en
Feedback
Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Open in Telegram

Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Show more
9 450
Subscribers
+224 hours
+267 days
+7530 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
June '26
June '26
+174
in 0 channels
May '26
+219
in 1 channels
Get PRO
April '26
+145
in 0 channels
Get PRO
March '26
+67
in 0 channels
Get PRO
February '26
+93
in 0 channels
Get PRO
January '26
+94
in 0 channels
Get PRO
December '25
+92
in 1 channels
Get PRO
November '25
+111
in 0 channels
Get PRO
October '25
+156
in 0 channels
Get PRO
September '25
+102
in 0 channels
Get PRO
August '25
+153
in 0 channels
Get PRO
July '25
+124
in 1 channels
Get PRO
June '25
+98
in 0 channels
Get PRO
May '25
+143
in 0 channels
Get PRO
April '25
+155
in 0 channels
Get PRO
March '25
+193
in 0 channels
Get PRO
February '25
+136
in 0 channels
Get PRO
January '25
+242
in 0 channels
Get PRO
December '24
+420
in 0 channels
Get PRO
November '24
+346
in 0 channels
Get PRO
October '24
+443
in 0 channels
Get PRO
September '24
+462
in 0 channels
Get PRO
August '24
+837
in 0 channels
Get PRO
July '24
+830
in 0 channels
Get PRO
June '24
+642
in 0 channels
Get PRO
May '24
+839
in 0 channels
Get PRO
April '24
+813
in 1 channels
Get PRO
March '24
+896
in 0 channels
Get PRO
February '24
+595
in 0 channels
Get PRO
January '24
+514
in 1 channels
Get PRO
December '23
+391
in 1 channels
Get PRO
November '23
+45
in 1 channels
Get PRO
October '23
+43
in 0 channels
Get PRO
September '23
+23
in 0 channels
Get PRO
August '23
+29
in 0 channels
Get PRO
July '23
+19
in 0 channels
Get PRO
June '23
+27
in 0 channels
Get PRO
May '23
+59
in 0 channels
Get PRO
April '23
+32
in 0 channels
Get PRO
March '23
+67
in 0 channels
Get PRO
February '23
+83
in 0 channels
Get PRO
January '23
+253
in 0 channels
Get PRO
December '22
+324
in 0 channels
Get PRO
November '22
+190
in 0 channels
Get PRO
October '22
+88
in 0 channels
Get PRO
September '22
+52
in 0 channels
Get PRO
August '22
+80
in 0 channels
Get PRO
July '22
+276
in 0 channels
Get PRO
June '22
+207
in 0 channels
Get PRO
May '22
+125
in 0 channels
Get PRO
April '22
+63
in 0 channels
Get PRO
March '22
+551
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
28 June+5
27 June+6
26 June+10
25 June+8
24 June+10
23 June+5
22 June+6
21 June+6
20 June+2
19 June+6
18 June+8
17 June+5
16 June+7
15 June+8
14 June+9
13 June+11
12 June+6
11 June+6
10 June+12
09 June+3
08 June+4
07 June+3
06 June+4
05 June+5
04 June+8
03 June+5
02 June+5
01 June+1
Channel Posts
በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ አማካኝነት በበጀት ዓመቱ በገጠር ወረዳዎች 605 አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተቋቋመዋል የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ ያለፉት ወራት አፈፆፀምን በተመለከተ ከክልል የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች ጋር ውይይት  ተካሂዷል EED  ሰኔ 20/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ2018 በጀት ዓመት የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ ያለፉት ወራት አፈፆፀምን በተመለከተ ከክልል የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች ጋር ውይይት አካሂዷል:: በመድረኩ ሪፖርቱን ያቀረቡት በልማት መ/ቤቱ የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ  አስተባባሪ የሆኑት አቶ አበበ በላይ እንደገለፁት  በበጀት ዓመቱ የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍን መሰረት በማድረግ 495 አነስተኛ እና 110 መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማቋቋም መቻሉን ገልፀዋል። ይህም በ2017 ዓ.ም ከነበረው ክንውን ጋር ሲነጻጸር እድገት የታየበት መሆኑን የገለፁት አቶ አበበ አዲስ በተቋቋሙት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አማካኝነትም ለ8,736 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር ተችሏል። እንደ አቶ አበበ ገለፃ አበረታች ስራዎች ቢሰሩም አፈጻጸሙን በተፈለገው ልክ እንዳይጓዝ ካደረጉ ተግዳሮቶች መካከል ስራውን በልዩ ትኩረት ያለመምራት፣ የመረጃ ጥራት ጉድለት ፣ ዘርፉን ለተቀላቀሉ ኢንተርፕራይዞች የመሰረተ ልማት አቅርቦት ችግር ትልቅ ማነቆ እንደሆነ በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በቀጣይ በገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ለሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች በልዩ ሁኔታ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበትን እድል ማመቻቸት እንደሚገባ አሳስበዋል:: እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢኒሽየቲቭ የአካባቢን እምቅ ሀብት መሰረት በማድረግ በገጠር አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን በማቋቋም የስራ እድል መፍጠር እና ድህነትን መቀነስ  ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

2
+9
No text...
