EFGBC GSFGBlC፡ በኢት/ሙሉ/ወ/አ/ቤ/ክ የጎሮ ሰፈራ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤ/ክ
Open in Telegram
ይህ የቴሌግራም ቻናል በኢትዮጽያ ሙሉ ወንጌል አማኛች ቤተክርያን የጎሮ ሰፈራ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ፣የሚከናወኑና የሚተገበሩ ፕሮግራምዎችን መከታተያ page ነው፡፡ this is official page of goro sefera full gospel believers church... If you have any question Contact: @Kirubel76 @pastor_sisay
Show more513
Subscribers
+224 hours
+37 days
+1830 days
Posts Archive
ሮሜ 16
17: ወንድሞች ሆይ፤ መለያየትን ከሚፈጥሩትና የተማራችሁትን ትምህርት በመቃወም በጒዞአችሁ መሰናክል ከሚያደርጉት እንድትጠነቀቁ አሳስባችኋለሁ፤ ከእነርሱም ራቁ።
18: እንደ እነዚህ ያሉት ሰዎች የሚያገለግሉት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሳይሆን፣ የራሳቸውን ሆድ ነው፤ በለሰለሰ አንደ በታቸውና በሽንገላ፣ የዋሆችን ያታልላሉ
Romans 16 አመት - ሮሜ
17: ወንድሞች ሆይ፤ መለያየትን ከሚፈጥሩትና የተማራችሁትን ትምህርት በመቃወም በጒዞአችሁ መሰናክል ከሚያደርጉት እንድትጠነቀቁ አሳስባችኋለሁ፤ ከእነርሱም ራቁ።
18: እንደ እነዚህ ያሉት ሰዎች የሚያገለግሉት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ሳይሆን፣ የራሳቸውን ሆድ ነው፤ በለሰለሰ አንደ በታቸውና በሽንገላ፣ የዋሆችን ያታልላሉ።
በምህረቱ በተሰጠን በአገልግሎታችን ተስፋ አንቆርጥም
👉አገልግሎታችን ለለውጥ መሆን ይሁን
" ነገር ግን ተነሣና በእግርህ ቁም፤ ስለዚህ እኔን ባየህበት ነገር ለአንተም በምታይበት ነገር አገልጋይና ምስክር ትሆን ዘንድ ልሾምህ ታይቼልሃለሁና።"
(የሐዋርያት ሥራ 26:16)
✔የምህረታችን ምስጥር ክርስቶስ ነው።
(2ኛቆሮ4)--1፤ ስለዚህ ምክንያት ምሕረት እንደ ተሰጠን መጠን ይህ አገልግሎት ስላለን አንታክትም።2፤ ነገር ግን የሚያሳፍረውን ስውር ነገር ጥለናልና በተንኮል አንመላለስም የእግዚአብሔርንም ቃል በውሸት አንቀላቅልም፤ እውነትን በመግለጥ ግን በእግዚአብሔር ፊት ለሰው ሕሊና ሁሉ ራሳችንን እናመሰግናለን።
🙏ከአገልግሎታችን ዙሪያ ማስወገድ ያለብን ነገሮች ምንድናቸው?
(1) የሚያሳፍር ስውር ነገር መጣል
(2ኛጢሞ2)-14፤ ይህን አሳስባቸው፥ በቃልም እንዳይጣሉ በእግዚአብሔር ፊት ምከራቸው፥ ይህ ምንም የማይረባ የሚሰሙትንም የሚያፈርስ ነውና። 15፤ የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ።
(2) ተንኮል የሆነ ነገር ማስወገድ
🙏#ተንኮል ማለት ምን ማለት ነው?
