Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
کانال Zemedkun Bekele (ዘመዴ) (@zemedkunbekelez) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 201 464 مشترک است و جایگاه 108 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 84 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 201 464 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 20 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -2 824 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -59 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 16.98% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 11.08% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 34 207 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 22 324 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 948 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 21 ژوئیه | 0 | |||
| 20 ژوئیه | +10 | |||
| 19 ژوئیه | +23 | |||
| 18 ژوئیه | +16 | |||
| 17 ژوئیه | +3 | |||
| 16 ژوئیه | 0 | |||
| 15 ژوئیه | +5 | |||
| 14 ژوئیه | +6 | |||
| 13 ژوئیه | +3 | |||
| 12 ژوئیه | +6 | |||
| 11 ژوئیه | +1 | |||
| 10 ژوئیه | +2 | |||
| 09 ژوئیه | +1 | |||
| 08 ژوئیه | +5 | |||
| 07 ژوئیه | +6 | |||
| 06 ژوئیه | +6 | |||
| 05 ژوئیه | +27 | |||
| 04 ژوئیه | +5 | |||
| 03 ژوئیه | +4 | |||
| 02 ژوئیه | +10 | |||
| 01 ژوئیه | +1 |
| 2 | "…የዛሬው ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር መርሀ ግብራችን ያያችሁትን ይመስል ነበር። ጓዶች የዛሬውን መርሀ ግብራችንንስ እንዴት አያችሁት? | 25 421 |
| 3 | • አላችሁ አይደል?
"…ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር
"…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት ልክ 01:15 ሲሆን በዘመድ ቴቪ መርሀ ግብሩ ይጀምራል። እንደተለመደው ገባ ገባ በሉና ጠብቁን።
• ZemedTv 👉 zemedtv.com/live.html
• በትዊተር (×) 👉 x.com/i/broadcasts/1nxnRRlZwBExO
• በራምብል 👉 rumble.com/v7cyms0--zemede-july-19-2026.html?e9s=src_v1_cbl%2Csrc_v1_upp_a
• በሳታላይት ቴሌቭዥን 👉 Yahsat 52.5° East
11977 H 27500 ...ላይ ይከታተሉን።
"…በተረፈ የእኔን የስልክ ወጪን ጨምሮ አገልግሎቴን ለመደገፍ የምትፈቅዱ።
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል መለገስ ትችላላችሁ። ሁላችሁም ተመስግናችኋል።
• ሰብሰብ ብላችሁ ጠብቁን…! | 27 641 |
| 4 | ንክክሩን በተመለከተ…
"…የ 3 AAA የንክክር ኮሚሽን ጉባኤም በተፈለገው መንገድ አልሄደም። ወር ይቆያል የተባለው ተነካካሪ እስከአሁን መነካከር አልጀመረም።
"…በክፍለ ሀገር አሰልጥነው ያመጡአቸው የብልፅግና ካድሬዎች ከፌስቡክ እና ከቲክቶክ፣ ከዩቲዩብም እንዲርቁ ቢደረጉም ከፌስቡክ፣ ከቲክቶክና ከዩቲዩብ ከሚበልጡት አንዳንድ የከተማ ልጆች ጋር መገናኘታቸው የተጫነባቸውን የብልጽግና ሶፍትዌር ሳያራግፍባቸው አልቀረም።
"…ኦርቶዶክሳውያን በድሬደዋና በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ ብቻ እንዲወያዩ፣ የኦሮሞ ወሀቢያ እስላሞች ደግሞ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ እንዲወያዩ መመደባቸው ሌላ ቁጣን በመቀስቀሱ ንክክሩ አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ነው የተነገረው።
