es
Feedback
EFGBC GSFGBlC፡ በኢት/ሙሉ/ወ/አ/ቤ/ክ የጎሮ ሰፈራ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤ/ክ

EFGBC GSFGBlC፡ በኢት/ሙሉ/ወ/አ/ቤ/ክ የጎሮ ሰፈራ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤ/ክ

Ir al canal en Telegram

ይህ የቴሌግራም ቻናል በኢትዮጽያ ሙሉ ወንጌል አማኛች ቤተክርያን የጎሮ ሰፈራ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ፣የሚከናወኑና የሚተገበሩ ፕሮግራምዎችን መከታተያ page ነው፡፡ this is official page of goro sefera full gospel believers church... If you have any question Contact: @Kirubel76 @pastor_sisay

Mostrar más
507
Suscriptores
+124 horas
+27 días
+1130 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+17
en 0 canales
junio '26
+23
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+26
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+11
en 1 canales
Get PRO
marzo '26
+13
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+8
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+7
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+9
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+10
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+13
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+16
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+19
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+15
en 1 canales
Get PRO
junio '25
+12
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+19
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+12
en 1 canales
Get PRO
marzo '25
+11
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+16
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+10
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+28
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+36
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+12
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+34
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+34
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+15
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+12
en 1 canales
Get PRO
mayo '24
+21
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+19
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+17
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+31
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+45
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+226
en 1 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
