cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
410 021
مشترکین
-36424 ساعت
-2 4557 روز
-7 44530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

"…በሉ ጉማ ሰቀታን ጥሩልኝ። እኔምለው ይሄ ግማሽ ጉራጌ፣ በእግሩ በሜክሲኮ በኩል አማሪካ የገባው የመርካቶ ልጅ፣ አሁን የኦሮሞ ነፃ አውጪ የሆነው ዳንኤል ዳባ በለፀገ እንዴ? ጉማዬ ጉማ የድሬው ልጅ አፍቃሬ ወያነው፣ ፀረ ዐማራው ጉማ ና ይህን መልስልኝ። ዳኒ በልጽጓል ወይ…? • ዶካር ደግሞ ምንድነው? 😂 "…ሐረርጌ ተርቦ ስለ ካካቤት መጨነቅ ምን የሚሉት ነው? እነ ጃዋርስ የት ጠፉ…? ኧረ ተንቀሳቀሱ። የካካ ቤቱ እህል ሲገኝ ይደርሳል።
نمایش همه...
👍 410😁 118 31🙏 16🔥 7🏆 4🤯 1
"…ለሽንት እና ካካ ቤቱ… "…የአባ መዓዛ ተማሪው፣ የቀድሞው ዝነኛ ሰባኬ ወንጌል፣ አሁን መኖሪያውን በሀገረ አማሪካ ያደረገው ቀሲስ ደረጀ ስዩምም ለካካ ቤት ማሠሪያው 5 ሺ ብር መርዳቱን ራሱ በፌስቡክ ገጹ ለጥፎ ሴቶች በእልልታ፣ ወንዶች በጭብጨባ አንዴ አመስግኑልኝ ብሏል። 5ሺ ብር በዶላር ሲመታ ስንት ነው ማለት ነው? "…ድሮ ጎበዝ መምህር ነበር እኔ ሳውቀው። በነገራችን ላይ ደሬም ኦሮሞ ነው ማለት ነው…? …ኦሮሞ ከሆነ ደግሞ ለዐማራና ለትግሬ ባይመለከተው ባይራራላቸው እንኳ እነ አቢይ IMFን ለመሸወድ ሲሉ ላመጡት የማጭበርበሪያ ዘዴ እወደድ ብሎ፣ በንጉሡ ፊት ሞገስ አገኝ እንደሁ ብሎ ለካካ ማሠሪያ 5 ሺ ብር ከሚያዋጣ ለተራበው ለሐረርጌ ኦሮሞ ዳቦ መግዣ ቢያስተባብር ምንአለበት? "…በወይራ ጢስ የምትጠነቁለው የሻሺቱን የልጅ ልጅ የአቢይ አሕመድን እናት ባለ ራዕይ ብሎ ማንቆለጳጰሱም አልዋጥህ ነው ያለኝ። እኔ ግን ምን ሆኜ ነው? እስከዛሬ ያልለኮፍኩት ደሬ ብቻ ነበር። ይሄ ዓይኔ ወስዶ ይኸው ከወዳጄ ከደሬም ጋር አላተመኝ። አሁን ይህን በማለቴ ደሬም ይቀየመኝ ይሆን…? የራስዎት ጉዳይ…😂 ኬሬዳሽ። "…ወይ የካካ ቤት ከስንቱ ሊያጣላኝ ነው ደግሞ…
نمایش همه...
👍 115😁 28 12🔥 4🏆 2
ጥያቄ ነው። "…ትግሬ ቢርበውም ራያና ወልቃይትን ከሰጣችሁኝ እችለዋለሁ ብሏል። ዐማራ አቻዮ ብረት ስለሆነ ራቡን እየተጋፈጠ ይገኛል። ሐረርጌ ራቡ ስለጠናበት ፈንቅሎ ወጥቶ ሀረር እና አዲስ አበባ ድረስ መጥቶ ሜዳ ላይ ፈስሷል። ይሄ ሁሉ ሆኖ ሳለ ግን ግራ የሚያጋባ ነገር እየታዘብኩ ነው። "…ለራባቸው ዜጎች ምግብ ለምኖ መስጠት፣ ራባቸውን ማስታገስ ነው ወይስ ሽንትቤት ልሠራልህ ነውና የሽንት ቤት ማሠሪያ ብር አዋጡልኝ ማለት? "…እሺ እናንተ አቢቹም፣ አቢይም፣ ሽሜም ያለ ሃሳብ፣ ያለ ችግር ስለምትበሉ ሽንት ቤት ያስፈልጋችኋል። የተራበው ሕዝብ ካካ ለማድረግስ ከየት ያመጣዋል? ሰው ሲበላ እኮ ነው ካካ የሚለው? ምን ጉዶች ላይ ነው የጣለን የፈጣሪ ያለህ? "…ደግሞ እኮ በዶላር ሁላ ነው የሚለምኑት። ካካው ከየት ይመጣል ነው የምልህ?
