en
Feedback
Mulugeta Anberber

Mulugeta Anberber

Open in Telegram

ለፈጣን መረጃ እንዲሁም ለዕለታዊ ክንውኖች ወዳጅ ይሁኑ! መረጃ ለመላክ @Mulugetaanberber1

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Mulugeta Anberber

Channel Mulugeta Anberber (@mulugetaanberber) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 049 subscribers, ranking 11 009 in the News & Media category and 1 643 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 049 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 14 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 32.48%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 12.66% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 839 views. Within the first day, a publication typically gains 2 666 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 53.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ለፈጣን መረጃ እንዲሁም ለዕለታዊ ክንውኖች ወዳጅ ይሁኑ! መረጃ ለመላክ @Mulugetaanberber1”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

21 049
Subscribers
-224 hours
-27 days
+1430 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+27
in 0 channels
August '26
+187
in 1 channels
Get PRO
July '26
+176
in 0 channels
Get PRO
June '26
+526
in 0 channels
Get PRO
May '26
+111
in 2 channels
Get PRO
April '26
+99
in 1 channels
Get PRO
March '26
+44
in 0 channels
Get PRO
February '26
+21
in 0 channels
Get PRO
January '26
+31
in 1 channels
Get PRO
December '25
+13
in 0 channels
Get PRO
November '25
+16
in 1 channels
Get PRO
October '25
+945
in 3 channels
Get PRO
September '25
+215
in 1 channels
Get PRO
August '25
+25
in 1 channels
Get PRO
July '25
+46
in 1 channels
Get PRO
June '25
+147
in 0 channels
Get PRO
May '25
+142
in 4 channels
Get PRO
April '25
+255
in 3 channels
Get PRO
March '25
+403
in 7 channels
Get PRO
February '25
+164
in 5 channels
Get PRO
January '25
+789
in 13 channels
Get PRO
December '24
+2 842
in 9 channels
Get PRO
November '24
+869
in 9 channels
Get PRO
October '24
+2 403
in 10 channels
Get PRO
September '24
+675
in 10 channels
Get PRO
August '24
+3 105
in 19 channels
Get PRO
July '24
+3 453
in 13 channels
Get PRO
June '24
+24
in 0 channels
Get PRO
May '24
+46
in 0 channels
Get PRO
April '24
+117
in 1 channels
Get PRO
March '24
+100
in 2 channels
Get PRO
February '24
+85
in 0 channels
Get PRO
January '24
+62
in 0 channels
Get PRO
December '23
+68
in 17 channels
Get PRO
November '23
+35
in 2 channels
Get PRO
October '23
+243
in 1 channels
Get PRO
September '23
+1 056
in 0 channels
Get PRO
August '23
+3 844
in 0 channels
Get PRO
July '23
+145
in 0 channels
Get PRO
June '23
+3 975
in 0 channels
Get PRO
May '23
+4 650
in 0 channels
Get PRO
April '23
+1 598
in 0 channels
Get PRO
March '23
+41
in 0 channels
Get PRO
February '23
+111
in 0 channels
Get PRO
January '23
+38
in 0 channels
Get PRO
December '22
+24
in 0 channels
Get PRO
November '22
+31
in 0 channels
Get PRO
October '22
+25
in 0 channels
Get PRO
September '22
+33
in 0 channels
Get PRO
August '22
+36
in 0 channels
Get PRO
July '22
+29
in 0 channels
Get PRO
June '22
+58
in 0 channels
Get PRO
May '22
+38
in 0 channels
Get PRO
April '22
+21
in 0 channels
Get PRO
March '22
+15
in 0 channels
Get PRO
February '22
+11
in 0 channels
Get PRO
January '22
+25
in 0 channels
Get PRO
December '21
+36
in 0 channels
Get PRO
November '21
+60
in 0 channels
Get PRO
October '21
+70
in 0 channels
Get PRO
September '21
+35
in 0 channels
Get PRO
August '21
+54
in 0 channels
Get PRO
July '21
+71
in 0 channels
Get PRO
June '21
+379
in 0 channels
Get PRO
May '21
+21
in 0 channels
Get PRO
April '21
+29
in 0 channels
Get PRO
March '21
+20
in 0 channels
Get PRO
February '21
+16
in 0 channels
Get PRO
January '21
+20
in 0 channels
Get PRO
December '20
+2 258
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September0
07 September+4
06 September+5
05 September0
04 September+8
03 September+2
02 September+1
01 September+7
Channel Posts
📌ጃዋርና ልደቱ ምን እያሉ ነው!? በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ምህዳር ውስጥ ጎልቶ እየተሰማ ያለው የሁለቱ ፖለቲከኞች—የአቶ ልደቱ አያሌው እና የአቶ ጃዋር መሐመድ—የሃሳብ ፍጥጫና የፖለቲካ
+1
📌ጃዋርና ልደቱ ምን እያሉ ነው!? በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ምህዳር ውስጥ ጎልቶ እየተሰማ ያለው የሁለቱ ፖለቲከኞች—የአቶ ልደቱ አያሌው እና የአቶ ጃዋር መሐመድ—የሃሳብ ፍጥጫና የፖለቲካ ሙግት፣ የአገሪቱን ነባራዊ የህልውና አደጋና የሥርዓቱን የመበስበስ ደረጃ በግልጽ የሚያሳይ ነው። አቶ ልደቱ አያሌው ባወጡት ግልጽ ደብዳቤና በሰጡት አጠቃላይ ቃለመጠይቅ የአቶ ጃዋር መሐመድን ስውር ስሌቶች በጥልቀት ያጋለጡ ሲሆን፣ የነዚህን ሁለት ፖለቲከኞች ሙግትና መከራከሪያ ነጥቦች መነሻ በማድረግ የወቅቱን የፖለቲካ አሰላለፍ መገምገም ተገቢ ነው። ልደቱ በአደባባይ እንደሞገቱት፣ ጃዋር መሐመድ «አልደገፍኩም፣ አልተቃወምኩም» በሚል የቃላት ጨዋታ ተሸፍኖ የታጣቂና የተቃዋሚ ኃይሎችን ትብብር በስውር ለማደናቀፍ፣ «የጥምረቱ ኃይሎች አዲስ አበባ የመግባት መብት የላቸውም» በሚል ትርክት የትብብሩን መሪዎች ለማጥላላትና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትን (ኦላ) ያልተገባ ቅራኔ ውስጥ ለማስገባት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ልደቱ አያሌው በጃዋር ላይ ያቀረቧቸውን መሠረታዊ ክሶች በግልጽ ሲያስቀምጡ፣ ጃዋር «የመንግሥት ሳይሆን የመሪ ለውጥ ብቻ ነው የሚፈልገው» ሲሉ ይሞግታሉ። ልደቱ እንደሚሉት፣ ጃዋር አገዛዙ ከስልጣን እንዲወርድ ወይም የኦሕዴድ-ብልጽግና ፋሺስታዊ መዋቅር እንዲፈርስ ሳይሆን «የዐቢይ አህመድ መወገድ ብቻ ይበቃል» በሚል ስሌት የሥርዓቱ አስቀጣይ ሆኖ ለመቀጠል ይፈልጋል። ይባስ ብሎም፣ አገሪቱ ያለችበትን አጠቃላይ የህልውና አደጋና የዜጎችን እልቂት ክዶ «የሕዝቡ ጥያቄ የሰላም እጦትና የኢኮኖሚ መበላለጥ ነው» በማለት ማቃለሉን ልደቱ አጋልጠዋል። በአንጻሩ ጃዋር ለተቃውሞው እንደ ምክንያት የሚያቀርበው «የጥምረቱ ኃይሎች እነማን ናቸው? ሮድ ማፓቸውስ ምንድነው?» የሚል ጥያቄ ሲሆን፣ «በጥምረቱ ውስጥ ያሉ ኃይሎች የርዕዮተ-ዓለምና የድንበር ጉዳዮችን አስቀድመው ሳይፈቱ መተባበራቸው ስህተት ነው» የሚል መከራከሪያ ያቀርባል። ነገር ግን ልደቱ እንደተነተኑት፣ ይህ የጃዋር መከራከሪያ 99.9 በመቶ ትብብሩን እየተቃወመ በአደባባይ ግን በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ሸፍኖ ትግሉን ለማክሸፍ የሚያደርገው የፖለቲካ ሸፍጥ ነው ብሎታል። ሌላው ልደቱ አያሌው በጥብቅ ያጋለጡት አደገኛ የጃዋር ስሌት ወታደራዊውን መዋቅር የመጠቀምና የመፈንቅለ-መንግሥት ሕልሙን ነው። ልደቱ እንደሚሉት፣ ጃዋር «መከላከያ ሠራዊቱና ጀነራሎቹ የሰላም ኃይል ናቸው» እያለ የሚያቆላምጠው፣ ወታደራዊውን ክንፍ ተጠቅሞ «በመፈንቅለ-መንግሥት ዐቢይ አህመድን በመተካት የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን ለመያዝ» በመመኘት ነው። ጃዋር በበኩሉ በወለጋ ያለውን የፋኖ እንቅስቃሴ ሲኮንን «ፋኖ በወለጋ መደራጀቱ የአካባቢውን ህዝብ ህይወት ያባብሳል እንጂ አያድንም» በማለት አገዛዙ ለሚያደርገው ጭፍጨፋ ፋኖን እንደ ምክንያት አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። እዚህ ላይ በጃዋር ትርክት ውስጥ የሚታየውን ቅራኔ ልደቱ ሲያጋልጡ «ጃዋር በወለጋ ያለውን ፋኖ መንግሥት ነው ያደራጀው እያለ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ይሄንኑ ኃይል የሚያዘውን የጦር ሠራዊት ጀነራሎች ጥሩና ሰላም ወዳድ ናቸው ማለቱ እርስ-በርስ የሚጣረስ አመክንዮ ነው» ብለዋል። ሠራዊቱ በየቦታው ሕዝብ እየጨፈጨፈ መሆኑን ራሱ እያወቀ፣ ለሥልጣን መንገዱ ሲል ጦሩን «ጨዋ» ብሎ መጥራቱ አደገኛ የፖለቲካ ቁማር ነው። በአጠቃላይ ሲታይ፣ ልደቱ አያሌው ያቀረቡት የፖለቲካ ግምገማ የጃዋር መሐመድን ድብቅ ስሌትና የሃሳብ መዘበራረቅ አደባባይ ያወጣ ነው። ልደቱ «እንደ ብርሃኑ ነጋና ዳንኤል ክብረት ያሉ ፋይዳ-ቢስ አካላትን ንቆ በመተው፣ የፖለቲካ ልሂቃን በሕዝብ ፊት ቀርበው በግልጽና በጨዋነት ሊከራከሩ ይገባል» ሲሉ ያቀረቡት ጥሪ፣ በሸፍጥና በስውር ሴራ ሕዝብን ከማደናገር ይልቅ በግልጽነት የመታገልን አስፈላጊነት የሚያሳይ ነው። አገሪቱ በከፍተኛ የህልውና አደጋ ውስጥ ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ጃዋር «የህልውና አደጋ ያለበት የኦሕዴድ-ብልጽግና መንግሥት ነው፣ እሱ ከፈረሰ ሁላችንም እንጎዳለን» እያለ ለአገዛዙ ሕልውና የሚጨነቀው ጭንቀት የታጋዩንና የፖለቲካ ነጋዴውን ልዩነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። እውነተኛ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው ከግል የሥልጣን ሩጫና ከወታደራዊ መፈንቅለ-መንግሥት ቀቢጸ-ተስፋ ወጥቶ፣ የሕዝብን የሕልውና አደጋ ለማስቆም በቅንነትና በተቋማዊ ትግል በጋራ ሲቆሙ ብቻ ነው! ትግላችን ያሸንፋል!

