ch
Feedback
Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

Ethiopian Enterprise Development (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

前往频道在 Telegram

Ethiopian Enterprise Developmen (የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት)

显示更多
9 484
订阅者
+1124 小时
+397
+11430

数据加载中...

吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+50
在0个频道中
六月 '26
+184
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+219
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+145
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+67
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+93
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+94
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+92
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+111
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+156
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+102
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+153
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+124
在1个频道中
Get PRO
六月 '25
+98
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+143
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+155
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+193
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+136
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+242
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+420
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+346
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+443
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+462
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+837
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+830
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+642
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+839
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+813
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+896
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+595
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+514
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+391
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+45
在1个频道中
Get PRO
十月 '23
+43
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+23
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+29
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+19
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+27
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+59
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+32
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+67
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+83
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+253
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+324
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+190
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+88
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+52
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+80
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+276
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+207
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+125
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+63
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+551
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
06 七月+12
05 七月+8
04 七月+6
03 七月+7
02 七月+8
01 七月+9
频道帖子
2
‎የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የተቋሙ አመራርና ባለሙያዎች  የእውቅና መርሀ ግብር አካሄደ ‎EED ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ‎ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ኢንተርፕራይዞች እንዲሳተፉ በምልመላ፣ በድጋፍና ክትትል ስራ የላቀ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የተቋሙ አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም ድጋፍ ላደረጉ ተቋማት የእውቅና እና ምስጋና መርሀ ግብር አካሄደ:: ‎የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ በመድረኩ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ስኬታማ እንደነበር ገልፀው፤  በዚህ መሳካት ውስጥ የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተሳትፎ  የላቀ እንደነበር አብራርተዋል። ለኤክስፖው መሳካት የላቀ አስተዋጽኦ ያደረጉ አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም ድጋፍ ያደረጉ ተቋማት መመስገንና መበረታታት ስለሚገባቸው መድረኩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል:: ‎ ‎በቀጣይ ኢንተርፕራይዞች የተሳትፎ ቁጥራቸው እንዲያድግና ጥራት ያላቸውን ምርቶች ይዘው እንዲቀርቡ ለማድረግ ከወዲሁ በእቅድ አካቶ መስራት እንደሚገባም ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል። በመድረኩ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018  ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷበታል:: ‎ኤክስፖው አጠቃላይ ሀገራዊ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የደረሰበትን ደረጃ ያስተዋወቀና በአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ብቻ ከ490 ሚሊዮን ብር በላይ ሽያጭና የገበያ ትስስር የተከናወነበት፣ ሰፊ የገበያና የእርስ በእርስ ትስስር የተፈጠረበት፣ ከትልልቅ ኢንዱስትሪዎች ጋር ልምድና ተሞክሮ የተወሰደበት እንዲሁም የዘርፉን ችግሮች የሚፈቱ መድረኮች የተከናወኑበት በመሆኑ ስኬታማ እንደነበር በመድረኩ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል። ‎ ‎በቀጣይ በ2019 የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የክልሎችን ተሳትፎ  በማሳደግና  ኢንተርፕራይዞች በተሻለ የምርት ጥራት እንዲሳተፉ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራበትም ተጠቁሟል። ‎ ‎በኤክስፖ 136 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች እንዲሳተፉ በምልመላ፣ በድጋፍና ክትትል ስራ የላቀ አስተዋጽኦ ለነበራቸው የተቋሙ አመራርና ባለሙያዎች የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት በተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች  ተበርክቷል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል ከሚያዝያ 25 እስከ ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም መካሄዱ ይታወቃል። ‎ ‎#ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት ‎ ‎#Made_in_Ethiopia ‎ ‎#ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‎ ‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen
599
3
+9
没有文字...