نمایش همه...
👍 150😡 26😁 23 14🤔 2🕊 1
"…መጪው በዓል ማለት ፋሲካ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው አይደል እንዴ? • ሳንሰማ ካላንደሩ ከተቀየረ ብዬ ነው።
نمایش همه...
👍 51😁 23🏆 6🙏 4😡 4🔥 2
መልካም… አሁን ደግሞ በርዕሰ አንቀጹ መሠረት በተለይ የኦሮሞ ነጻ አውጪ አፈቀላጤዎች በጨዋ ደንብ ሓሳባችሁን ስጡ። • ማሳሰቢያ፦ ሓሳብ እንጂ ዱላ ይዘህ መጥተህ ሜንጫህን እያወዛወዝክ ማለባሺ ምናምን ብትል አልሰማህም። ውይይት ልመድ። የእኔ ሥራ የሚያበሳጭም ይሁን የሚያስደስት፣ የሚያስለቅስም የሁን የሚያስቅ ሓሳብ አቀርባለሁ በዙያ ላይ ተረጋግተህ አንተ ትመልሳለህ ማለት ነው። "…እነ GGጂጂገግ እናንተ ደግሞ አረፍ በሉና ወደ በኋላ አጀንዳ ሰጥቼ ትንሽ አንዘረዝራችኋለሁ። ለአሁኑ አረፍ በሉ። ትእዛዜን ጥሰህ ዱላና ሜንጫ ይዘህ የምትመጣ ወነግም ሆነ "ከእስክንድርና ከሀብታሙ ራስ ውረድ የምትል GGጂጂገግ እቀነድብህሃለሁ። እቀስፍሃለሁ። ሰምተሃል። • ዳይ ወደ ውይይቱ። የፋኖን ሴራ አከሸፍኩ የሚለው የኦሮሞ መንግሥት የአቶ በቴን የግፍ ገዳዮች ከምን አደረሳቸው? ወይስ ገዳዩ ራሱ ነው?
نمایش همه...
"ርዕሰ አንቀጽ" "…የከሸፈው ሴራ የተሰኘውና በሁሉም መንግሥታዊና ክልላዊ መንግሥታት መገናኛ ብዙሃን የቀረበው ዘጋቢ ፊልም የከሸፈው ወዲያው ነበር። ፒፕሉ ኢግኖር ገጭቶት ነው ኩም ያደረገው። የኦሮሙማው ሓሳብና ምኞት የነበረው ሀገሪቷ ጠንካራ የሆነ የስለላና የደኅንነት ተቋማት እንዳሏት በማሳየት እና ሕዝቡንም "ምንም ብትሠሩ አይደለም በልባችሁ ብታስቡ እንኳን "በየሱስ ስም፣ በጌታቸው ስም" ብዬ እይዛችኋለሁ አታመልጡኝምም፣ አሳድጄ እይዛችኋለሁ፣ በቁጥጥር ስርም አውላችኋለሁ የሚል መልእክት ነበር ማስተላለፍ የፈለገው። ነገር ግን ያሰበው ሳይሆን በሌላ በኩል ዘጋቢ ፊልሙ ሌላ ጣጣ ነው ያመጣበት። "…አጥፍቼዋለሁ ያለው ፋኖ፣ ደምስሼዋለሁ ያለው ፋኖ፣ አቅሙ ደካማ ነው። በእጁም ያለው ቆመህ ጠብቀኝ የድሮ መሳሪያ ብቻ ነው ብሎ የሚያናንቀውና መግለጫም፣ ዜናም ሲሠራበት የከረመው የዐማራ ፋኖ መሀል አዲስ አበባ ድረስ ዘልቆ ገብቶም ተቀጣጣይ ፈንጂ፣ ቦንቦች፣ ክላሽን ጨምሮ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ይዞ በ3 ፋኖ ግማሽ ቀን መንገድ አዘግቶ ሲታኮስ መዋሉና መገኘቱን በሃላል ማወጁ መጥፎ መልእክት ነበር ያስተላለፈበት። የመንግሥትን መግለጫ እያመኑ አገዛዙን እንደ ቁምነገረኛ መንግሥት የሚቆጥሩት የዓለም መንግሥታት በሙሉ አገዛዙ እየዋሻቸው እንደሆነና የፋኖ ኃይላት ከሚጠበቀውም ከሚገመተውም በላይ የተደራጁ መሆናቸውን እንዲያምኑ ነው ያስገደዳቸው። ተገደዱ። ኪሣራ… "…አራዶቹ ምዕራባውያንም ሁል ጊዜ እንደሚያደርጉት ጊዜ ሳያጠፉ ነው በዐማራ ጉዳይ ለቃለ መጠይቅ ሰው በፈለጉ ጊዜ በቅርብ ወደሚያገኟቸው ትሪፕል AAA የእነ ቴዎድሮስ ትርፌ ዘንድ የደወሉት። እባካችሁ የፋኖ መሪዎችንም እንዴት እናግኛቸው? በማለት ጥያቄ ያቀረቡላቸው። እነ ቴዎድሮስ ትርፌም ወደ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ በመደወል የፋኖ መሪዎችን አነጋገሯቸው። ከሁለት ሰዓት በላይ በፈጀው የጋዜጠኞቹ ቃለመጠይቅ ውስጥ ዋነኛው ነጮቹ የፈለጉት ሁለት ጥያቄ ብቻ ነው። አንደኛው አዲስ አበባ የተደረገው ሙከራ ላይ እጃችሁ አለበት ወይ የሚል አንደኛው ሲሆን ለዚህም ፋኖዎቹ አዎ እኛ ነን፣ ገና ከዚህ የባሰ ተግባር እንፈጽማለን። ይኼኛው ቅምሻ ነው በማለት የመለሱላቸው ሲሆን ድርድርን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄም "አረመኔ ጨፍጫፊ አቢይ አሕመድን ለፍርድ ሳናቀርብ፣ 4 ኪሎም ሳንገባ ድርድር የለም።" በማለት ነበር እቅጩን የነገሯቸው። ምዕራባውያኑም ይህቺን ነበር የፈለጉት ቁርጣቸውን ዐውቀው ጮጋ ብለው ወደ ራሳቸው ውሳኔ ነው የሄዱት። "…የአሜሪካን እንጃላቷ እንጂ እነ እንግሊዝ፣ ካናዳ ወዘተ ወዲያውኑ ነው ዜጎቻቸው ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ጉዞ እንዲያዘገዩ መግለጫ ያወጡት። ይሄ ማለት በራሳቸውም የደረሱበት ጉዳይ አለ ማለት ነው። አዲስ አበባ የገባ ኃይል አለ ብለው ያምናሉ። ዛሬ እንኳ አዲስ አበባ ውስጥ የተገደለው የፀጥታ ሓላፊ አገዛዙን አስደንግጦታል። መረጃውንም እስከአሁን ድረስ አገዛዙ ይፋ አላወጣውም። ሰሞኑንም የሆነ ነገር ይከሰታል ብለው እየተሸበሩ ነው። እናም የከሸፈው ሴራ በተለቭዥን ዘጋቢ ፊልም ብቻ ነው እንጂ መሬት ላይ የሚገርም ሆኗል። "…ወደ ጥያቄው እንገባለን…? "…የዐማራ ፋኖን ሴራ ለማክሸፍ ኦሮሙማው ተአምር መሥራቱን ሲበጠረቅ ቆሞ ሲያጨበጭብ የነበረው ኦሮሞው መሆኑን ስታይ ግን በሳቅ ነው የምትፈርሰው። እነ ጉማ ሰቀታ፣ እነ ዳኒ ዳባ፣ ወዘተረፈ የፋኖ ሴራ ከሸፈ እያሉ ከብልፅግና በላይ ላንቃቸው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሲጮሁ እያየሁ እነዚህ ሰዎች ምን ዓይነት ክትባት ነው የዘለላቸው ይሆን በማለት ወደ መጠየቅ ነው የሄድኩት። "…ይሄ ያደነቃችሁት እና የዐማራን ፋኖ ሴራ አከሸፈ ብላችሁ ያንጨበጨባችሁለት የኦሮሙማ ብልጽግና የስለላ ተቋም፣ የደኅንነት መሥሪያ ቤት፣ የፖሊስም ኃይል "6 ፖሊሶች ሆነው ከሌሊቱ 6 ሰዓት፣ ከሆቴሉ አውጥተው፣ በገዛ ቀበቶው የፊጥኝ አስረው በ6 ጥይት በሳስተው፣ በገዛ ሀገሩ በመቂ ከተማ ቆሻሻ መጣያ ስፍራ ወስደው የጣሉት አቶ በኬ ኡርጌሳን የገደሉት እስከአሁን እንዴት አልተያዙም። ወደ ኋላ ሄጄ ሃጫሉ ሁንዴሳን መኪናው ውስጥ አፍኖ ገድሎ ጎኑን በጥይት ያፈረሰው አካል ምነው እስከዛሬ የያዘው ሰው የለም? አይ ኦሮሞ አለ አቢይ ዐማራ ላይ እንዳፈጠጥክ የአንተን ልጆች ቀንድሸው፣ ቀንድሸው ሊጨርሱልህ ነው ኦህዴዶች? • ሌሊት 6 ሰዓት፣ 6 ፖሊሶች፣ በ6 ጥይት በኦሮሚያ መሬት ኦሮሞውን ሰው የገደሉት ሰዎች ከምን ደረሱ? ለማለት ነው? • አስመሰግናለሁ…! • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ…!
