GSFGBC፡ ጎሮ ሰፈራ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ
ይህ የቴሌግራም ቻናል በኢትዮጽያ ሙሉ ወንጌል አማኛች ቤተክርያን የጎሮ ሰፈራ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ፣የሚከናወኑና የሚተገበሩ ፕሮግራምዎችን መከታተያ page ነው፡፡ this is official page of goro sefera full gospel believers church... If you have any question Contact: @Kirubel76 @pastor_sisay
Show more301
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1430 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Repost from GSFGBC፡ ጎሮ ሰፈራ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ
ሰላም ለእናንተ ይሁን ቅዱሳን
አሰራት ፣የወንጌል ማህበርተኝነት ፣ለርህራሄ አገልግሎት ፣፣የፍቅር ሰጦታ ፣ለግንባታ ሰራ እና ለሌሎችም ጉዳዮች ብር ለማሰገባት ከዚህ በላይ ያሉትን የባንክ አካውንት እንድትጠቀሙ ስንል በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን
ቤተክርስቲያን
#ዜና #እረፍት
ዶ/ር መጋቢ #ዘለቀ #አለሙ ወደ #ጌታ #ሄዱ::
የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው፡፡ መዝ 116፡15
ህዳር 5/3/56 ዓ.ም ገና በልጅነት ጌታ ኢየሱስን የሕይወታቸው አዳኝ አድርገው በመቀበል በመንፈስ ቅዱስ በመሞላት ሕይወታቸው ተለወጠ።
ዶ/ር መጋቢ አለሙ ዘለቀ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ስትመሰረት ቀደምት አባቶች መካከል ቀዳሚ የነበሩና ከመጀመርያዎችሁ ከተመረጡት ሰባት ሽማግሌዎች መካከል አንዱ በመሆን ስማቸው በጉልህ ይጠቀሳል።
ዶ/ር መጋቢ ዘለቀ አለሙ በሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን በነበራቸው የአገልግሎት ዘመን ላልዳኑ ወገኖች ልዩ የወንጌል ሸክም የነበራቸው፣ በመንፈስ ቅዱስ ጰንጠቆስጣዊ እንቅስቃሴ በመሰጠት ያገለገሉ እና የእግዚአብሔርን ቃል በትጋት በማስተማር ይታወቃሉ።
ለትውልዱም መማርያ ይሆናል ብለው ያሰቡትን መንፈስ ቅዱስ በሕወታቸው ያከናወነውን ተግባር የሚገልፅ "ህይወቴ እና ጴንጤቆጤያዊ እንቅስቃሴ አጀማመር በኢትዮጲያ" የተሰኘው መፅሀፍ አበርክተው በጎ አሻራቸውን አኑረዋል።
በአገልግሎት ከ 60 ዓመታት በላይ በመቆየት ለብዙዎች በረከት ሆነዋል። በትዳር 46 ዓመታትን ከወ/ሮ ወይኒ ጋር አሳልፈዋል። ለብዙ ወጣት አገልጋዮችና አዲሱ ትዉልድ መልካም ልብ ያላቸው አባት መሆናቸው ለማወቅ ተችሎአል።
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በወንድማችን በሥጋ መለየትና እንደ ቤተክርስቲያናችን ውድ ወንድማችንን ከጎናችን በማጣታችን የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለቅርብ ወዳጆቻቸው እና በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚኖሩ የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና አባላት እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከጌታ ዘንድ መፅናናትን እንመኛለን ፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
👉በዩትዩብ፡ https://www.youtube.com/@efgbc
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/etfullgospel/
ቴሌግራም፡ https://t.me/EFGBC_JESUS
ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@efgbchurch/ ይከታተሉን።
👉የዶ/ር መጋቢ ዘለቀ አለሙ ወደ ጌታ መሄድን አስመልክቶ የሀዘን መግለጫ ከሰዓታት ቦሃላ ፦
👉ከኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ የሚተላለፍ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን!
👉በዩትዩብ፡ https://www.youtube.com/@efgbc
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/etfullgospel/
ቴሌግራም፡ https://t.me/EFGBC_JESUS
ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@efgbchurch/ ይከታተሉን።
#የሀዘን #መግለጫ
የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው፡፡ መዝ 116፡15
የምንወዳቸውና የምናከብራቸው ውድ መጋቢ ዶ/ር ዘለቀ አለሙ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ስትመሰረት ጀምሮ ቀደምት ከነበሩት አባቶች መካከል አንዱ የነበሩና ለመጀመርያ ጊዜ ከተመረጡት ሰባት ሽማግሌዎች ስማቸው በጉልህ የሚጠቀሱት እስካሁንም ለቤተክርስቲያናችን ከፍተኛ ፍቅር ያላቸው በተለይም በሰሜኑ ክፍል ላይ ለወንጌል ተልኮ ሚሽነሪዎችን በመላክ ፣የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ፣ወንጌል ላልደረሳቸው ከፍተኛ ሸክም የነበራቸው ዶ/ር መጋቢ ዘለቀ አለሙ የምድር የአገልግሎት ዘመናቸውን ጨርሰው ወደ ሚወዱትና ወደሚወዳቸው ሰማያዊ አባታቸው እቅፍ ሄደዋል።
ዶ/ር መጋቢ ዘለቀ አለሙ በቤተክርስቲያናችን በነበራቸው የአገልግሎት ዘመን ላልዳኑ ወገኖች ልዩ የወንጌል ሸክም የነበራቸው፣ በመንፈስ ቅዱስ ጰንጠቆስጣዊ እንቅስቃሴ በፈውስ ስጦታዎች ያገለገሉ እና የእግዚአብሔርን ቃል በትጋት አስተምረዋል።
ለትውልዱም መማርያ ይሆናል ብለው ያሰቡትን መንፈስ ቅዱስ በሕወታቸው ያከናወነውን ተግባር የሚገልፅ "ህይወቴ እና ጴንጤቆጤያዊ እንቅስቃሴ አጀማመር በኢትዮጲያ" የተሰኘው መፅሀፍ አበርክተው በጎ አሻራቸውን አኑረዋል።
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በወንድማችን በሥጋ መለየትና እንደ ቤተክርስቲያናችን ውድ ወንድማችንን ከጎናችን በማጣታችን የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለቅርብ ወዳጆቻቸው እና በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚኖሩ የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና አባላት እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከጌታ ዘንድ መፅናናትን እንመኛለን ፡፡
#መጋቢ #ላኮ #በዳሶ
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንት
“በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።”
— ዮሐንስ 3፥36