541
4
የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ስራ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የእቅድ ስኬት ሚናው የላቀ ነው (አቶ ዮናስ መኩሪያው) ===================== EED ሰኔ 26/2018 ዓ.ም የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከክልልና ከተማ አስተዳደር የኢንዱስትሪ ዘርፉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን የስራ ኃላፊዎች ጋር እንደ ሀገር በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመጡ ለውጦችን በተመለከተ  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አካሄደ። በስልጠና መድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፋት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮናስ መኩሪያ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የእቅድ ስኬት እየተጫወተ ያለው አዎንታዊ ሚና የላቀ መሆኑን ገልፀው የኢትዮጵያ ታምርት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራን ውጤታማነት በማሳያነት ጠቅሰዋል። የጽ/ቤት ኃላፊው አክለውም የዘርፉን ስራ ውጤታማነት በማስቀጠል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራን መደገፍና ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ተከታታይነት ባለው መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል። የስልጠና  ሰነዱን ያቀረቡት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባ ታመነ በበኩላቸው በዘርፉ ያለን ተመሳሳይ ዓላማና ሀገራዊ  ተልዕኮን ለማሳካት እየሰራን ያለን በመሆኑ ተቀራርበን በጋራ መስራት አስፈላጊና ለዘር ስኬት ቁልፍ  ጉዳይ ነው ብለዋል። በቅንጅት በመስራት የተሻለ ውጤት ማስመዝግብ እንደሚቻል አንዱ ማሳያ በኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ የመጡ ለውጦች  እንደማሳያ የሚጠቀስ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ አበባ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራ የሁሉም ሀገራዊ ዕቅዶቻችን ስኬታማነት ሚናው የላቀ እንደሆነ በመገንዘብ የተጣለብንን ሀገራዊ ኃላፊነት በስኬት ለመፈፀም ዘመኑ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ ዕውቀት መታጠቅና በትጋት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል  ። የኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ የመንግስት ተቋማት ለአንድ ሀገራዊ ተልዕኮ መሳካት ተቀራርበው እንዲሰሩ በር የከተፈ መሆኑን በመጥቀስ የተፈጠረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
740
5
+7
没有文字...
614
6
https://www.youtube.com/watch?v=_Awh0RVEWXY #ዮናስ_ሶልሽን:- የተለያዩ ማሽኖችን አምራች ኢንተርፕራይዝ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
745
7
#ኦሪት_ፈርኒቸር ========////===== በሲዳማ ክልል የሚገኘውና ተኪ ምርት በማምረት ላይ የተሰማራው ኦሪት ፈርኒቸር አምራች ኢንተርፕራይዝ ከሚያመርታቸው ምርቶች በከፊል ምንጭ: https://w+9
#ኦሪት_ፈርኒቸር ========////===== በሲዳማ ክልል የሚገኘውና ተኪ ምርት በማምረት ላይ የተሰማራው ኦሪት ፈርኒቸር አምራች ኢንተርፕራይዝ ከሚያመርታቸው ምርቶች በከፊል ምንጭ: https://www.facebook.com/share/1DESe65rwh/ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 060
8
በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ አማካኝነት በበጀት ዓመቱ በገጠር ወረዳዎች 605 አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተቋቋመዋል የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ ያለፉት ወራት አፈፆፀምን በተመለከተ ከክልል የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች ጋር ውይይት  ተካሂዷል EED  ሰኔ 20/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ2018 በጀት ዓመት የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ ያለፉት ወራት አፈፆፀምን በተመለከተ ከክልል የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች ጋር ውይይት አካሂዷል:: በመድረኩ ሪፖርቱን ያቀረቡት በልማት መ/ቤቱ የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ  አስተባባሪ የሆኑት አቶ አበበ በላይ እንደገለፁት  በበጀት ዓመቱ የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ስትራቴጂካዊ ማዕቀፍን መሰረት በማድረግ 495 አነስተኛ እና 110 መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ማቋቋም መቻሉን ገልፀዋል። ይህም በ2017 ዓ.ም ከነበረው ክንውን ጋር ሲነጻጸር እድገት የታየበት መሆኑን የገለፁት አቶ አበበ አዲስ በተቋቋሙት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አማካኝነትም ለ8,736 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር ተችሏል። እንደ አቶ አበበ ገለፃ አበረታች ስራዎች ቢሰሩም አፈጻጸሙን በተፈለገው ልክ እንዳይጓዝ ካደረጉ ተግዳሮቶች መካከል ስራውን በልዩ ትኩረት ያለመምራት፣ የመረጃ ጥራት ጉድለት ፣ ዘርፉን ለተቀላቀሉ ኢንተርፕራይዞች የመሰረተ ልማት አቅርቦት ችግር ትልቅ ማነቆ እንደሆነ በሪፖርታቸው አመላክተዋል። በቀጣይ በገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ለሚቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች በልዩ ሁኔታ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበትን እድል ማመቻቸት እንደሚገባ አሳስበዋል:: እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢኒሽየቲቭ የአካባቢን እምቅ ሀብት መሰረት በማድረግ በገጠር አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን በማቋቋም የስራ እድል መፍጠር እና ድህነትን መቀነስ  ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 062
9
+9
没有文字...