نمایش همه...
👍 976 90😁 24👌 22🔥 16🤯 16🙏 11🏆 11
"…የዛሬው "ርዕሰ አንቀጼ" ይህን ምስኪን ደመ ከልብ የተደረገ ሰው ጉዳይ ስለሚመለከት ለመልሱ የኦሮሞ ነፃአውጪዎች ተዘጋጁ። • አንድ ሦስት ደቂቃ ጠብቁኝ መጣሁ…
نمایش همه...
👍 618🙏 45 27🔥 18😱 7🏆 6😁 4🕊 3🤔 2💔 1
መልካም… ያመሰግን ዘንድ የሚጠበቀው 1ሺ አመስጋኝ ሞልቷል። ከምስጋናው ቀጥሎ በቀጥታ የምንገባው ወደ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን በጥያቄ መልክ ነው የተዘጋጀ ነው። • ማሳሰቢያ ለ GGጂጂግግ አባላት እና አድናቂዎች በሙሉ። "…ሰሞኑን በፔጄ ላይ በፉጨት ተጠራርታችሁ መምጣታችሁ ይታወቃል። መምጣታችሁ ጥሩ ሆኖ ሳለ ነገር ግን ታከብሩት ዘንድ የቤቱን ሕግ በድጋሚ ልነግራችሁ እወዳለሁ። "…አብዛኛው የGGጂጂግግ አባላት ከርዕስ ውጪ ያልተጻፈ በማንበብ፣ ያልተባለ በመዘባረቅ ትታወቃላችሁ። በጩኸት፣ በሚገማ፣ በሚከረፋ፣ በሚሸት ስድብ ተናጋሪን በማጥረግረግ ሰውን በማሸማቀቅ ፀጥ በማሰኘት እንደምትታወቁ ይታወቃል። ይሄን አብሮአችሁ ተወልዶ፣ አብሯችሁ አድጎ አብሯችሁ ያረጀን ድንቁርና በፔጄ ላይ እንድታራግፉ አልፈቅድም። አንድ በሉ። "…ሌላው በምስጋና ሰዓት እግዚአብሔር ይመስገን የሚል ጽሑፍ ብቻ ነው የሚጻፈው። በዚያ ወቅት እናንት ኮሚንስቶች አደብ ገዝታችሁ ተቀመጡ እንጂ በምስጋናው መሃል ክፍት አፋችሁን እከፍታለሁ ማለት አይፈቀድም። ቤቱ ሥነ ሥርዓት ያለበት ቤት ነው። መንበጫበጫቻችሁን እዚያው የለመዳችሁበት እሺ? "…በተረፈ ለአቅመ አስተያየት መስጠት ያልደረሳችሁ ደናቁርት፣ ከተጻፈው ሓሳብ ውጪ የምትቀባጥሩም ብትኖሩ። "ቀንተህ ነው፣ ከራሱ ላይ ውረድ፣ እሱን አትንካብን፣ ይቦንስህሃል፣ አትደርስበትም፣ ከትግሉ ውጣ" ወዘተ የሚሉ ኮዋሻኮር የሆኑ ኮመንቶች ብትሰጡም በአፋችሁ እስካልተጸዳዳችሁ ድረስ መብታችሁ ነው። ለተቃውሞ ሓሳብም ቦታው ክፍት ነው። እኔን ብቻ ሳይሆን ሌላ አስተያየት ሰጪ መሳደብ ግን ያስቀስፋል። "…ብትበሽቁም፣ ብትናደዱም፣ ጨጓራችሁ ቢያርም፣ ቆሽታችሁ ቢነድም እንደምንም ዋጥ አድርጋችሁ በጨዋ ደንብ ሓሳባችሁን ተንፍሱ። ለኒው ካመርስ ነው። • ዝግጁ…?
