cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
381 867
مشترکین
-13224 ساعت
-1 3517 روز
-6 83830 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
"…በካቶሊክና በፕሮቴስታንቶች የፕሮሞሽን ብዛት ስለተሸፈነው ጥንታዊውን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት በተመለከተ እንዴት ያለ ርዕሰ አንቀጼን አዘጋጅቼ ነበር መሰላችሁ። "…ሰሞኑን እንግዶች ስለሚመጡ መኖሪያ ቤታችን ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ይጽዳ የሚል ቀጭን ትእዛዝ ከክብር ሚስት ቀጭን ትእዛዝ ስለወረደ እኔም በአቅሜ የወደቀብኝን ዕጣ አንሥቼ የቤቱን መስታወት ለማጽዳት ስል እንደ ወፍራም ዝንጀሮ ከጣሪያ ጣሪያ ስዘል ቆይቼ ገና አሁን መሬት መንካቴ ነው። የማዳም ቅመሞች ድካም፣ የሚስቶች፣ የእህቶች ድካም ዛሬ አይደል እንዴ ያየሁት። የመድኃኔዓለም ያለህ። "…አሁን ደግሞ ጨረስኩ ስል ቤተሰቡ አድሞ በል በል የምን ስልክ ላይ መጣድ ነው። አልጨረስክም። የቤቱን ደረጃና ምንጣፎች የሚያጸዳው ማሽን ቢሆንም ዕጣው የወደቀው አንተላይ ነው። እናም ሥራው የሚጠብቀው አንተኑ ተብዬ ወደዚያው ልነካው ነው። "…ዛሬ ብዙ የምሥራች፣ ቁንጥጥ፣ ልምዝግ የሚያደርግም ጦማር ለማዘጋጀት ዝግጁ የነበርኩ ቢሆንም የቤተሰብ ጉባኤው ፍርድ አላላወሰኝም። • ዳይ ወደ ጥግረራዬ… ጊዜ፣ ፋታ ካገኘሁ እመለሳለሁ። እስከዚያው በፋኖ ፍቅር የወደቀው የወለይ ስታሊን እና የዐማራ ፋኖ ቃለ የስብሰባ ጉባኤ ያዥ ሆኖ የተከሰተው የባለአደራው፣ የባልደራሱ የአዲስ አበቤው የእስክንደር ነጋ የአማሪካ ተወካይ የነበረው ኤርሚ ኤል ዋቅጅራን ዘገባ እየሰማሁ ልጠግረር። 😂😂😂 • 🖐🖐🖐
نمایش همه...
👍 1432😁 203 102🙏 66 30🏆 16🕊 15🤔 12👌 10🤯 8😱 8
Photo unavailableShow in Telegram
“…ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ።” መዝ 84፥7 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
نمایش همه...
🙏 1623👍 290 245🕊 30🏆 24 19🔥 17👌 7😁 5🤯 3 2
Photo unavailableShow in Telegram
• ጀምረናል ገባ ገባ በሉ…! "…አላችሁ አይደል…?
نمایش همه...
👍 771 91🙏 62😡 17🕊 14 8😁 6🤯 5🏆 1
Photo unavailableShow in Telegram
መጥተናል ገባ ገባ በሉማ…! "…ዘወትር በየሳምንቱ በእለተ ሐሙስ በኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የምናቀርብላችሁ ሳምንታዊ መርሀ ግብራችን አሁን ጀምሯል። የዛሬውንም ዝግጅታችንን፦ በ 👉YouTube https://www.youtube.com/live/W-w7yQ5WNh0?feature=shared 👉በረንብል /Rumble https://rumble.com/v56j2nm--ethiobeteseb.html 👉 ቴሌግራም / Telegram https://t.me/ethiobeteseb "…ሻሎም !  ሰላም !
نمایش همه...
