cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Show more
Advertising posts
5 883
Subscribers
+2524 hours
+2407 days
+78530 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
Addis Zemen
9945Loading...
02
9750Loading...
03
“የአፋር ክልል የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ሊዝ አክሲዮን ማሕበርን ለማቋቋም ያሳየው ተነሳሽነት ለክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዕድገት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው” አቶ አብዱልፈታ የሱፍ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋ/ ዳይሬክተር EED ግንቦት 21 2016 ዓ.ም በአፋር ክልል በም/ ርዕስ መስተዳደር የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ ክቡር አቶ አሊ መሐመድ የሚመራ ቡድን ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር የሊዝ ፋይናንስ አክሲዮን ማሕበርን ለማቋቋም የሚያስችል ውይይት አደረገ። የካፒታል ዕቃ ሊዝ ፋይናንስ አክሲዮን ማሕበራት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የማሽነሪና የቴክኖሎጂ ችግር ለመቅረፍ በብድር መልክ ለማቅረብ የተቋቋሙ ሲሆን ይህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማነቱ በግልፅ የታየ ሆኗል፡፡ ነገር ግን አክሲዮን ማሕበራቱ በ4 ክልሎችና በ1 ከተማ አስተዳደር ብቻ የተቋቋሙ በመሆኑ ሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ደረጃ ከዘርፉ ተጠቃሚ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ የአፋር ክልልም ይህ አክሲዮን ማሕበር ካልተቋቋመባቸው ክልሎች አንዱ እንደመሆኑ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች በተሟላ መልኩ የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ተስኖት ቆቷል፡፡ ይህን ክፍተት የተረዳው ክልሉም በክልሉ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሚመራ ቡድን አቋቁሞ በክልሎች ያለውን የአክሲዮን ማሕበራቱን አፈፃጸም ሲገመግምና ሲያጠና ቆይቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር አክሲዮን ማሕበሩን ለማቋቋም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙርያ ለመምከር ቡድኑ በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ተገኝቶ ውይይት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፉ በመድረኩ እንደተናገሩት በካፒታል ዕቃ ሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ የሆኑ ክልሎችና አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ ስራ እየሰሩ እንደሆነ ጠቁመው በተመሳሳይ መልኩ የማይጠቀሙ ክልሎች ደግሞ ዝቅተኛ አፈፃፃም እንዳላቸው ም/ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። አቶ አብዱልፈታ አክለውም መንግስት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች የሚሰጠውን ድጋፎች በወጥነት በመስጠት በሁሉም ክልሎች ያሉ ኢንተርፕራይዞች ተቀራራቢ ውጤት እንዲያመጡ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሊዝ ፋይናንስ አቅራቢዎች ኢንተርፕራይዞችን እየወለዱ የሚያሳድጉ ተቋማት እንደመሆናቸው ከዚህ ቀደም ያልተቋቋሙባቸው ክልሎች እንዲያቋቁሙ ምክረሀሳብ በማቅረብና አስፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን የተናገሩት ም/ ዋና ዳይሬክተሩ የአፋር ክልል የሊዝ ፋይናንስን ለማቋቋም ላሳዩት ተነሳሽነት አመስግነዋል። በክልሉም የሊዝ ፋይናንስ እንዲቋቋምና ያሉ አምራች ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የልማት መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደረጉ አቶ አብዱልፈታ ተናግረዋል።
7660Loading...
04
በአንድ ጊዜ ቻርጅ ለ1 አመት የሚያገለግል ድምፅ አልባ ጄኔሬተር የፈጠረው የወለጋው ፌዴሳ ሹማ ‹ ግንቦት 21/ 2016 ዓ.ም ፌዴሳ ሹማ ተወልዶ ያደገው በቄለም ወለጋ ሲሆን፣ በከተማው ውስጥ በኤሌክትሪክ ጥገና ሙያው ይታወቃል፡፡ ይህን የኤሌክትሪክ ጥገና ሥራውን የመብራት መጥፋት እና መቆራረጥ ብዙ ጊዜ አስተጓጉሎበታል። "ችግር ብልሃትን ይወልዳል" እንዲሉ ወጣቱ ሥራውን በተደጋጋሚ ላስተጓጎለበት ችግር መላ መዘየድ እንዳለበት አሰበ፤ አስቦም ወደ ተግባር ገባ። ከብዙ ጥረት በኋላ አንድ ጊዜ ቻርጅ ተደርጎ እስከ አንድ ዓመት ድረስ አገልግሎት መስጠት የሚችል ቴክኖሎጂ እውን አደረገ። ወጣት ፌዴሳ ሹማ በኃይል አማራጭ ዘርፍ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ የታመነበት መሣሪያ የፈጠራ ባለቤት ነው፡፡ ቴክኖሎጂው የመብራት አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ለሞባይል፣ ለቴሌቭዥን፣ ለፍሪጅ እና የትኛውንም ዓይነት የኤሌክትሮኒክስ መጠቀሚያዎችን ቻርጅ የሚያደርግ፣ የሚያንቀሳቅስ እና በገመድ እና ገመድ አልባ ቴክኖሎጂ መጠቀም እንዲቻል ተደርጎ የተሠራ ነው። አንዴ የያዘውን ኃይል ደጋግሞ እያደሰ (recycling) ራሱን ቻርጅ ከማድረግ አልፎ ለረዥም ጊዜ ኃይል ማመንጨት የሚችለው ይህ ቴክኖሎጂ በሀገራችን ብቻ ሣይሆን ምን አልባትም በዓለማችን ላይ በኃይል አማራጭ ዘርፍ አብዮት መፍጠር እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል። ከ300 ዋት ጀምሮ እንደ ተጠቃሚው አቅም እና ፍላጎት የሚዘጋጀው ይህ ድምፅ አልባ ጄኔሬተር አንድ ጊዜ ቻርጅ ተደርጎ ከአንድ ዓመት በላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚችል ነው ወጣቱ ያረጋገጠው።
9645Loading...