👉ተንኮል ማለት ሌላውን ሰው ለመጉዳት፣ ለማጥመድ፣ ለማታለል ወይም ከሱ ላይ ተጠቃሚ ለመሆን በማሰብ የሚፈጸም ስውር ዕቅድ ነው፡፡ ዋና መለያውና አላማው ክፉነት ነው። ተንኮል ማለት እውነትን በመደበቅ፣ በማጭበርበር ወይም በማታለል ሌላውን ተጎጂ የማድረግ ወይም ሌላኛውን ተጠቃሚ የማድረግ ድርጊት ነው።
🙏#የተንኮል ዓይነቶች
✔ ማታለል፦ አንድን ሰው ውሸት በመናገር ወይም እውነቱን በመደበቅ ሌላውን ማሳሳት።
✔ አድፍጦ ማጥቃት ፦ አንድን ሰው ሳያውቀው እና ሳይጠብቀው በሆነበት ላይ መውደቅ። (ለምሳሌ: በስውር ተከትሎ ተጎጂ በሚሆንበት ሰዓት ማጥቃት)
✔. ሴራ፦ከአንድ በላይ ሰዎች ተሰባስበው በሌላ ሰው ላይ ክፉ ነገር ለመሥራት በድብቅ ማቀድ። (ለምሳሌ: ሁለት ሰዎች ተማክረው ሌላውን ከሥራ ለማባረር ወሬ ማሰራጨት)
✔. ክደት፦ ወዳጅ ወይም ታማኝ መስሎ ሳለ በስተጀርባ በእሱ ላይ ክህደት መፈፀም። (ለምሳሌ: ጓደኛ መስሎ ሚስጥሩን ለጠላቱ መንገር)
✔ የፈተና ወጥመድ፦ አንድን ሰው ተሳስቶ መጥፎ ስራ እንድሰራ በማታለል፣ በምኞት በማጥመድ ላይ መጣል ነው። ይኸውም አንድን ሰው ክፉ ነገር እንዲሠራ በማበረታታት ከዚያም በኋላ ተጠያቂ ለማድረግ መፈለግ ነው፡፡
✔ሽንገላ፦ሆን ተብሎ የተዛባ እና አጥፊ ወሬ በማሰራጨት የሌላውን ሰው ስም ማጥፋት።
✔ ምቀኝነት፦ በምቀኝነት ምክንያት ሌላው እንዳይሳካለት ወይም እንዲጎዳ በማሰብ ተንኮል መፍጠር።
✔. ማንጎራጎር፦ ሁለት ሰዎችን ወይም ወገኖችን በማጋጨት እነሱ እንዲጣሉ እና እሱ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ።
✔ ውሸት ምስክር፦በአንድ ሰው ላይ ሆን ብሎ ውሸት በመመስከር ተጠያቂ እንዲሆን ማድረግ።
✔. ጥላ መከተል፦አንድን ሰው እሱ በማያውቀው መልኩ በድብቅ መከታተል እና ስለ እሱ መረጃ መሰብሰብ።
✔ ማጓደል እና ማፍረስ፦ የሌላን ሰው ሥራ፣ እቅድ ወይም ንብረት ሆን ተብሎ ማበላሸት።
✔ ጥቅም ላይ ማዋል፦ የሌላውን ድክመት፣ ድህነት ወይም ችግር በመጠቀም ከሱ ላይ ጥቅም ማግኘት።
👆" እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፥"(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4:14)
👆(1ኛ ጴጥ2)---1፤ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥
2-3፤ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።
(3)የእግ/ር ቃል ከውሸት ጋር አለማቀላቀል
" ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፥ እርስ በርሳችን ብልቶች ሆነናልና እያንዳንዳችሁ ከባልንጀሮቻችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4:25)
(4)እውነት በመግለጥ ለእግ/ር መታዘዝ
( ሮሜ 16)---17፤ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ፥ ከእነርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ፤18፤ እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።