🙏 279👍 155 46💔 10🕊 7👌 5😡 4🏆 1
Photo unavailableShow in Telegram
መልካም… "…እስከአሁን ርዕሰ አንቀጹ በ17 ሺ ሰው መነቡብን እያየሁ ነው። በርዕሰ አንቀጹ የተበሳጨም ሰው 😡 አላየሁም እስከአሁን። ቀጥሎ የሚቀርበው ደግሞ የእናንተ ሓሳብ የሚንሸራሸርበት መድረክ ነው። "…ዛሬ ከወትሮው ከተለመደው ሰዓታችን 1 ሰዓት ዘግይቶ የሚቀርበው የዕለተ ሐሙሱ የኢትዮ ቤተሰብ ሚድያ ዝግጅታችን እስኪደርስ ድረስ በርዕሰ አንቀጹ ላይ ሓሳብ እየሰጠን እንቆያለን። • 1…2…3…ጀምሩ…!✍✍✍
نمایش همه...
832👍 406🙏 55😡 23🕊 21 9🏆 8🤔 6🔥 3😁 3🤯 2
"ርዕሰ አንቀጽ" "…አቅም ያለው በአውሮጵላን፣ መለስ ያለው በመሂና፣ ሌላው በእግሩ ወደ አዲስ አበባ እየጎረፈ ነው። ጦርነቱን፣ ራቡን፣ እገታውን፣ ግድያውን፣ አስገድዶ መደፈሩን ሽሽት ዜጎች በሙሉ ወደ ሸገር አዲስ አበባ እየፈለሱ ነው። በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ከትግራይ፣ ከዐማራ፣ ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ፣ ከሱማሌ፣ ከጋምቤላ፣ ከሲዳማ፣ ከጉምዝ ተሰዶ ተከማችቷል። አፋር ብቻ ስለ መሰደዱ አልሰማሁም እንጂ በሙሉ አዱ ገነት ከትሟል አሉ። "…ዜጎች አዲስ አበባን ለስደት ተመራጭ ያደረጓት ደግሞ ቀሽሙ የኦሮሞ ብልጽግና ራሱን በራሱ ለማርካት ሲል በፈጠረው ፕሮፓጋንዳ ምክንያት ነው ተብሏል። በክልሎች ትምህርት ቤት ተቋርጧል። በአዲስ አበባ ግን እየተማሩ ነው። ስለዚህ ፍለሰት ወደ አዲስ አበባ እንደጉድ ነው። ቴሌቭዥኑ ሲከፈት አዳነች አበቤና አቢይ አህመድ በአውሮጳ ስታይል ከተማዋን ገነት እንዳስመሰሏት በስሎው ሞሽን፣ በቶፕ ቪው የድሮን ቀረጻ፣ የዲም ላይት የኮሪደር ልማቱን ደጋግመው ሲያሳዩ ዜጎች በበሳሶ፣ በሱዳን፣ በሊቢያ፣ በየመን በቀይባህር፣ በኬንያ ወደ ደቡብ አፍሪካ ምን አሰደደን በማለት ነው ወደ መሃል ሃገር እየፈለሱ የሚገኙት። "…አዲስ አበባ ደግሞ አብዛኛው ነዋሪዎቿ መንገድ ዳር በሚከፍቱት ሱቅ ውስጥ በሚሠሩት ሥራ ነበር ሚልዮኖች የዕለት እንጀራቸውን የሚበሉ የነበረው። አሁን በኮሪደር ልማቱ ምክንያት ጥርግ፣ ሙልጭ ተደርገው ፍርስርሳቸው ወጥቷል። ፒያሳ የሺዎችን ኑሮ ደግፎ የሚኖር ስፍራ ነበር። አራት ኪሎም እንደዚያው። ከአራት ኪሎ እስከ መገናኛ፣ ከፒያሳ እስከ ቄራ፣ ወዘተረፈ ሚልዮኖች ኑሮአቸውን የሚገፉበት ስፍራ ነበር። አሁን ሱቅ የሚባል በሙሉ ፈርሷል። የቀን ሠራተኛው፣ ተሸካሚ ወዛደሩ፣ ተሯሩጦ አዳሪው በሙሉ መዋያ የለውም። አጨብጭቦ ቀርቷል። ከባድ ነው የሚሰማው። "…መንገድ ላይ ሚዛን አስቀምጠው የሚሠሩ ህፃናት ሳይቀር ሚዛናቸውን ተቀምተው እየተባረሩ ነው። አሁን ለአረቦች እንተሸጠች በሚነገረው አዲስ አበባ ውስጥ  በአነስተኛና በመካከለኛ ሥራ የሚተዳደሩ ነዋሪዎች እሮሮ እየተበራከተ መጥቶአል። ያለምንም ምክንያት ንብረት ተወስዶባቸው ቤተሰብ አስተዳዳሪ ነን እባካችሁ አታስርቡን ቢሉም የሚሰጣቸው ምላሽ ገና በደንብ ትራባላችሁ የሚል ሆኗል። የብልፅግናው አገዛዝ ይዞ የተነሳው መሪ ቃል ድህነትን ለማጥፋት መጀመሪያ ደሀን ማጥፋት አለብህ የሚል እንደሆነ የተገነዘበ ነዋሪ ግን ያለ አይመስልም። "…የአራዳ ክፍለ ከተማ ሕዝቡን ሰብስቦ ፒያሳዎች በሦስት ወር ውስጥ ቤታችሁ ስለሚፈርስ ተዘጋጁ ይሏቸዋል። ሕዝቡም እሺ ግን የት እንውደቅ ብሎ ይጠይቃል። አላውቅም ነበር መልሱ ክፍለከተማው። አቢይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ናቸው የተባሉትን ጠራ፣ ሰበሰበ። ከዚያም ማንም የጠፈጠፈው ጭቃ ሁሉ ታሪክ ነው ተብሎ አይቀመጥም። ይፈርሳል። ይጠረጋል። በፍርድ ቤት የሚቆም የለም። ለልማት አፍርሰው ብሎ ዐወጀ። በማግስቱ የአራዳ ክፍለከተማ አስተዳዳሪ ቤቶቹን አፍርስ ተባለ። አላደርገውም ለ3 ወር በል ተብዬ አልነበረም ወይም አለ? አሰሩት አሰሩትና እና እነሱ ከኦሮሚያ ፎሊስ አምጥተው አካባቢውን አጥረው ናዱት። ናዱትና ድራሹን አጠፉት። አዲስ አበባ ሽንታም ነው ነው የሚሉት። ሌላም የወረዳ ይሁን የክፍለ ከተማ አመራር ባላረጋግጥም በልደታ ክፍለ ከተማ እንዴት ብዬ ነው ቤታችሁን ልቀቁ ላፈርሰው ነው የምለው? ቢያንስ የመዘጋጃ ጊዜ እንስጣቸው ያለ አመራር በአዳነች ፖሊሶች ተይዞ ከታሰረ ወራቶች ተቆጥረዋል። "…አዳነች አቤቤና አብይ አህመድ በሌሊት እየዞሩ የግለሰቦችን ቤት ተደብቀው ያያሉ አሉ። ለዓይናቸው ያላማረ ቤትና ግቢ ካዩ በቃል ነው ለአፍራሽ ግብረ ኃይሉ የሚነግሩት አሉ። 😁 ብስቅም መረጃው የእውነት ነው። ወደ አንዱ ሰፈር ወይም ቤት ሌሊት ጎራ ይላሉ። "ይሄን እስከዚህ አፍርሱት። ይሄኛውን ቤት ተውት አይደብርም" ብለው እዚያው ትእዛዝ ሰጥተው ይሄዳሉ። ከቀናት በኋላ ተመልሰው ይሄዳሉ። አሁንም ለአይናቸው ያላማረ ነገር ካዩ "ይሄንም አፍርሱት" ብለው ይሄዳሉ።