913
10
"በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የክትትልና ድጋፍ ስርዓቱ ችግርን የሚፈታና ውጤታማ መሆን አለበት!" የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር፣ ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ EED ሰኔ 20/2018 ዓ.ም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚደረገው የክትትልና ድጋፍ ስራ፣ ችግሮችን በመለየት መፍትሄ የሚያመጣና ዘላቂ ውጤት ማስመዝገብ የሚያስችል ሊሆን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ አስታወቁ። ዶ/ር አለባቸው ይህን የገለፁት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት መነሻ ዕቅድ ውይይት በተካሄደበት ወቅት ነው:: ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ውስብስብ የሆኑ ተቋማዊ አሰራሮችን እና ጥምረቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም ዘርፉን ለማሳደግ የሚደረገው የክትትልና ድጋፍ ስራ ተቋማትን ከመደገፍ ባሻገር ከግንዛቤ መፍጠር ጀምሮ እስከ ማቋቋም እና የመጨረሻውን ምርት ለገበያ ማቅረብ ድረስ ባለው ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶችን መለየት ይጠበቅበታል ብለዋል። ተቋማት አቅም ያላቸውን በራሳቸው እንዲፈቱ፣ አቅም የሌላቸውን ደግሞ ከተለያዩ አካላት ጋር በማስተሳሰር ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግን እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል። የዘርፉ ስራ በብቸኝነት ሳይሆን በትብብር የሚከናወን መሆኑን የጠቆሙት  ዶ/ር አለባቸው በተለይም የፋይናንስ አቅርቦት፣ የግብዓት አቅርቦት እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል። ትክክለኛ የክትትልና ድጋፍ ስራ ለመስራት ዝርዝር እቅድ አስፈላጊ ነው። በተለይም ለእያንዳንዱ የግብዓት ፍላጎት፣ የማምረቻ መሳሪያዎች እና የተቋማት አቅም በተደራጀ መንገድ ማቀድና መተግበር ይገባል። በአሁኑ ወቅት የክትትልና ድጋፍ ስራው እየተከናወነ ቢሆንም፣ በሪፖርት አቀራረብና በወቅታዊ መረጃ አያያዝ ላይ ክፍተቶች ይስተዋላሉ። ይህንን ለማስተካከል ዲጂታል አሰራርን መጠቀም እና የክትትል ስርዓቱን ዘመናዊ ማድረግ ቀዳሚ ስራ ሊሆን ይገባል ብለዋል። አለም አቀፍ የገበያ ሁኔታዎች እና የሎጂስቲክስ ችግሮች በዘርፉ ላይ የሚያሳድሩት ተጽዕኖ አለ። ይህም የዋጋ ንረትን ሊፈጥር ስለሚችል፣ ዘርፉን ከነዚህ ተግዳሮቶች ለመከላከል ስትራቴጂክ ድጋፍ ያስፈልጋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ማብራሪያ፣ በቀጣይ የክትትልና ድጋፍ ስራው የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በማጎልበት፣ ምርታማነታቸውን ማሳደግ: ግልጽ የሆነ የስራ መመሪያና የክትትል ስርዓት በመፍጠር ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል:: የተቀናጀ አሰራር ለመፍጠር ከፌዴራል እስከ ክልል ድረስ ያለው የዘርፉ አመራር እና ባለሙያዎች ለጋራ ግብ እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚገባ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል። ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ በማጠቃለያቸው፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክትትልና ድጋፍ ስራው ትኩረት ሰጥተው በመስራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
893
11
+9
没有文字...
