Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
Channel Zemedkun Bekele (ዘመዴ) (@zemedkunbekelez) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 199 001 subscribers, ranking 109 in the Religion & Spirituality category and 98 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 199 001 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -543 over the last 30 days and by -118 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 17.48%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.78% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 34 793 views. Within the first day, a publication typically gains 25 428 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 954.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | +2 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | +14 | |||
| 05 September | +17 | |||
| 04 September | +37 | |||
| 03 September | +20 | |||
| 02 September | +18 | |||
| 01 September | +181 |
| 2 | • ካህኔ …
"…በኦሮሞ ወጠጤ የገዳ ልዩ ኮማንዶ በቅርቡ በወለጋ የተሰው።
• በረከታቸው ይደርብን። አሜን 🙏 | 8 095 |
| 3 | • ካህኔ 🙏 | 8 073 |
| 4 | • ማስታወሻ ~
"…እኔጋ ወደ 170 ለሚያህሉ ተማሪዎች ደብተር ገዝተው ለመርዳት የሚፈልጉ የሠራዊተ ጌዴዎን አባላት ተቀምጠው ይጠባበቃሉ።
"…በተለይ በክፍለ ሀገር የሚገኙ፣ በጦርነት በተጎዳ ስፍራ የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች በሰንበት ትምህርት ቤቱ ውስጥ የሚያስተምሯቸውን አቅም የሌላቸውን፣ ወላጅ የሌላቸውን የሰንበት ተማሪዎች መርጠው ለመላክ እጅ እግራቸው ነው የተሳሰረባቸው። ምቀኝነት ይሁን ቸልተኝነት አላወቅኩም። የተማሪዎቹን ስም ዝርዝር፣ ዕድሜ፣ እና የትምህርት ደረጃ መዝግቦ በደብሩ ማኅተም፣ በሕጋዊ የባንክ አካውንት ላኩልን ብሎ መጻፍ ምኑ ነው የሚከብደው።
• ለዚህ ብዬ ቀበሌ አልሄድ መቼም። አሁንም በክፍለ ሀገር የምትገኙ በተለይ በሰንበት ትምህርት ቤታችሁ ውስጥ የሚማሩ ምስኪን ልጆች ይረዱ፣ ይደገፉ ዘንድ እናንት የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች በቅንነት ትተባበሯቸው ዘንድ በእግዚአብሔር ስም በድጋሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ። እንደምሳሌ ከዚህ በታች ያለውን ፎርም ተመልክታችሁ በዚያ መሠረት ላኩ።
• የተማሪ ብዛት ቢያንስ 10፣ ቢበዛ እስከ 20። ልብ በሉ የድሀ ድሀ ልጆችን ነው ያልኩት። እዚያው ሰንበት ትምህርት ቤት የሚማሩ፣ የሚያገለግሉ ሕፃናትን ነው ያልኳችሁ። ሰምታችኋል። ይሄ ለሰንበት ተማሪዎቹ ማበራታቻም፣ የጸሎታቸውም መልስ ነው።
• ፍጠኑ … | 12 896 |
| 5 | ቅዱስ ሩፋኤል
… ዕለቱ ጳጉሜን ፫ ነው። በዓሉ በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል። ሩፋኤል ማለት በዕብራይስጥ ሩፋ ሐኪም (ፈውስ) ኤል ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው። እግዚአብሔር ፈውስ ሐኪም ነው ማለት ነው።
