en
Feedback
Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Open in Telegram

Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Show more
9 449
Subscribers
+724 hours
+227 days
+7730 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
June '26
June '26
+166
in 0 channels
May '26
+219
in 1 channels
Get PRO
April '26
+145
in 0 channels
Get PRO
March '26
+67
in 0 channels
Get PRO
February '26
+93
in 0 channels
Get PRO
January '26
+94
in 0 channels
Get PRO
December '25
+92
in 1 channels
Get PRO
November '25
+111
in 0 channels
Get PRO
October '25
+156
in 0 channels
Get PRO
September '25
+102
in 0 channels
Get PRO
August '25
+153
in 0 channels
Get PRO
July '25
+124
in 1 channels
Get PRO
June '25
+98
in 0 channels
Get PRO
May '25
+143
in 0 channels
Get PRO
April '25
+155
in 0 channels
Get PRO
March '25
+193
in 0 channels
Get PRO
February '25
+136
in 0 channels
Get PRO
January '25
+242
in 0 channels
Get PRO
December '24
+420
in 0 channels
Get PRO
November '24
+346
in 0 channels
Get PRO
October '24
+443
in 0 channels
Get PRO
September '24
+462
in 0 channels
Get PRO
August '24
+837
in 0 channels
Get PRO
July '24
+830
in 0 channels
Get PRO
June '24
+642
in 0 channels
Get PRO
May '24
+839
in 0 channels
Get PRO
April '24
+813
in 1 channels
Get PRO
March '24
+896
in 0 channels
Get PRO
February '24
+595
in 0 channels
Get PRO
January '24
+514
in 1 channels
Get PRO
December '23
+391
in 1 channels
Get PRO
November '23
+45
in 1 channels
Get PRO
October '23
+43
in 0 channels
Get PRO
September '23
+23
in 0 channels
Get PRO
August '23
+29
in 0 channels
Get PRO
July '23
+19
in 0 channels
Get PRO
June '23
+27
in 0 channels
Get PRO
May '23
+59
in 0 channels
Get PRO
April '23
+32
in 0 channels
Get PRO
March '23
+67
in 0 channels
Get PRO
February '23
+83
in 0 channels
Get PRO
January '23
+253
in 0 channels
Get PRO
December '22
+324
in 0 channels
Get PRO
November '22
+190
in 0 channels
Get PRO
October '22
+88
in 0 channels
Get PRO
September '22
+52
in 0 channels
Get PRO
August '22
+80
in 0 channels
Get PRO
July '22
+276
in 0 channels
Get PRO
June '22
+207
in 0 channels
Get PRO
May '22
+125
in 0 channels
Get PRO
April '22
+63
in 0 channels
Get PRO
March '22
+551
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
27 June+3
26 June+10
25 June+8
24 June+10
23 June+5
22 June+6
21 June+6
20 June+2
19 June+6
18 June+8
17 June+5
16 June+7
15 June+8
14 June+9
13 June+11
12 June+6
11 June+6
10 June+12
09 June+3
08 June+4
07 June+3
06 June+4
05 June+5
04 June+8
03 June+5
02 June+5
01 June+1
Channel Posts
በማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የተመዘገቡ ተሞክሮዎችን የመቀመርና የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ»ን ስኬታማ ተሞክሮ አጋርቷል EED (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ» ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ የተገኘውን ምርጥ ተሞክሮ ለአዲስ አበባ ከተማ የቆዳና ጨርቃጨርቅ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አካፈለ። የምርጥ ተሞክሮ ቅመራውን ያቀረቡት በልማት መ/ቤቱ የጨርቃጨርቅ ዲዛይን ባለሙያ የሆኑት አቶ ታሪኩ አበበ በሰጡት ማብራሪያ ሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የምታደርገውን የልማት ሽግግር ለማፋጠን የሞዴል ተቋማትን ተሞክሮ ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ለስላሳ አሻንጉሊቶችና ትራሶችን የሚያመርተው መርድ አበበ የአሻንጉሊት ስራ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ካሉት 30 ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ 90 በመቶ ያህሉን (27ቱን) ሴቶች በማድረግ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለአሻንጉሊትና ትራስ መሙያነትም መልሶ ጥቅም ላይ የዋለ ፋይበር (Recycled Fiber) በመጠቀም ለአካባቢ ተስማሚ አሰራርን ዘርግቷል። በተጨማሪም ድርጅቱ የተለያዩ ማበረታቻዎችንና ምቹ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የሠራተኞችን የመቅረት ምጣኔ ወደ 5 በመቶ ዝቅ ማድረግ ችሏል። ኢንተርፕራይዙ ከመንግሥት ያገኘውን የ40 ካሬ ሜትር ጠባብ የማምረቻ ሼድ በአግባቡ በመጠቀምና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ማሽኖችን በሥራ ላይ በማዋል ምርታማነቱን አሳድጓል። ያጋጠሙትን የጥሬ ዕቃ እጥረትና የዋጋ ንረት ችግሮች ለመፍታትም ጨርቅን በቀጥታ ከዱከም ምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በመግዛት