05
አምራች ኢንተርፕራይዞች የሽግግር ስትራቴጂ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ እድገትን መሰረት ያደረገ ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው EED ግንቦት 20 /2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር ስትራቴጂ ላይ ለአማራ ክልል የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በዘርፉ ዙሪያ  ልምድ ያላቸው አቶ ቤዛወርቅ ከተማ ስትራቴጂው የኢንተርፕራይዞችን እድገት መሰረት ያደረጉ ድጋፎችን በመስጠት ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር እንዲያደርጉ በማስቻል ኤክስፖርትን ማስፋትና ተኪ ምርትን ማበራከት የሚያስችል መሆኑን በገለፃቸው አብራርተዋል። ስትራቴጂው በዘርፉ የተሻለ ልምድ ያላቸውን የህንድ፣ የቬትናምና የኬንያ ሀገሮችን ተሞክሮ ያካተተ መሆኑን ያብራሩት አቶ ቤዛወርቅ እነዚህ ሀገራት የዘርፉን ልማት  በክላስተር ልማት፣ በፋይናንስ አቅርቦት፣ በሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦትና በገበያ ትስስር ትኩረት ሰጥተው የሚደግፉና ሌሎች ማበረታቻዎችን የሚያቀርቡ መሆናቸውንም አመላክተዋል። ስትራቴጂው እንዲተገበር የዘርፉ አስፈፃሚ አካል አውቆና ተገንዝቦ በአግባቡ መተግበርና መምራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። በዚህም በ10 ዓመቱ በዘርፉ የተያዘውን የ5 ሺህ ተወዳዳሪና ውጤታማ ኢንተርፕራይዞች ሽግግር ማሳካት የሚቻል መሆኑ በስልጠናው ግንዛቤ ተወስዷል። #ኢትዮጵያ_ታምርት   #እኛም_እንሸምት
9040Loading...
06
በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ፍኖተ ካርታ ላይ ለአማራ ክልል የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ EED ግንቦት 19 /2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ለአማራ ክልል የዘርፍ በአመራርና ባለሙያዎች በ10 ዓመቱ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ልማት ፍኖተ ካርታ ላይ ስልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በዘርፉ ልምድ ያላቸው አቶ ቤዛወርቅ ከተማ የ 10 ዓመቱ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ፍኖተ ካርታ አምራች ኢንተርፕራይዞችን በፋይናንስና በመሰረተ ልማት፣ በስልጠና፣ በገበያ ትስስርና መሰል ድጋፎች በመደገፍ ተወዳዳሪና ውጤታማ ኢንተርፕራይዞች እንዲፈጠሩና ዘርፉ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችል መሆኑን በገለፃቸው አስረድተዋል። 10 አመቱ ፍኖተ ካርታ እንዲተገበር የዘርፉ አስፈፃሚና ድጋፍ ሰጪ አካላት ተቀናጅቶና ተቀራርቦ መስራትን ይጠይቃል ያሉት አቶ ቤዛወርቅ ፍኖተ ካርታው በቀጣይ 10 ዓመት 62 ሺህ አዲስ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን መፍጠር ፤ 2 ነጥብ 16 ሚሊየን አዳዲስ የስራ እድል መፍጠር ፤ 468 ሚሊየን ዶላር ከወጪ ንግድ ማግኘት ፤ 5 ሺህ ኢንተርፕራይዞችን የደረጃ ሽግግር እንዲደርጉ አሁን ያለውን 50 ፐርሰንት አማካይ የማምረት አቅም አጠቃቀም ወደ 85 ማድረስ የሚያስችል መሆኑንም አመላካተዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት ፣ #እኛም_እንሸምት
1 1300Loading...