የመልዕክቱ ማጠቃልያ
፦ አገልግሎታችን ለለውጥ ይሁን
(1)ዝማሬዎቻችን ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን
(2) ሕይወታችን ከአገልግሎታችን ይቅደም
(3)መድረኮቻችን እግ/ርን የሚያስከብር ይሁን
(4) ንግግራችን ተግባራችን በግልጽ ማሳየት
(5)ማለያውን ከመልበስ የበለጠ መንፈስ ቅዱስን መልበስን ማስቀደም
ዘኍልቍ 12:1-16
1 ሙሴ ኢትዮጵያዊት ሴት አግብቶ ነበርና ባገባት ኢትዮጵያዊት ምክንያት ማርያምና አሮን ይነቅፉት ጀመር።
2 እነርሱም፣ “ለመሆኑ እግዚአብሔር (ያህዌ) የተናገረው በሙሴ አማካይነት ብቻ ነውን? በእኛስ አልተናገረም?” ተባባሉ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ይህን ሰማ።
3 ሙሴ በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበር።
4 ወዲያው እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ አሮንንና ማርያምን፣ “ሦስታችሁም ውጡና ወደ መገናኛው ድንኳን ኑ” አላቸው፤ ሦስቱም ወጥተው ሄዱ።
5 ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) በደመና ዐምድ ወረደ፤ በድንኳኑም ደጃፍ ቆሞ አሮንንና ማርያምን ጠራቸው፤ ሁለቱም ወደ እርሱ በቀረቡ ጊዜ፣
6 እንዲህ አላቸው፤ “ቃሌን አድምጡ፤
“የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነቢይ በመካከላችሁ ቢኖር፣
በራእይ እገለጥለታለሁ፤
በሕልምም እናገረዋለሁ።
7 ለአገልጋዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም፤
እርሱ በቤቴ ሁሉ የታመነ ነው።
8 እኔ ከእርሱ ጋር የምነጋገረው ፊት ለፊት ነው፤
በግልጽ እንጂ በልዩ ዘይቤ አይደለም፤
እርሱ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) መልክ ያያል።
ታዲያ እናንተ አገልጋዬን ሙሴን
ትቃወሙ ዘንድ ለምን አልፈራችሁም?”
9 የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላያቸው ነደደ፤ እርሱም ትቷቸው ሄደ።
10 ደመናው ከድንኳኑ ላይ በተነሣ ጊዜ፣ እነሆ፤ ማርያም በለምጽ ተመታች፤ እንደ በረዶም ነጣች። አሮንም ወደ እርሷ ዘወር ሲል ለምጽ ወርሶአት አየ፤
11 ሙሴንም እንዲህ አለው፣ “ጌታዬ ሆይ፤ በስንፍናችን የሠራነውን ኀጢአት እባክህ አትቍጠርብን።
12 እርሷንም በእናቱ ማሕፀን ሳለ ሞቶ ግማሽ አካሉ ከተበላ በኋላ የተወለደ ጭንጋፍ መስላ እንድትቀር አታድርግ።”
13 ስለዚህም ሙሴ፣ “አምላክ (ኤል) ሆይ፤ እባክህ ፈውሳት” ብሎ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጮኸ።
14 እግዚአብሔርም (ያህዌ) ለሙሴ፣ “አባቷ እፊቷ ላይ ቢተፋባት እስከ ሰባት ቀን በኀፍረት መቈየት አይገባትምን? አሁንም ከሰፈር ውጭ ሰባት ቀን እንድትገለል አድርግ፤ ከዚያ በኋላ ግን ልትመለስ ትችላለች” ሲል መለሰለት።
15 ስለዚህም ማርያም ከሰፈር ውጭ ሰባት ቀን ተገለለች፤ ከዚያ እስክትመለስም ሕዝቡ ጕዞውን አልቀጠለም ነበር።
