አካሄዱ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከል በተጓዦችና ድንበር ጤና ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት የተከሰተውን የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ዝግጁነት ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር የመግቢያና መውጫ የጤና ቁጥጥር ባለሙያዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የጤና ልየታ፣ የቁጥጥር፣የቅኝት ስራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ተግባራዊ ልምምድ አካሄዱ፡፡ የተግባር ልምምዱ (Simulation exercise) ዋና ዓላማ የግብዓትና የሰው ኃይል ዝግጁነት ክፍተት በመለየት በሽታው ወደ አገር እንዳይገባ የመከላከል እንዲሁም በሽታው ቢከሰት እንኳን የመከላከል እና የምላሽ ስራዎች በምን ያህል ደረጃ ውጤታማ ይሆናሉ፣ ምን ጠንካራ ጎኖች አሉ፣ ክፍተቶችስ ምን ይመስላሉ የሚሉትን በመለየት በቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን በማስተካከል ጠንካራ ዝግጁነትን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር በተግባር ልምምዱ የማጠቃለያ ግምገማ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው እንደገለጹት የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ከተገለጸበት ጊዜ አንስቶ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ሲሰራ መቆየቱን እና የተግባር ልምምድ መካሄዱ ትልቅ ተግባር መሆኑን አድንቀው፣ ከዚህ በፊት የነበሩትን ልምዶችና አሁን የተገኘውን እውቀት መሰረት በማድረግ በቀጣይ እስከ ታችኛው የጤና ተቋምና የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች በማውረድ ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ አገራችንን፣ ቤተሰባችንን፣ ሕብረተሰባችንን ከማንኛውም የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ችግሮች በመጠበቅና በመታደግ ለትውልድ የሚሻገር ስራ በመስራት ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተግኝተው በተግባር ልምምዱ ወቅት እንደገለጹት ኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልን ጥብቅ የሆነ የቅኝትና የልየታ ስራ እንዲሰራ የተደረገ መሆኑን፣ በኢትዮጵያ ባሉ በአየርም ሆነ በየብስ በሚገኙ የመግቢያና መውጫ በሮች በኩል በሽታው ከተከሰተባቸው አገራት የሚመጡ ተጓዦችን የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥርና ቅኝት ስራዎችን ተጠናክረው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ማንኛውንም የተላላፊ ወረርሽኝ በሽታ ናሙናዎች ለመመርመር የሚያስችል የሪፈረንስ እና የሪፈራል የላቦራቶሪ ዝግጁነት መጠናቀቁን አብራርተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም በኢትዮጵያ የኢቦላ ቫይረስ ተጠርጣሪ የሌለና በሽታውም ወደ ሀገር ያልገባ መሆኑን አረጋግጠው፣ በሽታው ሊከሰት ቢችል እንኳን ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙዎች የተግባር ልምምድ በማድረግ የክህሎት እና የብቃት ደረጃቸውን ያሳደጉ በመሆኑ በበሽታው የተጠረጠረ ሰው ቢገኝ ወደ ሌሎች ሰዎች በሽታውን ሳያስተላልፍ በተዘጋጁ የለይቶ ማቆያ ቦታዎች በመውሰድ አስፈላጊውን ህክምና የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ሕብረተሰቡ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚሰጡ መልዕክቶችን በሚገባ በመከታተል ተግባራዊ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር መልካሙ አብቴ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ለመከላከልና ዝግጅትን ከማጠናከር አንጻር ወረርሽኙ ከተከሰተባቸው አገራት አውሮፕላን ወደ አገራችን በረራ ከማድረጉ አስቀድሞ እያንዳንዱ ተሳፈሪ የጤና መረጃ ከመሙላት (e-THDF) አንስቶ እስከ መጨረሻው መደረግ የሚገባቸውን የቅኝት፣ የልየታ እና ክትትል ስራዎች በሚገባ እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የተካሄደው የጤና ባለሙያዎች የተግባር ልምምድ ወረርሽኙን በመከላከል ደረጃ ያሉትን ጠንካራ ጎኖች ለማስቀጠል፣ ክፍቶችን ደግሞ በማረምና በማስተካከል በዝግጁነት በኩል ያሉ ተግባራት አስተማማኝ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የተከናወነ መሆኑን ሰፊ ገለጻ አድርገዋል፡፡ አቶ ተመስገን ለሚ የኢንስቲትዩቱ የተጓዦችና ድንበር ጤና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የኢቦላ ቫይረስ ምንነት ሲያስረዱ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት በ DRC እና Uganda አገራት የተከሰተው የኢቦላ በሽታ Bundibugyo Ebola Virus አማካኝነት የሚመጣ እጅግ ከባድና ለህልፈተ ህይወት የሚዳርግ ተላላፊ በሽታ ሲሆን በሽታው ፈጣን ህክምና ካላገኘ የሞት ምጣኔው እስከ 90% ሊደርስ የሚችል በጣም አደገኛ ወረርሽኝ መሆኑን፣ ምልክቶቹም ድንገተኛ ትኩሳት፣ ከፍተኛ የጡንቻና የራስ ምታት፣ የጉሮሮ መቁሰል፣ ማስመለስ፣ ተቅማጥ እና