• የኦሮሞ የወሀቡያ እስላሞቹ የሥልጤ እስላሞችን ዘውረው የሃይማኖት ጉዳዮችን በሚፈልጉት መንገድ ጠምዝዘው ለመዘውር ነው ያሰፈሰፉት።
~ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር መቀየር
• ዓመተ ምሕረትን ወደ ዓመተ ሂጅራ
• ሰኞን ወደ ሰኑይ
• ዓርብን ወደ ሥራ ዝግ ማድረግ
• መስቀል አደባባይን ወደ ኢድ አደባባይ
• በቀደሙ ነገሥታትና ጀግኖች የሚጠሩ ትምህርት ቤቶችን፣ መንገዶችን፣ ሆስፒታሎችን ወዘተ በእስላሞች መቀየር
• ሼሪአን በኢትዮጵያ መተግበር ወዘተ የሚል አጀንዳ ይዘው ነው ከች ያሉት፣ ሂጃብ ምናምን መከልከል የለበትም። በእውቀት ሳይሆን በኮታ እስላሞች ይመደቡልን ሁላ ነው የሚሉት።
"…4ሺ ካድሬ ካርድ ወስዶ ወደ አዳራሽ ሊገባ ቢሞክርም 3 ሺ ኦህዴድ በጎን ካርድ ሠርቶ አዳራሹን በመሙላቱ ተሰብሳቢዎቹ ግራ ተጋብተው እንደጦዙ ናቸው። መስፍን አርአያ መጦዙ ነው የሚሰማው። እነ አምባሳደር መሀመድ ድሪር ግብፅ ቆይተው ከመጡ በኋላ ጉባኤውን እንዲመራ በመመደቡ እስላሞቹ ጮቤ ረገጣ ላይ ናቸው።
"…ኦሮሞና ተሰብሳቢው ቦክስ ገጥሞ ጉዳት የደረሰባቸው ወደ ሆስፒታል ደብዳቢዎቹ ወደ ጣቢያ ቢወሰዱም በአካም አካም ደንብ መሠረት ተፈተዋል።
"…ንክክሩ እንደ አዲስ ነገ ይጀመራል ቢባልም ብዙዎቹ ወፍ የለም ነው የሚሉት። እንዲህና እንዲያ ብለው አዛ ካደረጓቸው በኋላ ተሰብሳቢው ሰልችቶት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ኦህዴዶቹ ብሔር ብሔረሰቦችን ወክለው አቢይ አሕመድ የፈለገውን አጽድቀው ፕሬዘዳንት አድርገው ሊያነግሡት በዝግጅት ላይ ናቸው ነው የሚሉት።
• ለማንኛውም ንክክሩ የተበላ እቁብ ቢሆንም በኢትዮጵያ ቦለጢቃ ላይ ለሰላም የሚጨምረው ቅንጣት ያህል አስተዋጽኦ የለውም። ትግሬ፣ ዐማራ ያልተሳተፈበት፣ ከኦሮሞ ራሱ ኦነግ ያልተሳተፈበት፣ የግል ሚዲያዎች እንዳይዘግቡ፣ እንዳይታዘቡ የተከለከሉበት ንክክር ምንም የሚፈይደው ነገር እንደሌለ ነው የሚናገሩት።
• ለማንኛውም ንክክሩ እስከአሁን ዜሮ… | 26 195 |
| 5 | መልካም…
"…ዛሬ ምሽት ከ1:00 ሰዓት ጀምሮ ጎጃም ምድር አብረን እናመሻለን። አገዛዙ ደጋ ዳሞት ከመግባቱ በፊት አስቀድሞ በጎጃም ፋኖ አመራሮች እንዲፈርሱ ስለተደረጉ ብርጌዶች እና ክፍለጦሮችም ከነ አፍራሾቹ ጭምር በስም እና በፎቶ መረጃ እና ማስረጃም በግልጽ እንወያያለን።
"…አመራር ሆኖ ስላፈረሱ እና ስለተበተኑ ዕዞችና ክፍለጦሮች መረጃ የሌለው እና ሻለቃ ዝናቡ ከ4 ጄኔራሎች እና ከ7 ኮሎኔሎች ጋር ብቻውን ከወንድሞቹ ጋር ሆኖ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አጋዥ አድርጎ ሲገጥም ሌሎቹ የት እንደገቡ አብረን እንመለከታለን። ይሄ ምድረ ሸንጎና ቅባታም የጎጃም አክቲቪስት፣ ጋዜጠኛና ቲክቶከር ፌስቡከራም ሁላ ስለ ደጋ ዳሞት ትንቅንቅ ትንፍሽ የማይለው ለምን እንደሆነም እንመለከታለን።
"…ሻለቃ ዝናቡን እንኳን ሊያግዙት ሞቱን የሚናፍቁ አመራር ጋዜጠኛና አክቲቪስቱ የትየለሌ ነው። እሱንም በሰፊው እናያለን። የዝናቡ አይሳካም እንጂ ከተሳካ ከጎጃም ቀጥሎ አገዛዙ አማቾቹን ስኳድን ይዞ ወደ እነ አርበኛ ባዬ ቀናው ለመዝመት ነው ፍላጎቱ። ይሄንንም በደንብ እናየዋለን።
"…ከሦስት ዓመት በፊት ዳሞትን ለማንበርከክ 80% ጦሩን ወደ ዐማራ ግዛት የላከው አብይ አህመድ ደጋ ዳሞት ላይ አከርካሪውን ባይሰበር እና በለስ ቢቀናው ኖሮ ዛሬ ዐማራ አይኖርም ነበር። ፋኖም እንደሚወራው ራሱን ችሎ ከመቆም አልፎ አቅም ፈጥሮ ከትግራይ ከኤርትራና ሱዳን ጋር አብሮ ስለመሥራት አያስብም ነበር::
"…ወደ ቀሪው ጎጃም ጎንደር ሸዋና ወሎ ሊገባ የነበረውን በሰው ይልም ሆነ በትጥቅም ፈርጣማ የነበረውን የሚያስፈራውን የኦሮሙማ መከላከያ የሚባለውን የኦነግን ጦር እንዳያገግም አድርጎ የሰበረው "ዳሞት" ነው። ዳሞት ማለት ሻለቃ ዝናቡን የወለደው ሕዝብ ነው።
"…ዳሞት ከተንበረከከ ዐማራ ተንበረከከ ማለት ነው። የጄነራል አሳምነው እና የፕሮፌሰር አስራት መንፈስ ለኦነግ ሰገደ ማለት ነው። ዳሞት ሲዋደቅ በመላው ዐማራ በገጠር በከተማው የጦፈ ጦርነት እየተካሄደ እንደሆነ ማወቅ አለብን። ዐብይ ዐማራን ሊገጥም ሲል ጠቅልሎ ዳሞት ገባ። ዳሞትም ጠቅልሎ ቀበረው። ይኸው ዛሬም ወደ ትግራይ ከመግባቱ በፊት ጠቅልሎ ዳሞት ገብቷል። አህዴድ ሌላውን ከመጤፍ አይቆጥረውም የሚሉም መተርጉማን አሉ።