16 ከዚያ በኋላ ሕዝቡ ከሐጼሮት ተነሣ፤ በፋራን ምድረ በዳም ሰፈረ።
ዘኍልቍ 12:1-16
1 ሙሴ ኢትዮጵያዊት ሴት አግብቶ ነበርና ባገባት ኢትዮጵያዊት ምክንያት ማርያምና አሮን ይነቅፉት ጀመር።
2 እነርሱም፣ “ለመሆኑ እግዚአብሔር (ያህዌ) የተናገረው በሙሴ አማካይነት ብቻ ነውን? በእኛስ አልተናገረም?” ተባባሉ፤ እግዚአብሔርም (ያህዌ) ይህን ሰማ።
3 ሙሴ በምድር ላይ ካሉት ሰዎች ሁሉ ይልቅ እጅግ ትሑት ሰው ነበር።
4 ወዲያው እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ አሮንንና ማርያምን፣ “ሦስታችሁም ውጡና ወደ መገናኛው ድንኳን ኑ” አላቸው፤ ሦስቱም ወጥተው ሄዱ።
5 ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) በደመና ዐምድ ወረደ፤ በድንኳኑም ደጃፍ ቆሞ አሮንንና ማርያምን ጠራቸው፤ ሁለቱም ወደ እርሱ በቀረቡ ጊዜ፣
6 እንዲህ አላቸው፤ “ቃሌን አድምጡ፤
“የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነቢይ በመካከላችሁ ቢኖር፣
በራእይ እገለጥለታለሁ፤
በሕልምም እናገረዋለሁ።
7 ለአገልጋዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም፤
እርሱ በቤቴ ሁሉ የታመነ ነው።
8 እኔ ከእርሱ ጋር የምነጋገረው ፊት ለፊት ነው፤
በግልጽ እንጂ በልዩ ዘይቤ አይደለም፤
እርሱ የእግዚአብሔርን (ያህዌ) መልክ ያያል።
ታዲያ እናንተ አገልጋዬን ሙሴን
ትቃወሙ ዘንድ ለምን አልፈራችሁም?”
9 የእግዚአብሔር (ያህዌ) ቍጣ በላያቸው ነደደ፤ እርሱም ትቷቸው ሄደ።
10 ደመናው ከድንኳኑ ላይ በተነሣ ጊዜ፣ እነሆ፤ ማርያም በለምጽ ተመታች፤ እንደ በረዶም ነጣች። አሮንም ወደ እርሷ ዘወር ሲል ለምጽ ወርሶአት አየ፤
11 ሙሴንም እንዲህ አለው፣ “ጌታዬ ሆይ፤ በስንፍናችን የሠራነውን ኀጢአት እባክህ አትቍጠርብን።
12 እርሷንም በእናቱ ማሕፀን ሳለ ሞቶ ግማሽ አካሉ ከተበላ በኋላ የተወለደ ጭንጋፍ መስላ እንድትቀር አታድርግ።”
13 ስለዚህም ሙሴ፣ “አምላክ (ኤል) ሆይ፤ እባክህ ፈውሳት” ብሎ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጮኸ።
14 እግዚአብሔርም (ያህዌ) ለሙሴ፣ “አባቷ እፊቷ ላይ ቢተፋባት እስከ ሰባት ቀን በኀፍረት መቈየት አይገባትምን? አሁንም ከሰፈር ውጭ ሰባት ቀን እንድትገለል አድርግ፤ ከዚያ በኋላ ግን ልትመለስ ትችላለች” ሲል መለሰለት።
15 ስለዚህም ማርያም ከሰፈር ውጭ ሰባት ቀን ተገለለች፤ ከዚያ እስክትመለስም ሕዝቡ ጕዞውን አልቀጠለም ነበር።
16 ከዚያ በኋላ ሕዝቡ ከሐጼሮት ተነሣ፤ በፋራን ምድረ በዳም ሰፈረ።
የቤተክርስቲያን ጉዳይ፤ የእኔም፣ ያንተም፣ ያንቺም... የሁላችንም ነው!
ቤተክርስቲያን የአንድ ወገን ብቻ አይደለችም። የጥቂት አገልጋዮች ወይም የመሪዎች ብቻ ተደርጋ ልትወሰድ አይገባም። ቤተክርስቲያን የእኔም፣ ያንተም፣ ያንቺም፣ የሁላችንም የደኅንነት መጠለያ እና መንፈሳዊ ቤታችን ነች።
አንድ አካል ሙሉ ሊሆን የሚችለው እያንዳንዱ ብልት የራሱን ስራ ሲሰራ ብቻ ነው። እኔ ካልሰራሁ፣ አንተ ካልረዳህ፣ አንቺ ካልጸለይሽ... የቤተክርስቲያናችን አገልግሎት እንዴት ሙሉ ሊሆን ይችላል?