07
ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች በሚሰጥ የመንግስት የድጋፍ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከቻይና የተቀመረ ምርጥ ተሞክሮን ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በስልጠና ኢንዲስፋፋ አደረገ EED ግንቦት 19/2016  (መቐለ) ለሶስተኛ ቀን በቀጠለው ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና በውጤታማ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርራይዞች ድጋፍ አሰጣጥ ዙሪያ ከቻይና የተቀመረ ምርጥ ተሞክሮን ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ለማስፋት ስልጠና በመስጠት ቀጥሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አቅም ግንባታ ባለሙያ አቶ መኮንን ሞላ ስልጠናውን ሲሰጡ እንደገለፁት ቻይና በአለም ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚዋ ሁለተኛ ደረጃ የያዘችው ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርቷ 60% የሚሆነው በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርት ነው፡፡ ይህም ዘርፉን ለመምራት የምትጠቀምበት ፖሊሲ ውጤታማ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ በቻይና የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማትን ከብሄራዊና ከማህበራዊ ስትራቴጂክ ልማት ጋር ተሰናስሎ ታቅዷል፡፡ በተጨማሪም ወደ ዘርፉ መቀላቀል ፍላጎት ላላቸው የግል ባለሀብቶች ብድር ያለ ወለድ በማመቻቸትና ሌሎች መሰረተልማቶችን በማመቻቸት መልካም የኢንቨስትመንት ከባቢን መፍጠር ችለዋል፡፡ ቻይና አንድ ምርት ለአንድ ከተማ የሚል ፖሊሲ ትከተላለች፡፡ ይህ ማለት እያንዳንዱ ከተማ ያለውን ፀጋ በመለየት ከገበያ ፣ከሰው ሀብት እና ከሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር በማስተሳሰር ትኩረቱን በአንድ ምርት ላይ ብቻ  ያደረገ ከተማ መፍጠር ማለት ነው፡፡ አንድ ምርት ለአንድ ከተማ ፅንሰ-ሀሳብ ተመሳሳይ ምርት የሚያመርቱ ኢንተርፕራይዞች በአንድ ከተማ ተሰባስበው ስለሚገኙ ለምርት የሚያስፈልጋቸውን መሰረተ ልማትና ግብዓት አንድላይ ለማቅረብ ከማስቻሉም ባሻገር በምርት ሂደት ለሚያጋጥሙ ችግሮችን በቶሎ ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ በዚህ ረገድ የቻይናዋ ጉዋንዢንግ በኬብል ምርት፣ ሻንጊዝ በሲልኪ(በሃር) ምርት እንዲሁም ይኢ-ዉ በጅምላ ንግድ የሚታወቁ ከተሞች ናቸው፡፡ ቻይና ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የምትሰጠውን የብድር አቅርቦት የወለድ ምጣኔው በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ በተጨማሪም በየከተማው ብዙ ቅርንጫፍ ያላቸውና በልዩ ሁኔታ ኤክስፖርትን የሚደግፉ  እንደ የቻየይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ (Exim bank) ፣ የቻይና ኤክስፖርት ብድር ኢንሹራንስ ህብረት (Sinosure) ፣ የቻይና ልማት ባንክ እንዲሁም የቻይና ግብርና ልማት ባንክ የመሳሰሉ ተቋማት አሏቸው፡፡            የቻይና መንግስት ከአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለሚፈፀም ግዢ ቅድሚያ ከመስጠቱም ባሻገር  ለዘርፉ የገበያ አስተዳደር ISO9001 ጥራት ደረጃን የሚያሟላ የተለየ የግብይት ስርዓት በመዘርጋቱ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተፈጠረላቸውን የገበያ ዕድል በመጠቀም በአጭር ግዜ ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል ችለዋል፡፡  ቻይና "የለም" የሚባል ነገር የለም ፡፡ የትኛውንም አይነት ምርት በሚፈለገው መጠንና ጥራት ማቅረብ የሚችል የላቀ የስራ ባህል ያላቸው ህዝቦቿ ለእድገቷ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል፡፡ የቻይና ዜጎች በስራ ባህላቸው ብቻ ሳይሆን የሀገራቸውን ምርት ብቻ በመጠቀምም በአለም ተወዳዳሪ የሌላቸው ሀገር ወዳድ ህዝቦች ናቸው፡፡ በመጨረሻም ከትግራይ ክልል የተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክልሉን ተሞክሮ በማቅረብ ከቻይና ተሞክሮ ያገኙትን ዕውቀት ለቀጣይ ስራቸው ግብአት በማድረግ እንደሚጠቀሙበት ገልፀዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት ፣ #እኛም_እንሸምት
9150Loading...
08
Media files
8450Loading...