… ቅዱስ ሩፋኤል በ፪ተኛው ዓለመ መላዕክት በራማ ለሚገኙ ነገደ መላእክት አለቃ የሆነ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና… በሰው ቁስል ላይ ለፈውስ የተሾመም መልአክ ነው። ፈታሄ ማኅጸንም ነው ቅዱስ ሩፋኤል። "ከከበሩ መላዕክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ሄኖ 6፥3። የጦቢትን ዓይን ያበራ፣ የራጉኤልንም ልጅ ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቃት ይህ መላእክ ነው።
"…ጳጉሜን ፫ ቀን በዚኽች ዕለት ርኅወተ ሰማይ ነው። የሰማይ ደጃፍ የሚከፈትበት የሰዎች ሁሉ ጸሎትም የሚያርግበት፤ ፬ኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፤ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት፤ ሰማይም የሚከፈትባት ቀን ነው። ሊቃውንቱ ይሄን ሲያመሰጥሩት "አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት፣ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለኾነ እንዲህ ተባለ እንጂ ብለው ያመሰጥሩታል።
"…ይህንኑ በማስመልከት ነው አባቶቻችን በዚህች ሌሊት "365" አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ የሚያድሩት። በዚህች ዕለት በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል። "የሰማያት መዛግብትም ከእጁ በታች ተጠብቀው የሚኖሩ፣ እግዚአብሔር እንዳዘዘው የሚከፍታቸውና የሚዘጋቸውም ቅዱስ ሩፋኤል ነው።
"…ጳጉሜን ፫ ዳግመኛም በዛሬው ዕለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል።
"…ዳግመኛም ዛሬ ቅዱስ ሩፋኤልም በግብጽ ሀገር የምትገኝና በአንድ ዓሣ አንባሪ ላይ የታነጸችውን ቤተ ክርስቲያኑን ዓሣ አንበሪው እንዳይገለብጣት ያጸናበትም የተአምር ዕለት ነው።
"…በሌላ ወገን ደግሞ ጳጉሜን ፫ የጌታ የዳግም ምጽዓቱ ዕለት የሚታሰብባትም ዕለት ናት። በዚህ ዕለት ከሰማይ በሚዘንብ ዝናብ፣ በወራጅ ወንዝና ኩሬ፣ መጠመቅ የቆየ ትውፊት ነው። ለአዲስ ዓመት አዲስ ሰው የመሆኛም ዕለት ነው። ዝናብ ከሌለ እንኳ የቧንባ ውኃ የሚጠቀሙ አሉ። እንግዲህ ይህ የዕለቱ ዓበይት በዓል ነው።
• የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ምልጃና ጸሎት አይለየን አሜን።
"…ቆይተን ምሽት ላይ በዘመድ ቴቪ፣ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያና በመረጃ ቴቪ "ክብረ ክህነትን እና በዓለ ቅዱስ ሩፋኤልን ወደማክበሩ እናመራለን። እኔም ዘመዳችሁ የሩፋኤል ዝናብ ቢያገኘኝ ብዬ በጀርመን የደመነውን ሰማይ እያንጋጠጥኩ እየተጠባበቅኩም ነው። ጭራሽ ፀሐይ ብልጭ ብሎ እየሞቅሁም እገኛለሁ። ዝናቡ ከመጣ መጣ፣ ካልመጣ ካልዘነበ ግን እኔም ወደ ቧንቧ ውዘኃ ማምራቴ ነው። እናንተስ የቅዱስ ሩፋኤልን ዝናብ፣ ጠበሉን አገኛችሁ ይሆንን? ዝናቡ ከጠፋ ያው እንደ እኔ የቧንቧ ውኃውን መጠበል ነው እንግዲህ ምን ይደረጋል?
• ሰላም ቆዩኝ። | 13 388 |
| 6 | Voice message | 5 |
| 7 | Voice message | 35 |
| 8 | ጳጉሜን ፫ ~ ክብረ ክህነት / ቅዱስ ሩፋኤል
"…አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት። ካህናቶችህ ጽድቅን ይልበሱ፥ ቅዱሳንህም ደስ ይበላቸው። መዝ 132 ፥ 8-9
"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?
"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼ | 15 066 |
| 9 | የዛሬው መርሀ ግብራችን እንዴት አለፈ?