የቤተክርስቲያን መዳከምም ሆነ መጠንከር የሁላችንም ውጤት ነው። ስለዚህ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ ለአንዲት ቤተክርስቲያን ሁላችንም በጋራ እንቁም!
ኢያሱ 5:5-9
5 ከዚያ የወጡት ሰዎች ሁሉ ተገርዘው ነበር፤ ከግብፅ ከወጡ በኋላ በምድረ በዳ በጕዞ ላይ ሳሉ የተወለዱት ግን በሙሉ አልተገረዙም ነበር።
6 ግብፅን ለቀው በወጡ ጊዜ መሣሪያ ለመያዝ የደረሱ ወንዶች ሁሉ ለእግዚአብሔር ስላልታዘዙ፣ እነርሱ ሞተው እስኪያልቁ ድረስ፣ እስራኤላውያን በምድረ በዳ አርባ ዓመት ይንከራተቱ ነበር። እግዚአብሔር ለእኛ ይሰጠን ዘንድ ለአባቶቻቸው ቃል የገባላቸውን ያችን ማርና ወተት የምታፈስስ ምድር እንደማያዩአት ምሏልና።
7 ስለዚህ በእነርሱ ምትክ ወንዶች ልጆቻቸውን አስነሣ። እንግዲህ ኢያሱ የገረዛቸው እነዚህን ነበር፤ በጕዞ ላይ ሳሉ ባለመገረዛቸው ከነሸለፈታቸው ነበሩና።
8 ሕዝቡ ሁሉ ከተገረዙ በኋላ ቍስሉ እስኪሽር ድረስ እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ቈዩ።
9 ከዚያም እግዚአብሔር ኢያሱን፣ “እነሆ፤ ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ” አለው፤ ከዚህም የተነሣ የዚያ ቦታ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ጌልገላ ተባለ።
ኢያሱ 5:5-9
5 ከዚያ የወጡት ሰዎች ሁሉ ተገርዘው ነበር፤ ከግብፅ ከወጡ በኋላ በምድረ በዳ በጕዞ ላይ ሳሉ የተወለዱት ግን በሙሉ አልተገረዙም ነበር።
6 ግብፅን ለቀው በወጡ ጊዜ መሣሪያ ለመያዝ የደረሱ ወንዶች ሁሉ ለእግዚአብሔር ስላልታዘዙ፣ እነርሱ ሞተው እስኪያልቁ ድረስ፣ እስራኤላውያን በምድረ በዳ አርባ ዓመት ይንከራተቱ ነበር። እግዚአብሔር ለእኛ ይሰጠን ዘንድ ለአባቶቻቸው ቃል የገባላቸውን ያችን ማርና ወተት የምታፈስስ ምድር እንደማያዩአት ምሏልና።
7 ስለዚህ በእነርሱ ምትክ ወንዶች ልጆቻቸውን አስነሣ። እንግዲህ ኢያሱ የገረዛቸው እነዚህን ነበር፤ በጕዞ ላይ ሳሉ ባለመገረዛቸው ከነሸለፈታቸው ነበሩና።
8 ሕዝቡ ሁሉ ከተገረዙ በኋላ ቍስሉ እስኪሽር ድረስ እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ቈዩ።
9 ከዚያም እግዚአብሔር ኢያሱን፣ “እነሆ፤ ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ” አለው፤ ከዚህም የተነሣ የዚያ ቦታ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ጌልገላ ተባለ።
ኢያሱ 5:8-9
8 ሕዝቡ ሁሉ ከተገረዙ በኋላ ቍስሉ እስኪሽር ድረስ እዚያው በሰፈሩበት ቦታ ቈዩ።
9 ከዚያም እግዚአብሔር ኢያሱን፣ “እነሆ፤ ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ” አለው፤ ከዚህም የተነሣ የዚያ ቦታ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ጌልገላ ተባለ።
ዘፍጥረት 17:14
14 የሥጋ ሸለፈቱን ያልተገረዘ ማንኛውም ወንድ ኪዳኔን በማፍረሱ ከወገኖቹ ይወገድ።
ዘፍጥረት 17:14
14 የሥጋ ሸለፈቱን ያልተገረዘ ማንኛውም ወንድ ኪዳኔን በማፍረሱ ከወገኖቹ ይወገድ።”