22 julio+2
21 julio+1
20 julio+1
19 julio0
18 julio0
17 julio+1
16 julio+1
15 julio0
14 julio+2
13 julio0
12 julio+1
11 julio0
10 julio+1
09 julio0
08 julio0
07 julio0
06 julio+1
05 julio+1
04 julio+3
03 julio+1
02 julio+1
01 julio0
Publicaciones del Canal
እንደ ይሁዳ ስሞ ከሚያሸጥ አርተፊሻል ፈገግታ ጀርባ ሞት አድፍጦ የሽያጩን ገንዘብ እንኳ ያለመውን መሬት ሳይገዛበት እየተቅበዘበዘ በተነው እርሱም በገመድ ተንጠልጥሎ ሞተ .......    ወዳጅነትን ለጥላቻ በዱቤ የሚያሸጥ ክፉ ልብ አይብቀልባችሁ ክፋታቸውን ከሚያጋቡባችሁ ክፉ ሠዎች . እና መርዛማ ሰዎች እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ ... ...        ያልተዛመደው ዝምድና ያልተገመደው ገመድ .... ዝምድናው ይበጠሳል ገመዱም እንደ ፈትል . አቅም የለውምና፡ ይቆረጣል ፡ እግዚአብሔር ከግብዝ ፡ ፈረሳውያን ፡ እየሳሙ ፡ ከሚሸጡ ፦ ይሁዲዎች አርቴፊሻል ፡ ፈገግታ ካላቸው : የተለወጡ ከሚመስሉ ፡ ግን ካልተለወጡ : ሰዎች ፡ ቅርፅ ብቻ : ከሆኑ ፡ የአምልኮ መልክ ካላቸው : እግዚአብሔርን ከማይሩሩ ፡  ሰውን ከማያ ፍ:ሩ የአፍ ፡ ክርስቲያኖች ና አገልጋዮች ይጠብቃችሁ

2
- ማርቆስ 8 32: እርሱም ይህን በግልጽ ነገራቸው። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስን ለብቻው ወስዶ ይገሥጸው ጀመር። 33: ኢየሱስ ግን ዘወር ብሎ ደቀ መዛሙርቱን እያየ ጴጥሮስን፣ “አንተ ሰይጣን፣ ወደ ኋላዬ ሂድ! አንተ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን ነገር አታስብምና” በማለት ገሠጸው።
116
3
ከዚህ ነገድ እንደ ሙሴ ያለ ነጻ አውጪ፣ እንደ አሮን ያለ ሊቀ ካህን፣ እንደ ሳሙኤል ያለ ፈራጅ፣ እንደ ኤርሚያስና ሕዝቅኤል ያሉ ነብያት ወጥተዋል። የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነው እንደሚባለው በመሳ 17 ላይ የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከቤተልሔም ይሁዳ ሲንከራተት የነበረውም ሌዋዊ ከዚያ የወጣ ነው። እንዳለመታደል ሆኖ ሚካ የተባለ ጣዖት አምላኪ እጅ ወደቀ። አባትና ካህን ሁነኝ፣ እከፍልሃለሁ፣ ምግብና ልብስ ከእኔ ሲለው ልጸልይበት፣ ላስብበትም አላለውም። "በአንድ አፍ" አይነት ብሎ ነው የፈረመለት። ችግሩ ግን የተሻለ ለከፈለው ሁሉ መፈረሙ ነው። ገና የሚካ ቤት ፊርማ ሳይደርቅ "ለአንድ ሰው ቤት ካህን መሆን…ወይስ ለነገድና ለወገን ካህን መሆን ማናቸው ይሻልሃል?' ሲሉት "በልቡ ደስ አለው" ይላል (መሳ 19:18 ) የተሻለ ያሳየ ይወስደዋል ማለት ይሄ ነው እንግዲህ። ዛሬስ ስንቱ ፡ አገልጋይ ነው ለቃሉ ፡ የተገዛ ለእውነትና ለህሊናው ያልኖረ? በሕዝ 44:9-15 ሁለት አይነት የሌዋውያን አገልግሎትን እናያለን። የመጀመሪያው በቁጥር 10 ላይ እስራኤል በሳቱ ጊዜ ተከትለው የሳቱ ሌዋውያንን ሲሆን በቁጥር 15 ላይ ደግሞ እስራኤል በሳተ ጊዜ ተከትለው ያልሳቱ የሳዶቅ ልጆች ሌዋውያን ካህናት ናቸው። በእነዚህ ሁለት አገልጋዮች መካከል ያለው ልዩነት ደማቅ ነው። የመጀመሪያዎቹ የብዙሃኑን ፍላጎት የሚከተሉ ሲሆኑ የሁለተኛዎቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን ሃሳብ ለማገልገል የጨከኑ መሆናቸው ነው። የሚገርመው ግን ከነጣዖትዋ እስራኤልን የሚያገለግሉትን አገልግሎታቸውን አልነጠቃቸውም ወይም አላስቆማቸውም። ነገር ግን ወደ እኔ አይቀርቡም፣ በፊታቸው ያገለግሏቸዋል በማለት ራሱን ሰውሮ አገልግሎቱን ፈቀደላቸው። እነርሱም ያለ መገኘቱ የሆነ አገልግሎት "በአፍንጫችን ይውጣ" አላሉም ቀጠሉ። እስራኤል በሳተ ጊዜ ያልሳቱ ሌዋውያን አገልጋዮች ግን ወደ እኔ ይቀርባሉ፣ ያገለግሉኝም ዘንድ በፊቴ ይቆማሉ ይላል። ከዚህ የሚበልጥ ምን በረከት አለ?
135
4