09
ለአስፈፃሚው አካል የሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተመላከተ EED ግንቦት 19/2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት መደገፍ በሚያስችሉ ስትራቴጂክ ሰነዶች ዙሪያ ለአማራ ክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በባህርዳርና በኮምቦልቻ ከተሞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ በባህርዳር ከተማ እየተሰጠ ያለውን ስልጠና ያስጀመሩት የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ምክትል ሃላፊ ተወካይ አቶ ካሳሁን ታዬ ስልጠናውን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አምራች ዘርፉ ውጤታማ እንዲሆን ከክልሉ ጋር ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህ ስልጠናም ዘርፉን በውጤታማነት መደገፍ በሚያስችሉ በልዩ ልዩ ስትራቴጂክ ሰነዶች ላይ ኢንተርፕራይዞችን ለሚደግፉ አመራሮችና ባለሙያዎች አዘጋጅቷል ብለዋል። ለአስፈፃሚው አካል የሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት ለመደገፍ ትልቅ አቅም አለው ያሉት አቶ ካሳሁን ስልጠናው ተቀራራቢ እውቀትና ግንዛቤ ይዞ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ የሚያስችል በመሆኑ ሰልጣኞች ስልጠናበተገቢው ሁኔታ በመከታተል ወደታች ማውረድ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። ዛሬው ዕለት ለአማራ ክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች መሰጠት የጀመረው ስልጠና የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ፍኖተ ካርታ፣ የሽግግር ስትራቴጂ፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና በጥራት ስራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸው ተገልጿል። #ኢትዮጵያ_ታምርት   #እኛም_እንሸምት
9190Loading...
10
"ለብድር ካቀረብኩት 43.5 ቢሊዮን ብር ውስጥ 26 በመቶ የሚሆነውን ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሠጥቻለሁ" ኦሮሚያ ባንክ EED ግንቦት 18/2016 ዓ.ም ከተመሰረተ 15 ዓመታት ያስቆጠረው ኦሮሚያ ባንክ ለብድር ካቀረበዉ 43.5 ቢሊዮን ብር ዉስጥ 11.3 ቢልየን ብሩን ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ማሠራጨቱን አስታወቀ። ቀሪው የብድር አቅርቦት ለከፍተኛ ተበዳሪዎች ማቅረቡን የገለፀዉ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ይህም የብድር አቅርቦት በአማካይ አንድ ተበዳሪ 5 ሚሊዮን ብድር መውሰዱን ተናግረዋል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ጨምረዉ እንደተናገሩት የባንኩ የተበላሸ የብድር መጠኑ ከ1.6 በመቶ እስከ 2 በመቶ የሚደርስ እንደሆነ ገልፀዋል ። አሁን ላይ ቅርንጫፎችን ከመክፈት ወደ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት ፊቱን ያዞረዉ ባንኩ "ኦሮ ዲጂታል" በተሰኘው አገልግሎት ቴሌግራምን ጨምሮ በ7 አማራጮች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
1 0243Loading...
11
የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የሽግግር ስትራቴጂ ዙሪያ ለትግራይ ክልል የዘርፍ አስፈፃሚ አካላት ስልጠና ተሰጠ፡፡ EED ግንቦት 18 /2016 ዓ.ም (መቐለ) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የአምራች ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር በወጥነት ለመምራትና ለኢንተርፕራይዞች ፍላጎት ተኮር ድጋፎችን አቀናጅቶ ለማቅረብ በሚያስችለው የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር ስትራቴጂ ላይ ለትግራይ ክልል የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና በመሰጠት ላይ ነው፡፡ የስልጠናው አላማ አምራች ኢንተርፕራይዞች ከጥቅል የሀገር ውስጥ ምርት ያላቸውን ድርሻ የሚያሳድግ ማዕቀፍ ለመፍጠር ፤ አምራች ኢንተርፕራይዞች እንዲስፋፉና እንዲጠናከሩ ለማድረግ፣ ፍትሃዊ የሃብት ስርጭትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ  የሚጠበቀውን ግብ  በጋራ ጥረት ለማሳካት የሚያስችል አንድ ወጥ የሆነ ግንዛቤ  ለመፍጠር ነው፡፡ ስልጠናውን የሰጡት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጌታቸው ኪዳኑ እንደገለፁት የሽግግር ስትራቴጂው አምራች ኢንተርፕራይዞች እድገትን መሰረት ያደረገ ሽግግር እንዲያደርጉ በማድረግ ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለሚደረገው መዋቅራዊ ሽግግር የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ሳይባክን አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠትና በመከታተል የመዋቅራዊ ሽግግር ጉዞአችን ለማፋጠን ይረዳል። የሽግግር ስትራቴጂ ማዕቀፉ በ7 ምሰሶዎች የተከፋፈለ ሲሆን ፤ በእያንዳንዱ ምሰሶ ውስጥ አንድ ወይም ከዚያ በላይ የምሰሶው ማስፈጸሚያ ስልቶችን ያካተተ ሲሆን ፤ የስትራቴጂ ዝግጅቱም የወቅቱን የአምራች ኢንተርፕራይዞች ገጽታ፣ የአምራች ኢንተርፕራይዞች እንዳይሸጋገሩ የሚያደርጉ ገደቦች እና ተግዳሮቶች እንዲሁም የግሉን ሴክተር ልማት ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ ነው። እነዚህ ምሰሶዎች ለዘርፉ የሚቀርበውን የፋይናንስ አቅርቦትን እና የኢንቨስትመንት ዕድል ማሳደግ ፤ የሰው ሀይል ካፒታልን ማዳበር እና የሰራተኞችን ተሳትፎ እንዲሁም ምርታማነትን እንደ አንድ የአፈጻጸም መለኪያዎች መጠቀም ፤ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ኤክስቴንሽን አገልግሎት አጠቃቀም ፤ የእሴት ሰንሰለት እድገት ፤ በሀገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ የገበያ ትስስር መፍጠር ፤ የስራ ቅንጅት መንገድ እና ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን አቀናጅቶ ማካተትን ያጠቃልላል፡፡ የሽግግር ስትራቴጂውን በአግባቡ መፈፀም እንዲቻል የመንግስት የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን የማስተግበር አቅምን ፣ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ፣ ምቹ የማይክሮ ኢኮኖሚና የንግድ አካባቢን፣ በቀላል የሕግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎችን፣ በመልካም አስተዳደር ፣ ተደራሽ የፋይናንስ አቅርቦትን፣ ተስማሚ መሠረተ ልማት፣ ደጋፊ ትምህርት፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ ብቃት ያላቸው ድጋፍ ሰጪ የመንግሥትና የግል ተቋማትን እንዲሁም በተግባር መሬት ላይ ያሉ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮችን ታሳቢ አድርጓል፡፡ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ሽግግር ስትራቴጂ በዘርፉ ከፍተኛ ለውጥ በማምጣት ያደጉ አገሮችን ምርጥ ተሞክሮና ልምድ በመመርመርና ከኢትዮጵያ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማጣጣም የተዘጋጀ ስትራቴጂ ነው፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት   #እኛም_እንሸምት
9480Loading...
12
Media files
8970Loading...
13
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የሲዳማ ክልልን የኢንዱስትሪ ዘርፍ እንቅስቃሴ እየገመገመ ነው። EED ግንቦት 17/2016 ዓ.ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢንዱስትሪና ማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በሲዳማ ክልል የስራ ጉብኝት እያካሄዱ ይገኛሉ። በዛሬው የቋሚ ኮሚቴው ውሎ በሲዳማ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ ሰብሳብነት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የ9 ወር የሥራ አፈጻጸም የቀረበላቸው ሲሆን በተጨማሪም ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና  ምርቶች ማቀባበርያ  ፓርክና በሀዋሳ ከተማ የምገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ  አቶ ጎሳዬ ጎዳና እና ለሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል:: የቋሚ ኮሚቴው ጉብኝት በቀጣይ ቀናትም እንደሚቀጥል ከክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
9750Loading...
Show all...
👍 2
“የአፋር ክልል የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ሊዝ አክሲዮን ማሕበርን ለማቋቋም ያሳየው ተነሳሽነት ለክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዕድገት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው” አቶ አብዱልፈታ የሱፍ፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋ/ ዳይሬክተር EED ግንቦት 21 2016 ዓ.ም በአፋር ክልል በም/ ርዕስ መስተዳደር የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ ክቡር አቶ አሊ መሐመድ የሚመራ ቡድን ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር የሊዝ ፋይናንስ አክሲዮን ማሕበርን ለማቋቋም የሚያስችል ውይይት አደረገ። የካፒታል ዕቃ ሊዝ ፋይናንስ አክሲዮን ማሕበራት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የማሽነሪና የቴክኖሎጂ ችግር ለመቅረፍ በብድር መልክ ለማቅረብ የተቋቋሙ ሲሆን ይህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤታማነቱ በግልፅ የታየ ሆኗል፡፡ ነገር ግን አክሲዮን ማሕበራቱ በ4 ክልሎችና በ1 ከተማ አስተዳደር ብቻ የተቋቋሙ በመሆኑ ሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ደረጃ ከዘርፉ ተጠቃሚ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ የአፋር ክልልም ይህ አክሲዮን ማሕበር ካልተቋቋመባቸው ክልሎች አንዱ እንደመሆኑ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች በተሟላ መልኩ የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ተስኖት ቆቷል፡፡ ይህን ክፍተት የተረዳው ክልሉም በክልሉ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሚመራ ቡድን አቋቁሞ በክልሎች ያለውን የአክሲዮን ማሕበራቱን አፈፃጸም ሲገመግምና ሲያጠና ቆይቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር አክሲዮን ማሕበሩን ለማቋቋም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙርያ ለመምከር ቡድኑ በኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ተገኝቶ ውይይት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፉ በመድረኩ እንደተናገሩት በካፒታል ዕቃ ሊዝ ፋይናንስ ተጠቃሚ የሆኑ ክልሎችና አምራች ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ ስራ እየሰሩ እንደሆነ ጠቁመው በተመሳሳይ መልኩ የማይጠቀሙ ክልሎች ደግሞ ዝቅተኛ አፈፃፃም እንዳላቸው ም/ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። አቶ አብዱልፈታ አክለውም መንግስት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች የሚሰጠውን ድጋፎች በወጥነት በመስጠት በሁሉም ክልሎች ያሉ ኢንተርፕራይዞች ተቀራራቢ ውጤት እንዲያመጡ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሊዝ ፋይናንስ አቅራቢዎች ኢንተርፕራይዞችን እየወለዱ የሚያሳድጉ ተቋማት እንደመሆናቸው ከዚህ ቀደም ያልተቋቋሙባቸው ክልሎች እንዲያቋቁሙ ምክረሀሳብ በማቅረብና አስፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን የተናገሩት ም/ ዋና ዳይሬክተሩ የአፋር ክልል የሊዝ ፋይናንስን ለማቋቋም ላሳዩት ተነሳሽነት አመስግነዋል። በክልሉም የሊዝ ፋይናንስ እንዲቋቋምና ያሉ አምራች ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የልማት መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደረጉ አቶ አብዱልፈታ ተናግረዋል።
Show all...