"…አብይ አህመድ የዐማራ ግዛት ጦርነቱ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ ያልረገጠው የዐማራ ክፍል የለም። ዳሞት ላይ ግን በዝናቡ ፈቃድ ብቻ ነው መግባት የሚችለው። የእነ ዝናቡ የእነ ታዱ አገር እንደ ትግራይ የራሱን ምርጫ ማካሄድ፣ የራሱን ሲኖዶስ ማቋቋም ፈተና አዘጋጅቶ የነገ ጀግና ታዳጊ ልጆቹን ማትሪክ መፈተን ብቻ ነው የቀረው።
"…ዛሬ በፋኖ ስም መሪ ነን የሚሉት፣ በፋኖ ስም ሚልየነር የሆኑት፣ እከካቸውን፣ ጭቅቅታቸውን አራግፈው እንደ ሞዴላ ሞዴል ፎቶ እየተነሡ ጀግና ጀግና የሚጫወቱት በሙሉ የዐማራ ፋኖ በደጋ ዳሞት በፈረስ ቤት ጡሩንባ እየተነፋ ወንድ ሴት ሕጻን አዛውንት ሳይል ሕዝባዊ ሆኖ ወጥቶ ግዙፉን የአቢይአሕመድ ጦር ፊት ለፊት ገጥሞ በሻለቃ ዝናቡ ልንገረውና በወንድሞቹ መሪነት ከሰባበረው ከየጎሬአቸው ወጥተው አናት ላይ ቂብ ያሉ ናቸው። እነ አስረስ መዓረይ፣ እነ ጥላሁን አበጀ፣ እነ አበጀ በለው፣ እነ ዘመነ ካሤ፣ እነ ማርሸት ፀሐዩ በሙሉ ተግተልትለው የመጡት ዳሞት የቤሥራውን ሠርቶ የፋኖን ሰንሰለት ከበጣጠሰው ወዲህ ነው።
ዳሞት
ያስተፋል ሃሞት
"…ትናንት በብልፅግና መንደር የፌክ ድል ሲወራ፣ ሲበተን እስከ ዛሬ ጎጃሜ ነን የሚሉ ፀረ ጎጃም አክቲቪስቶች ጭጭ ነበር ያሉት። አንዳቸውም አልተነፈሱም። ምድረ ባንዳ አስመሳይ የብልፅግና ገረድ በስመ ጎጃሜ ተደራጅቶ ጎጃምን የሚግጥ መንጋ ሁሉ ትንፍሽ አላለም። እንዲያውም ዝናቡ ተመትቶ፣ ሠራዊቱ ወድሞ ለመጨፈር የተዘጋጁ ነበር የሚመስሉት። እነዚያ ተደራጅተው ሲዘምቱብኝ የከረሙት ፀረ ጎጃም የጎጃም ፋኖ አክቲቪስቶች ጭራሽ ለዶር ደሳለኝ መኪና መግዣ የገቢ ማሰባሰቢያ ሲዳክሩ ነው የዋሉት ያመሹት። ለሌላቀን ሁላ ማስተላለፍ አልፈለጉም። ቅባትና የፖለቲካ አገው ሸንጎ የትግሬና የኦሮሞ ዲቃላ ሁላ ዳሞት በመወረሩ በልቡ እመበር ተጋዳላይ ሲል ነው የዋለው፣ ያመሸው።
"…እኔ አፍራሹ ዘመዴ የዐማራ ፋኖ የልብ ወዳጁ ዘመዴ ግን መጥቼ አንዲት መረጃ ከለጠፍኩ በኋላ ቀውጢ ፈጥሮ የነበረው የብልጽግና የሚዲያ ሠራዊት የት እንደገባ ነው የጠፋው። ብትንትናቸውን ነው ያወጣሁት። የምድር አጋንንቱን ዳሞቶች በዝናቡ በኩል ሃሞት ሲያተፉት የአየሩን አጋንንት ደግሞ እኔ ዘመዴ የደብተራው ልጅ የነፍጠኛ ወዳጅ በታተንኩት። የሆነው እንደዚያ ነው። ለማንኛውም ምሽት ላይ የመረረ ነጭ ነጯን በዘመድ ቴቪ እንጋታለን።
• የምለው ገብቷችኋል አይደል? | 25 892 |
| 6 | • ወገኖቼ አንደምን አደራችሁ ? | 26 188 |
| 7 | "…ነገረ ደጋ ዳሞት…
"…ወደ ኤርትራም ሆነ ወደ ትግሬ ለመዝመት መጀመሪያ የዐማራ ብሔርተኛ እና አክራሪ የዐማራ ኦርቶዶክስ እና እስላሞች ያሉባቸውን የዐማራ ፋኖ ኃይላት ባለ በሌለ ኃይል የፈጀውን ፈጅቶ መደምሰስ አለበት የሚል ውሳኔ ላይ የተደረሰው ከጎንደር እነ ፕሮፌሰር ኢያሱ፣ ከጎጃም እነ ማስረሻ ሰጤ፣ ከወሎ እነ ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀባው ከመጡ በኋላ ለመንግሥት ምክረ ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ነው። ይሄም ብቻ ሳይሆን አሁን በቀጣይ ወደ መንግሥት ለመግባት ዝግጁ የሆኑት ከጎንደር የእነ ሀብቴ ወልዴ፣ ከጎጃምም የእነ አስረስ ማረ ቡድን በቅድሚያ "በሞዓ ተዋሕዶ ስም እና ከትግሬና ከኤርትራ ጋር የተጻመዱ" የሚል ስም በመስጠት ካልተደመሰሱ ምንም ማድረግ አይቻልም ከሚል ውሳኔ ላይ ነው የተደረሰው። እናም ከጎጃም በቅድሚያ መወገድ አለበት ተብሎ የተፈረደበት የደጋ ዳሞት ፋኖ እና ሕዝብ ሆነ። ለዚህ ነው ከወሎ ጭምር ያሉት እነ በላይነህ ሰጣርጌ ጭምር ሻለቃ ዝናቡን ከእነ ጥላሁን ጋር ሆነው ሲሰድቡ የከረሙት።
"…በዚህ መሠረት እምነቱን ከወሀቢ እስላምነት ወደ የብልጽግና ጴንጤነት ቀይሮ ዐማራን አጠፋለሁ ብሎ ዝቶ ዐማራ ክልል ገብቶ የኦሮሙማውን ሠራዊት ሲያሳጭድ የከረመው ጄነራል መሀመድ ተሰማ ያለ የሌለ ኃይሉን አስተባብሮ ወደ ዳሞት እንዲዘምት የተመደበው። ጎጃምን በተለይ ደጋ ዳሞትን መስበር ለሌሎቹም ስብራት መንገድ ጠራጊ ስለሚሆን የተከፈለው መስዋዕትነት ተከፍሎ ሻለቃ ዝናቡ እና የደጋ ዳሞት ሕዝብን ከመደምሰስ እንቅስቃሴ የተደረገው።