አፍራሽ ግብረ ኃይሉ "ክብርት ከንቲባ የዚህኛው ግቢ ባለቤት እኮ አጥሩ እንጅ ቤቱ እንደማይፈርስ ተነግሮት አጥሩን አስተካክሎ አጥሮ ጨርሷል። አዳነች አቤቤ " አይ ይፍረስ ይፍረስ አፍርሰው" በቃ ይፈርሳል። "…ኦሮሙማ ሆዳሙን የአዲስ አበባ ሕዝብ አስተሳሰብ በሚገባ የተረዳ እጅግ በሳል በጥበብ የተሞላ አካሄድ ነው እየተከተለ ያለው። ለምሳሌ አስፋልቱን ሲጨርሱ ወደ ውስጥ ገባ ማለት ጀመሩ። ቤቱ የፈረሰባቸው ያለቅሳሉ። ከእነርሱ ቀጥሎ ያሉ ጎረቤቶች ደግሞ ይስቃሉ ይደሰታሉ። ከፊት ያለው ቤት ሲፈርስ "የእኛ አይፈርስም ተብሏል። እንግዲህ እግዜር ያውቃል። እንዲያውም የእኛ ቤት አስፋልት ፊት ስለወጣ ለቢዝነስ ያመቻል በማለት ጮቤ ይረግጣሉ። በጎረቤቱ እምባ የራሱን ተስፋ እያዬ ፈገግ ይላል። ቆዬት ብሎ አጅሬው ተስፈኞችን በዶዘር ይጎበኛቸዋል። ቀስ በቀስ ሁሉም ሰፈሩን ለቅቆ ይሄዳል። አሁንም በአዲስ መልክ እዬቀጠለ ነው። ከፒያሳ ያልተማረ ከማን ይማራል?የቀደሙት በግርግር በጥድፊያ ተደናብረው የእውነት ልማት ብሎ በማሰብም እያለቀሱ ሄደዋል። የፈረሰው ላይ ሳርና ቅጠል ሲጎዘጎዝ እያዩ ያሉ ናሪዎች ግን ምን ነክቷቸው ይሆን? አንዳንዱ የቀበሌ ቤት ነዋሪማ ጭራሽ የእኛ ቤት ፈርሶ ኮንዶሚንየም የሚሰጠን መቼ ነው ብሎ ይጸልያል አሉ። ከዚያ ይመጣና አቢይ ይንድበትና ድራሽ አባቱን አጥፍቶ ይገላግለዋል። "…የብልፅግናን አገዛዝ ወይም አቢይ አህመድ አሊ በሥልጣን ከቀጠለ እነዚህ ሕጎች አብረው ይቀጥላሉ። መፍረስ፣ መጽዳት፣ መፈናቀል፣ መታገት፣ መደፈር፣ መዘረፍ፣ መከፋፈል እና መገደል ይቀጥላሉ። ይሄን ሕግ የሳዲስቶች ሕግ ለማስቆም ከፈለግህ ደግሞ መጀመሪያ መንቃት፣ ከዚያ መደራጀት፣ መሰልጠን፣ ከዚያ መመከት፣ በመጨረሻም ለማነከት የፋኖን እና የጀነራሎቹን መንገድ መከተል። ያለበለዚያ በቁምህ ትቃዣለህ፣ በቁምህም ሟምተህ ታልቃለህ። አሁን በየቀኑ በኑሮ ምክንያት የሚያብደው ሰው በመብዛቱ ምክንያት ታንቆ ከሚሞተው፣ መርዝ ከሚጠጣው የተረፈው ወደ አማኑኤል ሆስፒታል የሚጎርፈው ብዛቱ ይሄ ነው አይባልም የሚል ዘገባ እየወጣ ነው። "…ትናንት ነዳጅ ጨምሯል። ደሞዝ የለም። ኑሮ ሰማይ ይነካል። አዳነች አበቤ ፋብሪካ ሳይሆን 33 ቢልዮን ብር ወጪ አድርጋ ሱቆች፣ መንደሮች፣ ትምህርት ቤቶች፣ መኖሪያ ቤቶች አፍርሳ አበባ ነው የተከለችልህ። በቤትህ መብራት ከጠፋ እና በዳፍንት መኖር ከጀመርክ ስንት ዘመንህ። ውኃ በቤትህ በስንት ቀን ነው የሚመጣው? እየሸትክ፣ እየገማህ፣ እየራበህ፣ እየጠማህ መኖርን ለለመድክ ለአንተ እነ አቢይ አህመድ ተመችተሃቸዋል። ሚልዮን ትግሬ ገድሎ ፈታ ብሎ የሚኖር አቢይ ለሚልዮን አዲስ አበቤ መራብ ደንታውም አይደል። አንተን ውኃ አሳጥቶ እሱ አስፓልት ያጥብበታል። አንተን ጨለማ ውስጥ አሳድሮ እሱ የኮሪደር ልማቱነረ ዲም ላይት ያንቦጎቡግበታል። 👇 ከታች ይቀጥላል ✍✍✍ 👆ከላይኛው የቀጠለ… ✍✍✍ …ልማት የሚጠላ የለም። ልማት ግን ሕዝብን አጥፍቶ አይደለም።
نمایش همه...