ከውስጥና ከውጭ አካላት የሚወጣ የደም መፍሰስ (Hemorrhage) የመሳሰሉት ምልክቶች መሆናቸውን ጠቁመው በሽታው ወደ አገር እንዳይገባ በሁሉም የዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች እና የየብስ መግቢና መውጫ በሮች ላይ በተለይም በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከፍተኛ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ሁሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ከበበው በቀለ በአትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት የቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ዳይሬክተር የሕረተሰቡን ጤንነት ከማስጠበቅ አንጻር አየር መንገዱ እየሰራ ያለውን በተመለከተ ሲገልጹ የአደጋ ጊዜ የምላሽ ዝግጁነት ተግባራትን አንዱ የስራችን ክፍል በማድረግ እቅድ ወጥቶ፣ አፈጻጸሙንም በየጊዜው እየተገመገመ መሆኑንና የህብረተሰቡን ጤና ችግር የሚፈጥሩ ተላላፊ በሽታዎችንም ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንጻር ከኢትዮጰያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በቅንጅት አስፈላጊውን ስራ ሁሉ እየተሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ምናባዊ የሆነ የኢቦላ ተጠርጣሪ ሰው በማዘጋጀት በሽታው ከተከሰተባቸው አገራት ጀምሮ መረጃዎችን በማዘጋጀት እስከ ለይቶ ማቆያ ድረስ መደረግ ያለባቸውን አስፈላጊ ተግባራት ሁሉ ያካተተ የተግባር ልምምድ ያካሄዱ ሲሆን በልምምዱ ወቅት የነበሩ ጠንካራ ጎኖች እና ክፍተቶችን ተለይተው የማስተካከያ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል፡፡ የቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ባለድርሻ አካላት የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፥ NISS, Immigration, Customs, Federal Police, እንዲሁም አጋር ድርጅቶች፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)፣ የአሜሪካ በሽታዎች መከላከል ማዕከል (US CDC) ፣ የዓለም የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ፥ UK HSA እና ሌሎችም የተግባር ልምመዱ ላይ በአካል በመገኘት የገንዘብ ፥የእውቀት እና የክህሎት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
1 932
11
+3
没有文字...
1 910
12
+9
没有文字...
2 081
13
ለሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ለማስጣት አስፈላጊ የሆኑ የግብዓቶች ዝርዝር መመሪያ ማጠናቀቂያ አውደ ጥናት ታካሄደ ኢትዮጵያ ውስጥ ማንኛውም ዓይነት የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ በሚከሰትበት ጊዜ ፈጣን፣ የተቃነጀ እንዲሁም ሕይወት አድን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች የግብአቶች ዝርዝር መመሪያ ለማጠናቀቂያ አውደ ጥናት (ወርክሾፕ) ከግንቦት 18 - 22, 2018 ዓ.ም ተካሂዷል። በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ዝግጁነት ዳይሬክቶሬት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት አስተዳደር ዲቪዥን አስተባባሪ አቶ ቢቂላ ዲሪባ እንደገለጹት፤ አሁን ላይ እየተዘጋጀ ያለው የግብአት ዝርዝር መመሪያ ድንገተኛ አደጋዎች ከመከሰቱ በፊት የሚደረግ የቅድመ ዝግጁነት ስራ አካል ነው። ዋናው ዓላማው አደጋ ከመከሰቱ በፊት ለእያንዳንዱ የድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ምን ዓይነት ግብአቶች እንደሚያስፈልጉ አስቀድሞ መለየት፣ ሀገር አቀፍ ደረጃ ያለው ወጥ መመሪያ ማውጣት እንዲሁም የአቅርቦት ሰንሰለት ዘላቂነትን ማረጋገጥ ነው። አስተባባሪው አክለውም፥ ይህ ወጥ የሆነ አሰራር መዘርጋቱ ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ምላሽ መስጠ የሚያስችል ጠንካራ፣ ተቋማዊ እና ዘላቂ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት ሥርዓት መገንባት ነው። አውደ ጥናቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች አቅርቦት ሥርዓትን ለማዘመን፣ የግብአት ድግግሞሽ እና ብክነትን ለመቀነስ፣ ወጥ የሆነ የምላሽ ሂደት እንዲኖር ለማድረግ እንደሚረዳ ተሳታፊዎች አጽንኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም መመሪያው ተቋማት አንድ አይነት የምላሽ አሰጣጥ እንዲከተሉ በማድረግ ቅንጅታዊ አሠራር ለመፍጠር እንደሚረዳ ተመላክቷል። በአውደ ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት፣ ከኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን፣ WHO፣ Project Hope፣ JSI፣ UKHSA፣ CHAI፣ ከክልሎች እና ከሆስፒታሎች የተውጣጡ፣ በቀጥታ የስራው ባለድርሻ የሆኑ አካላት ተሳትፈዋል። ይህ መመሪያ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ግብአቶች ዝግጁነትን የሥራ ባህል ለማድረግ መሠረታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
3 792
14
+7
没有文字...