📖 #አገልጋይ_እና_አገልግሎት ✨ #መግቢያ አገልግሎት በክርስትና ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ያለው ጥሪ ነው። እግዚአብሔር አማኞችን የጠራቸው ለእርሱ ክብር፣ ለቤተ ክርስቲያን ማነጽ፣ እና ለዓለም ወንጌልን ለማድረስ ነው። አገልጋይ መሆን ማዕረግ ሳይሆን የሕይወት ጥሪና ኃላፊነት ነው። 📖 “የሰው ልጅ ሊያገለግል እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።” (ማርቆስ 10፥45) 🙋 1. #አገልጋይ_ማን_ነው? አገልጋይ ማለት በእግዚአብሔር የተጠራ፣ በመንፈስ ቅዱስ የተሾመ፣ ለእግዚአብሔር ፈቃድ ራሱን የሰጠ ሰው ነው። 📌 #የአገልጋይ_መለያዎች ❤️ እግዚአብሔርን ይወዳል። 🤝 ሰዎችን በፍቅር ያገለግላል። 🙏 የጸሎት ሰው ነው። 📖 ቃሉን ያውቃልና ይኖረዋል። 🌿 የመንፈስ ፍሬ ይታይበታል። 🌟 2. #አገልግሎት_ምንድን_ነው? አገልግሎት ማለት ለእግዚአብሔርና ለሰዎች በፍቅር እና በታማኝነት መስራት ነው። #አገልግሎት_ማለት፦ 📖 ቃሉን ማስተማር 🙏 መጸለይ 🎵 ማመስገን ❤️ የተቸገሩትን መርዳት 🌍 ወንጌልን ማድረስ 👑 3. #ኢየሱስ – #የአገልጋይ_ፍጹም_ምሳሌ 👉 ኢየሱስ በትሕትና አገልግሏል። 🦶 የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ። ❤️ ሕመምተኞችን ፈወሰ። 🍞 የተራቡትን መገበ። ✝️ ለዓለም መዳን ሕይወቱን ሰጠ። 🔥 4. #የአገልጋይ_መንፈሳዊ_ባህርያት 🙇 ትሕትና ❤️ ፍቅር 🤲 ታማኝነት 🙏 ጸሎት 📖 የእግዚአብሔር ቃል እውቀት 🕊️ ቅድስና ⏳ ትዕግሥት 😊 ርኅራኄ ⚠️ 5. #የአገልጋይ_አደጋዎች 😔 ትዕቢት 💰 ገንዘብን መውደድ 🌍 ዓለማዊነት 😴 መንፈሳዊ ስንፍና ⚡ የሥልጣን ፍላጎት ❌ የሥነ ምግባር ውድቀት 🎁 6. #የመንፈስ_ቅዱስ_ስጦታዎችና_አገልግሎት እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ አማኝ የተለያዩ ስጦታዎችን ሰጥቷል። 📖 ማስተማር 🎤 መስበክ 🤲 ማገልገል 💝 መስጠት 🧭 መምራት 🤝 ማበረታታት 📚 7. #የአገልጋይ_ኃላፊነቶች 📖 ቃሉን በትክክል ማስተማር 🛡️ መንጋውን መጠበቅ 🌱 ደቀ መዛሙርት ማፍራት 🤲 ሌሎችን ማገልገል 💡 መልካም ምሳሌ መሆን 💎 8. #እውነተኛ_አገልጋይ_ምን_ይፈልጋል? 👑 የእግዚአብሔርን ክብር 😊 የሰዎችን መዳን 🌱 የአማኞችን እድገት ❤️ የክርስቶስን ፈቃድ 📖 9. #የአገልጋይ_ቁልፍ_መርሆች ✝️ ክርስቶስን መምሰል 🙏 በጸሎት መትጋት 📖 ቃሉን በትክክል መከፋፈል 🤝 በፍቅር ማገልገል 🕊️ በመንፈስ ቅዱስ መመራት ⭐ እስከ መጨረሻ ታማኝ መሆን 📝 #ማጠቃለያ አገልጋይ መሆን ክብርን ወይም ዝናን መፈለግ አይደለም፤ ራስን ለእግዚአብሔር እና ለሰዎች በፍቅር መስጠት ነው። እውነተኛ አገልጋይ በትሕትና፣ በቅድስና፣ በታማኝነት፣ በጸሎት እና በእግዚአብሔር ቃል ይመላለሳል። 📖 #ቁልፍ_የመጽሐፍ_ቅዱስ_ጥቅሶች 📜 ማርቆስ 10፥42–45 📜 1 ጴጥሮስ 4፥10–11 📜 ኤፌሶን 4፥11–13 📜 1 ጢሞቴዎስ 3፥1–13 📜 2 ጢሞቴዎስ 2፥15 📜 ቆላስይስ 3፥23–24 “ማንም ታላቅ ሊሆን የሚፈልግ አገልጋያችሁ ይሁን።” (ማርቆስ 10፥43)
195
5
ከእግዚአብሔር ዐይን የሚሰወር ነገር የለም፤ እርሱ አየ ማለትም ፈጽሞ አወቀ ነው። አይቶ፣ አመዛዝኖና አገናዝቦ አይደለም ነገሮችን የሚረዳው፤ ያ የሰዎች ተግባር፣ የማወቅም ሂደት ነው። የኢዮብ በዕድሜ ትንሹ ወዳጅ--ኤሊሁ-- እንዲህ አለ፤ “ዐይኖቹ የሰውን አካሄድ ይመለከታሉ፤ ርምጃውንም ሁሉ ይከታተላሉ። ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፣ ጨለማ ስፍራ ወይም የሞት ጥላ የለም" (ኢዮ 34፥21-22)። ሁሉን የሚመለከት ጌታ፣ ለሁሉ እንደ ልቡ፣ እንደ ሥራው ይከፍላል። እግዚአብሔር ያየውን (የቀዳውን) መሰረዝ ወይም ማጥፋት የሚችል ማንም የለም።
141
6