نمایش همه...
🙏 687👍 271 89😁 18🔥 10🕊 9🏆 7👌 6🤯 2
"…እንበለ ደዌ ወሕማም፤ እንበለ ፃማ ወድካም፤ አመ ከመ ዮም፤ ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በፍሥሐ ወበሰላም… ፩፥ ምክረ አይሁድ "…በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥ ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤ ማቴ 26፥ 3-4 ፪፥ የመልካም መዓዛ ቀንም "…ኢየሱስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ፥ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው። ማቴ 26፥ 6-7                    ፫፥ የእንባ ቀን "…በስተ ኋላውም በእግሩ አጠገብ ቆማ እያለቀሰች በእንባዋ እግሩን ታርስ ጀመረች፥ በራስ ጠጕርዋም ታብሰው እግሩንም ትስመው ሽቱም ትቀባው ነበረች።” ሉቃ 7፥38 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
نمایش همه...
👍 1056🙏 435 184🕊 28🏆 21🔥 6🤯 5😁 2
ነገርየው እየበሰለ ነው። "…በየትኛውም ስፍራ እንደ እኔ ዓይነት አንድ መራታ ዐውቆ አበድ የግድ ያስፈልጋል። የግድ ነው። ሁሉም ለክብሩ፣ ለስሙ ሲል የሚጠነቀቅበትን ጉዳይ ነካክቶ አፈር ከደቼ የሚያበላ እንደ እኔ ዓይነት መራታ ያስፈልጋል። "…አስኳሉን ለማፍሰስ አሁን ቅርፊቱን እያሻሸሁ ነው። ኩርኩሜን ለማሳረፍ አሁን የእነ ሀብትሽን፣ የእነ 360ን ፀጉር እያሻሸሁ ነው። በጥፊ ከማጮሌና አይነስቡን ከማጥፋቴ በፊት ጉንጮቹን እየዳሰስኩ ነው። ዐማራ በሀብታሙ አያሌውም ሆነ በአበበ በለው መበጥበጥ የለበትም። "…አይደለም ለፀረ ዐማራው የትግሬው ፓስተር ለምን ኦነግ ጋር የፈለጋችሁበት ሄዳችሁ አታለቅሱም። ይኸው የእስክንድር ነጋና የሀብታሙ አያሌው ቡችላ ለወያኔው ፓስተር ሄዶ ሲከሰኝ ተመልከቱት። ምን እንዳያደርገኝ ነው አንት መሳቂያ። እኔ እኮ የምትቆጣኝ ጁንታ ሚስት አይደለም ያገባሁት። ገና ደም ነው የማስተፋህ አዳሜ። ሳይገባው ለሚንጫጫው መንጋ እኔ ምንም ቦታ የለኝም።  "…ለጊዜው ጋዜጠኛ ብሩክ ይባስን ብቻ ነው የማልነካው። ሌሎቹን ግን አልለቃቸውም። የእስክንድር ጉዳይ በጣም ቀላል ነው። እሱ በረሃ ስላለ ከወንድሞቹ ጋር ፋኖዎች ጋር ተመካክሮ ይሠራል። በእሱ ስም ዶላር ሰብሳቢው፣ ከፋፋዩ የጂጂግግGG መንጋ ነው ደቼ የማበላው። እንደ ሀብታሙ አያሌው ዓይነቱ ተመክሮ፣ ተዘክሮ አልሰማ ያለውን ነው በጋዜጠኝነት ስም ፋኖ ገዝቶ መከፋፈሉን የማስቆመው። የዳያስጶራ ዶላርም በእነ አበበ በለው እና ሀብታሙ አያሌው በኩል፣ በየGGጂጂግግ ዎች በፌክ ኢትዮጵያኒስት በኩል አይደለም መሄድ፣ መሰብሰብ ያለበት። ራሱ ምድር ላይ ያለው ፋኖ በመረጠው፣ በወደደው በኩል ነው ማለፍ የለበት። ቀልድ የለም። ደፈር ካላልኩ አይስተካከልም። በግል ሚስቴን አልቀማኝ፣ ርስቴን አልነጠቀኝ። ሂእ • መንጋ እያረፍክ ተንጫጫ…!
نمایش همه...
👍 177 20🙏 8🏆 7😁 6 4🔥 3