2
📌የአብይ አህመድ አዲስ ቁማር! (ሙሉጌታ አንበርብር) የኦሕዴድ-ብልጽግና አገዛዝ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር መሠረትኩት ያለውና "የኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ብድር ማ
📌የአብይ አህመድ አዲስ ቁማር! (ሙሉጌታ አንበርብር) የኦሕዴድ-ብልጽግና አገዛዝ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር መሠረትኩት ያለውና "የኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ብድር ማሻሻያ ኩባንያ" በሚል ስያሜ የ100 ቢሊዮን ብር እና የ200 ሚሊዮን ዶላር ካፒታል ፈሰስ የተደረገበት አዲሱ ፕሮጀክት፣ በወረቀት ላይ ሲታይ እጅግ ዘመናዊና "1.5 ሚሊዮን ቤቶችን" ለዜጎች የሚያቀርብ የልማት ተቋም ይመስላል። ነገር ግን ከዚህ የተለሰለሰ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ጀርባ፣ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት ለውጭ ካፒታል አሳልፎ የሚሰጥ፣ የሀብት ክፍተቱን በማስፋት ጥቂት የፖለቲካ ኤሊቶችን የሚያበለጽግና አብዛኛውን ድሀ ዜጋ ከቀዬው የሚያፈናቅል እጅግ አደገኛ መዋቅራዊ የዕዳ ወጥመድ ተደብቋል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ በከፍተኛ የምግብ ዋጋ ንረት፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረትና በደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ በምትገኝበት እጅግ ፈታኝ ወቅት፣ የመንግሥትን የኢኮኖሚ ቅደም ተከተል መዛባትና የህዝብን ነባራዊ ስቃይ ማሾፍ በሚያሳይ መልኩ አዲስ አበባን ማዕከል ያደረገ የቅንጦት ሪል እስቴት ገበያን ለማስፋፋት የተወጠነ ስትራቴጂካዊ ሸፍጥ ነው። ይህ ግዙፍ የፋይናንስ ፍሰት በዋናነት የሚያገለግለው ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያለውን ዜጋ ሳይሆን፣ በስርዓቱ ዙሪያ የተኮለኮሉትን የሪል እስቴት አልሚዎችና ከፍተኛ የገንዘብ አቅም ያላቸውን ግለሰቦች ብቻ ነው። ባንኮች ብድር የሚሰጡት አስተማማኝ መያዣ (Collateral) ላለው አካል በመሆኑ፣ 100 ቢሊዮን ብር ወደ ኮንስትራክሽን ዘርፉ ሲገባ የመሬት፣ የቤትና የግንባታ እቃዎች ዋጋን በከፍተኛ ፍጥነት በማናር አደገኛ የዋጋ ንረት (Housing Bubble) መፍጠሩ አይቀርም። በዚህም የተነሳ ተራው ዜጋ ከቤት ባለቤትነት ህልሙ ይበልጥ ሲገለል፣ አዲሱ የሞርጌጅ ፈንድ ትልልቅ አልሚዎች የመሬት ቅርሚያ (Land Grabbing) እንዲያካሂዱ ትልቅ የፋይናንስ አቅም ይፈጥርላቸዋል። ይህ ደግሞ "ለአዲሱ የቤት ልማት መሬት ማዘጋጀት" በሚል የልማት ሰበብ፣ ድሀውን ዜጋ ያለ በቂ ካሳ ከቀዬው እያፈናቀሉ ለሀብታሞች የተከለሉ የመኖሪያ መንደሮች (Gated Communities) የሚገነቡበትን የከተማ ማፍረስ ዘመቻ በከፍተኛ ደረጃ ያፋጥነዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ሀገሪቱ ግልጽ የሆነ ጠንካራ የፋይናንስ ቁጥጥር በሌላት ሁኔታ፣ ይህ ፕሮጀክት በሙስናና በኮንትሮባንድ የተገኘን ሕገ-ወጥ ገንዘብ በሪል እስቴት ስም ህጋዊ ለማድረግ (Money Laundering) ሰፊ በር የሚከፍት ነው። በጂኦ-ፖለቲካዊና ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ ትንታኔ መነጽር ሲታይ ደግሞ፣ የዓለም አቀፉ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) እና የዓለም ባንክ ይህንን 200 ሚሊዮን ዶላር የሰጡት ለኢትዮጵያ ህዝብ አዝነው ሳይሆን፣ የራሳቸውን የኒዮ-ሊበራል ፖሊሲና የካፒታል ፍላጎት ለማስፈጸም ነው። የእነዚህ ተቋማት ዋና ዓላማ የኢትዮጵያን የፋይናንስና የመሬት ገበያ ለውጭ ካፒታል ክፍት ማድረግ ሲሆን፣ የሚሰጠውም ገንዘብ በወለድ የሚመለስ የውጭ ዶላር ብድር ነው። የብር እሴት በከፍተኛ ፍጥነት እያሽቆለቆለ ባለበት በዚህ ወቅት ይህንን የዶላር ዕዳ መሸከም፣ ሀገሪቱን በቀጥታ ወደ ከፋ የዕዳ ወጥመድ የሚከት ነው። በሂደትም ይህንን ብድር መክፈል ሲያቅታት፣ ዓለም አቀፍ ተቋማቱ የመንግሥትን የብድር ፖሊሲ በቀጥታ በመቆጣጠር፣ ማህበራዊ ድጎማዎች እንዲነሱና ሀገሪቱ ፖሊሲዎቿን በነሱ ትዕዛዝ ብቻ እንድታስፈጽም በማድረግ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነቷን ይገፏታል። አገዛዙም በበኩሉ ይህንን ብድር የሚቀበለው የህዝብ አመኔታ ባጣበት በአሁኑ ወቅት "የኢኮኖሚ ማሻሻያው እየሰራ ነው" የሚል የውሸት የፖለቲካ ሕጋዊነትና የዲፕሎማሲ ሽፋን ከምዕራባውያን ለማግኘት ሲል ብቻ ነው። ይህ የሞርጌጅና የፋይናንስ ሊበራላይዜሽን ሙከራ በሌሎች ታዳጊ ሀገራት ያስከተለው መዘዝ የነገ እጣ-ፈንታችንን በግልጽ ያሳየናል። ጋና የባንክና የሞርጌጅ ዘርፏን ለነዚህ ተቋማት ክፍት አድርጋ በዶላር ብድር በመዘፈቋ፣ የገንዘቧ እሴት ሲወድቅ ብድሯን መክፈል አቅቷት ለታሪካዊ የዕዳ ቀውስ ተዳርጋለች። ናይጄሪያ ከ IFC ጋር በመሆን ያቋቋመችው (NMRC) የሞርጌጅ ተቋም፣ የወለድ ምጣኔውን እስከ 25 በመቶ በማድረስ ድሀውን አግልሎ ለፖለቲካ ኤሊቶች የቅንጦት ሪል እስቴት መገንቢያ ብቻ ሆኗል። አርጀንቲና የዓለም ባንክን የገበያ ነፃነት ፖሊሲ ተቀብላ ዛሬም ድረስ መውጫ ባጣችበት የዋጋ ንረትና የዕዳ አዙሪት ውስጥ ትገኛለች። በቅርቡ ደግሞ ኬንያ በተመሳሳይ ከዓለም ባንክና ከ IFC ጋር ባቋቋመችው የሞርጌጅ ኩባንያ (KMRC) ጫና ምክንያት፣ ብድሩን ለመክፈል መንግሥት በህዝቡ ላይ የጫነው ከባድ ታክስ የኬንያ ወጣቶችን (Gen Z) ወደ አደባባይ አውጥቶ ደም አፋሳሽ ህዝባዊ እምቢተኝነትን አስከትሏል። ይህ በተጨባጭ የሚያሳየው ዓለም አቀፍ ተቋማቱ የቤት ልማት በሚል ማታለያ ገብተው፣ ሀገራትን የዶላር ዕዳ ጥገኛ በማድረግና በመጨረሻም መንግሥታት ታክስ ጭነው ህዝባቸውን እንዲያማርሩ በማድረግ ወደ ሀገር አቀፍ የኢኮኖሚ ውድቀትና የህዝብ አደጋ የሚያመሩ መሆናቸውን ነው። በአጠቃላይ፣ በመላው ኢትዮጵያ ግጭትና መፈናቀል በነገሰበት፣ አብዛኛው የገጠሩ ህዝብና ሌሎች ክልሎች ከማንኛውም የልማት አውታር በተገለሉበት፣ እንዲሁም አጠቃላይ የባንክ ስርዓቱ የህዝቡ የመግዛት አቅም መዳከም በፈጠረው የመክፈል አቅም ማጣት (High Default Rate) አደጋ በተጋለጠበት ሁኔታ፤ ይህ አዲስ የሞርጌጅ አሰራር የችግራችን መፍትሄ ሊሆን አይችልም። እርምጃው የአገዛዙን የፖለቲካ እድሜ ለማራዘምና የሪል እስቴት ባለሀብቶችን ለማበልጸግ የተጠነሰሰ፣ ተራውን ህዝብ ከቀዬው እያፈናቀለ ለባሰ ድህነት የሚዳርግ፣ እንዲሁም ሀገሪቱን የውጭ ኃይሎች የኢኮኖሚ ጥገኛ የሚያደርግ ታሪካዊ ስህተት ነው። አገዛዙ የፖለቲካና የወታደራዊ ክስረቱን በእንዲህ ዓይነት መዋቅራዊ የፋይናንስ ሸፍጥ ሊሸፍነው አይችልም፤ እውነተኛው መፍትሄ ያለው መሰረታዊ የፖለቲካ ለውጥ በማምጣትና ሀገሪቱን ከውድቀት በመታደግ ላይ ብቻ ነው! ትግላችን ያሸንፋል!