👍 4🤷‍♂ 1 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
በአንድ ጊዜ ቻርጅ ለ1 አመት የሚያገለግል ድምፅ አልባ ጄኔሬተር የፈጠረው የወለጋው ፌዴሳ ሹማ ‹ ግንቦት 21/ 2016 ዓ.ም ፌዴሳ ሹማ ተወልዶ ያደገው በቄለም ወለጋ ሲሆን፣ በከተማው ውስጥ በኤሌክትሪክ ጥገና ሙያው ይታወቃል፡፡ ይህን የኤሌክትሪክ ጥገና ሥራውን የመብራት መጥፋት እና መቆራረጥ ብዙ ጊዜ አስተጓጉሎበታል። "ችግር ብልሃትን ይወልዳል" እንዲሉ ወጣቱ ሥራውን በተደጋጋሚ ላስተጓጎለበት ችግር መላ መዘየድ እንዳለበት አሰበ፤ አስቦም ወደ ተግባር ገባ። ከብዙ ጥረት በኋላ አንድ ጊዜ ቻርጅ ተደርጎ እስከ አንድ ዓመት ድረስ አገልግሎት መስጠት የሚችል ቴክኖሎጂ እውን አደረገ። ወጣት ፌዴሳ ሹማ በኃይል አማራጭ ዘርፍ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ የታመነበት መሣሪያ የፈጠራ ባለቤት ነው፡፡ ቴክኖሎጂው የመብራት አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ለሞባይል፣ ለቴሌቭዥን፣ ለፍሪጅ እና የትኛውንም ዓይነት የኤሌክትሮኒክስ መጠቀሚያዎችን ቻርጅ የሚያደርግ፣ የሚያንቀሳቅስ እና በገመድ እና ገመድ አልባ ቴክኖሎጂ መጠቀም እንዲቻል ተደርጎ የተሠራ ነው። አንዴ የያዘውን ኃይል ደጋግሞ እያደሰ (recycling) ራሱን ቻርጅ ከማድረግ አልፎ ለረዥም ጊዜ ኃይል ማመንጨት የሚችለው ይህ ቴክኖሎጂ በሀገራችን ብቻ ሣይሆን ምን አልባትም በዓለማችን ላይ በኃይል አማራጭ ዘርፍ አብዮት መፍጠር እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል። ከ300 ዋት ጀምሮ እንደ ተጠቃሚው አቅም እና ፍላጎት የሚዘጋጀው ይህ ድምፅ አልባ ጄኔሬተር አንድ ጊዜ ቻርጅ ተደርጎ ከአንድ ዓመት በላይ አገልግሎት መስጠት እንደሚችል ነው ወጣቱ ያረጋገጠው።
Show all...
2
አምራች ኢንተርፕራይዞች የሽግግር ስትራቴጂ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ እድገትን መሰረት ያደረገ ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው EED ግንቦት 20 /2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር ስትራቴጂ ላይ ለአማራ ክልል የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በዘርፉ ዙሪያ  ልምድ ያላቸው አቶ ቤዛወርቅ ከተማ ስትራቴጂው የኢንተርፕራይዞችን እድገት መሰረት ያደረጉ ድጋፎችን በመስጠት ኢንተርፕራይዞች የደረጃ ሽግግር እንዲያደርጉ በማስቻል ኤክስፖርትን ማስፋትና ተኪ ምርትን ማበራከት የሚያስችል መሆኑን በገለፃቸው አብራርተዋል። ስትራቴጂው በዘርፉ የተሻለ ልምድ ያላቸውን የህንድ፣ የቬትናምና የኬንያ ሀገሮችን ተሞክሮ ያካተተ መሆኑን ያብራሩት አቶ ቤዛወርቅ እነዚህ ሀገራት የዘርፉን ልማት  በክላስተር ልማት፣ በፋይናንስ አቅርቦት፣ በሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦትና በገበያ ትስስር ትኩረት ሰጥተው የሚደግፉና ሌሎች ማበረታቻዎችን የሚያቀርቡ መሆናቸውንም አመላክተዋል። ስትራቴጂው እንዲተገበር የዘርፉ አስፈፃሚ አካል አውቆና ተገንዝቦ በአግባቡ መተግበርና መምራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። በዚህም በ10 ዓመቱ በዘርፉ የተያዘውን የ5 ሺህ ተወዳዳሪና ውጤታማ ኢንተርፕራይዞች ሽግግር ማሳካት የሚቻል መሆኑ በስልጠናው ግንዛቤ ተወስዷል። #ኢትዮጵያ_ታምርት   #እኛም_እንሸምት
Show all...