ከእግዚአብሔር ዐይን የሚሰወር ነገር የለም፤ እርሱ አየ ማለትም ፈጽሞ አወቀ ነው። አይቶ፣ አመዛዝኖና አገናዝቦ አይደለም ነገሮችን የሚረዳው፤ ያ የሰዎች ተግባር፣ የማወቅም ሂደት ነው። የኢዮብ በዕድሜ ትንሹ ወዳጅ--ኤሊሁ-- እንዲህ አለ፤ “ዐይኖቹ የሰውን አካሄድ ይመለከታሉ፤ ርምጃውንም ሁሉ ይከታተላሉ። ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፣ ጨለማ ስፍራ ወይም የሞት ጥላ የለም" (ኢዮ 34፥21-22)። ሁሉን የሚመለከት ጌታ፣ ለሁሉ እንደ ልቡ፣ እንደ ሥራው ይከፍላል። እግዚአብሔር ያየውን (የቀዳውን) መሰረዝ ወይም ማጥፋት የሚችል ማንም የለም።
1
7
በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ የማይታዩ ነገር ግን የጉዞአችንን መድረሻ ሙሉ በሙሉ የሚወስኑ ሁለት ተቃራኒ መንገዶች አሉ፤ እነርሱም ትዕቢት እና ትህትና። መጽሐፍ ቅዱስ የሁለቱን መንገዶች መነሻ፣ አካሄድ እና መድረሻ በግልጽ ነው የሚያሳየን። 1. የትዕቢት መንገድ፡ የውድቀት ትዕቢት ማለት አንድ ሰው ከፈጣሪዎ እና ከሌሎች ሰዎች በላይ ራሱን ከፍ አድርጎ የሚያስብበት የልብ ሕመም ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን፣ የትዕቢት መነሻው የሳጥናኤል ውድቀት ነው። "ወደ ሰማይ እወጣለሁ... ከልዑልም ጋር እስከታካከላለሁ" ብሎ በልቡ በተመኘ ጊዜ ከክብሩ ተዋረደ (ኢሳ 14: 13-15)። በትዕቢት መንገድ ላይ የተጓዙ ሰዎችን ታሪክ ስንመለከት መድረሻቸው ሁልጊዜ ውድቀት እንደሆነ እንረዳለን፤ ለምሳሌ፦ #ንጉስ_ናቡከደነጾር፡ በባቢሎን ቤተ መንግስት በረንዳ ላይ ቆሞ 30“በብርቱ ኀይሌ፣ ለገናናው ክብሬ ንጉሣዊ መኖሪያ ትሆን ዘንድ ያሠራኋት ታላቂቷ ባቢሎን ይህች አይደለችምን?” አለ። 31ንግግሩን ገና ከአፉ ሳይጨርስ፣ እንዲህ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ፤ “ንጉሥ ናቡከደነፆር ሆይ፤ ስለ አንተ የታወጀው ይህ ነው፤ መንግሥትህ ከአንተ ተወስዷል፤ 32ከሕዝብ መካከል ትሰደዳለህ፤ ከዱር አራዊት ጋራም ትኖራለህ፤ እንደ ከብት ሣር ትበላለህ፤ ልዑሉ በሰዎች መንግሥት ሁሉ ላይ ሙሉ ሥልጣን እንዳለውና እነዚህንም መንግሥታት ለወደደው እንደሚሰጥ እስክታውቅ ድረስ ሰባት ዓመት ያልፋል።” 33ወዲያውኑ በናቡከደነፆር ላይ የተነገረው ሁሉ ተፈጸመ፤ ከሕዝቡ መካከል ተሰደደ፤ እንደ ከብትም ሣር በላ። የራስ ጠጕሩ እንደ ንስር ላባና፣ ጥፍሮቹም እንደ ወፍ ጥፍሮች እስኪያድጉ ድረስ ሰውነቱ በሰማይ ጠል ረሰረሰ።  (ዳንኤል 4፡30-33)። መጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌ 16፡18 ላይ 'ትዕቢት ጥፋትን፣ የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች። ' ትዕቢተኛ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ይጋጫል፣ ምክንያቱም እግዚአብሄር ትዕቢትን ስለሚቃወም። 2 የትህትና መንገድ፡ የታላቅነት ትህትና ማለት የደካማነት ምልክት ሳይሆን፣ የእውነተኛ ጥንካሬና የልብ ቅንነት መገለጫ ነው። ራሳችንን በእግዚአብሄር እና በሰው ፊት ዝቅ አድርገን የምናይበት መንፈሳዊ ዓይን ነው። የትህትና ትልቁና ፍጹሙ ምሳሌ የኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት ነው፡ ⏭️ የዓለም ፈጣሪና ንጉስ ሆኖ ሳለ፣ በበረት ተወለደ፣ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ፣ እስከ መስቀል ሞት ድረስ ታዘዘ (ፊልጽ 2:5-8)። ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 11፡29 ላይ "ቀንበሬን ተሸከሙ፤ ከእኔም ተማሩ፤ እኔ በልቤ የዋህና ትሑት ነኝና፤ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤    በማለት የእርሱን አርኣያነት እንድንከተል አስተምሮናል። ⏭️ ዮሴፍ በወንድሞቹ ተሽጦ፣ በግብጽ እስር ቤት ውስጥ እያለ እንኳ እግዚአብሄርን መፍራትና ትህትና  በህይወቱ ላይ ይታዩ ነበር፤ በጊዜውም እግዚአብሄር ከእስር ቤት አውጥቶ የግብጽ ሁሉተኛ መሪ አደረገው። መጽሐፍ ቅዱስ 'ነገር ግን ጸጋን አብዝቶ ይሰጠናል፤ መጽሐፍም፣ “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ያለው ስለዚህ ነው። ' ያዕቆብ 4:6 ሁለቱንም በንጽጽር ስናይ ትዕቢተኛ  ራሱን ከፍ ያደርጋል ግን ደግሞ ይዋረዳል፤ ትሁት ራሱን ዝቅ ያደርጋል ግን ደግሞ ከፍ ይላል። ትዕቢተኛ እግዚአብሄርን ይቃወማል ትሁት ግን ከእግዚአብሄር ጸጋን ይቀበላል፤ ትዕቢተኛ ሰዎችን እና እግዚአብሄርን ይቃወማል፤ ትሁት ከሰዎችና ከእግዚአብሄር ጋር  ይቀራረባል፤ ትዕቢተኛ ሰው መጨረሻው ወይም መድረሻው ጥፋት ነው፣ ትሁት ሰው ግን መጨረሻው እና መድረሻው ክብርና ሕይወት ነው።  