👍 925 98👌 25🤔 17😁 15🙏 14🏆 11🕊 8🤯 4 3😱 1
"…ዐማራ ብቻ ይሄን አረመኔ ፀረ ሰው አውሬ ቡድን ለመፋለም ነፍጥ ያነሣው። ዐማራ ብቻ ነው ከዚህ ልቡሰ ሥጋ ጋኔን ጋር ተናንቆ፣ እየተዋደቀ የሚገኘው። ዐማራ ብቻ ነው እምቢኝ ባርነት፣ እምቢኝ፣ በቃኝ ብሎ የተነሣው። ዐማራ ብቻ ነው የተሰባሰበው፣ እየተመካከረም ያለው። ዐማራ ብቻ ነው የአገዛዙን አሽከር ገረዶች እየቀነደሸ እያስበረገገ ያለው። ዐማራ ብቻ ነው አምባገነንነትን እምቢኝ አሻፈረኝ ብሎ ከዜሮ ተነሥቶ ዛሬ ሚልዮን ጀግና ያፈራው። ዐማራ ብቻ ነው ከፍቶኛል ወደ ሱማሌ፣ ኬንያ፣ ሊቢያና የመን ልሰደድ ሳይል ወደ ጫካ ወደ በረሃ ገብቶ እየተፋለመ ያለው። ዐማራ ብቻ ነው አልኩህ። ብራቮ ዐማራ። ሌሎቻችሁ እየተገደላችሁ፣ እየተፈናቀላችሁ፣ እየተሰደዳችሁ፣ እየለመናችሁ፣ እየተንከራተታችሁ፣ እያለቀሳችሁ፣ እየተራባችሁ ኑሩ። ዐማራ ያሸንፋል። ዐማራ ድል ያደርጋል። አሁን ከዚህ አውሬ አገዛዝ ጋር እየተዋጋ የሚሞት ዐማራ እንደሞተ አይቆጠርም። ገነት እንደገባ እንደ ሰማእት ነው የሚቆጠረው። በስደት ሲና በረሀ እና የመን በረሀ ውስጥ በውኃ ጥም ከመሞት ፋኖ ሆኖ ጥሎ መውደቅ በስንት ጣዕሙ። • ዋሸሁ እንዴ…? • ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።
نمایش همه...
🙏 1253👍 463 141 23🔥 19😁 19🏆 19👌 17🕊 17😡 14🤯 12
መልካም… "…እግዚአብሔር ይመስገን። ያመሰግን ዘንድ የሚጠበቀው 1ሺ ሰው ሞልቶ ተትረፍርፏል። ከምስጋናው በመቀጠል ደግሞ ያው እንደተለመደው ወደ ርዕሰ አንቀጽ ንባባችን እንሄዳለን ማለት ነው። "…በዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ደግሞ ስለ ኮሪደር ልማቱ ፀጋ እነ ቱሩፋት ስላመጣውም በረከት፣ በውበት እያማረች፣ እየተዋበች፣ እያሸበረቀች ስላለችው፣ ስደተኛ እየጎረፈባት ስላለችው አዲስ አበባችን ጻፍ ጻፍ አሰኘኝ። እናም በተለመደው ኮምጣጤ የጦማሬ አጻጻፌ ርዕሰ አንቀጼን መጻፍ አምሮኝ አዘጋጀሁላችሁ። • እህሳ እናንተስ ርዕሰ አንቀጹን ለማንበብ ዝግጁ ናችሁ?