"…እነ መሀመድ ተሰማ ወደ ደጋ ዳሞት የተንቀሳቀሱት የ12 ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ተፈትነው ወደ ቀዬአቸው የሚመለሱ የዐማራ ተማሪዎችን እንደ ጭዳ እንደ ጋሻ በመጠቀም ነበር። ለዐማራ ሕዝብ መጥፋት በእልህ ጎጃም የገባው ጴንጤው ጀነራል እንደ ጦር ጥበብ የተጠቀመው ይህን ዘዴ ነበር። ተማሪዎቹን ሰበሰበ፣ ከፊት እነሱን አስቀደመ፣ ከዚያ እሱ ከኋላ ተከተለ፣ ፋኖም መከላከያው ላይ መተኮስ ሲጀምር ፀረ ዐማራው ቡድን የ12 ተኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው ወደ ቀዬአቸው የሚመለሱት ተማሪዎች ላይ መተኮስ ጀመረ። እስከአሁንም ወደ 26 ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል። በዚህ ፖለቲካ ለመሥራት የፈለገው የመሀመድ ተሰማ ጦር ሳይሳካለት የሻለቃ ዝናቡ የፋኖ ሠራዊት "ቆይ ይግቡ ግድየለም የሚወጣውን እናያለን" በማለት ሠራዊታቸውን ከውጊያው ሜዳ ዞር አድርገዋል። ሁሉም ካለፈ፣ እነ መሀመድ ተሰማም ወደ ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ከገቡ በኋላ ለጊዜው አንድም ጉዳት ሳይደርስበት ዞር ያለው የደጋ ዳሞት የበላይ ዘለቀ አናብስት ምሽቱን መውጫ መግቢያውን ወደሚያውቁት ሀገራቸው በመመለስ መሀመድ ተሰማን ጦር ይለበልቡት ይዘዋል። ቀጥታ ስርጭት ነው እያየሁ ያለሁት።
"…እስላም የነበረው የአሁኑ ጴንጤ መሀመድ ተሰማ የጎጃምን ኦርቶዶክስ ለማጥፋት ሲዝት ከንፈሩ ሁላ ነው የሚንቀጠቀጠው ይባላል። እስላሙ አቢይ አሕመድም ጴንጤውን እንደ እሱ እስላም ተነበረውን መሀመድ ተሰማን ወደ ጎጃም ከላከ በኋላ በቀደም ዕለት ደብረ ማርቆስ የአውሮጵላን ማረፊያውን ካስመረቀ በኋ በዝግጅቱ ላይ " ጎጃሞች አፄ ዮሐንስ ያደረገባችሁን አስታውሱ" በማለት እኔ ከአፄ ዮሐንስ የበለጠ ነው የምጨፈጭፋችሁ በማለት ከዛተ በኋላ ነው ጨፍጫፊ የጴንጤና ተአክራሪ የወሀቢያ እስላም ጦሩን ወደ ጎጃም ምድር የላከው። የገባው ጦር ያገኘውን ሁሉ አላህ ወአክበር፣ ኢየሱስ ጌታ ነው እያለ እንዲያወድም ነው የታዘዘው። እያወደሙም ነው።
"…እንደ ደረሰኝ መረጃ ከሆነ ወደ ደጋ ዳሞት ለመግባት የተሠለፈው ኃይል እንደሚከተለው ቀርቧል። 4 ጄነራሎች፣ 7 ኮሎኔሎች፣ 3 ክፍለ ጦሮች፣ 2 ዕዞች እና ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች ጭምር ናቸው የገቡት። ጀሌ ብቻ ክላሽ ያላስያዙት ከኦሮሚያና ከደቡብ አፍሰው ብር ሸለቆ ያስገቧቸውን ከ500 በላይ ሰልጣኝ ወታደሮችን ለጥይት ማስጨረሻና ማብረጃ በሚል ወደ ደጋ ዳሞት ይዘዋቸው እንደገቡ ነው የመረጃ ምንጮቼ የሚናገሩት።
• ለጊዜው 3 ቱን በዝርዝር እንመልከታቸው?
1ኛ፦ በደንበጫ በኩል ብ/ጀነራል ሶፊያን ሸህ የሚመራው የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር የተወጣጡ ጥምር ሬጅመንቶች እስከ ሙሉ ሞተራይዝድ ሻለቃው (መድፍ+BM+ዙ-23...) ልብ በል የወሀቢያ እስላም ነው ሱፊያን። ትግራይ ማኅበረ ዶጌ እነዚያን ንጹሐን ትግሬዎች ገደል አፋፍ ወስዶ የረሸነው ማለት ነው። አሁን ጎጃም ገብቷል።
2ኛ፦ በቋሪት ሐሙስ ገበያ በኩል ብ/ጀነራል መላኩ ገላነህ የሚመራው የምሥራቅ ዕዝ 302ኛ ኮር የተወጣጡ ክፍለጦሮች + ሞተራይዝድ ሻለቃ(መድፍ+BM)
3ኛ፦ ዋሸራን አስሶ በአስተርዮ በኩል በተወሰነ ቦታ በእግር ጭምር በብ/ጀነራል አዲሱ መሃመድ የሚመራው ምሥራቅ ዕዝ 304ኛ ኮር ሁለት ሬጅመንቶች ሞተራይዝድ ሻምበል አንድ መድፍ እና አንድ BM ተሠማርቷል። 3ቱ ጀነራሎች በአካል በየግንባሮቻቸው ተሠልፈዋል።
በአጠቃላይ:
- 3 መድፍ
- 3 BM
- ዙ-23
- አንድ ታክቲካል የግንኙነት መኪና
"…ይህንን ኦፕሬሽኑን በልዩ ሁኔታ የሚመሩት ደግሞ…
1ኛ፦ ሌ/ጀነራል ደሣለኝ ተሾመ
2ኛ፦ ሌ/ጀነራል መሃመድ ተሠማ
3ኛ፦ ሜ/ጀነራል ብርሃኑ ጥላሁን ናቸው።
[
• የአዳር ሁኔታ❗️
"…ወደ ፈረስ ቤት ለመግባት ኃይል ይዘው የተንቀሳቀሱት የጠላት ጦር አመራሮች:
• ሌ/ጀነራል መሐመድ ተሰማ የቀጠናው ኮማንድ አዛዥ
• ሜ/ጀነራል ተስፋዬ ረጋሳ(የጎጃም ቀጠና ኮማንድ ዘመቻ ሓላፊ)
• ብ/ጀነራል መላኩ ገላነህ የ302ኛ ኮር አዛዥ
• ብ/ጀነራል ሶፊያን በክሪ የ602ኛ ኮር አዛዥ
• ኮ/ል አበበ ምስራቅ ዕዝ 23ኛ ክፍለጦር አዛዥ በገነት አቦ እና በማክሰኝት ወደ ጠሊም