4 038
3
የጉባኤ ማጠቃለያ እና የአቋም መግለጫ፡ "የልሂቃን ሚና በአማራ ህልውና" August 29 እና 30, 2026 በዙም (Zoom) ሲካሄድ የቆየውና በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ላይ በጥልቀት የመከረው ታላቁ የውይይት ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል። የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ እጅግ ፈታኝ፣ ውስብስብ እና አደገኛ በሆነ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ህዝባችን በየአቅጣጫው የተከፈተበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ወደር የለሽ ተጋድሎ እያደረገ ቢሆንም፤ መጠነ ሰፊ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ የኢኮኖሚ ውድመት፣ እና ሁለንተናዊ የመዋቅር ማግለል የዕለት ተዕለት እውነታው ሆኗል። ይህ የተደራጀና ዘርፈ ብዙ ጥቃት ህዝባችንን በከፍተኛ የህልውና ስጋት ውስጥ የከተተው ሲሆን፣ የተቀናጀና አገር አቀፍ መፍትሄ ባለመገኘቱ ምክንያት ውድ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል። ከዚህ መሪርና አሳሳቢ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ፣ እኛ የአማራ ምሁራን እና ልሂቃን ቆም ብለን ራሳችንን ስንገመግም፣ ለህዝባችን የሚመጥንና በታሪክም የሚጠበቅብንን ያህል የበኩላችንን የአመራርና የተግባር ሚና እንዳልተወጣን በግልጽ እናምናለን። በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ ለማስቀረትም ሆነ የህልውና ትግሉን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማቆም፤ በዕውቀት፣ በስትራቴጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ እና ህዝብን በማስተባበር ረገድ የነበረን ተሳትፎ ውስን፣ የተበታተነ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ልክ ያላሟላ እንደነበር ጉባኤው በጽኑ ገምግሟል። ሆኖም ይህ ጉባኤ የታሪክ ማዕዘን መታጠፊያ ነው። ከእንግዲህ ወዲህ የአማራ ምሁራን ከዳር ቆሞ የመመልከትም ሆነ ተበታትኖ የመጓዝ ምዕራፍ በይፋ አብቅቷል። የህዝባችንን ህልውና ለማስጠበቅ፣ ትግሉን በዕውቀት ለመምራት፣ ጠንካራ አንድነት ለመፍጠር፣ እና ለችግሮቹ ሳይንሳዊና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ተነስተናል። አቅማችንን፣ እውቀታችንን እና ጊዜያችንን አሟጦ በመጠቀም ከህዝባችን ጎን በጽናት ቆመን ኃላፊነታችንን ለመወጣት ቃል ገብተናል። በዚህ የምስረታ ጉባኤና በቅድመ ጉባኤ በአጠቃላይ ለአንድ ወር የአማራ ልሂቃን ባደረግነው ጥልቅ ውይይት መሰረት ትግሉን ወደ ሚገባው የድል ምዕራፍ ለማሸጋገር ወስነናል፣ ይህንን ቁርጠኝነት ወደ ተግባር ለመቀየር አበይት ኃላፊነቶች የተከፋፈሉ ሲሆን በሚከተሉት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ዙሪያ ጠንካራ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል፦ ♦️የህዝባዊ ዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግንኙነት፡ ትግሉን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በግልጽ የማስረዳት ስራ። የአለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብት፡ በህዝባችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን በህግ ማዕቀፍ የመከታተልና ፍትህ የመፈለግ ዘርፍ። ♦️የሽግግር ወቅት እቅድና የፍትህ ስርዓት፡ ለቀጣይ የፖለቲካና የፍትህ መዋቅር አስቀድሞ መዘጋጀት። የታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጥበቃ፡ የህዝባችንን እሴቶች የመንከባከብና የማስቀጠል ስራ። ♦️የኮሙኒኬሽን፣ ሚዲያና የትርክት ግንባታ፡ የተበታተኑ ድምጾችን በማሰባሰብ ጠንካራ ትርክት የመገንባት ዘርፍ። የትብብር፣ ጥምረትና አጋርነት፡ ከሌሎች ሀይሎች ጋር የሚኖረውን ጤናማ ግንኙነት ማስተዳደር። ♦️የህልውና አቅም ግንባታና መረጃ ትንተና ዘርፍ፡ የህዝቡን የመቋቋም አቅም ማጎልበትና ትክክለኛ የመረጃ ፍሰትን ማረጋገጥ። ♦️የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ፡ ዘላቂ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን መንደፍ። ♦️የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ደህንነት፡ የመረጃ ደህንነትን መጠበቅና በቴክኖሎጂ መታገዝ። ♦️ የዓለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋችነት ዘርፍ ♦️ የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስና የሃብት ማሰባሰብ ዘርፍ በሚል ተቋቁሟል። "አስተዋይና ብሩህ ህዝብ የማይጠፋ ታሪክ አለው፤ የወደፊት ዕጣ ፈንታውንም እራሱ ይገነባል።" ይህን ታላቅ እውነት ሰንቀን ለጋራ ህልውናችን በአንድነት የምንቆምበት ወሳኝ ሰዓት አሁን ነው። የተጋረጡብንን የህልውና ስጋቶች በተቀናጀ መንገድ ለመመከትና ለህዝባችን የተሻለ ነገን ለመፍጠር፣ መላው ህዝባችን በነዚህ በተዋቀሩት ዘርፎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርሻውን አዎንታዊ አሻራ እንዲያሳርፍ በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን። እንተባበር! እንወያይ! እንገንባ! የዓለም አቀፍ የአማራ ሊህቃን መማክርት ምስረታ ጉባኤ! ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
5 853
4
🎯 የዕውቀት ሠራዊት ለህልውና ትግል፦ የአማራ ልሂቃን መማክርት ምስረታና ታሪካዊ ጠቅላላ ጉባኤ! ​(አዲሱ ደረበ) ​የአማራ ሕዝብ ዛሬ በታሪኩ ፈታኝና አሳሳቢ ወቅት ላይ ይገኛል። የህልውና፣ የደህንነት፣ የሰብአዊ መብትና የባህል መቃወስ አደጋዎች ተደራርበውበት በሚገኙበት በዚህ ወሳኝ ሰዓት፣ ህዝቡን ከወደቀበት አዙሪት ለማውጣት የዕውቀት፣ የጥበብና የባለሙያዎች አስተዋጽኦ ተራ ምርጫ ሳይሆን ፍጹም የህልውና ጉዳይ ሆኗል። በመላው ዓለም የሚገኙ አቅሞችና ባለሙያዎች ተቀናጅተው የሚንቀሳቀሱበት የአማራ ልሂቃን መማክርት መቋቋም ለዚህ ታሪካዊ ጥሪ የተሰጠ ወቅታዊና ትክክለኛ ምላሽ ነው። ​ይህ መማክርት የአቅም ስብጥርንና አለማቀፋዊነትን መሠረት በማድረግ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የሚገኙ ምሁራንን ዕውቀት፣ ልምድና ዓለም አቀፍ ትስስር በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ አጣምሮ የሚይዝ ነው። የተበታተኑ ጥረቶችን ወደ ማዕከላዊ አውታር በማምጣት፣ የምሁራኑን ድምጽና አቅም በተናጥል ከሚደረግ እንቅስቃሴ አውጥቶ፣ ተቋማዊና ስልታዊ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም ማዋል አስገዳጅ በመሆኑ ይህ ጉባኤ ታሪካዊ ምዕራፍ ይከፍታል። የሕዝብን ትግል በሳይንሳዊ፣ በስትራቴጂካዊ እና በጥናት ላይ በተመሰረተ መንገድ ለመምራት የሚያስችለው የዕውቀት መሪነት ክፍተት የሚሞላውም በዚህ መልኩ ነው። ​የመማክርቱ ዋና ዋና ዓላማዎች የህልውና ትግሉን በዕውቀት መደገፍ፣ የአማራን ሕዝብ የመብት፣ የሰላም እና የህልውና ትግል በጠንካራ ምርምሮች፣ በፖሊሲ ሃሳቦች እና በስትራቴጂያዊ መፍትሄዎች ማገዝ ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ በሕዝባችን ላይ የሚደርሰውን ግፍ፣ መፈናቀል እና ስልታዊ ጥቃት በአለም አቀፍ መድረኮች፣ በተቋማት እና በማህበራዊ ሚዲያ በሰነድ አስደግፎ በማቅረብ ፍትህ እንዲሰፍን ማድረግ የትኩረት ማዕከሉ ነው። በመላው ዓለም የተበተኑ የአማራ ምሁራን የሐሳብ ልውውጥ እንዲያደርጉ፣ ልምድ እንዲለዋወጡ እና ለጋራ አላማ እንዲቆሙ የትስስር መድረክ በመፍጠር ምሁራዊ አንድነትና አብሮነትን ይገነባል። ​መማክርቱ ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ ስትራቴጂካዊ ጥናቶን ሰርቶ፣ የህዝቡን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች የሚተነትኑ ሰነዶችን በማዘጋጀት ለሚመለከታቸው አካላት፣ ድርጅቶች እና መሪዎች አዋጭ የመፍትሄ ሃሳቦችን ያቀርባል። በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች የውጭ ሀገር ቋንቋዎችን በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማህበረሰብን፣ መገናኛ ብዙኃንን እና የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን በማነጋገር፣ በዲያስፖራ የሚገኙ ምሁራንን በማቀናጀት የሎቢ እና የዲፕሎማሲ ስራዎችን ያከናውናል። ​በተጨማሪም ሕዝቡ ስለወቅታዊው ሁኔታ ትክክለኛውን መረጃ እንዲያገኝ መድረኮችን፣ ሲምፖዚየሞችን እና የሚዲያ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የህዝብ ግንዛቤ ማሳደግና የማስተማር ስራዎችን ይሰራል፤ በባህልና በማንነት ላይ የሚነሱ የተዛቡ ትርክቶችን በምሁራዊ ምርምር ያርማል፣ ያስረዳል። በግፍ ከተፈናቀሉ፣ ጉዳት ከደረሰባቸው እና አቅም ካጡ ወገኖች ጎን በመሰለፍ ሙያዊ፣ ማህበራዊ እና ሰብአዊ ድጋፎችን ያስተባብራል። ​ይህ መማክርት ለህልውና ትግሉ የሚያበረክተው ልዩ ጥቅም አለ። የስሜታዊነት እና የዕውቀት ቅንጅት በመፍጠር ትግሉን ከስሜታዊ ምላሽ ይልቅ በሂደት ላይ የተመሰረተ፣ ግልጽ ግብ ያለው እና በሳይንሳዊ ትንተና የሚመራ ያደርገዋል። ምሁራኑ ባላቸው ሙያዊ አቅም፣ እና የዲፕሎማሲ ክህሎት የትግሉን ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት ከፍ ያደርጉታል። አሁን ያለው ትውልድ የሚከፍለውን ዋጋ በባለሙያ ድጋፍ አቀናጅቶ ለመሰነድ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ጠንካራ ተቋማዊ መሰረት ይጥላል። ​ይህንን ታሪካዊ ተልዕኮ እውን ለማድረግና የዕውቀት ሠራዊቱን በአንድነት ለማሰለፍ ነሐሴ 23 እና ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (August 29 & 30, 2026) ከ 1:00 PM እስከ 5:00 PM EST በዙም ስብሰባ (Zoom Meeting) መርሃ-ግብር ታላቁ የልሂቃን መማክርት ምስረታና ጠቅላላ ጉባኤ የሚካሄድ ይሆናል። ​ሁላችንም እንገኝ! ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
7 015
5
📌 የአገዛዙ የትንኮሳ ሴራ፣ የ"ፅምዶ" ተረክ ቅዠት እና የአፋብን መዋቅራዊ የትብብር መስመር! የአቢይ አህመድ ፋሺስታዊ አገዛዝ በየጊዜው የሚያደርጋቸው ተከታታይ ትንኮሳዎች የተጠኑ፣ የታቀዱ መዋቅራዊ ሴራዎች ናቸው። የአገዛዙ ዋና ዓላማ የሕዝባዊ ኃይሎች አንድነትና መዋቅር በደንብ ሳይደራጅና ሳይጠናከር ቀድሞ ወደ ያልተዘጋጀ "ውጊያ" እንዲገቡ በማድረግ መበተን ነው። አገዛዙ ከሦስት ዓመታት በፊት ራሱ ለስድስት ወራት ተዘጋጅቶ ፋኖን "በሦስት ቀን ውስጥ አጠፋለሁ" በሚል የከፈተው የትዕቢት ውጊያ፣ ዛሬም በሌላ መልክ ሊደገም ሲቃጣ ይታያል። በዚህ የሦስት ዓመታት የውጊያ ምዕራፍ ውስጥ አገዛዙ በመረጃና በስነ-ልቦና ጦርነት (Information Warfare) በፋኖ ውስጥ መከፋፈልን፣ ውዥንብርንና ተስፋ መቁረጥን ለመፍጠር ከፍተኛ በጀት መድቦ ሲሠራ ቆይቷል። በመሆኑም አሁን ባለንበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በትግሉ ማኅበረሰብ ዘንድ በቂና የጠራ ግንዛቤ መፈጠር ይኖርበታል። ሕዝባዊ ትግሉ ስሜታዊነትን አስወግዶ የጠላትን ሰርጎ-ገብ አጀንዳዎች በንቃት ማምከን አለበት። ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ሰሞኑን የሚነዛው የ"ፅምዶ" ተረክና በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ላይ የሚለጠፈው አጀንዳ ፍጹም መሠረት የሌለውና የተሳሳተ ነው። "ፅምዶ" የአማራ ሕዝብ የፖለቲካ ጥያቄም ሆነ የፋኖ የትግል ግብ አይደለም። ይህ አጀንዳ ከቃሉ መጠሪያ ጀምሮ የራሱ የሆነ ጂኦ-ፖለቲካዊ መነሻ ያለው የትግራይና የኤርትራ ነጠላ ፕሮጀክት (Single Project) እንጂ የአማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል አካል አይደለም። አፋብን ከአምባገነኑ አገዛዝ ጋር በሚደረገው ትግል ከሌሎች ኃይሎች ጋር የሚያደርገው ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የሚቃኘው በራሱ ድርጅታዊ መርሆዎች ላይ ብቻ ነው። የአፋብን የትብብር አቅጣጫ ግልጽ በሆኑ ሦስት መዋቅራዊ መርሆዎች ላይ የተመሠረተ ነው፦ ራሱን የቻለ አዋጅና ስያሜ፦ ፋኖ የሚፈጥረው ማንኛውም ጥምረት በራሱ የፖለቲካ ማንነት የሚገለጽ እንጂ የሌሎችን የጂኦ-ፖለቲካ ፕሮጀክቶች አጀንዳና ስም እንደወረደ የሚጋራ አይሆንም። ድርጅታዊ አሰራርና ማዕከላዊ ውሳኔ፦ ትብብሮች የሚፈጠሩት በግለሰቦች ፍላጎት፣ በስሜት ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ ጫና ሳይሆን፣ በግልጽ ድርጅታዊ ውይይትና በማዕከላዊ አመራሩ ውሳኔ ብቻ ነው። ከድርጅታዊ አዋጅ ውጭ አየር ላይ የሚነዛ የትኛውም አጀንዳ ተቀባይነት የለውም። የአማራን ስትራቴጂካዊ ጥቅም ማስከበር፦ ማንኛውም ታክቲካልም ሆነ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የአማራን ሕዝብ ሕልውና፣ ታሪካዊ ርስቶችና ስትራቴጂካዊ ጥቅሞች አሳልፎ በማይሰጥና ሳይሸራረፉ በሚያስከብር መልኩ ብቻ የሚቃኝ ይሆናል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የአገዛዙን የፈጠራ ፕሮፓጋንዳና የውስጥ ብተና ሴራዎች በድርጅታዊ ብስለቱና በአላማ ጽናቱ በማለፍ፣ የትግሉን ማዕከላዊ መስመር ጠብቆ የሕዝባችንን ዘላቂ ጥቅም የማስከበር ታሪካዊ ኃላፊነቱን በብቃት ሊወጣ ይገባል! የአገዛዙን የመጨረሻ መፍጨርጨር በበሰለ መዋቅራዊ ትግል መክተን ወደ ድል እንገሰግሳለን! ትግላችን ያሸንፋል!
7 101
6
Live https://youtu.be/GJrMFvUvcJc?si=RZCE10e-shcCIIBm
6 363
7
📌ናፍቀኸናል ጀነራል፣ የዘራኸው የትግል ዘር አፍርቶ የድል ጎዳናን እየገሰገስን ነው! (ሙሉጌታ አንበርብር) በታሪክ የትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ አሻራቸው የማይጠፋ፣ በአካል ቢለዩንም በመንፈስና በሐሳብ ከእኛ ጋር ወደፊት የሚራመዱ ብርቅዬ የሕዝብ ልጆች አሉ። ጀነራል አሳምነው ጽጌ ዛሬ እጅግ ናፍቀኸናል! የአማራ ሕዝብ ዛሬ አንተን ሲናፍቅ፣ ያጣውን አባቱን፣ የነፃነት አርማውንና የቁርጥ ቀን የጦር መሪውን እያሰበ ነው። ጋሼ፣ "ሰው በልቡ ያሰበውን፣ በክንዱ ይፈጽመዋል" እንደሚባለው፣ አንተ በሕይወት ዘመንህ ለሕዝብህ ያሰብከውን የነፃነትና የህልውና ራዕይ፣ ዛሬ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ልጆችህ በክንዳቸው እየፈጸሙት ይገኛሉ። መናፈቅህ የትዝታ ማዕበል ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት እንድንገሰግስ የሚያደርገን የማያልቅ የሞራል ስንቅ ሆኗል። አንበሳ ሲያልፍ ጫካው ባዶ አይሆንም፣ ሺህ ደቦል አንበሶች ይወለዳሉ እንጂ፣ አንተም በተሰዋህበት ምድር ዛሬ ሺህ አንበሶች ፈልቀው ጠላትን እያርበደበዱት ነው። ያኔ አርቀህ ያየኸው የጥፋት ደመና ዛሬ በሕዝባችን ላይ ሲያንዣብብ፣ አንተ ያስተማርከው የአትንኩኝ ባይነት መንፈስ ጋሻ ሆኖን በጀግንነት እየታገልን እንገኛለን። ነብዩ አሳምነው፣ ዛሬ የአማራ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር ተነስቷል፤ የህልውና ትግሉ በአንድ ልብና በአንድ የጋራ ዓላማ ተሳስሮ ወደማይቀለበስበት የድል ጎዳና እየገሰገሰ ነው። አንተ "ተደራጁ፣ ታጠቁ፣ ራሳችሁን አድኑ" ያልከው ትንቢታዊ ቃል ዛሬ መሬት ወርዶ፣ ሕዝባችን በከፍተኛ ንቃትና እንቅስቃሴ የራሱን ዕድል በክንዱ ለመወሰን ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። "ጅረት መንገዱን ካገኘ ገደል አይመልሰውም" እንዲሉ፣ የአማራ ሕዝብ የጀመረው የነፃነት ጉዞ በምንም ዓይነት የአፈና መዋቅርና ፋሺስታዊ ኃይል ሊቆም የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ትናንት የዘራኸው የትግል ፍሬ ዛሬ አብቦ፣ ሀገርን ከውድቀት የሚያድን ትልቅ የጥላ ዛፍ ሆኗል። ጀነራል፣ አንተን ማጣት መራር ቢሆንም፣ የከፈልከው የሕይወት መስዋዕትነት ግን የትውልድ ማንቂያ ሆኗል። አሁን በየግንባሩ የሚሰማው የፋኖ ድምፅ፣ የትንቢትህ ማረጋገጫ፣ የራዕይህ ማሳያና የናፍቆታችን መጽናኛ ነው። አባቢ፣ በደምህ የጻፍከውን የነፃነት ቃል-ኪዳን ሳናጥፍ፣ አድማስ አቋርጠን፣ ተራራን ንደን የጀመርከውን ትግል ከዳር እናደርሰዋለን። ዛሬ ትግላችን ከስሜት አልፎ በከፍተኛ ስትራቴጂካዊና ወታደራዊ ብስለት እየተመራ፣ ጠላትን በየአውደ-ውጊያው እያሳፈረና እያፈረሰ ይገኛል። ናፍቆትህ ወደ ኃይል፣ ሀዘናችን ወደ ቁርጠኝነት ተቀይሮ የድልን ጽዋ የምንጠጣበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። በአንተ መንገድ የጀመርነውን የነፃነት ጉዞ፣ በድል አክሊል አስውበን የሕዝባችንን ደህንነት እናረጋግጣለን! ትግላችን ያሸንፋል!
7 155
8
No text...
6 194
9
“እኔ ሠርቼ እየኖርኩ ስለሆነ ለራሴ አላንስም። የእኔን ተውትና የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ደግፉ፤ በብዙ መከራ ውስጥ እያለፈ ያለውን ወገናችንን ደግፉ” ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው በትናንትናው ዕለት ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸውን የሚመለከት አንድ ቪዲዮ በማኅበራዊ ሚዲያው ተለቆ ስለነበር ከዚህ ጋር በተያያዘ ብዙ ሰዎች አስተያየታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። ቪዲዮው ዶ/ር ገዱ በሥራ ላይ እያሉ የሚያሳይ ሲሆን፣ እሳቸውን ለማዋረድ በማሰብ በድብቅ ተቀርጾ የተሰራጨ ይመስላል። ዓላማውም ቀደም ሲል ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነት የነበራቸው ሰው በዚህ ዐይነት ሥራ ላይ እንዳሉ በማሳየት ለማዋረድ የታሰበ ይመስላል። ነገር ግን ቪዲዮው ከታሰበው በተቃራኒው የዶ/ር ገዱን ክብር እንጂ ውርደት አላመጣም። በእርግጥም፣ “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” በሚባልበት ሀገር፣ ሥልጣንን ተጠቅመው የሀገርና የሕዝብ ሀብት በሚመዘበርበት ሀገር፣ ለረጅም ዓመታት በከፍተኛ ሥልጣን ላይ የቆዩ ባለሥልጣን በእርጅና ዕድሜያቸው በጉልበታቸው ሠርተው ኑሯቸውን ለመደጎም ሲጥሩ መታየታቸው ያልተለመደ በመሆኑ ያስገርም ይሆናል። ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው ለሕዝብ ወገንተኝነት ያላቸው ሰው እንደመሆናቸው፣ እንደ ሌሎች ሥልጣንን ተጠቅመው ባካብቱት ሀብት ተንደላቀው ከመኖር ይልቅ በንጽሕና መኖርን በተግባር አሳይተዋል። ሊያዋርዳቸው ብሎ ቪዲዮውን የቀረጸው ሰውም ሳያስበው የዶ/ር ገዱን ክብር ከፍ አድርጎታል። በዚህ ምክንያትም ብዙ ሰዎች “ዶ/ር ገዱን ልንደግፈው ይገባል፤ አንድ ነገር እናድርግለት” በማለት ሀሳቡን በሰፊው ማንሳት ጀመሩ። ይህንን ድጋፍ ለማስተባበርና የእውቅና መርሐ-ግብር ለማዘጋጀትም ታስቦ ነበር። ሆኖም እንቅስቃሴው ከመጀመሩ በፊት የዶ/ር ገዱን አስተያየት እንጠይቅ ተብሎ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተዋል። “እኔ ሠርቼ እየኖርኩ ስለሆነ ለራሴ አላንስም። የእኔን ተውትና የአማራን ሕዝብ የህልውና ትግል ደግፉ፤ በብዙ መከራ ውስጥ እያለፈ ያለውን ወገናችንን ደግፉ” ብለዋል። በዚህ ሀሳባቸው መሠረት የታሰበው የድጋፍና የእውቅና እንቅስቃሴ ሊቆም ችሏል። በተጨማሪም፣ የዶ/ር ገዱን ክብር ለማዋረድ በማሰብ ቪዲዮውን ቀርጾ ያሰራጨው ሰው በሕግ አግባብ እንደሚጠየቅ ገልጸዋል። እየሠሩበት ያለው ድርጅት ከ10,000 በላይ ኢትዮጵያውያን የሚሠሩበት ትልቅ ድርጅት መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። ዶ/ር ገዱ አንዳርጋቸው የአብይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ሕዝብ ላይ ጦርነት ሲያውጅ፣ ይህንን አዋጅ በፓርላማ በጽኑ ተቃውመዋል። ከሀገር ከተሰደዱ በኋላም በአመራር ዘመናቸው ለተፈጸመው ጥፋት ወደፊት የድርሻቸውን እንደሚወስዱ በመግለጽ፣ ለአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል በሚችሉት ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል። በዚህም አቋማቸው መሠረት በትግሉ የድርሻቸውን እያበረከቱ ይገኛሉ። ትግላችን ያሸንፋል!
7 246
10
No text...
5 820
11
📌በእስክንድር ነጋ የፖለቲካ ሸፍጥ ተጠያቂው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው! (ሙሉጌታ አንበርብር) በፖለቲካዊና ወታደራዊ የህልውና ትግል ውስጥ፣ ከግልጽ ጠላት ይልቅ በውስጥ መዋቅር ተሰግስጎ የትግሉን ራዕይ የሚያጨልምና የሚያደናቅፍ ኃይል እጅግ አደገኛ ነው። በእስክንድር ነጋ ጉዳይ አሁን እየታየ ያለው መዋቅራዊ ብልሽትና አሻጥር፣ ግለሰቡ በራሱ ከሚፈጥረው የጥፋት ማዕበል ባሻገር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄን (አፋብን) የታሪክ ተጠያቂ የሚያደርግ ነው። እስክንድር "ከፖሊት ቢሮ አባልነት ወጥቼ ተራ አባል እሆናለሁ" ካለ በኋላ በተግባር እየፈጸመው ያለው ሸፍጥ፣ ድርጅታዊ መዋቅርን የሚንድና በርካታ ጀግኖች የወደቁለትን የሰማዕታት ደም የሚያረክስ በመሆኑ በግልጽ መነጋገር ጊዜ የማይሰጠው ግዴታ ሆኗል። በአማራ የህልውና ትግል ላይ እውነተኛ እምነት የሌለው፣ በትህትና ካባ የተደበቀ እቡይ (ትዕቢተኛ) እና "ከእኔ ውጭ ላሳር" የሚል የተዛባ ስነ-ልቦና ያለው ግለሰብ መሆኑን አብረውት የሰሩ ሰዎች ሁሉ በግልጽ የመሰከሩት መራራ ሀቅ ነው። ይህ ግለሰብ ትግሉን ለመጥለፍና ለመበተን እየተጠቀመባቸው ያሉ ስልቶች አሳፋሪና አደገኛ ናቸው። "የአዲስ አበባ ሚዲያ ካውንስል" የሚባል አደረጃጀት በራሱ ሊቀመንበርነት በመመስረት፣ ትግሉን እንደ ትናንቱ በገንዘብና በአላዋቂነት ለመግዛትና ለመበተን ሲሞክር እጅ ከፍንጅ ተይዟል። ተራ አባል ነኝ እያለ ነገር ግን ከድርጅቱ እውቅና ውጭ እንደ መሪ መግለጫዎችን በመስጠት፣ እንዲሁም አፋብን እውቅና ሳይኖረው የትዊተር (X) ስፔስ እና የቲክቶክ መድረኮችን እየከፈተ መዋቅራዊ ያልሆነ ውዥንብር ሲፈጥርና ሲንቦጫረቅ ማየት የተለመደ ሆኗል። የዚህ ሁሉ የጥፋት እንቅስቃሴ ዋና ተጠያቂው ግን ራሱ እስክንድር ብቻ ሳይሆን፣ ይህንን እያየ ዝምታን የመረጠው አፋብን ነው። ስለ ግለሰቡ ሸፍጦች በየጊዜው በመረጃና በማስረጃ ለሚመለከታቸው የአፋብን አመራሮች ቢቀርብም፣ አስቸኳይ የእርምት እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ጉዳዩን አቅልለው ተመልክተውታል። ድርጅቱ ይህን ህገ-ወጥ አካሄድ ዝም ማለቱ፣ በስርዓት አልበኝነት ትግሉን ለከፍተኛ አደጋ እያጋለጠው ይገኛል። በዚህ ውዥንብር ውስጥ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀጠና ስለተቀመጠ ብቻ፣ የቀጠናውን ታጋዮች ነጥሎ ለመምታትና ለማንቋሸሽ መሞከር ፍጹም አላዋቂነትና ከእውነት የራቀ ፍርድ ነው። አፋብን እንደ ማዕከላዊ ድርጅት በዚህ ግለሰብ ጉዳይ ላይ ቁርጥ ያለ ውሳኔ አሳልፎ፣ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት (የአሳምነው 5ኛ ዕዝ) ያንን ውሳኔ ማስፈጸም አቅቶት ወይም ፍላጎት አጥቶ ቢሆን ኖሮ ዕዙን መውቀስ በተቻለ ነበር። ነገር ግን ዋነኛው ችግር የዕዙ ሳይሆን የድርጅቱ (የአፋብን) የውሳኔ አልባነትና የድፍረት ማነስ መሆኑን በጥብቅ ማስመር ያስፈልጋል። ይህ አሁን እየታየ ያለው የስርዓት አልበኝነት እንቅስቃሴና አካሄድ በጊዜ ካልታረመ፣ ነገ ውድ ዋጋ ማስከፈሉና "ምነው በእንቁላሌ በቀጣሽኝ" ማሰኘቱ አይቀርም። ይህን ለመረዳት ደግሞ የሴረኛውን የእስክንድር ነጋን ባህሪ መረዳት እንጂ የፖለቲካ ነቢይ መሆን አይጠይቅም። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የታሪክ ተጠያቂነትን ከመውሰዱ በፊት፣ መዋቅራዊ ልዕልናውን ለማስከበር አፋጣኝ አስተዳደራዊ እርምጃ ሊወስድ ይገባል! ትግላችን ያሸንፋል!
7 344
12
አርቲስት ዳኜ ዋለ ለመጪው አዲስ ዓመት አዲስ ዜማ ሊለቅ መሆኑ ተሰማ! ታዋቂው ድምፃዊ አርቲስት ዳኜ ዋለ ለመጪው የ2019 አዲስ ዓመት በጉጉት የሚጠበቅ አዲስ የሙዚቃ ሥራውን ለሕዝብ ለማድረስ ዝግጅ
አርቲስት ዳኜ ዋለ ለመጪው አዲስ ዓመት አዲስ ዜማ ሊለቅ መሆኑ ተሰማ! ታዋቂው ድምፃዊ አርቲስት ዳኜ ዋለ ለመጪው የ2019 አዲስ ዓመት በጉጉት የሚጠበቅ አዲስ የሙዚቃ ሥራውን ለሕዝብ ለማድረስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተሰምቷል። አርቲስቱ ሊለቀው ባዘጋጀው በዚህ አዲስ ዜማው ውስጥ ስለአዲስ አበባ ጉዳይ እንደሚዘፍንም እና የተለያዩ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጭብጦችን ያካተተ እንደሆነ ታውቋል። እንደተገኘው መረጃ፣ የሙዚቃ ሥራው ሙሉ ዝግጅት ተጠናቆ፣ በአሁኑ ወቅት ለመልቀቂያ ቀናት ዝግጁ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርብ ቀናት ውስጥ በዳኜ ዋለ ዩቱዩብ ቻናል https://youtube.com/@dagnewale?si=-DVmUq4DALOZQFLZ አማካኝነት ለሕዝብ እንደሚሰራጭ ታውቋል። የዩቱዩብ ቻናሉን በዘመቻ መልክ የማስተዋወቅ ስራ እንጀምራለን፣ አሁን ካለው 266K ወደ 500K የማስገባት ዘመቻ ይህን ዘመቻ በዋነኝነት ፍቃደኛ የሆኑ ሰዎች እናስተባብረዋለን፣ ፍቃደኛ የሆናችሁ አሳውቁኝ! https://youtube.com/@dagnewale?si=-DVmUq4DALOZQFLZ እንተባበር!
8 600
13
ስለብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ተብዬው፣ ስለጃዋር መሐመድ አደገኛ ፍላጎትና ስለአፋብን አሁናዊ ቁመና ውይይት አድርገናል፣ የምትችሉ ተከታተሉት! https://youtu.be/cW6X7JAN8CI?si=L3eL0WtJ-3NQuWCp
7 955
14
📌 የ Jawar Mohammed የፖለቲካ ዕብደትና ምንጩ…! (ሙሉጌታ አንበርብር) የጃዋር የፖለቲካ ሸፍጥና የአገዛዙ አጋርነት በመጨረሻም ተጋልጧል፣ ግለሰቦች አንዳንድ ጊዜ ያሰቡት ሳይሳካ ሲቀር ወደ
📌 የ Jawar Mohammed የፖለቲካ ዕብደትና ምንጩ…! (ሙሉጌታ አንበርብር) የጃዋር የፖለቲካ ሸፍጥና የአገዛዙ አጋርነት በመጨረሻም ተጋልጧል፣ ግለሰቦች አንዳንድ ጊዜ ያሰቡት ሳይሳካ ሲቀር ወደ ፖለቲካዊ ዕብደት ማምራታቸው አይቀሬ ነው። ሰሞኑን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ ከአንከር ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ፋኖና ኦላ (OLA) በወለጋ በጋራ እየሰሩ መሆናቸውንና ትብብራቸውም በቅርቡ በይፋ እንደሚደረግ ማብሰራቸው ይታወሳል። ይህ ዜና የጃዋር መሐመድን የፖለቲካ ሚዛን ክፉኛ አናግቶት ወደ ሙሉ መደናገጥና ዕብደት ውስጥ ከቶታል። ጃዋር ያበደበት ዋነኛው ምክንያት ይህ የጋራ ትብብር የኦህዴድ/ብልጽግናን የሥልጣን እድሜ በእጅጉ እንደሚያሳጥር ጠንቅቆ ስለተረዳ ነው። በዚህም የተነሳ በተለይ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አካል የሆነውን «አንሻ ሰይድ 4ኛ እዝ» "በመንግስት የሚደገፍ ነው" የሚል የፈጠራ ስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቶበታል። የዚህ የጥፋት ዘመቻው ማሳያ ደግሞ፣ ዛሬ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አይን የሆነውን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊውን "ለአገዛዙ እጁን ይሰጣል" ብሎ ለማንቋሸሽና ስነ-ልቦናዊ ጫና ለመፍጠር የሄደበት ርቀት ነው። ይህ ሁሉ መፍጨርጨር በአጠቃላይ የወለጋን ፋኖ የማፍረስና የጀመረውን ትብብር በማምከን አገዛዙን የመታደግ አደገኛ ሴራ ነው። የጃዋር መሐመድ የፖለቲካ እሳቤ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ግልጽ ሆኗል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከሚያስተባብረው አገራዊ ትብብር ይልቅ፣ ኢትዮጵያን እያደማና ህዝብን እየጨፈጨፈ ያለው የኦህዴድ-ብልጽግና ስርዓት ለዘላለም እንዲነግስ ይመርጣል። ከአብይ አህመድ ጋር ያለው ቅራኔ የግለሰብ የሥልጣን ሽኩቻና የግል ጸብ እንጂ፣ የኦህዴድ አፋኝ መዋቅር እንዲፈርስ ፈልጎ አይደለም። አጠቃላይ የኦህዴድ ስርዓት እንዲቀጥል ያለው ጽኑ ፍላጎት፣ ዛሬ ብልጽግናን ለማዳን እየመጣ ያለውን ትብብር ለማፍረስ በሚያደርገው የዕለት ተዕለት የፕሮፓጋንዳ ስብከቱ በተግባር አስመስክሯል። ጃዋር "ወለጋ ላይ ኦሮሞ እየተገደለ ነው" የሚለውን አሮጌና ስሜት ቀስቃሽ የፖለቲካ ካርድ በመምዘዝ፣ በወለጋ ያለውን የፋኖ አደረጃጀት ለማፍረስ ይጥራል። ነገር ግን ይህ የማፍረስ አዝማሚያው ከጀርባው የተለየ ስጋት አለው። ወለጋ ላይ እየተደረገ ያለውን የፋኖ እንቅስቃሴ ዝም ካልነው፣ በሌሎችም አካባቢዎች ያለው አማራ ይበልጥ ተደራጅቶ የስርዓቱን የጀርባ አጥንት ይሰብረዋል የሚል ከፍተኛ ፍርሃት ውስጡን ውስጡን እየበላው ይገኛል። ስለዚህም የጃዋር አደገኛ እንቅስቃሴ ዋና ዓላማ፣ አገዛዙን ማትረፍና የብልጽግናን ዕድሜ ማራዘም ነው። ይሁን እንጂ ይህ በተቃዋሚ ስም የጃዋርና መሰሎቹ ብልጽግናን የማዳን መንገድ ፈጽሞ አያዋጣም፤ የሕዝብን የነፃነት ማዕበልም ሊገታው አይችልም። በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ መዋቅራዊ ትኩረቱን ይበልጥ ወደ ወለጋ ማድረግ ይኖርበታል። በተለይም ወደ ወለጋ አንሻ ሰይድ 4ተኛ እዝ፣ ከሌሎች ግንባሮችም በተለየና በላቀ ሁኔታ ልዩ የሎጂስቲክስ፣ የሞራልና የሚዲያ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል። የወለጋው ግንባር የጠላትን የፖለቲካ ቁማር የምናከሽፍበትና ሥርዓቱን ከመሰረቱ የምናፈርስበት ስትራቴጂካዊ ምሰሶ ነው! ትግላችን ያሸንፋል!
