en
Feedback
Ministry of Irrigation and Lowlands- Ethiopia

Ministry of Irrigation and Lowlands- Ethiopia

Open in Telegram

MILLs Ethiopia

Show more
7 239
Subscribers
No data24 hours
+237 days
+14030 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+65
in 0 channels
August '26
+169
in 0 channels
Get PRO
July '26
+150
in 0 channels
Get PRO
June '26
+128
in 0 channels
Get PRO
May '26
+192
in 0 channels
Get PRO
April '26
+142
in 0 channels
Get PRO
March '26
+36
in 0 channels
Get PRO
February '26
+62
in 0 channels
Get PRO
January '26
+66
in 0 channels
Get PRO
December '25
+49
in 0 channels
Get PRO
November '25
+101
in 0 channels
Get PRO
October '25
+82
in 0 channels
Get PRO
September '25
+65
in 0 channels
Get PRO
August '25
+94
in 0 channels
Get PRO
July '25
+120
in 0 channels
Get PRO
June '25
+97
in 0 channels
Get PRO
May '25
+97
in 0 channels
Get PRO
April '25
+140
in 1 channels
Get PRO
March '25
+159
in 0 channels
Get PRO
February '25
+156
in 9 channels
Get PRO
January '25
+183
in 1 channels
Get PRO
December '24
+325
in 0 channels
Get PRO
November '24
+383
in 1 channels
Get PRO
October '24
+457
in 1 channels
Get PRO
September '24
+324
in 0 channels
Get PRO
August '24
+494
in 0 channels
Get PRO
July '24
+807
in 1 channels
Get PRO
June '24
+610
in 1 channels
Get PRO
May '24
+628
in 1 channels
Get PRO
April '24
+775
in 1 channels
Get PRO
March '24
+818
in 1 channels
Get PRO
February '24
+428
in 0 channels
Get PRO
January '24
+232
in 1 channels
Get PRO
December '23
+186
in 1 channels
Get PRO
November '23
+917
in 1 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
10 September+2
09 September+5
08 September+7
07 September+2
06 September+8
05 September+6
04 September+7
03 September+6
02 September+12
01 September+10
Channel Posts
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የእመርታ ቀንን (ጳጉሜ 1ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውና
+1
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የእመርታ ቀንን (ጳጉሜ 1ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው! #EthiopiaDelivers