2 686
15
በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ደህንነትን ለማጠናከር የሚያስችል የአንድ ጤና የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ማነቃቂያ አውደጥናት ተካሄደ:: የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በብሔራዊ የአንድ ጤና (One Health) ሴክሬታሪያት አማካኝነት በኢትዮጵያን ያሉ የጤና ስጋቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የዝግጁነትና ምላሽ አቅም ለማጠናከር ያለመ የቴክኒክ የሥራ ቡድኖች (TWGs) ማነቃቂያ ወርክሾፕ ከግንቦት 20–21 ቀን 2018 ዓ. ም አካሂዳል ። በአውደጥናቱ የመንግሥት ተቋማትን፣ የልማት አጋሮችን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በአንድ ጤና አቀራረብ በማሰባሰብ ከአስተዳደር፣ ከቅንጅት፣ ከተጠያቂነት እና ዘላቂነት ጋር የተያያዙ ችግሮች ላይ ተወያይቷል። በዝግጅቱ ላይ የብሔራዊ የአንድ ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር ፈይሳ ረጋሳ የሰው፣ የእንስሳት እና የአካባቢ ጤና ሥርዓቶችን በተቀናጀ መንገድ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። “ዋና ግባችን ለጊዜው ለሚከሰቱ የጤና ችግሮች መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ፣ ከወረርሽኞች ውጪም በየዕለቱ የሚሰራ እና ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ ጠንካራ የሥራ ሥርዓት መገንባት ነው” ብለዋል። የአውደ ጥናቱ ቁልፍ ውጤቶች የመመሪያ ሰነዶችን (Terms of Reference - TORs) በማሻሻል የሥራ ኃላፊነቶችንና የሪፖርት ማቅረቢያ መዋቅሮችን ግልጽ ማድረግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ እንዲሁም ለቴክኒክ የሥራ ቡድኖች ቋሚ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎችን በመሾም እና መደበኛ የመግባቢያ መድረኮችን በመፍጠር እንደገና ማነቃቃትን ያካትታሉ። በአውደ ጥናቱ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ከግብርና ሚኒስቴር፣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን እንዲሁም እንደ FAO፣ Resolve to Save Lives፣ UKHSA፣ JSI፣ Core Group Partners Project፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር እና Project HOPE ያሉ አለማቀፍ አጋሮች ተሳትፈውበታል:: ተሳታፊዎች በሰው፣ በእንስሳት እና በአካባቢ ጤና መስኮች መካከል የሚከሰቱ አዳዲስ የጤና ስጋቶችን ለመቋቋም በቅጽበት የመረጃ ልውውጥን ማሻሻል፣ ሀብት ማሰባሰብ እና የተቀናጀ ምላሽ መስጠትን ለማጠናከር ቃል ገብተዋል። ይህ የተሳካ አውደጥናት የአንድ ጤና አቀራረብን በኢትዮጵያ ውስጥ ተቋማዊ ለማድረግ እና የዘርፎች መካከል ትብብርን ለሰዎች፣ ለእንስሳት እና ለአካባቢው ጤና መደበኛ የሥራ ባህል ለማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ታይቶበታል:: EPHI Concludes One Health TWGs Revitalization Workshop to Strengthen Ethiopia’s Health Security The Ethiopian Public Health Institute (EPHI), through the National One Health Secretariat, has successfully concluded a two-day Technical Working Groups (TWGs) Revitalization Workshop held from May 28–29, 2026, aimed at strengthening Ethiopia’s preparedness and response to interconnected health threats. The workshop brought together government institutions, development partners, and stakeholders to address challenges related to governance, coordination, accountability, and the sustainability of the One Health approach. Speaking at the event, Dr. Feyisa Regassa, Chairperson of the National One Health Secretariat, emphasized the need to integrate human, animal, and environmental health systems. “Our ultimate objective is to pivot away from temporary fixes and build a resilient, everyday operational mechanism that endures well beyond active outbreaks,” he said. Key achievements of the workshop included refining draft Terms of Reference (TORs) to clarify mandates and reporting structures, strengthening