211
3
"በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የክትትልና ድጋፍ ስርዓቱ ችግርን የሚፈታና ውጤታማ መሆን አለበት!" የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር፣ ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ EED ሰኔ 20/2018 ዓ.ም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚደረገው የክትትልና ድጋፍ ስራ፣ ችግሮችን በመለየት መፍትሄ የሚያመጣና ዘላቂ ውጤት ማስመዝገብ የሚያስችል ሊሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ አስታወቁ። ዶ/ር አለባቸው ይህን የገለፁት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት መነሻ ዕቅድ ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው:: ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ውስብስብ የሆኑ ተቋማዊ አሰራሮችን እና ጥምረቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረገው የክትትልና ድጋፍ ስራ ተቋማትን ከመደገፍ ባሻገር ከግንዛቤ መፍጠር ጀምሮ እስከ ማቋቋም እና የመጨረሻውን ምርት ለገበያ ማቅረብ ድረስ ባለው ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን መለየት ይጠበቅበታል ብለዋል። ተቋማት አቅም ያላቸውን በራሳቸው እንዲፈቱ፣ አቅም የሌላቸውን ደግሞ ከተለያዩ አካላት ጋር በማስተሳሰር ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግን እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል። የዘርፉ ስራ በብቸኝነት ሳይሆን በትብብር የሚከናወን መሆኑን የጠቆሙት  ዶ/ር አለባቸው በተለይም የፋይናንስ አቅርቦት፣ የግብዓት አቅርቦት እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። ትክክለኛ የክትትልና ድጋፍ ስራ ለመስራት ዝርዝር እቅድ አስፈላጊ ነው። በተለይም ለእያንዳንዱ የግብዓት ፍላጎት፣ የማምረቻ መሳሪያዎች እና የተቋማት አቅም በተደራጀ መንገድ ማቀድና መተግበር ይገባል። በአሁኑ ወቅት የክትትልና ድጋፍ ስራው እየተከናወነ ቢሆንም፣ በሪፖርት አቀራረብና በወቅታዊ መረጃ አያያዝ ላይ ክፍተቶች ይስተዋላሉ። ይህንን ለማስተካከል ዲጂታል አሰራርን መጠቀም እና የክትትል ስርዓቱን ዘመናዊ ማድረግ ቀዳሚ ስራ ሊሆን ይገባል ብለዋል። አለም አቀፍ የገበያ ሁኔታዎች እና የሎጂስቲክስ ችግሮች በዘርፉ ላይ የሚያሳድሩት ተጽዕኖ አለ። ይህም የዋጋ ንረትን ሊፈጥር ስለሚችል፣ ዘርፉን ከነዚህ ተግዳሮቶች ለመከላከል ስትራቴጂክ ድጋፍ ያስፈልጋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ማብራሪያ፣ በቀጣይ የክትትልና ድጋፍ ስራው የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግ: ግልጽ የሆነ የስራ መመሪያና የክትትል ስርዓት በመፍጠር ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል:: የተቀናጀ አሰራር ለመፍጠር ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ ያለው የዘርፉ አመራር እና ባለሙያዎች ለጋራ ግብ እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚገባ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ በማጠቃለያቸው፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክትትልና ድጋፍ ስራው ትኩረት ሰጥተው በመስራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
491
4
+9
No text...