2
+1
No text...
614
3
የህብር ቀን!! ሕብረ-ብሔራዊነት ማለት ልዩነቶቻችንን እንደ ውበትና ሀብት በመቁጠር፣ እኩልነትንና ፍትሕን መሠረት ያደረገ ጠንካራ አንድነት መገንባት ነው። የቋንቋ፣ የባህል፣ የታሪክና የብሔር ስብጥራችንን እንደ ትስስር ገመድ በመጠቀም የጋራ የወደፊት እድላችንን በጋራ መቅረፅን ይጠይቃል። ልዩነታችን የመለያያ ምክንያት ሳይሆን፣ የወደፊቷን ሀገራችንን በጋራ የምንገነባበት ታላቅ ጥንካሬያችን ምንጭ ነው! የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር!!
599
4
+1
No text...
841
5
ህዝባዊ ጽናትና የሃገር ሉዓላዊነት!! የአንድ ሀገር ሕዝብ ጽናት እና የሀገር ሉዓላዊነት በቀጥታ የተያያዙ ናቸው። ጽናት የሕዝብ አቋም፣ አንድነት፣ በችግር ጊዜ መቆም እና የሀገርን ጥቅም ማስቀደም ሲሆን፤ ሉዓላዊነት ደግሞ አንድ ሀገር በግዛቷ፣ በፖለቲካዋ፣ በኢኮኖሚዋ እና በውሳኔዎቿ ላይ የራሷን ሥልጣን በራሷ የምትወስንበት ነፃነት ነው። ጽናት ሉዓላዊነትን እንዴት ያጠናክራል? አንድነትን ያጠናክራል፦ በውጫዊም ሆነ በውስጣዊ ተጽዕኖ ጊዜ አንድ ሆኖ የሚቆም ሕዝብ የሀገሩን ነፃነት ለመጠበቅ የበለጠ አቅም ይኖረዋል። የኢኮኖሚ ነፃነትን ያሳድጋል፦ በራስ አቅም ምግብ፣ ኃይል፣ ቴክኖሎጂና አስፈላጊ ሀብቶችን ማምረት ከውጭ ጥገኝነትን ይቀንሳል። ችግርን የመቋቋም አቅምን ያዳብራል፦ ጽኑ ሕዝብ በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ ወይም ሌሎች ቀውሶች ጊዜ በቀላሉ አይፈርስም። የሀገር ጥቅምን ያስከብራል፦ የግልና የቡድን ጥቅምን ከሀገራዊ ጥቅም ጋር በማመጣጠን ሀገርን በጋራ ለማልማት ያነሳሳል። የውጭ ጫናን ለመቋቋም ያስችላል፦ በራሱ አቅም የሚተማመንና በጋራ የሚቆም ሕዝብ የሀገሩን ውሳኔ በሌሎች እንዲወሰን አይፈቅድም። በአጠቃላይ የሀገር ሉዓላዊነት የሕዝብ ጽናት ላይ ይቆማል፤ የሕዝብ ጽናት ደግሞ በአንድነት፣ በራስ አቅም እና በሀገራዊ ኃላፊነት ይገነባል። ስለዚህ ሉዓላዊነትን መጠበቅ የወታደራዊ አቅም ብቻ ጉዳይ ሳይሆን ጽኑ ሕዝብ፣ ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ አንድነት፣ የራስ አቅም እና ኃላፊነት የተሞላበት ዜግነት የሚጠይቅ ሀገራዊ ጉዳይ ነው። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር !!
679
6
+1
No text...
769
7
"ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! ኢትዮጵያ ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት ላይ ቆማለች”፦ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጳጉሜን 2 - የማንሠራራት ቀንን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢትዮጵያ ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት ላይ መቆሟን አበክረው በመግለጽ "ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም!" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክታቸው፣ "ትናንት ‘ኢትዮጵያ ተነሥታለች’ ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው" ሲሉ ሀገራችን እያስመዘገበች ያለውን ሁለንተናዊ ለውጥ አብራርተዋል። ለዚህም ማሳያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ እንዲሁም ከቢሾፍቱው ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ዐበይት ሥራዎች የኢትዮጵያን መነቃቃት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ይህ የማንሠራራት ለውጥ በዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣ በከተሞች መዘመን እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ እውነተኛ ብርሃን የፈነጠቀ መሆኑን ያነሡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ከዚህም ባለፈ ለልጆች የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በተጀመረው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይልን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል። #Ethiopia #EBC #resurgence #Pagumen
740
8
https://www.facebook.com/share/p/1FiqSENj5E/
828
9
+4
No text...
964
10
ትላንት ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም የመስኖና ቆላማ አከባቢ ሰራተኞች ለስራ ጉዳይ አዳማ ደርሰው ሲመለሱ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ 1 ባልደረባችን ህይት ያለፈ ሲሆን ሌሎች 4 ባልደረቦቻችን የአካል ጉዳት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በደረሰው አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልፃል፡፡ በአደጋው ህይወቱን ላጣው አቶ አበባው ካሳ ቤተሰቦች፣ወዳጅ፣ ዘመዶች፣ እንደዚሁም ለመላው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መጽናናትን ይመኛል፡፡ በአደጋው ጉዳት የደገሰባቸውም ባልደረቦቻችንን የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ በደረሰው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ያለፈው የሚኒስቴር መ/ቤታችን ባልደረባ የነበሩት አቶ አበባው ካሳ የተወለዱት ጥር 24/1981 አመተ ምህረት በደቡብ ጎንደር ዞን ታች ጋይንት ወረዳ ሲሆን እድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በታች ጋይንትና በላይ ጋይንት ንፋስ መውጫ ተከታትለዋል። ወደ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አቅንተውም በስነልቦና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በፐብሊክ ፖሊሲ አግኝተዋል። አቶ አበባው ካሳ የአንድ ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆኑ:- ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ተቋማት በተለያዩ የስራ መደቦች ያገለገሉ ሲሆን -ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ድረስ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የወጣቶች ጉዳይ ከፍተኛ ባለምያ እንዲሁም ከ2018 ዓ.ም ሐምሌ 1 ጀምሮ የአየር ንብረት ለውጥ ባለሞያ ሆነው ሃገራቸውንና ህዝባቸውን አገልግለዋል። የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በባልደረባችን አቶ አበባው ካሳ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው በማለፉ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰቦቹና ወዳጆቹ እንዲሁም ለመላው የተቋሙ ሠራተኞች በድጋሚ መጽናናትን ይመኛል።