7 989
15
📌 አዲስ አበባን ለመሰልቀጥ ያሰፈሰፈው የኦሕዴድ ኃይልና የሌላው ኢትዮጵያዊ ተጠባቂ ትግል! (ሙሉጌታ አንበርብር) የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ፣ በታሪኳ አ
📌 አዲስ አበባን ለመሰልቀጥ ያሰፈሰፈው የኦሕዴድ ኃይልና የሌላው ኢትዮጵያዊ ተጠባቂ ትግል! (ሙሉጌታ አንበርብር) የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ፣ በታሪኳ አይታው በማታውቀው መዋቅራዊና ስነ-ሕዝባዊ (Demographics) ከበባ ሥር ወድቃ ትገኛለች። የኦሕዴድ-ብልጽግና አገዛዝ ወደ ሥልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የመዲናዋን ነዋሪዎች ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶች በመጨፍለቅ፣ ከተማዋን በ"ሸገር ከተማ" መዋቅር በመክበብና መሬቷን በይፋ በመቀራመት ሙሉ በሙሉ ለመሰልቀጥ ከፍተኛ እቅድ ዘርግቶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ይህ አካሄድ የከተማዋን ነዋሪ ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያውያንን የጋራ ቤትና አገራዊ ሕልውና የሚንድ በመሆኑ፣ ሁለገብና የተቀናጀ ሕዝባዊ እምቢተኝነት መከፈቱ የማይቀየር መራራ እውነት ነው። አገዛዙ የመዲናዋን ማንነትና አወቃቀር በኃይል ለመቀየር የሚያካሂዳቸው አደገኛ እርምጃዎች መዋቅራዊ ይዘት አላቸው። "ሸገር ከተማ" በሚል ሽፋን አዲስ አበባን ከዙሪያዋ በመዝጋትና ወሰኖቿን በመከለል ነፃ የመንቀሳቀስ እድሏን ማደናቀፍ፣ መሬቷን ለፓርቲው ካድሬዎችና ደጋፊዎች በነፃ በማደል የስነ-ሕዝብ ስብጥሩን በኃይል የመቀየር ስልት እየተተገበረ ነው። ይባስ ብሎም በ"ኮሪደር ልማት" ስም የቆዩ የመዲናዋን ነዋሪዎች ማፈናቀል፣ ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶችን በመደመስ የአንድ ቡድን የበላይነት የሚያንፀባርቁ ምልክቶችን በኃይል መትከል፣ እንዲሁም የከተማዋን የፋይናንስና የግብር ሀብት ለፓርቲው መዋቅር ማስፈጸሚያ ማድረግ ተለምዷል። አዲስ አበባን "ልዩ ጥቅም" ከሚል ተረክ ወደ "ቀጥተኛ ባለቤትነት" በማሸጋገር ነዋሪውን እንደ ሁለተኛ ዜጋ የመቁጠር አካሄድ ተያይዞታል። በሌላ በኩል፣ የመዲናዋ አስተዳደር በካድሬዎችና በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ሥር መውደቁ የዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ውድቀትን ፈጥሯል። ነዋሪዎች ራስን በራስ የማስተዳደር ሕገ-መንግሥታዊ መብታቸው ተነፍገው፣ ከተማዋ በሌተናል ጄነራል አስራት ዴኔሮ እና በወታደራዊ አዛዦች ሥር እንድትወድቅ ተደርጓል። ጋዜጠኞች፣ ባለሃብቶች፣ ወጣቶችና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚታሰሩበትና የሚሰቃዩበት ወታደራዊ አፈና ሰፍኗል። ያልተመጣጠነ የግብርና የታክስ ጭማሪ በማድረግም ነዋሪው ለከፋ የኑሮ ውድነትና የኢኮኖሚ ጫና ተዳርጓል። ነገር ግን የአዲስ አበባ ጥያቄ የከተማዋ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ አጀንዳ ነው። አዲስ አበባ የሁሉም ብሔር ብሔረሰቦችና ሃይማኖቶች መኖሪያና የታሪካዊ እድገታቸው ማዕከል በመሆኗ፣ የመዲናዋ መፍረስ የሀገሪቱን መፍረስ ያፋጥነዋል። በአፋር፣ ሶማሌ፣ ሲዳማ፣ አማራና ደቡብ አካባቢዎች የሚካሄደው የመሬት ቅርምት በአዲስ አበባም መደገሙ፣ አገዛዙ የያዘውን አደገኛ የመስፋፋት ፍላጎት ያሳያል። አገዛዙ ይህንን የመሬት ወረራ የ"40 ሚሊዮን ኦሮሞ ጥያቄ" አድርጎ ለማቅረብ የሚያደርገው ጥረትም ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የተሸረበ ርካሽ ሴራ እንጂ የኦሮሞ ሕዝብ እውነተኛ ጥያቄ አይደለም በሚል አንዳንድ የኦሮሞ ምሁራን ለጊዜው እየተናገሩ ይገኛሉ። ይህንን መዋቅራዊ አደጋ ለመመከት የመላው ኢትዮጵያውያን ተጠባቂ የጋራ ትግል እየተጠናከረ ይገኛል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የጋራ ጥምረት፣ እንዲሁም የፋኖ ሕዝባዊ ትግልና የሌሎች ነፃነት ኃይሎች ስልታዊ ግስጋሴ የአገዛዙን የኃይል ማዕከል እያዳከሙት ነው። የታጠቁና ያልታጠቁ የፖለቲካ ኃይሎች የጋራ ፍኖተ-ካርታ በመቀረፅና በከተማዋ የተሰማሩ የፖሊስና የመከላከያ አባላት ከሕዝብ ጎን እንዲቆሙ በማድረግ አጠቃላይ ሕዝባዊ አመፅና የኢኮኖሚ እምቢተኝነትን ማቀጣጠል ቀጣዩ የትግል ምዕራፍ ነው። ወደፊት ሀገርንና አዲስ አበባን ከውድቀት ለማዳን፣ የነዋሪዎች ራስን በራስ የማስተዳደር ዲሞክራሲያዊ መብት በይፋ መረጋገጥ አለበት። የ"ሸገር ከተማ" መዋቅርና ሕገ-ወጥ የድንበር ማካለል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተሰርዘው፣ በኃይል የተወሰዱ መሬቶችና ንብረቶች ለባለቤቶቻቸው የሚመለሱበት ፍትሐዊ አሰራር መዘርጋት ይኖርበታል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የደኅንነትና የኢኮኖሚ መብት ተከብሮ፣ የወታደራዊ ኮማንድ ፖስት አሰራር በመሻር የሕግ የበላይነት ሊነግስ ይገባል። የኦሕዴድ-ብልጽግና አገዛዝ አዲስ አበባን ለመሰልቀጥ የሚያደርገው የመጨረሻ መፍጨርጨር የሕዝቡን ቁጣ በማቀጣጠል የስርዓቱን ውድቀት የሚያፋጥነው ይሆናል። አዲስ አበባ የኦሕዴድ የግል ሀብት አይደለችም፤ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ቤትና የአገራዊ ሕልውናችን ማዕከል እንጂ! አምባገነኑን አገዛዝ በማስወገድ የሕግ የበላይነትና የሕዝብ ሉዓላዊነት የሚያብብባትን አዲስ ኢትዮጵያ የማረጋገጡ ትግል ተጠናክሮ ይቀጥላል! ትግላችን ያሸንፋል!
6 285
16
ተጨማሪ መረጃ (UPDATE) በዶ/ር መስፍን አረዓያ ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎ እንደነበርና በዶ/ር ሂሩት ገብረስላሴ ለመተካት ጥረት ሲደረግ መቆየቱ ታወቀ! (ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ
ተጨማሪ መረጃ (UPDATE) በዶ/ር መስፍን አረዓያ ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎ እንደነበርና በዶ/ር ሂሩት ገብረስላሴ ለመተካት ጥረት ሲደረግ መቆየቱ ታወቀ! (ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ 251 ሚዲያ) የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር መስፍን አረዓያ ሀገር ለቀው ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውን ተከትሎ በተገኘ አዲስ መረጃ፣ ከአስራ አምስት ቀን በፊት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ውስጥ በእርሳቸው ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው እንደነበር ታውቋል። በተጨማሪም የኦህዴድ/ብልፅግና አገዛዝ ዶ/ር መስፍን አረዓያን ከኃላፊነታቸው በማንሳት በምክትል ኮሚሽነሯ ዶ/ር ሂሩት ገብረስላሴ የመተካት ከፍተኛ ፍላጎትና ድብቅ እንቅስቃሴ ሲያደርግ እንደነበር ከተለያዩ ምንጮች የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ይህ አዲስ ይፋ የሆነው መረጃ ዋና ኮሚሽነሩ በይስሙላው የምክክር ኮሚሽን ውስጥ ያለውን ከባድ የፖለቲካ ጫና፣ የውስጥ ፍጥጫ እና የአገዛዙን ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት ይበልጥ ያጋለጠ ክስተት መሆኑ ተጠቅሷል። ኢትዮ 251 ሚዲያ የነጻነት አንደበት!
6 281
17
ሰበር ዜና! የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር መስፍን አረዓያ አሜሪካ መግባታቸው ታወቀ! (ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ 251 ሚዲያ) የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር የ
ሰበር ዜና! የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር መስፍን አረዓያ አሜሪካ መግባታቸው ታወቀ! (ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ 251 ሚዲያ) የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር የሆኑት ዶ/ር መስፍን አረዓያ ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውና በዚያው መግባታቸው ታውቋል። ዋና ኮሚሽነሩ ወደ አሜሪካ ያቀኑበት ትክክለኛ ምክንያት ይፋ ባይደረግም፣ ጉዟቸው የተሰማው አገዛዙ የኦህዴድ/ብልጽግናን አጀንዳ ለማስፈጸም አስቸግረዋል ያላቸውን ከ200 በላይ የምክክር ኮሚሽኑ ተሳታፊዎችን ከየአልጋ ቤታቸው አፍኖ ወደ አልታወቀ ቦታ በወሰደበት ማግስት መሆኑ ጉዳዩን አነጋጋሪ አድርጎታል። የኮሚሽኑ ገለልተኛ አለመሆንና የአገዛዙ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈጸሚያ መሣሪያ መሆን በተለያዩ ወገኖች በከፍተኛ ደረጃ ሲተች የቆየ ሲሆን፣ የዋና ኮሚሽነሩ ወቅታዊ የአሜሪካ ጉዞ ከዚሁ የኮሚሽኑ ውጥረት፣ ተዓማኒነት ማጣት እና ከተፈጠረው አፈና ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል የፖለቲካ ታዛቢዎች ግምታቸውን አስቀምጠዋል። ዝርዝር መረጃዎችን ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል። ኢትዮ 251 ሚዲያ የነጻነት አንደበት!