accountability mechanisms, and revitalizing Technical Working Groups through the appointment of dedicated chairs and co-chairs and the establishment of regular communication platforms. The workshop also reinforced collaboration among key stakeholders, including the Ministry of Health, Ministry of Agriculture, Environmental Protection Authority, Ethiopian Wildlife Conservation Authority, and international partners such as FAO, Resolve to Save Lives, UKHSA, JSI, core group partners project , Ethiopia Red Cross Society and Project HOPE. Participants committed to enhancing real-time information sharing, resource mobilization, and coordinated responses to emerging health threats at the human-animal-environment interface. The successful workshop marks an important step toward institutionalizing the One Health approach in Ethiopia, making cross-sector collaboration a routine practice for protecting the health of people, animals, and the environment.
2 840
16
+6
没有文字...
2 973
17
የምርምር ስነምግባር፣ የጥናታዊ ፅሁፎች ቅድመ ምርምር ግምገማና እዉቅና አሰጣጥ ቦርድ አሰራር እና የ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጥናታዊ ፅሁፎች መቀበያ ደህረ ገፅ ትዉዉቅና ስልጠና ተሰጠ፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት መከታተያ ጽ/ቤት ከግንቦት 20 አስከ 22/2018 ዓ.ም የምርምር ጽሁፍ ስነ ምግባርን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምርምር ጽሁፎች ጋር የተያያዙ የሥነ ምግባር ጉዳዮችን አንስቶ የተወያየ እንዲሁም አገልግሎቱን በማዘመንና ዲጂታላይዝ በማድረግ የግምገማ ሂደቱን የሚከወንበትን ድረ-ገጽንም አስተዋዉቋል። የኢንስቲትዩቱ የምርምር ሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤት ዳይሬክተር ዶ/ር ማህደር ሚሊዮን በመድረኩ ላይ ጽ/ቤታቸው የተለያዩ የምርምር ጽሑፎች ከኢንስቲትዩቱም ሆነ ከሌሎች አጋር ተቋማት የሚመጡን የምርምር ስነምግባር ፋቃድ ጥያቄ በመገምገም ወደ ሥራ የሚያስገባ ጽ/ቤት መሆኑን ጠቅሰዉ በክልሎች ለሚገኙ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችና ጤና ቢሮዎች ለሚገኙ ባለሙያዎች የምርምር ጽሁፍን ሥነ-ምግባር አስመልክቶ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል:: የስልጠናው አላማም ከጽህፈት ቤታቸው ጋር በጋራ የሚሰራ ቦርድ (IRB) ፕሮፖዛሎችን የሚገመግምና አጽድቆ ምርምሮችን ወደ ሥራ እንዲገቡ የሚያደርግ ቦርድ ያላቸው ተቋማት ለሌሎች ልምድ የሚያካፍሉበት እና የሌላቸው ደግሞ የሚያቋቁሙበትን ሁኔታ መነሻ እውቀት እንዲቀስሙ ለማስቻል ሲሆን በመድረኩ ተቋማዊ የምርምር ጽሁፎች የግምገማ ቦርድ (Institutional Review Board) የሌላቸው የክልል የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የምርምር ስነምግባር መክታተያ ቦርዱ ማቋቋም የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይም ምክክር ተካሂዷል:: በምክክር መድረኩ አዳዲስ ከሥነ ምግባር የተያያዙ ጉዳዮችን ዲጂታላይዝ በማድረግ የምርምር ፍቃድ ጽሑፎችንና ጥያቄ የሚላኩትም ድህረ ገፅ የሚተዋውቅበት መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል። የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በመስኩ በሙያ ልምዳቸው እና እውቀታቸው ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች የተሰጠ ሲሆን የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የክልል ጤና ቢሮዎች እና የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ተመራማሪ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታልየኢንስቲትዩቱ የምርምርሥነ-ምግባር እና ህትመት ጽ/ቤቱ ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ የምርምር ፁሑፎችን ገምግሞ ፍቃድ የሰጠና የአለም አቀፍ የምርምር ግምገማና ፍቃድ አሰጣጥ ስርዓትን በመከተል ከStratgic initiative for Developing Capacity in Ethical Review ( SIDCER) በ 2023 እ.ኢ.አ እዉቅና የተሰጠዉ ተቋም መሆኑ ይታወሳል::
2 197
18
+1
没有文字...