👍 7 2👏 1
በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ፍኖተ ካርታ ላይ ለአማራ ክልል የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ EED ግንቦት 19 /2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ለአማራ ክልል የዘርፍ በአመራርና ባለሙያዎች በ10 ዓመቱ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ልማት ፍኖተ ካርታ ላይ ስልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በዘርፉ ልምድ ያላቸው አቶ ቤዛወርቅ ከተማ የ 10 ዓመቱ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ፍኖተ ካርታ አምራች ኢንተርፕራይዞችን በፋይናንስና በመሰረተ ልማት፣ በስልጠና፣ በገበያ ትስስርና መሰል ድጋፎች በመደገፍ ተወዳዳሪና ውጤታማ ኢንተርፕራይዞች እንዲፈጠሩና ዘርፉ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችል መሆኑን በገለፃቸው አስረድተዋል። 10 አመቱ ፍኖተ ካርታ እንዲተገበር የዘርፉ አስፈፃሚና ድጋፍ ሰጪ አካላት ተቀናጅቶና ተቀራርቦ መስራትን ይጠይቃል ያሉት አቶ ቤዛወርቅ ፍኖተ ካርታው በቀጣይ 10 ዓመት 62 ሺህ አዲስ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን መፍጠር ፤ 2 ነጥብ 16 ሚሊየን አዳዲስ የስራ እድል መፍጠር ፤ 468 ሚሊየን ዶላር ከወጪ ንግድ ማግኘት ፤ 5 ሺህ ኢንተርፕራይዞችን የደረጃ ሽግግር እንዲደርጉ አሁን ያለውን 50 ፐርሰንት አማካይ የማምረት አቅም አጠቃቀም ወደ 85 ማድረስ የሚያስችል መሆኑንም አመላካተዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት ፣ #እኛም_እንሸምት
Show all...
👍 6 2
ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች በሚሰጥ የመንግስት የድጋፍ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከቻይና የተቀመረ ምርጥ ተሞክሮን ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በስልጠና ኢንዲስፋፋ አደረገ EED ግንቦት 19/2016  (መቐለ) ለሶስተኛ ቀን በቀጠለው ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና በውጤታማ የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርራይዞች ድጋፍ አሰጣጥ ዙሪያ ከቻይና የተቀመረ ምርጥ ተሞክሮን ለትግራይ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ለማስፋት ስልጠና በመስጠት ቀጥሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አቅም ግንባታ ባለሙያ አቶ መኮንን ሞላ ስልጠናውን ሲሰጡ እንደገለፁት ቻይና በአለም ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚዋ ሁለተኛ ደረጃ የያዘችው ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርቷ 60% የሚሆነው በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርት ነው፡፡ ይህም ዘርፉን ለመምራት የምትጠቀምበት ፖሊሲ ውጤታማ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ በቻይና የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ልማትን ከብሄራዊና ከማህበራዊ ስትራቴጂክ ልማት ጋር ተሰናስሎ ታቅዷል፡፡ በተጨማሪም ወደ ዘርፉ መቀላቀል ፍላጎት ላላቸው የግል ባለሀብቶች ብድር ያለ ወለድ በማመቻቸትና ሌሎች መሰረተልማቶችን በማመቻቸት መልካም የኢንቨስትመንት ከባቢን መፍጠር ችለዋል፡፡ ቻይና አንድ ምርት ለአንድ ከተማ የሚል ፖሊሲ ትከተላለች፡፡ ይህ ማለት እያንዳንዱ ከተማ ያለውን ፀጋ በመለየት ከገበያ ፣ከሰው ሀብት እና ከሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ጋር በማስተሳሰር ትኩረቱን በአንድ ምርት ላይ ብቻ  ያደረገ ከተማ መፍጠር ማለት ነው፡፡ አንድ ምርት ለአንድ ከተማ ፅንሰ-ሀሳብ ተመሳሳይ ምርት የሚያመርቱ ኢንተርፕራይዞች በአንድ ከተማ ተሰባስበው ስለሚገኙ ለምርት የሚያስፈልጋቸውን መሰረተ ልማትና ግብዓት አንድላይ ለማቅረብ ከማስቻሉም ባሻገር በምርት ሂደት ለሚያጋጥሙ ችግሮችን በቶሎ ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ በዚህ ረገድ የቻይናዋ ጉዋንዢንግ በኬብል ምርት፣ ሻንጊዝ በሲልኪ(በሃር) ምርት እንዲሁም ይኢ-ዉ በጅምላ ንግድ የሚታወቁ ከተሞች ናቸው፡፡ ቻይና ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የምትሰጠውን የብድር አቅርቦት የወለድ ምጣኔው በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ በተጨማሪም በየከተማው ብዙ ቅርንጫፍ ያላቸውና በልዩ ሁኔታ ኤክስፖርትን የሚደግፉ  እንደ የቻየይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ (Exim