450
5
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የበጀት ዓመቱ እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ በይፋ ተጀመረ EED ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋ+9
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የበጀት ዓመቱ እቅድ  አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ በይፋ ተጀመረ EED ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው:: የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጳውሎስ በርጋ በመድረኩ የመክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የውይይቱ መሠረታዊ ዓላማ በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራትን ጥንካሬዎችና ያጋጠሙ ማነቆዎችን ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።  በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት በጋራ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ ስልቶች ይቀመጣሉ ያሉት አቶ ጳውሎስ ይህም ተቋማዊ ግቦችን በብቃት ለማሳካት የሚያስችሉ ቁልፍ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ እንደሚረዳ ጠቁመዋል። በመድረኩ የበጀት አመቱ የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ይደረግበታል። እንደ ሀገር በቀጣይ ዓመት ሊከናወኑ በታቀዱ ተግባራት እና አዳዲስ የሥራ አቅጣጫዎች ላይ ጥልቅ ምክክር ይካሄዳል። በውይይት መድረኩ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት: የክልል የዘርፉ ቢሮዎች የሥራ ኃላፊዎች: የእቅድ ባለሙያዎችና የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢኒሺየቲቭ አስተባባሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
533
6
በማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የተመዘገቡ ተሞክሮዎችን የመቀመርና የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ»ን ስኬታማ ተሞክሮ አጋርቷል EED (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ» ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ የተገኘውን ምርጥ ተሞክሮ ለአዲስ አበባ ከተማ የቆዳና ጨርቃጨርቅ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አካፈለ። የምርጥ ተሞክሮ ቅመራውን ያቀረቡት በልማት መ/ቤቱ የጨርቃጨርቅ ዲዛይን ባለሙያ የሆኑት አቶ ታሪኩ አበበ በሰጡት ማብራሪያ ሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የምታደርገውን የልማት ሽግግር ለማፋጠን የሞዴል ተቋማትን ተሞክሮ ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ለስላሳ አሻንጉሊቶችና ትራሶችን የሚያመርተው መርድ አበበ የአሻንጉሊት ስራ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ካሉት 30 ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ 90 በመቶ ያህሉን (27ቱን) ሴቶች በማድረግ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለአሻንጉሊትና ትራስ መሙያነትም መልሶ ጥቅም ላይ የዋለ ፋይበር (Recycled Fiber) በመጠቀም ለአካባቢ ተስማሚ አሰራርን ዘርግቷል። በተጨማሪም ድርጅቱ የተለያዩ ማበረታቻዎችንና ምቹ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የሠራተኞችን የመቅረት ምጣኔ ወደ 5 በመቶ ዝቅ ማድረግ ችሏል። ኢንተርፕራይዙ ከመንግሥት ያገኘውን የ40 ካሬ ሜትር ጠባብ የማምረቻ ሼድ በአግባቡ በመጠቀምና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ማሽኖችን በሥራ ላይ በማዋል ምርታማነቱን አሳድጓል። ያጋጠሙትን የጥሬ ዕቃ እጥረትና የዋጋ ንረት ችግሮች ለመፍታትም ጨርቅን በቀጥታ ከዱከም ምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በመግዛት የተረጋጋ የምርት ፍሰት የፈጠረ ሲሆን፣ ምርቶቹን ለማስተዋወቅና ሰፊ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ቲክቶክና ኢንስታግራም ያሉ የዲጂታል ማህበራዊ ገጾችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል። መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ ያሳየው ጠንካራ የአደረጃጀት፣ የጥራት ቁጥጥርና የገበያ ስልት በማንኛውም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ሊወሰድ የሚገባ የላቀ አርአያ መሆኑን አቶ ታሪኩ አስገንዝበዋል። በመልካም ተሞክሮ ልውውጥ መድረኩ  ላይ ከተሳተፉ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች መካከል የባህል አልባሳት አምራች የሆኑት ወ/ሮ ዘነበች ሰሎሜ እንደገለጹት የልምድ ልውውጥ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩባቸውን የአሰራር ክፍተቶች በግልጽ እንዲረዱ እንዳስቻላቸው ገልፀው ፤ በተለይም በስራ ገበታቸው ላይ ይገጥሟቸው የነበሩ ማነቆዎችን እንዴት መፍታት እንደሚችሉ አዳዲስ ግንዛቤዎችን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
844
7
+9
No text...