https://kedusbible.com
የዘመናችን ሌላ እሳት "Strange Fire"
“የአሮንም ልጆች ናዳብና አብዩድ በየራሳቸው ጥናውን ወስደው እሳት አደረጉበት፥ በላዩም ዕጣን አኖሩበት፥ በእግዚአብሔርም ፊት እርሱ ያላዘዛቸውን ሌላ እሳት አቀረቡ።” (ዘሌ. 10:1-2
ለወንጌሉ እውነት እንግዳ የሆነ ልምምድ ሁሉ የእግዙአብሔርን ቁጣ ቀስቃሽ እንግዳ ወይም ሌላ ተግባር ነው። በመሰውያው ላይ ከእግዚአብሔር እሳት ሌላ ከራስ የሆነ እሳት ማቅረብ ጌታን ያስቆጣል ደግሞም ያስቀጣል። እግዚአብሔርንና ፈቃዱን ያልተከተለ ድፍረት የተሞላበት አካኼድ መቼም ቢሆን አይደገፍም። እግዚአብሔር በመንፈሱ በሚቀባበት ዘመን የምግብ ዘይት ለመንፈስ ቅዱስ ቅባትነት እንዲሆን በቡቱሌ ሰፍረው በመያዝ ሰዎችን ሲለቀልቁ መዋል የእግዚአብሔርን አሠራር በመተው የራስን አሠራርና ልምምድ ማቅረብን የሚያመለክት ሌላ ተግባር ነው።
እነዚህ ሁለቱ በስም የተጠቀሱት ካሕናት በእግዚአብሔር ዘንድ እውቅና እና ፈቃድ የሌለውን ድርጊት በተቀደሰ መሠውያው ይዘው መቅረባቸው እንዳስቀጣቸው ሁሉ ከቃሉ ያፈነገጠ የትኛውም የግል ልምምድ በእግዚአብሔር ዘንድ እንደሚያስቀጣ መናገር የወንጌሉ አገልጋዮች ተግባር መሆን አለበት ብዬ አምናለሁ። እነዚህ ክፍል ላይ የካሕኑ አሮን ልጆች ናዳብና አብዩድ በግዴለሽነት ይሁን በአላዋቂነት ወይም በድፍረት ባይታቅም በእግዚአብሔር መሰውያ ላይ እንግዳ እሳት ከራሳቸው አቀረቡ። በሌዋውያን ነባር ሥርዓት መሠረት ምን መሆን ነበረበት? እሳቱ ራሳቸው የሚያዋጡት ሳይሆን ከእግዚአብሔር የሚወጣ መሆን ነበረበት። ከፍ ብሎ ባለው ክፍል:- “እሳትም ከእግዚአብሔር ዘንድ ወጣ፥ በመሠዊያውም ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ስቡንም በላ፤ ሕዝቡም ሁሉ አይተው እልል አሉ፥ በግምባራቸውም ወደቁ።” (ዘሌ. 9:24) ይላል። ደንቡ ይህ ነበር። እነሱ ግን በተቃራኒው እሳት ከራሳቸው ወደ መሰውያው ይዘው ቀረቡ። የግል ልምምድ መሆኑ ነው።
እግዚአብሔር ቅዱስ አምላክ ነው። እውነተኛም ታማኝም ነው። እርሱን የሚያመልኩትና የሚያገለግሉት ሰዎች የልቡን ፈቃድና ሀሳብ ተከትለው ቃሉን መሠረት አድርገው እንዲያገለግሉት ይፈልጋል። “የትም ፍጪው ዱቀት አምጪው” አምላክ የለንም። ሥርዓቱንና ሕጉን ተከትለን እንድንኼድለት ስለሚፈልግ ውጤቱን ብቻ ሳይሆን ሂደቱንም ይከታተላል። ደስ እንዳለንና እንደተመቸን ስሜታችንን ተከትለን በራሳችን መንገድ ልባችንን አድምጠን ልምምዳችንን ገንብተን የምንፈጽመው ተግባር እግዚአብሔርን አያስደስተውም መቼም ቢሆን አያስከብረውምም። Unauthorized and unholy practice በእግዚአብሔር ፊት ሞገሥ የለውም። መድረኮቻችንን በችርቻሮ ዘይት ሞልተን እየሸቃቀጥን መድረኩንም ንጹህ አምልኮ በመንፈስ የሚቀርብበት ሳይሆን ምኞታችን የሚሳካበት አድርገን ስናበቃ “አሳስቦኝ ነው” ወይም ደግሞ “ጌታ ተናግሮኝ ነው” በሚሉ ማታለያዋች ብናሳምር የእግዚአብሔርን ቁጣ ከመቀስቀስ የሚከለክል አይሆንም። እግዚአብሔር የራሱን እሳት በሚልክበት መሠውያ የራስን እሳት ይዞ መቅረብ ነውር ነው።
የቤተክርስቲያን ጉዳይ፤ የእኔም፣ ያንተም፣ ያንቺም... የሁላችንም ነው!