"…ከቴሌቭዥን ውጪ በእኔ ቲክቶክ ብቻ 31 ሺ ሰው ቁጭ ብሎ ሲከታተለን አምሽቷል። እግዚአብሔር ይመስገን።
"…በዛሬው በጳጉሜን ፪ የፊደል ገበታ መርሀ ግብራችን ለዘመድ ሚዲያ የሳታላይት ኪራይ ክፍያ 10 ሺ ዶላር ለማግኘት አቅደን ከዕቅዳችን ውጪ 5 ሺ ዶላር ጭማሪ 15 ሺ ዶላር አግኝተናል።
"…ነገ ጳጉሜን ፫ የክብር ክህነት እና ዓመታዊው የቅዱስ ሩፋኤል በዓላችንን እያከበርን የምንውልበት ዕለት ነው። በነገውም ዕለት የዘመድ ሚዲያን ለመርዳት 10 ሺ ዶላር ለማግኘት አቅደን እነመጣለን። ከእግዚአብሔርም ጋር እናሳካዋለን።
"…የነገ ሰው ይበለን 🙏🙏🙏 | 17 628 |
| 10 | • ዘመድ ሚዲያን የሳታላይት ወጪ ለመሸፈን በዚህ መንገድ መደወል ትችላላችሁ።
Zemede Media Network Inc.
Wells Fargo Act# 5694797266
Routing # 125008547
Domestic Wire# 121000248
Int'l Wire# WFBIUS6S
Zelle # 360-500-2066
Zemede Media Network Inc.
Chase Bank
Checking # 699533603
Routing # 325070760
Zelle +1-360-500-2066
Cash up $zemedetv
Email. zemedetv@gmail.com | 20 645 |
| 11 | ጳጒሜን ፪ የፊደል ገበታ ቀን
"…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት ልክ 12:40 ሲሆን በዘመድ ቴቪ፣ በመረጃ ቴቪ እና በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መርሀ ግብሩ ይጀምራል። እንደተለመደው ገባ ገባ በሉና ጠብቁን።
• ቲክቶክ 👉 tiktok.com/@zemedkun.b
• ZemedTv 👉 https://zemedtv.com/live.html
• በራምብል 👉 rumble.com/v7f73dm--september-07-2026.html?e9s=src_v1_cbl%2Csrc_v1_upp_a
• Youtube Ethio Beteseb 👉 https://www.youtube.com/@ETHIOBETESEB/streams
• በሳታላይት ቴሌቭዥን 👉 Zemed TV
Yahsat 52.5° East
11977 H 27500
• በሳታላይት ቴሌቭዥን 👉 Mereja TV
Niesat / Eutelsat 8 B
Freq. 11.636 Vertical
SR: 27.500
FEC: 5/6
• ላይ ይከታተሉን።
• ሰብሰብ ብላችሁ ጠብቁን…! | 20 756 |
| 12 | የእኔ መልስ … ኢትዮጵያዊ ።
• የእናንተስ ? | 20 558 |
| 13 | መልሱን ከራሴ ልጀምር
የዓለም ስሜ፦ ዘመድኩን ነው።
የክርስትና ስሜ፦ አክሊለ ገብርኤል።
"…እኔ ኢትዮጵያዊ ስለሆንኩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ በሆነው በአማርኛ ቋንቋዬ ነው የጻፍኩት። ደስ ሲል። የራስ ቋንቋ፣ በራስ ቋንቋ፣ በራስ ፊደል ራስን መግለጽ።
• የምቀላውጠው የለኝም። እናንተስ? | 20 901 |
| 14 | • የፊደል ገበታ ቀናችን ሸብረቅረቅ ብሎ እየሄደልን ነው። እግዚአብሔር ይመስገን።
• እስቲ እናንተም ደስ ያላችሁን ፊደል መርጣች በብሔራዊው የአማርኛ ቋንቋችሁ ጻፉ። | 19 432 |
| 15 | ለምሳሌ እኔ… ሐ ን ጽፌአለሁ። አንተም አንቺም አንድ ፊደል ጻፍ። | 19 886 |
| 16 | • አጭር መልስ ብቻ ✍✍✍ | 19 671 |
| 17 | • የአማርኛ ፊደላችን !!