837
11
No text...
835
12
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የእመርታ ቀንን (ጳጉሜ 1ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው! #EthiopiaDelivers
908
13
https://youtu.be/yDVcZmbVrg4?si=nceJbWCJZYbr6qGp
1 629
14
No text...
1 690
15
መገጭ የመስኖ ግድብ 33 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ ይዟል!! አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራ 94 በመቶ ተጠናቅቋል!! # የዋናው ግድብ ሙሌት 9.4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ሲሆን አሁን ላይ 8.25 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ተሞልቷል፤ ቀሪው የ 1.15 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የግድብ ሙሌት በቅርቡ የሚጠናቀቅ ይሆናል!! # የግድቡ ትርፍ ውሃ ማስወጫ spillway ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል # የመስኖ ውሃ መቆጣጠሪያ (intake tower) ሲቪል ስራ መቶ በመቶ ተጠናቋል ኤሌክትሮ መካኒካል ስራው አጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ ይሆናል # የመስኖ ውሃ ማስወጫ፡ መጠንና ሃይል መቆጣጠሪያ (Howell-Bunger Valve)ተገጥሟል # ለጎንደር ከተማ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚሆን ውሃ ማስወጫ ቱቦ እና መቆጣጠሪያ (valve) ገጠማ ተጠናቋል # የሎት 2 የወንዝ መቀልበሻ የአናት ስራው (wier) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል # የሎት 2 የዋና ቦይ 3 ኪሎ ሜትር ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፤ ቀሪ የዋና መስኖ ቦይ እና ሁለተኛ የመስኖ ቦይ ግንባታ ስራው እየተፋጠነ ይገኛል!!
1 649
16
+8
No text...
2 757
17
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር በቆላማ አከባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት 232 ሞተር ሳይክሎች ለክልሎች አስረከበ። ሞተር ሳይክሎቹ የቆላማ አከባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባቸው ድሬዳዋ አስተዳደርን ጨምሮ 7 ክልሎች ለሚገኙ 116 ወረዳዎች የሚከፋፈል ነው ። በርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ ተስፋዬ ይገዙ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የኢትዮጵያን ቆላማ አካባቢዎችን ለማልማት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጸው የፕሮጀክቶቹን ስራ ለማሳለጥ የሞተር ሳይክሎቹ ድጋፍ መደረጉን አሳውቀዋል። አቶ ሰኢድ ኡመር የቆላማ አከባቢ ኑ ሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አስተባባሪ ፕሮጀክቶቹ ተግባራዊ የሚደረጉት ገጠራማ በሆኑ አካባቢዎች በመሆኑ ፕሮጀክቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንደዚሁም የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን ለመከታተል ተሽከርካሪዎቹ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል።
1 682
18
+4
No text...
1 619
19
ክቡር ዶ/ር አብርሃም በላይ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር በኢትዮጵያ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ላጠናቀቁት በአለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ (IFAD) የደቡብ ሱዳን፣ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ባለብዙ ሀገራት ኃላፊ እና የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማዊራ ቺቲማን ሽኝት አደረጉ። ክቡር ሚንስትሩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቆላማ አከባቢ ልማትና በመስኖ ልማት ዘርፍ በሚሰራቸው ፕሮጀክቶች አለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ (IFAD) ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልፀዋል። IFAD በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስር ያሉ ፕሮጀክቾችን በአግባቡ እንዲደግፍ ዳይክተሩ ላደረጉት ትብብርና ቀናነት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስም አመስግነዋል። በአለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ (IFAD) የደቡብ ሱዳን፣ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ባለብዙ ሀገራት ኃላፊ እና የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማዊራ ቺቲማን በበኩላቸው በ IFAD የፋይናንስ አቅርቦት የተተገበሩ ፕሮጀክቶችን ውጤታማ ለማድረግ ክቡር ሚኒስትሩ ላሳዩትው ቁርጠኛ አመራር እውቅና ሰጥተዋል ። ለተደረገላቸው የሽኝትም አመስግነዋል ።
1 177
20
+1
No text...
1 413