ሳጠቃልለው ትዕቢት ልክ እንደ አየር እንደተሞላ ፊኛ ነው፤ ከወጣበት ከፍታ ላይ በትንሽ ነገር ይሰበራል፤ ትሁት ግን ሥሩ በጥልቁ እንደተተከለ ዛፍ ነው፤ ማዕበል አይጥለውም። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት በአንድ ታላቅ እውነት ይጠቃለላል፤  'በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ፣ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል። ' ያዕቆብ 4:10። የሕይወታችን ስኬት፣ ሰላምና ክብር የሚገኘው ራሳችንን በትህትና ስናስገዛ ነው።
150
8
https://youtu.be/d7vzCcHYlg0?si=oq6h_BGjdI9Tup5-
1
9
#ኢየሱስ_ማን_መሆኑን_በቅጡ_ማወቅ! ብዙ ነገሮች አጥተን ኖረን አይተነዋል፤ ብዙ ነገሮች ጥለውን ሄደው ስንቀጥል ራሳችንን አግኝተናል። ጌታ ኢየሱስን ላየ፣ ቸርነቱን ለቀመሰ ሰው ግን ከኢየሱስ መለየት፣ ያለ እርሱም መኖር ሞት ነው። የኢየሱስ ሁሉ በሁሉነት ሲገባን የሚያስፈልገን እርሱ ብቻ እንደሆነ፤ ያለ እርሱ መኖር፣ ምንም ማድረግ እንደማንችል እንረዳለን። ኢየሱስ ከያዕቆብ ጉድጓድ መብለጡ የእውነት ለገባው ሰው ኢየሱስ ጊዜያዊ ጥምን የሚያረካ ነገር ሳይሆን የዘላለም ውኃ ምንጭ፣ የሕይወት ውኃ ነው። ኢየሱስ ማን መሆኑን ማወቅ የዘላለም ሕይወትን ማትረፍ ነው። ያውም ትርፉ በምድር ስሌት የማይሰላ ዘላለማዊ ትርፍ ነው። ሳምራዊቷ ሴት ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ሳትረዳ በፊት የያዕቆብ ጉድጓድ የምታዜምለት፣ ታላቅነቱን የምትመሰክርለት፣ ከእርሱ ሌላ ምንጭ ያለ እንኳ እስካይመስላት ድረስ የምትመካበት ምንጯ ነበር። የኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት ሲገባት ግን አይደለም ደግማ ስለ ያዕቆብ ጉድጓድ ልታወራ፣ "አንተ ይህን ጉድጓድ ከሰጠን ከአባታችን ከያዕቆብ ትበልጣለህን?" ብላ ኢየሱስን ከያዕቆብ ጋር ልታወዳድር ይቅርና ስለ ኢየሱስ የዘላለም ውኃ ምንጭነት መለስ ብላ ለማሰብና ለመጠራጠር እንኳ ጊዜ አላገኘችም። ለእርሷ የበራላት ብርሃን ለብዙዎች እንዲበራ፣ ያየችውን ብዙዎች እንዲያዩት፣ የገባትንና የቀመሰችውን እውነት፣ ሕይወት ብዙዎች እንዲቀምሱ፣ ብዙዎችን ወደ እርሱ ልታፈልስ ወደ ሕዝቡ ሮጠች፤ እርሱ ማን መሆኑን አውቃለችና። ኢየሱስ ማን መሆኑን በቅጡ ማወቅ፦ ከብዙ ብክነት፣ በአላስፈላጊ፣ በሰው ሰራሽ፣ ጥምን በማይቆርጡ፣ በጥቃቅን ምንጮች ከመርካት ይጠብቃል፤ እርሱን ብቻ ለመጠማት፣ ከእርሱ ብቻ ለመጠጣት፣ በእርሱ ብቻ ለመርካት ይጠቅማል። ኢየሱስን በማንነቱ ማወቅ፣ እርሱ ማን መሆኑን በቅጡ መረዳት፣ ማስተዋል ይሁንልን!!
150
10
የእግዚአብሔር ዐይኖች የሚከለከሉባቸው ቦታዎች የሉም፤ እርሱ በሁሉም ስፍራ ይመለከታል፤ ሁሉንም አጥርቶ (አጥልቆ) ያያል። ዘማሪው ስለ እግዚአብሔር እንዲህ አለ፤ "ዐይኖቼ በምድሪቱ ታማኞች ላይ ናቸው፤ በንጽሕና መንገድ የሚሄድ፣ እርሱ ያገለግለኛል" (101፥6)። ሁሉን የሚያይ ጌታ ምርጦቹን በአንክሮ (በትኩረት) ይመለከታል፤ ይሳሳላቸዋል፤ ይጠነቅላቸዋል
147
11
ሰላም ለእናተ ተ: ይሁን የቤተክርስቲያናችን አባል እና ፡ አገልጋይ የሆነችው የእህታችን ትጓደድ (የወንድም ልዕል ስገድ ባለቤት/ እናቷ ፡ ሰላረፉ ዛሬ ቀብራቸው ስለሆነ ሓዘን እንድት ደረሱ፡ ስንል በጌታ ፍቅር እናሳስባለን ስልክ ..0913870898
172
12