የተረጋጋ የምርት ፍሰት የፈጠረ ሲሆን፣ ምርቶቹን ለማስተዋወቅና ሰፊ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ቲክቶክና ኢንስታግራም ያሉ የዲጂታል ማህበራዊ ገጾችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል። መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ ያሳየው ጠንካራ የአደረጃጀት፣ የጥራት ቁጥጥርና የገበያ ስልት በማንኛውም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ሊወሰድ የሚገባ የላቀ አርአያ መሆኑን አቶ ታሪኩ አስገንዝበዋል። በመልካም ተሞክሮ ልውውጥ መድረኩ  ላይ ከተሳተፉ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች መካከል የባህል አልባሳት አምራች የሆኑት ወ/ሮ ዘነበች ሰሎሜ እንደገለጹት የልምድ ልውውጥ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩባቸውን የአሰራር ክፍተቶች በግልጽ እንዲረዱ እንዳስቻላቸው ገልፀው ፤ በተለይም በስራ ገበታቸው ላይ ይገጥሟቸው የነበሩ ማነቆዎችን እንዴት መፍታት እንደሚችሉ አዳዲስ ግንዛቤዎችን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

2
+9
No text...
564
3
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢን+9
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በተቋሙ የማኔጅመንት አደራሽ በተካሄደው ውይይት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ከማቋቋምና ከማጠናከር አኳያ፣ ከስራ እድል ፈጠራ፣ ከተኪ ምርትና ከወጪ ምርት አንጻር እና እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ በውይይት መድረኩ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት እና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷባቸዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
725
4
ኢንተርፕራይዞች ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች በማምረት ተወዳዳሪነታቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተገለጸ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው! EED ሰኔ 15/2018 ዓ.ም   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማፋጠን የሚያግዝ የኢንተርፕራይዞች ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስፋፋት ስራ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደ። የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ እንደገለጹት፤ የአገር ውስጥ ኢንተርፕራይዞች በምርት ሂደታቸው ደረጃውን የጠበቁ አሰራሮችን መከተል እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። ይህም በአገር ውስጥ ገበያ ብቻ ሳይሆን ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ በመላክ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ቀደም ሲል የአገር ውስጥ ምርቶችን ከተወዳዳሪነት ለመጠበቅ ከፍተኛ ታሪፎችንና ታክሶችን መጣል እንደ አንድ አማራጭ ይወሰድ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም አገሪቱ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባል እየሆነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የፈለጉትን ያህል ታክስ መጣልና ምርቶችን መከልከል የማይቻልበት አሰራር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢንተርፕራይዞች ከወዲሁ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን በመጠቀምና ጥራትን በማስጠበቅ ራሳቸውን ለገበያ ውድድር ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል። አቶ አብዱልፈታ መንግስት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የሚሰጠውን የብድርና የፋይናንስ ድጋፍ እያሳደገ መሆኑን ገልጸው የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድኑ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚቀርበውን የብድር ድርሻ (ፖርትፎሊዮ) ካለው 12 በመቶ ወደ 20 በመቶ ለማሳደግ ወስኗል። ይሁን እንጂ ኢንተርፕራይዞች ይህንን የብድር አቅርቦት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላትና የተሳካ የቢዝነስ ፕላን ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። የልማት መስሪያ ቤቱም ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የቢዝነስ ፕላንና የባንክ ሰነዶችን በማዘጋጀት ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢንተርፕራይዞች ሌላኛው ትልቅ ማነቆ የግብዓት እጥረት መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን ለመቅረፍ ተቋማቱ ከጥሬ ዕቃ አምራቾች ጋር ዘላቂ የሆነ ቀጥታ ትስስር መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። በተለይም አብዛኛዎቹ ግብዓቶች ከአግሮ-ፕሮሰሲንግ ጋር የተያያዙና በአገር ውስጥ የሚመረቱ በመሆናቸው፣ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር የሚደረግ ቀጣይነት ያለው ትስስር ለኢንተርፕራይዞቹ ስኬት ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በመጨረሻም ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የቦታ፣ የፋይናንስና የግብዓት ችግሮች ለመፍታት መንግስት የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግና የተሳኩ ተሞክሮዎችን በማስፋፋት የዘርፉን ዕድገት ለማገዝ እንደሚሰራ አቶ አብዱልፈታ በንግግራቸው መደምደሚያ ላይ አስታውቀዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/Ethiopianenterprisedevelopment
733
5
+7
No text...