• ኮ/ል ጀማል የ73ኛ ዞብል ክፍለጦር አዛዥ በቋሪት ብር አዳማ ወደ ሐሙስ ገበያ
• ኮ/ል ገ/ኪዳን ሃድጉ የ79ኛ ክፍለጦር አዛዥ በብር አዳማ ሃሙስ ገበያ ማታ የተጨመረ ( ዐማራን ከመበቀል ለአገዛዙ ምሎ ወደ ዐማራ ለበቀል የተላከ ትግሬ ነው)
• ኮ/ል አታሉ የ6ኛ ዕዝ የ25ኛ ክፍለጦር አዛዥ በአረፋ በኩል
• ስሙ ያልተለየ የ75ኛ ፣የ18ኛ እና 32ኛ ሬጅመንቶች ጥምር ኃይል የሚመራ በደንበጫ በኩል ከጀነራል ሶፊያን ጋር በመሆን ወደ ፈረስቤት ተንቀሳቅሰዋል።
በአጠቃላይ በድምሩ:
• 4 ጀነራሎች
• ከ7 በላይ ኮለኔሎች (የኮር ዘመቻ እና ድጋፍ ሰጪ ኮለኔሎች ጨምሮ) የሁለት ዕዞች (የ6ኛ ዕዝ እና ምሥራቅ ዕዝ ጥምረት) መንቀሳቀስ ችለዋል።
• የሚጠበቀው ውጤት ‼
"…አመራሩ ገብቶ ፎቶ ይነሳል፤ ዜና ይሠራል፣ ጭዳው ምስኪን ሠራዊት ምሽግ ውስጥ ሠንብቶ ተጠዝጥዞ ረግፎ ይወጣል። ሌላ የተለየ የሚፈጥረው ነገር የለም !
"…ይኸው ነው። ከሕዝብ ጋር ተዋግቶ ያሸነፈ መንግሥት የለም። ያውም ጦርነት ለእሱ ድግስ የሆነለትን ዐማራ በጦርነት አታሸንፈውም። እንኳን የአክራሪ እስላም እና የብልፅግና ወንጌል ጀነራሎች የሚመሩት ጦር ይቅርና በሮሙ ፖፕ ተመርቆ በካቶሊካውያን ጀነራሎች የተመራ የአውሮጳ ጦር ዘምቶበት አላሸነፈውም። መፍትሄው መራሩን እውነት መቀበል ብቻ ነው። ዐማራ አይሸነፍም።
• ወይ ንቅንቅ ‼
• አፍራሹ ዘመዴ ነኝ ከራየን ወንዝ ማዶ። | 29 368 |
| 8 | "…ብዙዎች ወዳጆቼ በመከላከያው እና በጄነራል ዝናቡ ልንገረው መካከል ሲደረግ ስለዋለው ስለዛሬው ስለ ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት የውጊያ ውሎ ብዙዎቻችሁ መረጃ ፈልጋችሁ ስትጨቀጭቁኝ እንደዋላችሁ ይታወቃል።
"…በተለይ የብልጽግና የሚዲያ ሠራዊት ፌስቡኩን ግድግዳ በጄነራል መሀመድ ተሰማ ፎቶ አጥለቅልቀውት ስለዋሉ የሌለ ቀውጢም ስለፈጠሩ ግራ ተጋብታችኋል። እና ይሄንን ማጥራት የግድ ይላል።
"…የብልጼን የሚዲያ ሰራዊት ዜና በ10 መስመር እውነተኛ መረጃ ላፈርሰው ነኝ። አላችሁ አይደል?
• እስልምናውን ክዶ ጴንጤ የሆነው መሀመድ ተሰማ እና ኦርቶዶክሱ ባለማዕተቡ ዝናቡ ልንገረው በጎጃም ምድር ተናንቀዋል።
• አላችሁ አይደል? | 27 224 |
| 9 | • ጽምዶ ማለት…
"…ጽምዶ ማለት ትርጉሙ በፈረንሳይኛ ጌቾ እንደሚተነትነው ያለ ነው። የጎንደር ስኳድ እና የጎጃም ሸንጎ፣ የኦሮሞ ብልጽግና እና የወሀቢያ እስላሞች እንደሚያወሩት ያለ አይመስለኝም።
"…ምንድነው የሆነው… አቢይ አህመድ መጀመሪያ ትግሬን በኤርትራ፣ በሱማሌ፣ በሱዳን፣ በቤር ቤረሰቦች አስቀጥቅጦ ሽባ አደረጋት። ከዚያ እንዳትሞት ነፍሷ እንዳይወጣ አድርጎ ዊልቸር ላይ ካዋላት በኋላ ፕሪቶሪያ ወስዶ "ያሳሳቱኝ እኮ ዐማሮችና ሻአቢያ ናቸው። ስለዚህ አሁን ያለፈውን ይቅር እንባባልና መጀመሪያ ፋኖን ከዚያ ደግሞ ኢሳያስን ቀጥቅጠን እንበቀላቸው በማለት ወያኔን ቁማር ሊበሏት ያጃጅሏታል። ወያኔ ምኗ ሞኝ ነው። ጌቾ ሁሉንም አስቀድሞ ያውቅ ነበር እና ለትግሬዎቹ ነገራቸው። ታደሰ ወረደ ደግሞ ለዐማሮቹ ነገራቸው። ኢሳያስንም በትግርኛ አወሩት። አወሩት እና ኦሮሙማን ጠጠው በል፣ ሞኝህን ፈልግ አሉት።
"…ከዚያ ኦሮሙማ አበደ። በፊት አብረው ትግሬን የቀጠቀጡት ሻአቢያ፣ ሱዳን እና ዐማራ አንድ ላይ ገጠሙ። ትግሬም ተቀላቀላቸው። ይኸነዜ ነው ኦሮሙማው ትግሬን ለመቀጥቀጥ አብረውት የነበሩት ፋኖ፣ ሻአቢያና ሱዳን አሁን አንድ ላይ ሲሆኑ "ፅምዶ ናቸው፣ ጥምዶ ናቸው" አውግዙልኝ ሲል ውሎ የሚያድረው።
"…ሽመልስ ያሰለጠነው የኦሮሞ ወታደር ብቻውን ደግሞ እነዚህ 4ቱን የሚችላቸው አይመስለኝም። ብቻ ጽምዶ ጌቾ ክለብ ከመቀየሩ በፊት የሰጠው ትንተና ማለት ነው።
የማን ቤት ጠፍቶ የማን ሊበጅ
የአውሬ መፈንጫ ይሆናል እንጂ… አለ ጌቾ።
• የምለው ይገባችኋል ኣ? | 27 974 |
| 10 | • ቅዳሜ ከሰዓታችንን በውይይት እናሳልፋለን።
• ሌላው ደግሞ ብሔርን በተመለከተ ሁለት ጥያቄዎች አሉኝ። የመጀመሪያ ጥያቄዬን ላንሳ…
ጥያቄ ፩
"…ከላይ ቆመውና ተቀምጠው የምናያቸው የዛሬው ሰልፍ አዘጋጆች የሆኑት የራያ ቢራ ባለቤት ጄነራል ጻድቃን እና ጌታቸው ረዳ የየት አካባቢ ትግሬ ናቸው? ጌታቸው ጭራሽ ትግርኛም አይችልም ሲሉት ስለምሰማ ነው።
ጥያቄ ፪
"…አቶ ገብሩ አሥራትም ግማሽ ጎንደሬ ናቸው ይሏቸዋል። ይሄስ ምን ያህል እውነት ነው?