1 840
19
+9
没有文字...
2 187
20
የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር መረጃዎችን ከመነሻቸው በጤና ተቋማት አገልግሎት ለሚሰጡ የጤና ባለሙያዎችን አቅም በመገንባት የጤና መረጃዎችን ጥራት ማስጠበቅ እንደሚቻል ተገለጸ፡፡ የኢትዮጰያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቅኝትና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክቶሬት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቅኝትና በሽታ ኢንተለጀንስ ዲቪዥን የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ተግባራትን ለማከናወን በመረጃ መነሻነት አገልግሎት በሚሰጡ የጤና ተቋማት ላይ ለሚስሩ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች የመረጃ ጥራትን አስመልክቶ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የስልጠናው ዋና ዓላማ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ መረጃዎችን ጥራትና ወቅታዊነት ለማስጠበቅ መረጃዎችን ከመነሻቸው ከጤና ተቋማት በደረጃ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ለማድረግ፣ ባለሙያዎች ጥራት ያላቸውን መረጃዎች የማሰባሰብ፣ የማደራጀት ፣ የመተንተንና መተንተን በየደረጃው ለእቅድ፡ ለውሳኔ መጠቀም እና ሪፖርት የማድረግ ተግባራትን ለማሻሻል የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ነው፡፡ አቶ ደረጄ መሬ የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቅኝት ባለሙያና የስልጠናው አስተባባሪ ለጤና ባለሙያዎች የተሰጠውን የአቅም ግንባታ ስልጠና አስመልክቶ እንደገለጹት የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ማዕከልን የልህቀት ማዕከል ከማድረግ አንጻር በሀገር አቀፍ ደረጃ መረጃን በማዘመን እና ዲጂታላይዝ የማድረጉ ጉዳይ በርካታ ስራ የተሰራ በመሆኑ አመርቂ ውጤት እተመዘገበ ይገኛል ብለዋል፡፡ የመረጃ ጥራትን ለማስጠበቅ መረጃዎች ከሚነሱበት በጤና ተቋማት እንደ ሀገር የመረጃ አሰባሰብ፣ አያያዝ፥ ጥራት አጠባበቅና ለውሳኔ መጠቀም የቅድመ አስፈላጊነት ጥናት በማደረግ፥ ከባላድርሻ አካላት ጋር በመወያየት እና የቅድመ የአፈጸም መመሪያዎችን በማጠናቀቅ ለተመረጡ ተቋማት በኦሮሚያ፤ በአዲስ አባባ፣ በድሬዳዋ፣ በሲዳማ፣ በማእክላዊ ኢትዮጲያ አና በደቡብ ኢትዮጲያ የፓይለት/የሙክራ/ትግበራ እየተስራ መሆኑንና የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ስራ ላይ ለሚሰሩ ለተመረጡ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ከመሆኑም በላይ በቀጣይ በአገር አቀፍ ደረጃ ስልጠናውን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አቶ ደረጄ አያይዘው አብራርተዋል፡፡ የመረጃ አሰባሰብ፣ አደረጃጀት፣ጥራት አጠባበቅን፣ መረጃዎችን በኤክሴል እና በDHI2 እንዴት እንደሚያዝ፣ እንዴት እንደሚተነተንና ሪፖርት እንደሚደረግ አጠቃላይ በጤና ተቋማት መደረግ ስለሚገባቸው የመረጃ ጥራት ስራዎች በስፋትና በጥልቀት ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የጤና ባለሙያዎችም ባገኙት እውቀት እና ክሕሎት በመጠቀም ከጤና ተቋማት ተሰብስበው የሚወጡ መረጃዎች ተአማኒነተቸው፣ ወቅታዊነታቸው፣ አደረጃጀታቸውና ምሉእነታቸው እንዱሁም በሚፈለገው ደረጃ ጥራታቸው የተጠበቀ መረጃዎች ለሚመለከታቸው ማመንጨት፣ መያዝ፣ መጠቀም እና ማጋራት ባለድርሻ አካላትና ለውሳኔ ሰጪ ተደራሽ በማድረግ ተገቢውን የምላሽ ስራ ይሳለጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
3 656