እኛ እንደ ቤተ ክርስቲያን አካላትና አባላት ከማህበረሰቡ የተለየን ደሴት አይደለንም። ለመንግሥታት #እንጸልያለን፣ ህዝባችንን #እናገለግላለን፣ ለተቸገሩ #እንደርሳለን፣ ለሰላምንም #እናውጃለን፤ በዚህ የወርቅ ኢዮቤልዩ ማጠቃለያ በአል ላይ በድጋሚ ለህብረታችን መሥራቾች፣ ለቀደሙት መሪዎች፣ ለአባል ቤተ እምነቶች፣ ለመንግሥት አመራር አካላት፣ ለአጋር ድርጅቶች፣ ለዝግጅት ኮሚቴ አባላት፣ ለመድረክ አገልጋዮች፣ ለቴክኒክ ባለሙያዎች፣ በጸሎትና ለደገፋችሁ ምእመናን እና በማንኛውም መንገድ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። ዛሬ የመጀመሪያውን 50 ዓመታት በምስጋና እያገባደድን ሁለተኛውን 50 ዓመት በእምነት እንጀምራለን። ስለዚህ በእግዚአብሔር ፊትና በእርስ በርሳችን ፊት ተነስተን ቆመን ይህን ቅዱስ ቃል ኪዳን እንድንገባ በትህትና እጥይቃለሁ፤ I. የእግዚአብሔርን ቃል ከሁሉ በላይ እናስቀድማለን፤ II. የክርስቶስን ወንጌል በንጽሕና፣ በድፍረትና በፍቅር እንሰብካለን፤ III. በቅድስና እንመላለሳለን፤ በእውነት እንቆማለን፤ በፍቅር እንተባበራለን፤ IV. ለሰላምና ለእርቅ እንሠራለን፤ V. የሚቀጥለውን ትውልድ በእምነትና በታማኝነት እናሳድጋለን፤ VI. በትህትና እንመራለን፤ VII. ሁልጊዜም የክርስቶስን ክብር ከራሳችን ክብር እናስቀድማለን። አሜን! በዚህ አጋጣሚ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም ይህን ጥሪ ማቅረብ እውዳልሁ፤ የጋናው የነጻነት አባት ኑኩሩማ እንዳሉት #ሁላችንም_ኢትዮጵያዊ የሆነው ኢትዮጵያ ውስጥ ስለተወለድን ብቻ ሳይሆን #ኢትዮጵያ_በእኛ_ውስጥ_ስለተወለድች_ነው። ስለሆንም አንዳችን ኢትዮጵያዊ ሆነን ለመወለድ ምንም ስላላዋጣን #በእኛ_ልክ_ኢትዮጵያዊነት ላልገባቸወና ሆድ ለባሳቸው ማጭድ አናውሳቸው። ይልቁኑ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን፣ ከበቀል ይልቅ ይቅርታን፣ ከግጭት ይልቅ እርቅን፣ ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን፣ ከተስፋ መቁረጥ ይልቅ ብርታትን፣ ከጨለማ ይልቅ ብርሃንን በመምረጥ ጥላቻን እምቢ ማለት አለብን ብዬ አምናለሁ። በእኔ እምነት ኢትዮጵያ የሰላም፣ የፍትሕና የእርቅ አገር ልትሆን ትችላለች ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ፤ ይህም ከእኛ እንደምጅምር አልጠራጠርም። በመጨረሻም እግዚአብሔር አምላችን ፊታችን ባሉት ዓመታት፦ I. በአንድነት እንዲያጸናን II. በእውነት እንዲያቆመን፣ በቅድስና እንዲጠብቀን፣ በመንፈስ ቅዱስ እንዲመራን፣ III. ለኢትዮጵያ ሰላምን፣ እንዲሰጣት፣ IV. የወንጌል ብርሃንም ከኢትዮጵያ ወደ አሕዛብ ሁሉ እየበራ እንዲቅጣጠል ጸሎቴ ነው። በመጨረሻ፣ በአምላካችን ጸጋና በሁላችሁም ተሳትፎ የኢትዮጵያ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት 50ኛ ዓመት ማሳረጊያ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን በደስታ አሳውቃለህ። መጋቢ ደሳለኝ አበበ ኢጆ የህብረቱ የቦርድ ሰብሳቢ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
34
13
"#ወደ_ቀጣዩ_የታሪክ_ምዕራፍ_ስንሻገር_ራዕያችን_ግልጽ ነው፤ ይሄውም አንድም #ወንጌል፤ ሁለትም #ወንጌል፤ ሶስትም #ወንጌል መሆን ይኖርበታል።" መጋቢ ደሳለኝ አበበ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢና የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ይህን መልዕክት ያስተላለፉት በትላንትናው እለት በአዲስአበባ አራዳ ፓርክ በተካሄደው የህብረቱ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ የመዝጊያ ክብረበዓል ንግግራቸው ወቅት ነው። የህብረቱ የቦርድ ሰብሳቢ ሙሉ መልዕክት ከዚህ በታች ቀርቧል፦ የተከበራችሁ የቀድሞ መስራች አባቶች፤ የተከበራችሁ የቦርድ አባላት የተከበራችሁ የኢትዮጵያ የተለያዩ እምነት ተቋማት መሪዎችና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፤ የተከበራችሁ የዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ አጋር