811
12
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የበጀት ዓመቱ እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ በይፋ ተጀመረ EED ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋ+9
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የበጀት ዓመቱ እቅድ  አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ በይፋ ተጀመረ EED ሰኔ 20/ 2018 ዓ.ም የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው:: የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጳውሎስ በርጋ በመድረኩ የመክፈቻ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የውይይቱ መሠረታዊ ዓላማ በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራትን ጥንካሬዎችና ያጋጠሙ ማነቆዎችን ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።  በሥራ ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት በጋራ መፍትሄ ለመስጠት የሚያስችሉ ስልቶች ይቀመጣሉ ያሉት አቶ ጳውሎስ ይህም ተቋማዊ ግቦችን በብቃት ለማሳካት የሚያስችሉ ቁልፍ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ እንደሚረዳ ጠቁመዋል። በመድረኩ የበጀት አመቱ የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ይደረግበታል። እንደ ሀገር በቀጣይ ዓመት ሊከናወኑ በታቀዱ ተግባራት እና አዳዲስ የሥራ አቅጣጫዎች ላይ ጥልቅ ምክክር ይካሄዳል። በውይይት መድረኩ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት: የክልል የዘርፉ ቢሮዎች የሥራ ኃላፊዎች: የእቅድ ባለሙያዎችና የገጠር ኢንዱስትራላይዜሽን ኢኒሺየቲቭ አስተባባሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
920
13
በማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የተመዘገቡ ተሞክሮዎችን የመቀመርና የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ»ን ስኬታማ ተሞክሮ አጋርቷል EED (ሰኔ 17/2018 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ከ«መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ» ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ የተገኘውን ምርጥ ተሞክሮ ለአዲስ አበባ ከተማ የቆዳና ጨርቃጨርቅ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች አካፈለ። የምርጥ ተሞክሮ ቅመራውን ያቀረቡት በልማት መ/ቤቱ የጨርቃጨርቅ ዲዛይን ባለሙያ የሆኑት አቶ ታሪኩ አበበ በሰጡት ማብራሪያ ሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የምታደርገውን የልማት ሽግግር ለማፋጠን የሞዴል ተቋማትን ተሞክሮ ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ለስላሳ አሻንጉሊቶችና ትራሶችን የሚያመርተው መርድ አበበ የአሻንጉሊት ስራ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ካሉት 30 ቋሚ ሠራተኞች ውስጥ 90 በመቶ ያህሉን (27ቱን) ሴቶች በማድረግ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለአሻንጉሊትና ትራስ መሙያነትም መልሶ ጥቅም ላይ የዋለ ፋይበር (Recycled Fiber) በመጠቀም ለአካባቢ ተስማሚ አሰራርን ዘርግቷል። በተጨማሪም ድርጅቱ የተለያዩ ማበረታቻዎችንና ምቹ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የሠራተኞችን የመቅረት ምጣኔ ወደ 5 በመቶ ዝቅ ማድረግ ችሏል። ኢንተርፕራይዙ ከመንግሥት ያገኘውን የ40 ካሬ ሜትር ጠባብ የማምረቻ ሼድ በአግባቡ በመጠቀምና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ማሽኖችን በሥራ ላይ በማዋል ምርታማነቱን አሳድጓል። ያጋጠሙትን የጥሬ ዕቃ እጥረትና የዋጋ ንረት ችግሮች ለመፍታትም ጨርቅን በቀጥታ ከዱከም ምስራቅ ኢንዱስትሪ ዞን በመግዛት የተረጋጋ የምርት ፍሰት የፈጠረ ሲሆን፣ ምርቶቹን ለማስተዋወቅና ሰፊ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ቲክቶክና ኢንስታግራም ያሉ የዲጂታል ማህበራዊ ገጾችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል። መርድ አበበ አሻንጉሊት ሥራ ያሳየው ጠንካራ የአደረጃጀት፣ የጥራት ቁጥጥርና የገበያ ስልት በማንኛውም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ሊወሰድ የሚገባ የላቀ አርአያ መሆኑን አቶ ታሪኩ አስገንዝበዋል። በመልካም ተሞክሮ ልውውጥ መድረኩ  ላይ ከተሳተፉ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች መካከል የባህል አልባሳት አምራች የሆኑት ወ/ሮ ዘነበች ሰሎሜ እንደገለጹት የልምድ ልውውጥ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩባቸውን የአሰራር ክፍተቶች በግልጽ እንዲረዱ እንዳስቻላቸው ገልፀው ፤ በተለይም በስራ ገበታቸው ላይ ይገጥሟቸው የነበሩ ማነቆዎችን እንዴት መፍታት እንደሚችሉ አዳዲስ ግንዛቤዎችን ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 081
14
+9
没有文字...