603
6
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳ
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉት አዳዲስ አሠራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ሲላመዱ ብቻ ነው። ​ለአምራቾች፦ ዛሬውኑ የምርት ሂደታችሁን ፈትሹ፤ ወጪን በመቀነስና ጥራትን በመጨመር ተወዳዳሪነታችሁን አሳድጉ! ​ለባለድርሻ አካላት፦ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ማሽነሪዎችንና ግብዓቶችን እንዲያገኙ በማገዝ ተወዳዳሪነታቸውን በጋራ እንደግፍ! ​የኢትዮጵያ ምርት በውድድር መድረክ ላይ በኩራት እንዲቆም ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ! መልካም የስራ ሳምንት! ​ #ኢትዮጵያ_ታምርት #ዓለም_አቀፍ_ውድድር #Competitiveness #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
671
7
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) የመጀመሪያ ዙር ግንባታ እየተገነባ ይገኛል። ​ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ለኢንተርፕራይዞች ሰፊ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የስልጠና እና የጥናትና ምርምር ድጋፍ የሚሰጥ በመሆኑ፣ የመጀመሪያ ዙር ግንባታው በተያዘለት እቅድ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
970
8
አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲያመርቱ በትኩረት እየተሰራ ነው!   · ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ነው   EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት (Product Certification) እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ የሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በተለያዩ ንዑስ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች እየተሰጠ ነው፡፡   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ምርታማነትና የጥራት ደረጃ በማሳደግ ኢንተርፕራይዞች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን እንዲተኩና ወጪ ምርቶችን እንዲያሳድጉ በማድረግ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡   ከእነዚህም ስራዎች አንዱ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ደረጃ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ በማስቻል በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲመረቱ ማድረግ ነዉ። በልማት መ/ቤቱ የአግሮ ፕሮሰሲንግ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ሰለሞን ግዛው እንደተናገሩት ስልጠናው የተዘጋጀው ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ ለማስቻል የሚያግዝ በሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በመስጠት የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማጎልበት ነው።   በተመረጡ ኢንተርፕራይዞች አሁን ያለውን የሥራ ሂደት እና የምርት ጥራት አያያዝ ሥርዓትን በተመለከተ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን የገለጹት መሪ ስራ አስፈጻሚው በዳሰሳ ጥናቱ የመረጃ አያያዝ ላይ ክፍተት በመታየቱ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡   መሪ ስራ አስፈጻሚው አክለውም እያንዳንዱ ተሳታፊ ኢንተርፕራይዝ እንደሚያመርተዉ የምርት አይነት ለራሱ ተስማሚ የሆነ ሰነድ እንዲያዘጋጅና ቀጣይ ሂደቶችን በማሟላት የምርት ሰርትፊኬሽን ማረጋገጫ እስከሚያገኙ ድረስ አስፈላጊውን እገዛም እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡   በአመራረትና በመሠረተ ልማት ላይ ያሉ የምርት ጥራት ክፍተቶችን ለይቶ በማወቅ እና አስፈላጊዉን ድጋፍ በመስጠት ኢንተርፕራይዞቹ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እውቅና ካለዉ አካል እንዲያገኙ የማመቻቸት ስራም እንደሚሰራ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል፡፡   በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አዳራሽ እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ከአዲስ አበባና ሸገር ከተማ የተውጣጡ በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በኬሚካልና ቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ 24 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት   ለተጨማሪ መረጃ፡- https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 000
9
+9
No text...