"…መጀመሪያ ግን የሰልፉ አዘጋጆች ራሱ ትግሬዎች ናቸው ወይ የሚለውን መልሱልኝ። የጌታቸው ረዳ እህት የዐማራ ፖሊስ ውስጥ ሓላፊ ናት ሲሉም ሰምቻለሁ።
• ብቻ ነገሩ ትንሽ ውስብስብ ያለ ይመስላል። | 28 534 |
| 11 | "…ቆይ እንጂ ልጄ በወያኔ ታፈሰብኝ፣ በግዳጅ ወደ ጦር ሜዳ ተወሰደብኝ፣ ከዚያም ወደ ሱዳን ተሸጠብኝ እያለች ለተቃውሞ ሰልፍ አደባባይ የምትወጣ እናት ሰልፉ ላይ ማልቀስ፣ ማዘን መተከዝ እንጂ እንዲህ ፈንዲሻ መምሰል ማለት ምን ማለት ነው። ሰልፉ ላይ ብራኑ ጁላም ብርሃኑ ነጋም እንዲያዝኑላቸው አሳዛኝ የሆነ የእናትነት ፊት ማሳየት ነው ያለባት ወይስ መገልፈጥ? ይሄ ስህተት ነው። ለሌላ ጊዜ ጎንደር ወይ ባሕርዳር ጅማ ወይ ናዝሬት ሲዘጋጅ መታረም አለበት። ቢያንስ ሹሩባ አሠርታችሁ ሴቶቹን ብታስወጡ የሆነ ፐርሰንት ያህል ቅቡልነት የምታገኙ ይመስለኛል። ስልጤ ኦሮሞና ሀዲያ ወላይታ አሰለፎ ሲያበቁ በግድ ትግሬ ናቸው ማለት ምንሼ ነው?
"…ሌላው ደግሞ የገረመኝ ነገር የትግሬ እናት አዲስ አበባ ስትኖር በጊዜ ሂደት የስልጤ እናትን መልክ ነው እንዴ የምትመስለው?
• የምለው ገብቷችኋል ኣ…? | 28 584 |
| 12 | "…በፈለከው መንገድ ስበከኝ በምንም ተአምር ትግሬዎቹ በድጋሚ የኦሮሙማው መከላከያ ትግራይ ይግባልን አይሉም ባይ ነኝ።
• ሰልፈኞቹ ግን በብዛት ትግሬ አይመስሉም። | 27 164 |
| 13 | • እንደምን አደራችሁ? | 26 824 |
| 14 | "…ትግሬዎች በወያኔ ላይ ሰልፍ ሊወጡ ነው … ተባለ…
"…አቢይ ከመጣ ወዲህ ሰላማዊ ሰልፍ ፈቃድ ተሰጥቶት ሰልፍ የወጣ ፓርቲም ሆነ ሕዝብ የለም። ብልጽግና ግን በፈለገው ሰዓት በፈቀደው ቦታ የድጋፍ ሰልፍ ሲፈልግ እንደበግ እየነዳ ከበረት አውጥቶ የሚያሰማራው የራሱ መንጋ አለው። ውጡ ሲባሉ የሚወጡ፣ አልወጣም ቢሉ አይደለም ቢያረፍዱ ዘይት እና ዱቄት የሚከለከሉ ምስኪን ሴፍቲ ኔቶች፣ የወረዳና የቀበሌ ሠራተኞች ይወጧታል። ከእነሱ ሌላ ሰልፍ የማይታሰብ ነው።
"…ከጥቂት ዓመታት በፊትም ኢትዮጵያ በተለይም አዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ውስጥ በኦህዴድ መሪነት ትግራይ ያለውን ወያኔን በተመለከተ እንዲሁ ቤር ቤረሰቦች ጭምር አደባባይ ወጥተው መሰለፋቸው ይታወሳል። እነ ሰማንታ እነ ጆ ባይደን ሁሉ ሲወገዙ፣ እነ ጉታሬዝ ሲብጠለጠሉ ሁላ አስታውሳለሁ። "ሰማንታ እጅሽን ከኢትዮጵያ ላይ አንሺ። ባታነሺ ግን ዋቃ ጉራቻ ይፍረድብሽ" የሚል መፈክር ሁላ እንደነበር አስታውሳለሁ።
"…ከቤር ቤረሰቦችም በተጨማሪ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ ትግሬዎች፣ በጅምላ ከመታሰር፣ ከመዘረፍ፣ ከመደፈር የተረፉቱ በግዳጅ ሰልፍ ወጥተው ወያኔን እንዲያወግዙ መደረጉ ይታወሳል። ትግሬዎቹ እናቶች ገጻቸው እንዳይታይ ፊታቸውን በነጠላ እንደ ኒንጃ ተጠቅልለው ነበር ያነዜ ወያኔን ሲያወግዙ ያረፈዱት።
"…በዚያ ወቅት ትግሬዎቹን ለይቶ የሚያውቃቸው ኤርትራውያን ናቸው ተብለው ኤርትራውያንን እንደ ጀርመን አነፍናፊ ውሻ ተጠቅሞ ከገቡበት ገብቶ ለቅሞ ወደ ዘብጥያ ያጎራቸው ኦህዴድ ኦነግ ነበር። በወቅቱ ከትግራይ ሆነው በአዲስ አበባ የተደረገው የወያኔ ተቃውሞ ሰልፍ በኦህዴድ አስገዳጅነት የተደረገ ነው በማለት ሲቃወሙ የነበሩት ትግሬዎች በሙሉ በአሁኑ ግን እንደ አሜባ አስር ትናንሽ ቦታ ላይ ተከፋፍለው ታይተዋል።
"…በወቅቱ ትግራይ በረሃ ሆነው አቢይ አሕመድ ሂትለር፣ ሳዳም ሁሴን ነው፣ ፋሽስት ነው ይሉ የነበሩት እነ ጌታቸው ረዳ፣ ጻድቃን ገብረ ትንሣኤ፣ የመቀሌ ዩንቨርስቲው ሰውዬ ምናምን አሁን ማልያ ቀይረው ከአቢይ አህመድ ጋር ተሰልፈው በወቅቱ አለቆቻቸው ከነበሩት ከእነ ደብረ ፂ፣ ከእነ ሞንጆሪኖ ተቃራኒ ሆነው ከአዲስ አበባ ሆነው የወያኔ የተቃውሞ ሰልፉን ሲያስተባብሩ ታይተዋል።
"…መቼም ራብ ክፉ ነው። ማጣት ክፉ ነው። በተለይ ደግሞ አግኝቶ ማጣትን የሚያህል ክፉ ነገር የለም። በዘመነ ወያኔ አዛዥ፣ ናዛዥ የነበሩ ትግሬዎች ቀን ጥሎአቸው እንደ ገረድ፣ እንደ አሽከር ረግጠው ያዙአቸው በነበሩት ኦሆዴዶች ተረገጥው መታዘዝ ግድ ሆኖባቸዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን እንደ ትግሬ አሳዠኝ ፍጥረት የለም። ሀገር በስም አለው ሀገሩ መግባት አይችልም። ከሀገሩ ተሰዶም እንደዜጋ የሚቆጥረው የለም። ትግሬ ከኢትዮጵያ ፓርላማ ኦሮሞ ድራሽ አባቱን ካጠፋው 8 ዓመት ሆነው። ለክልሉ በጀት አይመደብም። በትግራይ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ከተከፈለ ዓመት አለፈው አሉ። ሸቀጥ ወደ ክልሉ አይገባም። ነዳጅማ ክልክል ነው። መድኃኒት የለም። እንዴት እንደሚኖሩ ፈጣሪ ይወቅ።
"…ከጥቂት ዓመታት በፊት በትግሬ ላይ ሰልፍ ይጠራ የነበረው ዐማራው ነው ብለው እነ ጌታቸው ረዳ አዋራ ያስነሱ ነበር። በዚህ የተነሣ ከዐማራ ኤሊት ጋር ሒሳብ እናወራርዳለን ብሎም ሲደነፋ ነበር። የጎንደር የፖለቲካ ቅማንቱ ስኳድ፣ የጎጃሙ ሸንጎን የሚዘውረው ኦሮሙማ ትግሬ ላይ ሰልፍ አላስወጣም ነበር ማለት ግን አይቻልም። አስወጥቷል። ኢዜማ ግንቦት ሰባቶች በኢሳት ጋዜጠኞች በኩል ሰፊ ቅስቀሳ ያደርጉ እንደነበርም አይረሳም። በውጭ ሲኖዶስ ውስጥ የነበሩት የጎንደር ፋርጣ፣ የጎጃም እና የወሎ ተወላጅ ጳጳሳትም ውሎና አዳራቸው በአሜሪካ መንግሥት ምክርቤት ቢሮ ነበር። መላው አውሮጳ፣ ካናዳና አሜሪካ የአቢይ አሕመድ ቲፎዞዎች ብቻ ሳይሆኑ መንጋው በሙሉ አንድ ላይ ቆሞ ወያኔን ያወግዝ ነበር።
"…ሸአቢያ እና የሻአቢያ ደጋፊዎችም ከሌላው በተለየ መልኩ አስመራ ላይ ሲረግጡ የኖሩትን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጭራሽ ለብሰውት ከፈክ ኢትዮጵያኒስቶች ጋር በመሆን የምዕራቡን ዓለም ቀውጢ ያደርጉት ነበር። አንዲት እናቷ ፕሮፌሰር የሆነች ትግሬ የአሜሪካ ጋዜጠኛ እና አንድ የኤርትራ ተወላጅ ጎረምሳ በጋራ ሆነው " ኖ ሞር" የሚል መፈክር ቀርጸው መንጋውን ሁሉ ሁለቱ ትግሬዎች ሲነዱት ነበር። እነ ደረጄ ሀብተ ወልድ፣ ኢሳቶች፣ ኢኤምኤሶች በሙሉ ገንዘብ ለመከላከያ፣ ሞት ለወያኔ ብለው ሲፎክሩ አድረው ሲፎክሩ ይውሉ ነበር። ብቻ ነገርየው ውስብስብ ያለ ነበር።
"…ዘመን ሄደና ዘመድ መጣ። አኬር ተገለበጠ። አቢይ አሕመድ እና ኦሮሙማው ይሄን ፌክ ኢትዮጵያዊ በሙሉ ከጳጳስ መነኩሴ እስከ ቄስ ዲያቆን ኡስታዝ ፓስተር ጋዜጠኛ ነርስ ዶክተር የኡበር ሹፌር ድረስ ያለውን መንጋ በሙሉ እንደ ኮንደም ቢሉ፣ እንደ ሸንኮራ፣ እንደማስቲካም ቢሉ ተጠቅሞባቸው ሲያበቃ ለስሜታቸው እንኳ ሳይጠነቀቅ ስብሃት ነጋን እና የዓደዋውን ሥርወ መንግሥት ፈትቶ ጃስ ብሎ ለቅቆባቸው በድንጋጤ እሳት የጎበኘው ፌስታል አስመስሎ በካልቾ ጠልዞ ከአጠገቡ ድራሽ አባታቸውን አጠፋቸው። (በዚህ ሥራና ተግባሩ አመስጋኙ ነኝ) አቀለላቸው። እነ አቡነ ጴጥሮስን እማ አዋርዶ፣ በቁም አስሮ፣ በመጡበት ሮጲላ አሳፍሮ ወደ አማሪካ አንገታቸውን አስደፍቶ መለሳቸው። አቤት ጭካኔው?