6 881
18
የአገዛዙ መዋቅራዊ ውድቀት፣ የፖለቲካ ሆድ-አደሮች እና የፋኖ ስትራቴጂካዊ ድል! (ኮረኔል ሞገስ ዘገዬ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አማካሪ!) በብልፅግና አገዛዝ ዘመን
የአገዛዙ መዋቅራዊ ውድቀት፣ የፖለቲካ ሆድ-አደሮች እና የፋኖ ስትራቴጂካዊ ድል! (ኮረኔል ሞገስ ዘገዬ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ 1ኛ ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አማካሪ!) በብልፅግና አገዛዝ ዘመን በየብሔሩ ስም የተደራጁ፣ ሕሊናቸውን ለሆዳቸው ያከራዩና መብላት-ማደርን ብቻ ዓላማቸው ያደረጉ የፖለቲካ ሆድ-አደሮች ሀገርንና ሕዝብን ለከፍተኛ መከራ ዳርገዋል። ትግራዋይ ሁኖ ትግራይን፣ አማራ ሁኖ አማራን፣ ኦሮሞ ሁኖ ኦሮሞን የካደው ይህ ርካሽና ፀረ-ሕዝብ ኃይል፣ በሁለቱ ሕዝቦች መካከል የጋራ ውይይትና ሰላማዊ የመፍትሔ በሮች እንዳይከፈቱ በማድረግ ሀገሪቱን ወደ አሰቃቂ ደም መፋሰስ መርቷታል። የዚሁ ቅጥረኛ ስብስብ ሴራ ውጤት የሆነው ጦርነት የወጣቱን ሕይወት እንደ ቅጠል አርግፎታል። ዛሬም ቢሆን እነዚህ የስርዓቱ አሽከሮች የሕዝብን ደም እያፈሰሱ የአገዛዙን የስልጣን ዘመን ለማራዘም ይፋገታሉ። በሌላ በኩል፣ የስርዓቱ ዙፋን ጠባቂ የሆነውና በደሞዝ የተሰማራው የመከላከያ ሰራዊት ለድሃ ልጅ ደንታ በሌለው አገዛዝ እየተገፋፋ በየገደሉና በየጫካው ሲረግፍ፣ ይፋዊ የሕዝብ ወገንተኝነት ያለውና ያለ ደሞዝ ለነፃነት የሚታገለው የፋኖ ኃይል ግን የአገዛዙን ሰራዊት በማማረክና መዋቅሩን በመበታተን ላይ ይገኛል። የስርዓቱ አባላትም ቢሆኑ የሥልጣኑን መጨረሻና የሕዝቡን ምሬት ተረድተው እጃቸውን በሰላም በመስጠት ላይ ናቸው። የዚህ ፋሺስታዊ አገዛዝ አካሄድና ውድቀት ከቀደመው የደርግ አገዛዝ የተለየ አይደለም። ደርግ በጥቁር ሳምንትና በቀይ ሽብር አደባባይ ላይ የሀገሪቱን 60 ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ምሁራን በመረሸን ሀገሪቱን አእምሮ-አልባ አድርጎ፣ የወጣቶችን በሬሳ ላይ የጥይት ዋጋ ሲያስከፍል ነበር። ከ17 ዓመታት መራራ የሕዝብ ትግል በኋላ ግን መሪዎቹ ፈርጥጠው ኢሕአዴግ ሥልጣኑን ተረከበ። ኢሕአዴግም በሐሰተኛ ትርክትና ዲሪቶ 27 ዓመታት ገዝቶ፣ በገዛ እጁ ኮትኩቶ ባሳደገው "የመደመር" ፍልስፍና አሸባሪው የብልፅግና ቡድን ተወለደ። ብልፅግና ሥልጣን ከያዘበት ዕለት ጀምሮ ሕዝብን በመጨፍጨፍ፣ በማፈናቀል፣ መሠረተ ልማቶችን በማፍረስና የሐሳብ የበላይነትን በማጥፋት ሀገሪቱን ወደ አደጋ ገፍትሯታል። ይህንን ፋሺስታዊ ሥርዓት ለመገርሰስና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ፋኖ የሚከተለው ወታደራዊና ስትራቴጂካዊ ጥበብ ከፍተኛ ብስለት ያየንበት ነው። በትጥቅ ትግል ውስጥ የዘመቻ ስልትን ጠንቅቆ ማወቅ፣ ሰራዊቱን ለትልቅ ተልዕኮ ማዘጋጀት፣ የጠላትን ወቅታዊ እንቅስቃሴ፣ የኃይል አሰላለፍና የሰርጎ-ገብ መዋቅር በጥብቅ መከታተል፣ እንዲሁም ወታደራዊ ምስጢርን በጥበብ መጠበቅ ዋነኛ የስኬት ቁልፎች ናቸው። ፋኖ እነዚህን መርሆች ጠንቅቆ በመረዳቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከሽምቅ ውጊያ አልፎ መደበኛ ውጊያን የሚመራ ጥበበኛ ኃይል መሆኑን አስመስክሯል። በወታደራዊ ሳይንስ የታወቁትን አምስቱን የውጊያ ዓይነቶች፦ 1. የመከላከል ውጊያ 2. የመመለስ ውጊያ 3. የማጥቃት ውጊያ 4. የደፈጣ ውጊያ 5. የከተማ ውጊያ ፋኖ በጥራትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን በመተግበር ላይ ይገኛል። በሽምቅ ውጊያ ስልቱ የአገዛዙን የጦር ማሽነሪ ኢላማ ያደረገ የማጥቃት እርምጃ በመውሰዱ፣ የጠላትን ኃይል በመደምሰስ ከፍተኛ ድል እያናጸፈና በሕዝቡ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት መቀነስ ችሏል። በሐሳብ የበላይነት የማያምነው ብልፅግና፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ውሸቶችን፣ ፍርሃትንና ክህደትን ተሸክሞ የሚኖር በድን አገዛዝ በመሆኑ ሀገሪቱን አዋርዶ እርቃኑን ቀርቷል። በአማራ ሕዝብ ላይ ከተፈጸመው ጅምላ ጭፍጨፋ፣ የእናትና እህቶች መደፈር፣ የንብረት ውድመትና የአዲስ አበባ ከበባ አንጻር ይህንን አገዛዝ ታግሎ ከማሸነፍና ለፍርድ ከማቅረብ ውጭ ሌላ አማራጭ የለም። የኦሮሞ ሕዝብም ቢሆን በብልፅግና የሐሰት ትርክትና የፖለቲካ ቁማር ምክንያት ልጆቹን ወደ ጦርነት እያካሄደ ሀብቱን ለዚሁ ፋሺስታዊ ሥርዓት እንዲገብር ተገዷል። ቋንቋና ባህል በፍቅርና በውበት እንጂ በኃይልና በጫና እንደማያድግ (ለአብነት እንደ እንግሊዝኛ) አገዛዙ ሊረዳ አልቻለም። በዚህ የጨለመ ዘመን ውስጥ ለሕዝባቸው ድምፅ የሆኑ የቁርጥ ቀን ልጆች መውጣታቸው ግን የታሪክ ተስፋችን ነው። ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በሕይወቱ ፈርዶ ለሕዝቡ ድምፅ ሆኖ አልፏል፤ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በእድሜያቸው ማጠቃለያ በእስር ቤት እየተሰቃዩ እውነቱን መናገራቸውን አላቆሙም። መስከረም አበራ፣ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ አቶ ዮሐንስ ቧያለውና ሌሎች በርካታ ወንድምና እህቶች የአገዛዙን ግፍ ፊት ለፊት በመጋፈጣቸው ብቻ በጨለማ ቤት ውስጥ አሰቃቂ እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛል። በአንጻሩ ሕሊናቸውን ሽጠው ሕዝባቸውን የሚያስጨፈጭፉ "ጥቁር አማራዎች" ነገ በሕዝብና የታሪክ ፍርድ ቤት መጠየቃቸው የማይቀር ነው። ለአማራ የነፃነት ትግልና ለሀገር ህልውና ሲሉ ከፍተኛ ዋጋ የከፈሉት እነ ጀነራል አሳምነው ጽጌ፣ አስቻለው ደሴ፣ ውባንተ አባተ፣ ናሁሰናይ አንዳንጌ፣ አስር አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ፣ ሞላ ደስየ፣ መሐመድ ቢሆነኝ፣ ሞክታር እንድሪስ፣ ጎሹ ከበደ፣ አለሙ ገብሩና ሞላ ከበደ የተቀደሰውን የአላማ ጽናትና መስዋዕትነት በተግባር አስተምረውናልም። ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ከአስር በላይ የነፃነት ግንባሮች (የአማራ፣ የሱማሌ፣ የሲዳማ፣ የአፋር፣ የትግራይ፣ የጋምቤላ፣ የወላይታ፣ የጋሞ ወዘተ) መፈጠራቸው አገዛዙ የደረሰበትን የፖለቲካ ከሰረና የመዋቅር መፈራረስ ያሳያል። በጂኦ-ፖለቲካው ረገድም አገዛዙ ከጎረቤት ሀገራት ከኤርትራ፣ ከጂቡቲና ከሱማሊያ ጋር በመቆራረጡ የተነጠለ ሆኗል። ይባስ ብሎም እንደ አቡዳቢው ቢን ዛይድ ካሉ የውጭ አጥፊ ኃይሎች ጋር በመሻሪክ የሱዳንንም ጦርነት ጨምሮ ቀጣናውን ለማበላሸት የሚጫወተው አደገኛ ሚና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጋልጧል። የአባቶቻችንን ኩሩ የታሪክ ውርስ የያዝን፣ ባርነትን የምንጸየፍና አትንኩኝ ባይ የሆንን ሕዝቦች፣ ይህንን ወራሪና ፋሺስታዊ ኃይል በማፍረስ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን ጋር በተከባበረና በሰላማዊ መንገድ የምንኖርባትን አዲስ ሀገር ከመገንባት ወደ ኋላ አንልም። ፋሺስታዊው ሥርዓት ለፍርድ ቀርቦ የሕዝብ ሉዓላዊነት እስኪረጋገጥ ድረስ ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል! አብይ አህመድ ይሸንፋል፣ አሳረኛው ፋኖ ያሸንፋል!