1 027
10
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት+8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው፡፡ የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ 7ኛው ጠቅላላዊ ሀገራዊ ምርጫ ነጻ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸው ለዚህም የህብረተሰቡ ሚና የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በምርጫ ሂደት ዉስጥ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላት መመስገን አለባቸው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ መድረኩ የተዘጋጀው ምርጫው በሰላም በመጠናቀቁ ለማመስገንና የምርጫው ውጤት እስከሚገለጽና አዲስ መንግስት እስኪመሰረት ድረስ እንደዜጋና እንደኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሠራተኛ ምን ይጠበቅብናል የሚለውን ለመወያየት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ ‹‹ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት›› በሚል መሪ ሃሳብ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎች ዙሪያ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ አቅርበዋል፡፡  #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
960
11
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 160
12
https://youtu.be/2AQ19JMrnx8?si=FFqzpZAAaHyfDK4A #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 472
13
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸምና በሌሎች ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ EED ሰኔ 2/2018 ዓ.ም የኢት+8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸምና በሌሎች ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ EED ሰኔ 2/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ ያለፉት 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም፣ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም፣ የቀጣይ በጀት ዓመት መነሻ እቅድ እና ሌሎች የዘርፉ ስራዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በተቋሙ የማኔጅመንት አዳራሽ በተካሄደው ውይይት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ የበጀት ዓመቱ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡ ለኢንሺየቲቩ ስኬት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጾ እንዲያደርግም ተጠይቋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የዋና ዋና ስራዎች በጀት አጠቃቀም ሪፖርት፣ የዘርፉ ቀጣይ ወራት እቅድና የስራ አካባቢን ምቹ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ውይይትና የጋራ መግባባት ተደርሷል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 591
14
https://youtu.be/_82DFVufJCA?si=bEoDjLFUnGiueodL #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 160
15
‹‹መሰረተ ሰፊ የኢንዱስትሪ ልማት ለመገንባት ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል!›› የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም
‹‹መሰረተ ሰፊ የኢንዱስትሪ ልማት ለመገንባት ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል!›› የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 176
16
https://www.youtube.com/watch?v=3A5F3LsrBKY   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 114
17
https://www.facebook.com/share/18tTvWWLxe/
1 139
18
https://www.youtube.com/watch?v=G_CyA8XBaww   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 275
19
እንቶት የፈሳሽ ሳሙና ========/////========== EED ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለምሳሌ እንቶት ፈሳሽ ሳሙና አምራች ማህበር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እነር መገር ወረዳ+6
እንቶት የፈሳሽ ሳሙና ========/////========== EED ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለምሳሌ እንቶት ፈሳሽ ሳሙና አምራች ማህበር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እነር መገር ወረዳ ሚቄ ከተማ የሚገኝ አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው። ኢንተርፕራይዙ በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ  በተፈጠረው ንቅናቄ በ5 ወጣቶች የተመሠረተና ለ27 ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረ የተለያዩ መጠን ያላቸውን ፈሳሽ ሳሙና የሚያመርት ኢንተርፕራይዝ ነው።   ‹‹እንቶት›› የጉራጌኛ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ተባብረን በሀገር እንስራ የሚል እንደሆነ የሚናገሩት የማህበሩ ሰብሳቢ ፈትለወርቅ ጸጋ በግብርና ስራ ያገኙትን ሀብት መነሻ በማድረግ እና ያለውን የገበያ ፍላጎት በመመስረት ስራውን እንደጀመሩ ይገልጻሉ፡፡ በቅርቡም የደረቅ ሳሙና ምርቶችን በማምረት ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ በዝግጅት ላይ እንደሆኑና የኤሌክትሪክ ሐይል አቅርቦት እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡   ለአካባቢው ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች ምርቶቻቸውን በስፋት እያቀረቡ መሆኑንና ከተጠቃሚዎችና ከባለሙያዎች የሚሰጣቸውን አስተያየትም እንደግብዓት በመጠቀም የምርቱን ጥራት ለመጠበቅ በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል፡፡   #አድራሻ፡ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን እነር መገር ወረዳ ሚቄ ከተማ  ☎️ስልክ፡  09 97 48 79 80/ 09 98 16 79 80 #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 369
20
አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ =======/////======== EED ግንቦት 27 ቀን 20178 ዓ.ም አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ ‹እናት ዱቄት› በሚል ስያሜ የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄ+6
አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ =======/////======== EED ግንቦት 27 ቀን 20178 ዓ.ም አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ ‹እናት ዱቄት› በሚል ስያሜ የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት እያመረተ የሚገኝና በሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ የሚገኝ  ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።   ኢንተርፕራይዙ በ4 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ  በተፈጠረው ንቅናቄ ስራ ጀምሯል። የእናት ዱቄት መስራች አንዋር ነስሮ እንደሚናገረው በአካባቢው ያለውን ክፍተትና የገበያ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደስራ መግባታቸውንና የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡   በአሁኑ ሰአት አጠቃላይ ሀብቱን ወደ 40 ሚልየን ብር ማሳደጉን የሚገልጸው አንዋር ለ9 ቋሚና  20 ለሚሆኑ ሰራተኞች ጊዚያዊ የስራ እድል መፍጠሩንም ይናገራል፡፡   በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች ምርታቸውን በስፋት እያቀረቡና በተጠቃሚዎች ዘንድ ተቀባይነታቸውንና የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡   በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት አማካኝነት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የወሰዷቸው ማሽኖቹ የማምረት አቅም በቀን 24 ቶን መሆኑን የሚገልጸው አንዋር የስራ ማስኬጃ እጥረትና የኤሌክትሪክ ሐይል መቆራረጥ በሚፈልጉት ደረጃ እንዳይሰሩ እንቅፋት እንደሆነባቸውና የአቅማቸውን 20 በመቶ ብቻ እየተጠቀሙ እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡   #አድራሻ፡ ሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ ☎️ስልክ፡ 0918999843   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #የገጠር_ኢንዱስትራላይዜሽን #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 207