965
15
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢን+9
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ =========/////========= EED ሰኔ 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የማኔጅመንት አባላት የበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በተቋሙ የማኔጅመንት አደራሽ በተካሄደው ውይይት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ከማቋቋምና ከማጠናከር አኳያ፣ ከስራ እድል ፈጠራ፣ ከተኪ ምርትና ከወጪ ምርት አንጻር እና እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ዋና ዋና ስራዎች እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ በውይይት መድረኩ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት እና ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷባቸዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት #እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ! https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 167
16
ኢንተርፕራይዞች ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች በማምረት ተወዳዳሪነታቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ ተገለጸ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው! EED ሰኔ 15/2018 ዓ.ም   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማፋጠን የሚያግዝ የኢንተርፕራይዞች ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስፋፋት ስራ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሄደ። የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ በመድረኩ እንደገለጹት፤ የአገር ውስጥ ኢንተርፕራይዞች በምርት ሂደታቸው ደረጃውን የጠበቁ አሰራሮችን መከተል እንደሚገባቸው ጠቁመዋል። ይህም በአገር ውስጥ ገበያ ብቻ ሳይሆን ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ በመላክ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል። ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ቀደም ሲል የአገር ውስጥ ምርቶችን ከተወዳዳሪነት ለመጠበቅ ከፍተኛ ታሪፎችንና ታክሶችን መጣል እንደ አንድ አማራጭ ይወሰድ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም አገሪቱ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባል እየሆነች ባለችበት በአሁኑ ወቅት የፈለጉትን ያህል ታክስ መጣልና ምርቶችን መከልከል የማይቻልበት አሰራር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው፤ ኢንተርፕራይዞች ከወዲሁ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን በመጠቀምና ጥራትን በማስጠበቅ ራሳቸውን ለገበያ ውድድር ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል። አቶ አብዱልፈታ መንግስት ለማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የሚሰጠውን የብድርና የፋይናንስ ድጋፍ እያሳደገ መሆኑን ገልጸው የማክሮ ኢኮኖሚ ቡድኑ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የሚቀርበውን የብድር ድርሻ (ፖርትፎሊዮ) ካለው 12 በመቶ ወደ 20 በመቶ ለማሳደግ ወስኗል። ይሁን እንጂ ኢንተርፕራይዞች ይህንን የብድር አቅርቦት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላትና የተሳካ የቢዝነስ ፕላን ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። የልማት መስሪያ ቤቱም ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር የቢዝነስ ፕላንና የባንክ ሰነዶችን በማዘጋጀት ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። የኢንተርፕራይዞች ሌላኛው ትልቅ ማነቆ የግብዓት እጥረት መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን ለመቅረፍ ተቋማቱ ከጥሬ ዕቃ አምራቾች ጋር ዘላቂ የሆነ ቀጥታ ትስስር መፍጠር እንዳለባቸው መክረዋል። በተለይም አብዛኛዎቹ ግብዓቶች ከአግሮ-ፕሮሰሲንግ ጋር የተያያዙና በአገር ውስጥ የሚመረቱ በመሆናቸው፣ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር የሚደረግ ቀጣይነት ያለው ትስስር ለኢንተርፕራይዞቹ ስኬት ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። በመጨረሻም ኢንተርፕራይዞች ያሉባቸውን የቦታ፣ የፋይናንስና የግብዓት ችግሮች ለመፍታት መንግስት የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግና የተሳኩ ተሞክሮዎችን በማስፋፋት የዘርፉን ዕድገት ለማገዝ እንደሚሰራ አቶ አብዱልፈታ በንግግራቸው መደምደሚያ ላይ አስታውቀዋል።   #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/Ethiopianenterprisedevelopment
892
17
+7
没有文字...