• በጣም ቆንጆ ናት ‼
• መልካም ገና ‼
ሀ
ለ
ሐ
መ
ሠ
ረ
•
•
•
ፐ ። | 21 746 |
| 18 | • ጳጉሜን ፪ ~ የፊደል ገበታ ቀን
"…ዛሬ ጳጉሜን 2/2018 ዓም በእኔ በዘመዴ ቤት ኢትዮጵያችንን ለሠሩ ቀደምት አባቶቻችን እና እናቶቻችንን እያመሰገንን፣ እያወደስን የምንውልበት ዕለት ነው። ምክንያታችን ደግሞ ግልጽ ነው። ይኸውም እኛ ኢትዮጵያውያን በዓለም ላይ ካሉ ጥቂት የራሳቸው ፊደል ካላቸው ሀገራት እኩል እንድንመደብ ስላደረጉን ነው ስናወድሳቸው የምንውለው።
"…እስቲ ፊደላችንን በቪድዮም፣ በፎቶም እየላካችሁ ቤታችንን ፊደል በፊደል አድርጉት። አጥለቅልቁት፣ ገበታው በፊደላችን ይሙላ ‼
• ሀ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ | 21 016 |
| 19 | • ይሔ ደግሞ አክሱም ነው።
"…የርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ሰንበት ትምህርት ቤት የሚያገለግሉ ረዳት የሌላቸው ተማሪዎችን በሚከተለው መልኩ ልከውልናል። እኔም የስፖንሰር ያለህ ብዬ ድንጋይ ተሸክሜ ለምኜ እንደነበር ይታወሳል።
"…የተመረጡት ተማሪዎች ተጨምቀው የባሰባቸው 25 ተማሪዎች ነበር የተላኩልኝ። ለሁሉም የደብተር መግዣ የመደብነው ለአንድ ተማሪ 1,500 ብር ሲሆን አክሱም ላይ ግን ዋጋው ይጨምራል፣ ይወደዳልም። እስከ 1800 እና 1900 ድረስ ይደርሳል።
"…እና ምን አደረግኩኝ ሊረዱ የመጡትን ሰዎች መጀመሪያ የሚረዱትን ተማሪ ብዛት ቆጠርኩ። ከዚያ ለአክሱሞቹ የሚያስፈልገው ብር እስኪሞላልኝ ደመርኩ። አክሱሞች የሚፈልጉት 25 ሲሆን እኔ ሦስት ሰዎችን ደምሬ ያገኘሁትን ቁጥር በ1,500 አባዝቼ ለ25 ቱ ተማሪዎች ስፖንሰር እንዲሆኑ መላ አበጀሁ። በዚያ መልኩ ተሳክቶልኛል።
"…እህቴ ፍሬ ከሀገረ እንግሊዝ የ20 ተማሪ በ1500, ወንድሜ ታሪኩ ካአማሪካ ለ10 ተማሪ ከሀገረ አማሪካ፣ እህቴ ላቀች ከሀገረ አማሪካ ለ8 ተማሪ በር 1,500 ብር አስቤ የሦስቱን ብር ድምር ውጤት ለአክሱሞች በመስጠት እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
"…እህታችን ፍሬ፣ ላቀች እና ታሪኩ ከእንግዲህ ወዲህ በሕይወት እስካሉ ድረስ እነዚህን ተማሪዎች በዓመቱ መጨረሻ ላይ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን በመግዛት እስከ መጨረሻው ድረስ እንደ ልጆቻቸው ይዘው ይቀጥላሉ ማለት ነው። ሦስቱም በደስታ ሓሳቡን ተቀብለውታል።
"…በፊደል ገበታ ቀን ስለ ዕውቀት፣ ስለ ትምህርት፣ ስለ ተማሪዎችም እንዲህ እየተወያየን እንውላለን። በዚህ መልኩ ከተረዳዳን፣ በመሃል ያለ ደላላ አጥፍተን፣ ቀሻቢ በላተኛ አስወግደን ተረጂና ረጂ ካገናኘን ይሄን የመከራ ዘመን እንሻገራለን።
• ትናንት ወ/ሮ ሮማን አንደኛዋ ነበረች የዋግኽምራን ተማሪዎች እስከ ፍጻሜ የተረከበች። ዛሬ ደግሞ ፍሬ፣ ታሪኩ እና ላቀች አክሱሞችን ተረክበውልኛል። የሌሎቹንም እንደዚሁ አሳውቃችኋለሁ።
• ክብሩን ሁሉ እግዚአብሔር ይውሰድ። | 20 768 |
| 20 | Voice message | 22 100 |