778
8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢን+9
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በተቋሙ የማኔጅመንት አደራሽ በተካሄደው ውይይት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ከማቋቋምና ከማጠናከር አኳያ፣ ከስራ እድል ፈጠራ፣ ከተኪ ምርትና ከወጪ ምርት አንጻር እና እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ በውይይት መድረኩ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት እና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷባቸዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
968
9
ኢንተርፕራይዞች ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች በማምረት ተወዳዳሪነታቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተገለጸ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው! EED ሰኔ 15/2018 ዓ.ም   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማፋጠን የሚያግዝ የኢንተርፕራይዞች ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስፋፋት ስራ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደ። የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ እንደገለጹት፤ የአገር ውስጥ ኢንተርፕራይዞች በምርት ሂደታቸው ደረጃውን የጠበቁ አሰራሮችን መከተል እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። ይህም በአገር ውስጥ ገበያ ብቻ ሳይሆን ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ በመላክ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ቀደም ሲል የአገር ውስጥ ምርቶችን ከተወዳዳሪነት ለመጠበቅ ከፍተኛ ታሪፎችንና ታክሶችን መጣል እንደ አንድ አማራጭ ይወሰድ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም አገሪቱ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባል እየሆነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የፈለጉትን ያህል ታክስ መጣልና ምርቶችን መከልከል የማይቻልበት አሰራር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢንተርፕራይዞች ከወዲሁ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን በመጠቀምና ጥራትን በማስጠበቅ ራሳቸውን ለገበያ ውድድር ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል። አቶ አብዱልፈታ መንግስት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የሚሰጠውን የብድርና የፋይናንስ ድጋፍ እያሳደገ መሆኑን ገልጸው የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድኑ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚቀርበውን የብድር ድርሻ (ፖርትፎሊዮ) ካለው 12 በመቶ ወደ 20 በመቶ ለማሳደግ ወስኗል። ይሁን እንጂ ኢንተርፕራይዞች ይህንን የብድር አቅርቦት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላትና የተሳካ የቢዝነስ ፕላን ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። የልማት መስሪያ ቤቱም ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የቢዝነስ ፕላንና የባንክ ሰነዶችን በማዘጋጀት ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢንተርፕራይዞች ሌላኛው ትልቅ ማነቆ የግብዓት እጥረት መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን ለመቅረፍ ተቋማቱ ከጥሬ ዕቃ አምራቾች ጋር ዘላቂ የሆነ ቀጥታ ትስስር መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። በተለይም አብዛኛዎቹ ግብዓቶች ከአግሮ-ፕሮሰሲንግ ጋር የተያያዙና በአገር ውስጥ የሚመረቱ በመሆናቸው፣ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር የሚደረግ ቀጣይነት ያለው ትስስር ለኢንተርፕራይዞቹ ስኬት ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በመጨረሻም ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የቦታ፣ የፋይናንስና የግብዓት ችግሮች ለመፍታት መንግስት የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግና የተሳኩ ተሞክሮዎችን በማስፋፋት የዘርፉን ዕድገት ለማገዝ እንደሚሰራ አቶ አብዱልፈታ በንግግራቸው መደምደሚያ ላይ አስታውቀዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/Ethiopianenterprisedevelopment
796
10
+7
No text...
690
11
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳ
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉት አዳዲስ አሠራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ሲላመዱ ብቻ ነው። ​ለአምራቾች፦ ዛሬውኑ የምርት ሂደታችሁን ፈትሹ፤ ወጪን በመቀነስና ጥራትን በመጨመር ተወዳዳሪነታችሁን አሳድጉ! ​ለባለድርሻ አካላት፦ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ማሽነሪዎችንና ግብዓቶችን እንዲያገኙ በማገዝ ተወዳዳሪነታቸውን በጋራ እንደግፍ! ​የኢትዮጵያ ምርት በውድድር መድረክ ላይ በኩራት እንዲቆም ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ! መልካም የስራ ሳምንት! ​ #ኢትዮጵያ_ታምርት #ዓለም_አቀፍ_ውድድር #Competitiveness #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
750
12
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) የመጀመሪያ ዙር ግንባታ እየተገነባ ይገኛል። ​ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ለኢንተርፕራይዞች ሰፊ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የስልጠና እና የጥናትና ምርምር ድጋፍ የሚሰጥ በመሆኑ፣ የመጀመሪያ ዙር ግንባታው በተያዘለት እቅድ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 023
13
አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲያመርቱ በትኩረት እየተሰራ ነው!   · ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ነው   EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት (Product Certification) እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ የሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በተለያዩ ንዑስ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች እየተሰጠ ነው፡፡   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ምርታማነትና የጥራት ደረጃ በማሳደግ ኢንተርፕራይዞች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን እንዲተኩና ወጪ ምርቶችን እንዲያሳድጉ በማድረግ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡   ከእነዚህም ስራዎች አንዱ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ደረጃ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ በማስቻል በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲመረቱ ማድረግ ነዉ። በልማት መ/ቤቱ የአግሮ ፕሮሰሲንግ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ሰለሞን ግዛው እንደተናገሩት ስልጠናው የተዘጋጀው ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ ለማስቻል የሚያግዝ በሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በመስጠት የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማጎልበት ነው።   በተመረጡ ኢንተርፕራይዞች አሁን ያለውን የሥራ ሂደት እና የምርት ጥራት አያያዝ ሥርዓትን በተመለከተ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን የገለጹት መሪ ስራ አስፈጻሚው በዳሰሳ ጥናቱ የመረጃ አያያዝ ላይ ክፍተት በመታየቱ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡   መሪ ስራ አስፈጻሚው አክለውም እያንዳንዱ ተሳታፊ ኢንተርፕራይዝ እንደሚያመርተዉ የምርት አይነት ለራሱ ተስማሚ የሆነ ሰነድ እንዲያዘጋጅና ቀጣይ ሂደቶችን በማሟላት የምርት ሰርትፊኬሽን ማረጋገጫ እስከሚያገኙ ድረስ አስፈላጊውን እገዛም እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡   በአመራረትና በመሠረተ ልማት ላይ ያሉ የምርት ጥራት ክፍተቶችን ለይቶ በማወቅ እና አስፈላጊዉን ድጋፍ በመስጠት ኢንተርፕራይዞቹ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እውቅና ካለዉ አካል እንዲያገኙ የማመቻቸት ስራም እንደሚሰራ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል፡፡   በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አዳራሽ እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ከአዲስ አበባና ሸገር ከተማ የተውጣጡ በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በኬሚካልና ቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ 24 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት   ለተጨማሪ መረጃ፡- https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 034
14
+9
No text...
1 073
15
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት+8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራርና ሠራተኞች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው፡፡ የውይይት መድረኩን የከፈቱት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ 7ኛው ጠቅላላዊ ሀገራዊ ምርጫ ነጻ፣ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ በሆነ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸው ለዚህም የህብረተሰቡ ሚና የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በምርጫ ሂደት ዉስጥ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላት መመስገን አለባቸው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ መድረኩ የተዘጋጀው ምርጫው በሰላም በመጠናቀቁ ለማመስገንና የምርጫው ውጤት እስከሚገለጽና አዲስ መንግስት እስኪመሰረት ድረስ እንደዜጋና እንደኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ሠራተኛ ምን ይጠበቅብናል የሚለውን ለመወያየት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ ‹‹ከምርጫ ድል ማግስት፣ ጠንካራ መንግስት›› በሚል መሪ ሃሳብ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስራዎች አፈጻጸምና የድህረ ምርጫ ስራዎች ዙሪያ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ አቅርበዋል፡፡  #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
981
16
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
#ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 186
17
https://youtu.be/2AQ19JMrnx8?si=FFqzpZAAaHyfDK4A #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 472
18
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸምና በሌሎች ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ EED ሰኔ 2/2018 ዓ.ም የኢት+8
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸምና በሌሎች ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ EED ሰኔ 2/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ ያለፉት 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም፣ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም፣ የቀጣይ በጀት ዓመት መነሻ እቅድ እና ሌሎች የዘርፉ ስራዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በተቋሙ የማኔጅመንት አዳራሽ በተካሄደው ውይይት የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢንሺየቲቭ የበጀት ዓመቱ 11 ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡ ለኢንሺየቲቩ ስኬት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጾ እንዲያደርግም ተጠይቋል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 አፈጻጸም ሪፖርት፣ የዋና ዋና ስራዎች በጀት አጠቃቀም ሪፖርት፣ የዘርፉ ቀጣይ ወራት እቅድና የስራ አካባቢን ምቹ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ውይይትና የጋራ መግባባት ተደርሷል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 591
19
https://youtu.be/_82DFVufJCA?si=bEoDjLFUnGiueodL #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 160
20
‹‹መሰረተ ሰፊ የኢንዱስትሪ ልማት ለመገንባት ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል!›› የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም
‹‹መሰረተ ሰፊ የኢንዱስትሪ ልማት ለመገንባት ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ትኩረት መስጠት ይገባል!›› የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 176