نمایش همه...
9.74 MB
3.29 MB
👍 1241 131💔 113🙏 48 20👌 16🕊 11😁 8🤔 7🔥 5🏆 2
Photo unavailableShow in Telegram
“…አሁንስ ምሳር ደግሞ በዛፎች ሥር ተቀምጦአል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።” ሉቃ 3፥9 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
نمایش همه...
🙏 1470👍 168 164🕊 38🔥 9😁 9🏆 9😡 6 2
የታገቱትን ተማሪዎች በተመለከተ… • ኦቦ ኃይሉ ጎንፋ (ኮሬ ነጌኛ) ~ የታገቱት 167 ተማሪዎች ናቸው። 160 ውን ተዋግተን አስለቅቀናል። የቀሩን 7 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። አረጋገጡ ነው የሚለው የአሻም ዜና። • የኦሮሚያ ክልል ደግሞ ያው (ሽመልስ አብዲሳ ዋናው ኦነግ ሸኔ የኦሮሞ ብልፅግና ማለት ነው) እንዲህ አለ። ~ ስለታገቱ ተማሪዎች ምንም መረጃ የለኝም። አላቅም። ስለምን እገታ ነው የምታወሩት? እንዲያውም እኔ ራሴ እናቴን አግተውብኝ 10 ሚልዮን ብር ለምኜ ነው ከፍዬ ያስፈታኋት። • የታገቱት ልጆች ቤተሰቦች ~ የተፈቱ፣ የተለቀቁም ልጆች የሉም። እንዲያውም አጋቾቹ በሰው 1 ሚልዮን አጠቃላይ 167 ሚልዮን ብር ክፈሉ ብለውናል። ልንከፍል ሕዝብ መለመን ስንጀምር ደግሞ መንግሥት ተብዬው መጥቶ ልመና መለመን አይቻልም ብሎ ይከለክለናል። አሁን ልጆቻችን ከሰላሌ ወደ ደምቢዶሎ ሳያዘዋውሩአቸው አልቀረም። • እሜቴ አሜሪካ… "…የታገቱት ተማሪዎች ከ100 በላይ ናቸው። በጣም ያሳዝናል። ምፅ ምን ይደረግ? (የታገቱት ዐማራ ስለሆኑ ነው እንጂ ትግሬ ቢሆኑ ነጠላ ዘቅዝቃ ታለቅስ ነበር) ብለው የሚያሙ ሐሜተኞች ግን አሉ። • የብልጽግና አክቲቪስቶች ~ አዲስ አበባ ዱባይ መስላለች። ኮሪደር ልማቱ ዋው ነው። ባይበላስ፣ ባይጠጣስ ቢቀርም ያሰኛል። አቢቹ ችግኝ ተከለ፣ ቅሪላ ገፋ፣ በሎጬ አለፈ። በሺ ዓመት አንዴ የሚታይ ፔናሊቲም አስቆጠረ። ሃሌሉያ… "…የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ~ ኢትዮጵያ ቡና ዋንጫ በላ። የስቴዲየም ወንበር ዲቻዎች ሰበሩ። የቢራ ዋጋ መጨመሩ ፌር አይደለም። እናስይዝ የዘንድሮውን የአውሮጳ ዋንጫ ቬንዝዋላ ይበላዋል። ቡርኪነፋሶ በሁለተኝነት ያጠቃልላል ብለው ሙግት ላይ ናቸው አሉ። ኮሪደር ልማት። • ይሄ በእንዲህ እንዳለ አቶ ንጉሡ ጥላሁንስ ምን ብለው ይሆን…?
نمایش همه...
👍 1560😁 263 122💔 65🤔 46🙏 24 19🏆 13🤯 12🕊 11😱 3
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.