ቤተክርስቲያን የአንድ ወገን ብቻ አይደለችም። የጥቂት አገልጋዮች ወይም የመሪዎች ብቻ ተደርጋ ልትወሰድ አይገባም። ቤተክርስቲያን የእኔም፣ ያንተም፣ ያንቺም፣ የሁላችንም የደኅንነት መጠለያ እና መንፈሳዊ ቤታችን ነች።
አንድ አካል ሙሉ ሊሆን የሚችለው እያንዳንዱ ብልት የራሱን ስራ ሲሰራ ብቻ ነው። እኔ ካልሰራሁ፣ አንተ ካልረዳህ፣ አንቺ ካልጸለይሽ... የቤተክርስቲያናችን አገልግሎት እንዴት ሙሉ ሊሆን ይችላል?
የቤተክርስቲያን መዳከምም ሆነ መጠንከር የሁላችንም ውጤት ነው። ስለዚህ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ ለአንዲት ቤተክርስቲያን ሁላችንም በጋራ እንቁም!
“ሞኞችን ሴቶች. . .”
ወደ ቤቶች ሾልከው እየገቡ፥ ኃጢአታቸው የተከመረባቸውን በልዩ ልዩ ምኞትንም የሚወሰዱትን ሁልጊዜም እየተማሩ እውነትን ወደ ማወቅ ሊደርሱ ከቶ የማይችሉትን ሞኞችን ሴቶች የሚማርኩ፥ ከእነዚህ ዘንድ ናቸውና።
2 ጢሞቴዎስ 3:6-7
አሳማን አጥበኸው ልክ እንደጨረሰክ ወደ ጭቃው ይሮጣል ሰለዚህ ሁሌ ታጥበው ከማይጸዱ አንዳንድ ሰዎች ራሳችሁን ጠብቁ
መዝሙር 10:7
7 አፉ መርገምን፣ ቅጥፈትንና ግፍን የተሞላ ነው፤
ሽንገላና ክፋት ከምላሱ ሥር ይገኛሉ
መዝሙር 10፡7 የክፉ ሰውን አንደበት (አፍና ምላስ) ይገልጻል።
አፉ መርገም፣ ቅጥፈት (ሐሰት) እና ግፍ የተሞላ ነው። ከምላሱ ሥር ደግሞ ሽንገላ (ተንኮል) እና ክፋት ይገኛሉ።
በአጭሩ፡ ክፉ ሰው በቃሉ መርገም፣ ሐሰት፣ ግፍ፣ ተንኮልና ክፋትን ይዘራል
መንፈሳዊ ድስፕሊን የሌለው አገልጋይ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል ፣ከመገንባት ይልቅ ማፍረስ ፣ከመሰብሰብ ይልቅ መበተን ከአንድነት ይልቅ መለያየት የሚያመጣ ራሱ ፈርሶ ሌሎችን የሚያፈርስ ነው