ድርጅቶች ተወካዮች፣ የተከበራችሁ የኢትዮጵያ አባል ቤተእምነት ፕሬዚዳንቶች፣ ዋና ጸሐፊዎች፣ መጋቢያን፣ የአህቶችና የወጣቶች አመራሮች፣ የተከበራችሁ የመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች እንዲሁም የተከበራችሁ ከመላው ኢትዮጵያ የመጣችሁ ውድ ወንድሞችና እህቶች፤ እናም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ስም ለሁላችሁንም ከልብ የሆነ የከበረ ሰላምታ አቀርባለሁ። መጽሐፍ ቅዱስ"እግዚአብሔር ቸር፥ ምሕረቱም ለዘላለም፥ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና።" (መዝ. 100፥5) ይላል። ከሁሉ አስቀድመን ሁሉን ቻይ ለሆነው ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና እናቀርባለን። ምክንያቱም ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ይህን ህብረት በጸጋው ጠብቆ፣ በመንፈሱ መርቶ፣ በፍቅሩ ደግፎ፣ ከብዙ ፈተናዎች አሳልፎ ዛሬ ለ50ኛው ዓመት ማሳረጊያ ክብረ በአል ስላደረስን እጅግ እናመሰግነዋለን። ይህ ቀን እንደ ሳሙኤልም "እስከዚህ ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል" ብለን በምስጋና የምንመሰክርበት ቀን ነው። ይህ የመዝጊያ ጉባኤ የፕሮግራም መጨረሻ ብቻ አይደለም፤ የ50 ዓመታት የአምላካችን ታማኝነትን በምስጋና የምናስብበት፣ ዛሬ በእጃችን ያለውን አደራ የምናረጋግጥበት፣ ወደ ሁለተኛው 50 ዓመታትም በእምነትና በተስፋ የምንገባበት የታሪክ ፌርማታ ነው። በዚህ አጋጣሚ የኢትዮጵያን ፌዴራል መንግሥትም ሆን የክልል መንግሥታትን እንዲሁም የአካባቢ አስተዳደሮችን እስካሁን ድረስ ላደረጋችሁልን ድጋፍ ከልብ እናመሰግናለን። በተለይ በተቻለ መጠን የሀይማኖት ነፃነት እንዲጠበቅ፣ የቤተ ክርስቲያናት አገልግሎት በሰላም እንዲከናወኑ፣ በተለያዩ መስኮችም ከእኛ ጋር በመተባበር ለሰጣችሁን አግልግሎት ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። እግዚአብሔርም ይባርካችሁ። ከውጭ አገር የመጣችሁ እንግዶቻችን፣ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት አጋር ድርጅቶች፣ በውጭ አገር የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ላለልፉት ዓመታት ከጎናችን የቆማችሁ ወዳጆቻችንን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን። በተለይ ደግሞ በጸሎት፣ በምክር፣ በሰው ኃይልና በሀብት ያደረጋችሁት አስተዋጽኦ በህብረታችን ታሪክ ለዘላለም ይታወሳል። ውድ ወንድሞችና እህቶች፣ የኢትዮጵያ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በ1968 ዓ.ም. በዘጠኝ መሥራች አባል ቤተ እምነቶች በትንሽ ጅማሬ የተመሠረተና ዛሬ የምናየውን እድገት ሊገምት በማይቻልበት ዘመን ቢሆንም ከእግዚአብሄር ቸርነት የተነሳ ዛሬ ህብረቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ አባል ቤተ እምነቶችን ያቀፈ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ምእመናንን የወክለ፣ በወንጌል ስብከት፣ በደቀ መዝሙርነት፣ በትምህርት፣ በልማት፣ በሰብዓዊ እርዳታ፣ በሰላም ግንባታና በማህበረሰብ አገልግሎት የሚታወቅ ታላቅ ህብረት ሆኗል። ይህ የአንድ ሰው ወይም የአንድ ቤተ እምነት ስኬት አይደለም፤ ይህ የእግዚአብሔር ጸጋ፣ የመሥራቾች እምነት፣ የአባል ቤተ እምነቶች ትብብር፣ የመሪዎች ታማኝነትና በምእመናን ጸሎት የተገኘ ፍሬ ነው። ስለዚህ የቀደሙትን መሪዎች፣ መሥራቾች፣ መጋቢያን፣ ሚስዮናውያን፣ በጸሎት የደገፉንን ሁሉ በክብር እናስታውሳለን ደግሞም እናመሰግናለን። ነገር ግን ባለፉት 50 ዓመታት ያገኘነው በረከት ዛሬ የሚገጥመንን ፈተና እንዳንዘነጋ ሊያደርገን አይገባም እላለሁ። #ዓለማችን በሐሰት ትምህርት፣ በሥነ ምግባር ውድቀት፣ በገንዘብ ፍቅር፣ በሥልጣን ፍላጎት፣ በብሔርና በፖለቲካ መከፋፈል፣ በማህበራዊ ሚዲያ በሚሰራጭ ጥላቻ እና ሰውን ከእግዚአብሔር ቃል በላይ በማስቀመጥ ፈተና እየተናወጠ ይገኛል። እኛ ግን የተጠራነው እና ህብረት የመስረትነው ጤናማ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትን ለመጠበቅ፣ በቅድስና ለመመላለስ፣ በእውነት ለመቆም፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ለማገልገል፣ ከሁሉ በላይ የሰበክነውን ለመኖር የኖርነወን ለመስበክ መሆኑን ለአፍታን ቢሆን መዘንጋት የለብንም፡፡ ለእውነተኛ ወንጌላዊ ክርስትና ትልቁ ኃይላችን የቁጥራችን ብዛት ሳይሆን በቃሉ እውነት ላይ የተመሰረተ አንድነታችን ነው። ስለዚህ ጎራ መፍጠር፣ የቤተ እምነት ፉክክር፣ የትውልድ ክፍተት፣ የብሔርና የፖለቲካ ተጽዕኖ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ያለገደብ የሚተላለፉ ጥላቻና ራስን የእውነት መለኪያ የማድረግ ስውር መርዝ የክርስቶስን አካል ያዳክማሉ እንጂ አንድነትን አይገነባም ፤ አንድነት በሌለበት ደግሞ ሰይጣን እንጂ እግዚአብሔር የለም። እኛ አገልጋዮች ለእግዚአብሔር ምስክሮች እንጂ ጠበቆች እንዳልሆንም ጠንቅቀን በማወቅ የወንጌል እውነትን ሳንለቅ ተባብረን ለክርስቶስ የአካል ህብረት ቅድሚያ እንድንሰጥ ማሳሰብም እውዳለሁ። በሌላ በኩል በተለይም ወጣቱን ትውልድ ተመልካች ብቻ እንዳይሆን ሆን ብለን በአመራር ማሳተፍ ይኖርብናል። ተተኪ የሚለውን ቃል በንግግራችንና በትምህርቶቻችን እያካተትን አዲሱን ትውልድ ነገን ናፋቂ ከከፋም ስልጣን ነጣቂ ማድረግ የለብንም ብዬ አምናለሁ። ምክንያቱም የነገው የቤተ ክርስቲያን እጣ ፋንታ ዛሬ ወጣት በሆኑና በአግባቡ ባላቀረብናቸው ወጣቶች እጅ እንጂ በእኛ እጅ አይደለችምና። እንዲሁም ሀገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዛሬ ሰላም፣ ፍትሕ፣ እርቅና ፈውስ ትፈልጋለች። በዚሁ አጋጣሚ በታሪካችን ለመጀምሪያ ጊዜ እየተደረገ ያለው ሐገራዊ ምክክር እንዲሳካ የህብረት ጸሎት ስላደረጋችሁ በራሴ እና በህብረቱ ቦርድ ስም የከበረ ምስጋናን ላቀርብላችሁ እወዳለሁ። ቤተክርስቲያን የመከፋፈል ድምፅ ሳትሆን የእርቅ ድምፅ መሆን አለባት። በጎሳ፣ በቋንቋ፣ በክልልና በፖለቲካ የሚከፋፈል ማንነት ሳይሆን፣ በክርስቶስ አንድነት የሚያገለግል ትውልድ መሆን ይኖርብናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ ቀጣዩ የታሪክ ምዕራፍ ስንሻገር ራዕያችን ግልጽ ነው፤ ይሄውም አንድም፤ ወንጌል ሁለትም፤ ወንጌል ሶስትም ወንጌል መሆን ይኖርበታል። በዚህ በዲጂታል ዘመን ክፉን ከመቃውም ጎን ለጎን ወንጌልን በጥበብ አንድ ቦታ ሆነን ወንጌልን ላልሰሙ ማህበረሰቦች ማድረስ፣ #እንችላለን! በመጽሐፍ ቅዱስ የተመሠረተ ደቀ መዝሙርነትን በማጠናከር፣ የክርስቶስን መልክ ለአለም ማጉላት #እንችላለን! በቅድስናና በግብረ ገብነት የተመሰከረ አመራር በመገንባት፣ አለምንና አለማዊነትን መኮነን #እንችላለን! ወጣቶችን ማ በትምህርት በማብቃት የነገዋን ቤተክርስቲያን ዛሬ መገንባት እንችላለን! ሰብዓዊ ድጋፍ በማድረግ ለተራቡ ጉርስ ለታረዙ ልብስ መሆን #እንችላለን!
1
14
Sin texto...
275
15
https://www.youtube.com/watch?v=V5GZV9E4T88&t=64s
109
16
Sin texto...
248
17
መቼም እግዚአብሔር ሐሳብ ፍለጋ የሰዎችን ዐሳብ አይፈትሽም። የሁሉን ሐሳብ ግን በአትኩሮት ይከታተላል፤ ከዘላለም ጊዜው፣ ጊዜ ሰጥቶ ይመለከታል፤ “እኔ እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደ መንገዱ፣ እንደ ሥራው ፍሬ ለመስጠት፣ ልብን እመረምራለሁ፤ የአእምሮንም ሐሳብ እፈትናለሁ” (ኤር 17፥10)። ጻድቅ አምላክ ስለሆነ ፍርድ አያጓድልም። ድርጊትን ከመነሻው (ሐሳብ) ጀምሮ ያያል። ለዚህም ነው እንደ ዘማሪው፣ "የአፌ ቃልና የልቤ ሐሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን" ብሎ መጸለይ የሚገባው።
250
18
Sin texto...
241
19
Sin texto...
42
20
Sin texto...
56