7 107
19
📌የነሐሴ 12 ታሪካዊ አንድምታና የዛሬው የህልውና ትግላችን! (ሙሉጌታ አንበርብር) በሀገር ግንባታና በሉዓላዊነት ማስከበር ሂደት ውስጥ ታሪክ በአጋጣሚ የሚከሰቱ ሁነቶች ስብስብ ሳይሆን፣ የትውልዶች
📌የነሐሴ 12 ታሪካዊ አንድምታና የዛሬው የህልውና ትግላችን! (ሙሉጌታ አንበርብር) በሀገር ግንባታና በሉዓላዊነት ማስከበር ሂደት ውስጥ ታሪክ በአጋጣሚ የሚከሰቱ ሁነቶች ስብስብ ሳይሆን፣ የትውልዶችን እጣ-ፈንታ የሚቀርፅና የጂኦ-ፖለቲካ ሚዛንን የሚወስን ሳይንሳዊ ሂደት ነው። ነሐሴ 12 ቀን በኢትዮጵያ የታሪክ መዝገብ ውስጥ ተራ የቀን መቁጠሪያ አይደለም፤ የሁለት ታላላቅ የሀገር ምሰሶዎች—የዳግማዊ አፄ ምኒልክ (እምዬ) እና የእቴጌ ጣይቱ ብጡል (ብርሃን ዘኢትዮጵያ)—የተቀደሰ የልደት ቀን ነው። የሁለቱ ታላላቅ መሪዎች በተመሳሳይ ቀን መወለድ ታሪካዊ አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የቆመችበት የወታደራዊ ስትራቴጂ፣ የዲፕሎማሲ ጥበብና የመንግሥትነት መዋቅር (Statecraft) ጥንድ ምሰሶዎች የታሰሩበት ድንቅ ዕለት ነው። በ1836 ዓ.ም ዕለት የተወለዱት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ፣ ሀገርን በወታደራዊና በፖለቲካዊ ብስለት የመምራት፣ የተቀደሰውን የሀገር ፍቅር ከዘመናዊ ቴክኖሎጂና መዋቅራዊ አስተዳደር ጋር የማዋሃድ ታላቅ ጥበብ ያሳዩ አርቆ-አሳቢ መሪ ነበሩ። ዓለም አቀፉ የጂኦ-ፖለቲካ ማዕበል አፍሪካን ለመቀራመት በተነሳበት በዚያ የጨለመ ዘመን፣ ምኒልክ የትራንስፖርት፣ የቴሌኮሙኒኬሽን፣ የባንክና የዘመናዊ ትምህርት መሠረቶችን በመጣል ሀገሪቱን ከኋላቀርነት ወደ ዘመናዊ መንግሥትነት የተሻገሩ ባሕረ-ጥበብ ነበሩ። ከሁሉ በላይ ደግሞ በዐድዋ ጦርነት ወቅት ልዩነቶችን አጥበበው መላውን ሕዝብ በአንድ ሀገራዊ ዓላማ ሥር አሰልፈው ያቀናጁበት ስትራቴጂ፣ ዛሬም ቢሆን ለተበታተነውና ለተከፋፈለው የፖለቲካ ምህዳራችንና ለሕልውና ትግላችን ታላቅ መዋቅራዊ ትምህርት የሚሰጥ ነው። በሌላ በኩል በ1832 ዓ.ም ዕለት ወደዚች ዓለም የተቀላቀሉት እቴጌ ጣይቱ ብጡል፣ የዲፕሎማሲያዊ ብልሃትና የማያወላውል የሉዓላዊነት ቁርጠኝነት ምሳሌ ናቸው። የአውሮፓ ኃያላን በውልና በስምምነት ስም ሀገርን በጽሑፍ ወጥመድ ሊከተቱ በሞከሩበት ወቅት፣ የውጫሌ ስምምነት አንቀጽ 17ን መዋቅራዊ ሸፍጥ ቀድመው በመረዳት ውድቅ ያደረጉት እቴጌ ጣይቱ ነበሩ። "እኔ ሴት ነኝ፤ ጦርነት አልወድም፤ ነገር ግን ይህንን ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ" ያሉት የማያወላውል የአቋም መስመር፣ ዛሬ በዲፕሎማሲና በትርክት የበላይነት (Narrative Dominance) ትግል ላይ ላለነው ወገኖች ታላቅ የስነ-ልቦና ስንቅ ነው። በዐድዋ ጦር ግንባርም የነበራቸው የመረጃና የስንቅ ስምሪት ሚና፣ ወታደራዊ ድል ያለ አስተማማኝ ከበሮና ስትራቴጂካዊ ደጋፊ ሊረጋገጥ እንደማይችል በተግባር ያስመሰከረ ነበር። እነዚህ ሁለት ጀግኖች ለዛሬው የሕልውና ትግላችን የሚያስተላልፉት አበይት ትምህርት አለ። ወታደራዊ ጥንካሬ ያለ ዲፕሎማሲያዊ ብልሃት፣ ወይም ዲፕሎማሲ ያለ ወታደራዊ ጡንቻ ዘላቂ ውጤት ሊያመጣ አይችልም። ዛሬም የሕልውና ትግላችን መሬት ላይ ያለውን ወታደራዊ ሚዛን ከመቀየር ጎን ለጎን፣ የትርክት የበላይነትን በመጨበጥ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ የሚያሳምን ዲፕሎማሲያዊ አቅም መገንባት ይኖርበታል። እቴጌ ጣይቱ በሉዓላዊነትና በርስት ጉዳይ ላይ ድርድር እንዳልተቀበሉ ሁሉ፣ ዛሬም የታሪክ ስርቆት፣ የቦታ ስሞች ለውጥና የመሬት ንጥቂያ በሚካሄድበት ዘመን የማያወላውል አቋም መያዝ የሕልውናችን ዋነኛ መሠረት ነው። ታሪክን ማወቅ ያለፈውን ማስታወስ ብቻ ሳይሆን፣ የወደፊቱን የትግል አቅጣጫ የመቀየሻ መነጽር ነው። የነሐሴ 12 የልደት ባለቤቶች የሆኑት አፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ የተዉልን ውርስ—የሀገር ፍቅር፣ የወታደራዊ ብቃት፣ የዲፕሎማሲ የበላይነትና የጽናት መስመር—ዛሬ በፈተና ውስጥ ላለው ሕዝባችን የታሪካዊ ድል መሪ መንገድ ነው። እነዚህን ታሪካዊ መሠረቶች አጽንተን በመያዝ፣ የተደቀነብንን ወታደራዊና ፖለቲካዊ አፈና በጥበብና በጽናት እንመክታለን! ትግላችን ያሸንፋል!
4 626
20
📌 በጀነራሎች እየተተካ የሚገኘው የፖሊስ መዋቅርና የአገዛዙ የመጨረሻ ሙከራ! (ሙሉጌታ አንበርብር) የአምባገነን ሥርዓቶች የፖለቲካ ቅቡልነት (Political Legitimacy) ሲክሰም፣ የሕዝብ አ
📌 በጀነራሎች እየተተካ የሚገኘው የፖሊስ መዋቅርና የአገዛዙ የመጨረሻ ሙከራ! (ሙሉጌታ አንበርብር) የአምባገነን ሥርዓቶች የፖለቲካ ቅቡልነት (Political Legitimacy) ሲክሰም፣ የሕዝብ አመፅ ሲበረታባቸውና የሲቪል መዋቅራቸው ሲፈራርስ የሚወስዱት የመጨረሻው የተስፋ መቁረጥ እርምጃ፣ የሕግ ማስከበር ተቋማትን ወታደራዊ ማድረግ (Militarization) ነው። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየታየ ያለው የፖሊስና የደኅንነት ተቋማትን በከፍተኛ የመከላከያ ጀነራሎች የመተካት አደገኛ ሂደት፣ አገዛዙ የገባበትን ጥልቅ የሕልውና ሥጋትና የስርዓቱን የመጨረሻ መፍጨርጨር ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የፖሊስ ኮሚሽኖችንና የብሔራዊ መረጃ አገልግሎቱን በጦር አዛዦች ሥር ማስገባት፣ ሀገሪቱ በይፋ በወታደራዊ ጁንታ (Military Junta) አስተዳደር ሥር መውደቋን የሚያረጋግጥ የአደባባይ ሀቅ ነው። ይህ መዋቅራዊ ንጥቂያ በአጋጣሚ የተከሰተ ሳይሆን፣ የሲቪል አስተዳደሩ መፍረስ ያስከተለው አስገዳጅ እርምጃ ነው። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን በሌ/ጀነራል አስራት ዴኔሮ፣ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንን በጀነራል ድሪባ መኮነን፣ እንዲሁም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንን በሌ/ጀነራል ጥጋቡ ይልማ ሥር ማዋቀር፣ ፖሊስን ከሕግ አስከባሪነት ወደ ወታደራዊ የጦር ግንባር ተዋጊነት ለማውረድ የተደረገ ስልታዊ ስምሪት ነው። ከዚህም አልፎ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትን (NISS) በሜጀር ጀነራል ማዕረግ ወዳለው ወታደራዊ አመራር ለማዛወር መታቀዱ፣ የሲቪል ደኅንነት ተቋሙን ወደ ወታደራዊ የስለላና የጥቃት ማዕከልነት የመለወጥ ሂደት ነው። ይህ አካሄድ የሀገር መከላከያንና የውስጥ ጸጥታን ልዩነት በማጥፋት፣ አጠቃላይ ሀገሪቱን በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ለማስተዳደር የተወጠነ ነው። ታሪክን ስንመረምር፣ ሥርዓቶች ወደዚህ ዓይነት የፖሊስ መዋቅር መበተን የሚያመሩት በራሳቸው የሲቪል ኃይል ላይ እምነት ሲያጡ ነው። አገዛዙ በመደበኛው ፖሊስ ላይ "በሕዝቤ ላይ አልተኩስም" የሚል እምቢተኝነት ሊገጥመኝ ይችላል በሚል ከፍተኛ የጥርጣሬ ሥነ-ልቦና ውስጥ ወድቋል። በተጨማሪም፣ የፖሊስ አባላት መሣሪያቸውን ይዘው ወደ ሕዝባዊ ትግሉ እየተቀላቀሉ መምጣታቸው፣ አገዛዙን የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መፍትሔ ከማመንጨት ይልቅ ከተሞችን በጥብቅ ወታደራዊ ቁጥጥር ሥር ወደ ማዋል አጣዳፊ ሥጋት ገፍቶታል። ይህ ወታደራዊ አስተሳሰብ በከተሞች ሲተገበር ግን የሚያስከትለው አደጋ እጅግ የከፋ ነው። ጀነራሎች ሕግን የማስከበር ሳይሆን "ጠላትን የማጥፋት" ልምዳቸውን በሲቪል ዜጎች ላይ ሲያዉሉ፣ ፖሊስ ከሕዝብ ጠባቂነት በቀጥታ ወደ ሕዝብ ጠላትነት ይለወጣል። ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚፈጸሙ እስራቶች፣ አፈናዎችና ድብደባዎች መዋቅራዊ ይሆናሉ። መደበኛ የፖሊስ አባላትም በጀነራሎች ጥብቅ ቁጥጥር ሥር ወድቀው የጥፋት መሣሪያ እንዲሆኑ ይገደዳሉ። ይሁን እንጂ፣ የጀነራሎች ሹም-ሽር የስርዓቱን ጥንካሬ ሳይሆን የመጨረሻ መፍጨርጨሩን የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው። በወታደራዊ ኃይል ብቻ ለመቆየት መሞከር የታሪካዊ አምባገነኖች የመጨረሻው ምዕራፍ ነው። በየደረጃው የሚደረገው የጀነራሎች ስምሪት መሬት ላይ ያለውን የኃይል ሚዛን ሊቀይረው አልቻለም። የሰራዊቱና የፖሊስ አባላት የመዋጋት ወኔ ፈጽሞ በከሰመበት ሁኔታ፣ ጀነራሎች ቢሾሙም የሕዝቡን የነፃነትና የፍትሕ ጥያቄ በማስፈራራት መመለስ አይቻልም። ሕዝባዊ ትግሉ የወታደራዊ ጀነራሎችን ግርማ ሞገስና ማስፈራሪያ ጥሶ የመሄድ አቅም ገንብቷል። በመሆኑም፣ ይህንን የተደቀነ ወታደራዊ አምባገነንነት ለመመከት ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል። መደበኛው የፖሊስ አባል የጨቋኙን ጀነራሎች ሕገ-ወጥ ትዕዛዝ ባለመቀበል ከሕዝቡ ጎን ሊቆም ይገባል። የከተሜው ማኅበረሰብም በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች የተቃጣበትን ወታደራዊ አፈና በሕዝባዊ እምቢተኝነት መስበር አለበት። ሕዝባዊ የነፃነት ኃይሎች ይህንን የፖሊስ መዋቅር መበተን ታሳቢ ያደረገ ስልታዊ የትግል አቅጣጫ በመቀየስ፣ ወታደራዊ ጁንታውን በሕዝባዊ ማዕበል ጠራርገው ሊያስወግዱት ይገባል። የፖለቲካ ቅቡልነቱን ያጣና በሕዝብ የተጠላ ሥርዓት በጀነራሎች ምሽግ ተከልሎ ሊኖር አይችልም። የሕግ የበላይነትና የሕዝብ ሉዓላዊነት የሚያብብባትን፣ ከፖለቲካና ከወታደራዊ ተጽዕኖ ነፃ የሆነ የሕግ አስከባሪ ፖሊስ የሚገነባባትን አዲስ ኢትዮጵያ የማረጋገጡ ትግል ከምንጊዜውም በላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ትግላችን ያሸንፋል!
6 302