798
18
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳ
በፈጠራ የተደገፈ ተወዳዳሪነት የዕድገታችን ምስጢር ነው! 🚀🇪🇹 ======///====== አነስተኛና መካከለኛ ​ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞቻችን በገበያ ውስጥ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉት አዳዲስ አሠራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ሲላመዱ ብቻ ነው። ​ለአምራቾች፦ ዛሬውኑ የምርት ሂደታችሁን ፈትሹ፤ ወጪን በመቀነስና ጥራትን በመጨመር ተወዳዳሪነታችሁን አሳድጉ! ​ለባለድርሻ አካላት፦ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ማሽነሪዎችንና ግብዓቶችን እንዲያገኙ በማገዝ ተወዳዳሪነታቸውን በጋራ እንደግፍ! ​የኢትዮጵያ ምርት በውድድር መድረክ ላይ በኩራት እንዲቆም ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ! መልካም የስራ ሳምንት! ​ #ኢትዮጵያ_ታምርት #ዓለም_አቀፍ_ውድድር #Competitiveness #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
850
19
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን
የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ልህቀት ማዕከል የመጀመሪያ ዙር የግንባታ ሂደት EED ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማጠናከርና የኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ታስቦ እየተገነባ የሚገኘው የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) የመጀመሪያ ዙር ግንባታ እየተገነባ ይገኛል። ​ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ለኢንተርፕራይዞች ሰፊ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የስልጠና እና የጥናትና ምርምር ድጋፍ የሚሰጥ በመሆኑ፣ የመጀመሪያ ዙር ግንባታው በተያዘለት እቅድ መሰረት እየተካሄደ ይገኛል:: #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት #ለተጨማሪ_መረጃ_የማህበራዊ_ሚዲያ_ገጾቻችንን ይጎብኙ! ‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 090
20
አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲያመርቱ በትኩረት እየተሰራ ነው!   · ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ነው   EED ሰኔ 11/2018 ዓ.ም አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት (Product Certification) እንዲያገኙ ለማድረግ የሚያግዝ የሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በተለያዩ ንዑስ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች እየተሰጠ ነው፡፡   የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ምርታማነትና የጥራት ደረጃ በማሳደግ ኢንተርፕራይዞች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን እንዲተኩና ወጪ ምርቶችን እንዲያሳድጉ በማድረግ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡   ከእነዚህም ስራዎች አንዱ ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ደረጃ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ በማስቻል በሀገር ዉስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸውን የምርት ጥራት ደረጃዎች ያሟሉ ምርቶች እንዲመረቱ ማድረግ ነዉ። በልማት መ/ቤቱ የአግሮ ፕሮሰሲንግ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ሰለሞን ግዛው እንደተናገሩት ስልጠናው የተዘጋጀው ኢንተርፕራይዞች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እንዲያገኙ ለማስቻል የሚያግዝ በሰነድ አዘገጃጀት እና አያያዝ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በመስጠት የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማጎልበት ነው።   በተመረጡ ኢንተርፕራይዞች አሁን ያለውን የሥራ ሂደት እና የምርት ጥራት አያያዝ ሥርዓትን በተመለከተ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን የገለጹት መሪ ስራ አስፈጻሚው በዳሰሳ ጥናቱ የመረጃ አያያዝ ላይ ክፍተት በመታየቱ ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡   መሪ ስራ አስፈጻሚው አክለውም እያንዳንዱ ተሳታፊ ኢንተርፕራይዝ እንደሚያመርተዉ የምርት አይነት ለራሱ ተስማሚ የሆነ ሰነድ እንዲያዘጋጅና ቀጣይ ሂደቶችን በማሟላት የምርት ሰርትፊኬሽን ማረጋገጫ እስከሚያገኙ ድረስ አስፈላጊውን እገዛም እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡   በአመራረትና በመሠረተ ልማት ላይ ያሉ የምርት ጥራት ክፍተቶችን ለይቶ በማወቅ እና አስፈላጊዉን ድጋፍ በመስጠት ኢንተርፕራይዞቹ የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርትፊኬት እውቅና ካለዉ አካል እንዲያገኙ የማመቻቸት ስራም እንደሚሰራ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል፡፡   በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አዳራሽ እየተሰጠ በሚገኘው ስልጠና ከአዲስ አበባና ሸገር ከተማ የተውጣጡ በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በኬሚካልና ቆዳ ዘርፍ የተሰማሩ 24 የሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ #ኢትዮጵያ_ታምርት_እኛም_እንሸምት   ለተጨማሪ መረጃ፡- https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment
1 088