bank) ፣ የቻይና ኤክስፖርት ብድር ኢንሹራንስ ህብረት (Sinosure) ፣ የቻይና ልማት ባንክ እንዲሁም የቻይና ግብርና ልማት ባንክ የመሳሰሉ ተቋማት አሏቸው፡፡            የቻይና መንግስት ከአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለሚፈፀም ግዢ ቅድሚያ ከመስጠቱም ባሻገር  ለዘርፉ የገበያ አስተዳደር ISO9001 ጥራት ደረጃን የሚያሟላ የተለየ የግብይት ስርዓት በመዘርጋቱ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተፈጠረላቸውን የገበያ ዕድል በመጠቀም በአጭር ግዜ ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል ችለዋል፡፡  ቻይና "የለም" የሚባል ነገር የለም ፡፡ የትኛውንም አይነት ምርት በሚፈለገው መጠንና ጥራት ማቅረብ የሚችል የላቀ የስራ ባህል ያላቸው ህዝቦቿ ለእድገቷ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል፡፡ የቻይና ዜጎች በስራ ባህላቸው ብቻ ሳይሆን የሀገራቸውን ምርት ብቻ በመጠቀምም በአለም ተወዳዳሪ የሌላቸው ሀገር ወዳድ ህዝቦች ናቸው፡፡ በመጨረሻም ከትግራይ ክልል የተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክልሉን ተሞክሮ በማቅረብ ከቻይና ተሞክሮ ያገኙትን ዕውቀት ለቀጣይ ስራቸው ግብአት በማድረግ እንደሚጠቀሙበት ገልፀዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት ፣ #እኛም_እንሸምት
Show all...
👍 7
ለአስፈፃሚው አካል የሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተመላከተ EED ግንቦት 19/2016 ዓ.ም (ባህርዳር) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት መደገፍ በሚያስችሉ ስትራቴጂክ ሰነዶች ዙሪያ ለአማራ ክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በባህርዳርና በኮምቦልቻ ከተሞች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ በባህርዳር ከተማ እየተሰጠ ያለውን ስልጠና ያስጀመሩት የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ምክትል ሃላፊ ተወካይ አቶ ካሳሁን ታዬ ስልጠናውን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አምራች ዘርፉ ውጤታማ እንዲሆን ከክልሉ ጋር ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህ ስልጠናም ዘርፉን በውጤታማነት መደገፍ በሚያስችሉ በልዩ ልዩ ስትራቴጂክ ሰነዶች ላይ ኢንተርፕራይዞችን ለሚደግፉ አመራሮችና ባለሙያዎች አዘጋጅቷል ብለዋል። ለአስፈፃሚው አካል የሚሰጡ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች አምራች ኢንተርፕራይዞችን በውጤታማነት ለመደገፍ ትልቅ አቅም አለው ያሉት አቶ ካሳሁን ስልጠናው ተቀራራቢ እውቀትና ግንዛቤ ይዞ ኢንተርፕራይዞችን ለመደገፍ የሚያስችል በመሆኑ ሰልጣኞች ስልጠናበተገቢው ሁኔታ በመከታተል ወደታች ማውረድ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። ዛሬው ዕለት ለአማራ ክልል የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች መሰጠት የጀመረው ስልጠና የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ፍኖተ ካርታ፣ የሽግግር ስትራቴጂ፣ የማምረት አቅም አጠቃቀምና በጥራት ስራ አመራር ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸው ተገልጿል። #ኢትዮጵያ_ታምርት   #እኛም_እንሸምት
Show all...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
"ለብድር ካቀረብኩት 43.5 ቢሊዮን ብር ውስጥ 26 በመቶ የሚሆነውን ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሠጥቻለሁ" ኦሮሚያ ባንክ EED ግንቦት 18/2016 ዓ.ም ከተመሰረተ 15 ዓመታት ያስቆጠረው ኦሮሚያ ባንክ ለብድር ካቀረበዉ 43.5 ቢሊዮን ብር ዉስጥ 11.3 ቢልየን ብሩን ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ማሠራጨቱን አስታወቀ። ቀሪው የብድር አቅርቦት ለከፍተኛ ተበዳሪዎች ማቅረቡን የገለፀዉ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ይህም የብድር አቅርቦት በአማካይ አንድ ተበዳሪ 5 ሚሊዮን ብድር መውሰዱን ተናግረዋል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ጨምረዉ እንደተናገሩት የባንኩ የተበላሸ የብድር መጠኑ ከ1.6 በመቶ እስከ 2 በመቶ የሚደርስ እንደሆነ ገልፀዋል ። አሁን ላይ ቅርንጫፎችን ከመክፈት ወደ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት ፊቱን ያዞረዉ ባንኩ "ኦሮ ዲጂታል" በተሰኘው አገልግሎት ቴሌግራምን ጨምሮ በ7 አማራጮች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
Show all...
👍 12