"…ዛሬ ለአቢይ አሕመድ መንግሥት ብሎ ድጋፍ የሚወጣ የለም። ነጩ ቤተ መንግሥት ሥር ግር ብሎ የሚወጣ የለም። በትግሬ ጉዳይ አንድ የሆነው በሙሉ አሁን አንዱም የለም። ኢሳት ተበታተነ፣ ዐማራ ፋኖ ሆኖ ወጣ፣ ከአቢይ ጋር የቀሩት የጎንደር እስኳድ፣ የወሎ ትግሬማሮች፣ የጎጃም ቅባቴና ሸንጎዎች ሲቀሩ ሁሉም ነፍጥ አንሥቶ መተግተግ ከጀመረ።ሁለት ዓመት አልፎ ሦስተኛ ዓመት መጥቷል።ኤርትራ አሰላለፏን ለውጣ በከፍተኛ ዝውውር ወደ ትግሬዋ ወያኔ ገብታለች። ሱዳንም ከአቢይ ወደ ሻአቢያና ወያኔ ዞረው ገብተዋል። ፋኖም ጥይት እስከሰጡት ድረስ አይደለም ከወያኔ እና ከሻአቢያ ከሰይጣን ለምን አይሆንም አብሬ እሠራለሁ ብሎ ከአቢይ አገልጋይነት፣ ተዋጊነት ወደራሱ ቀልብ ተመልሶ የነፃነት ትግሉ ላይ ወጥሮ ይዟል።
"…እንግዲህ ዘመን መጥቶ አቢይ አሕመድ ከዐማራው፣ ከቤርቤረሰቡ ሁሉ እንደ ድሮው ወያኔን ተቃውሞ ሰልፍ የሚወጣ ቢያጣም ነገር ግን ከትግራይ ተርበው፣ የሚበሉት አጥተው፣ ጠኔ፣ ችጋር ጠንቶባቸው "ይሞታል ወይ? ይሞታል ወይ ታዲያ? የሚል ዘፈን የሚዘፍኑ፣ እንደ ጌታቸው ረዳ፣ ጻድቃን ገብረ ተንሣይ የመሳሰሉ የወሎ ተወላጅ ትግሬዎችን ከፊት አሰልፎ ነገ ጠዋት አዲስ አበባ ላይ ትግሬ በትግሬ ላይ እንዲነሣ በማድረግ "ማልአባሺ" እያለ ከጀርባ በሳቅ ፍርፍር ሊበላ ለመዋል በዝግጅት ላይ ነው።
"…የኦሮሞ እናት፣ የዐማራ የደቡብ እናትን ከጉያዋ ልጇን እየነጠቀ በሸኔ፣ በትግሬ እና በዐማራ ፋኖ ጥይት የሚያስፈጀው አቢይ አሕመድ ነገ ጠዋት ለትግሬ አዛኝ የቅቤ አንጓች በመምሰል በትግራይ በግዳጅ በአፈሳ ወደ ጦርነት የሚወሰዱ የትግራይ ልጆች አሳዝነውት በሰላማዊ ሰልፍ ትግሬ በትግሬ ላይ ተነሥቶ ነገ ጠዋት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት በመስቀል አደባባይ ተገኝቶ "ፍትሒ ንሕዝቢ ትግራይ" ወያኔ ሌባ ኢዩ፣ ጁንታ ፀረ ሀንድነት ኢዩ፣ ንዚ እዛ ሽማግሌታት ሕወሓት ንፍርዲ ይቀረቡሉ። ንፌደራል መንግሥቲ ኢትዮጵያ አብ ትግራይ ጠጠው ብሎ ይግብአሎ፣ ንድሮን፣ ጄቲ ብትግራይ ይተኩሱሎ፣ ባንዳታት ትግራይ ይደምሰሱሎ ብሎ ትግሬ ራሱ ራሱ ላይ ሰልፍ ሊወጣ ነው። አቤት የመድኃኔዓለም ሥራ። ቢያንስ አሁን እንኳ ዐማራን የሚከሱበት አጀንዳ አሳጣቸው። ደግሞ ነገ ዣንጥራር ወይም አገኘሁ ተሻገር አልያም አረጋ ከበደ በሰልፉ ላይ ተገኝተው ዐማራን እንዳያሰድቡ እንጂ እግዚአብሔርስ ሥራውን ሠርቷል።
"…በነገው ሰልፍ ላይ በኦሮሙማው ለመወደድ፣ ላለመጠመድ፣ ላለመታሰር ሲሉ በአዲስ አበባ በስደት ላይ ያሉ ትግሬዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሰልፉ ላይ እንደባለፈው ጊዜ መሸፋፈን፣ መከናነብ፣ መልካቸው እንዳይለይ መደበቅ፣ ከካሜራና ከፎቶ መሸሽ አይቻልም ተብሏል። በተለይ በለሚ ኩራ የሚገኙ፣ በአንድ ቤት 20 እና 30 ሆነው በቀን ሥራ እና በሴተኛ አዳሪነት ኑሮአቸውን እንዲገፉ ህወሓት እና ኦህዴድ የፈረዱባቸው ሀገር አልባ ትግሬዎች የግዳቸውን መሰለፍ አለባቸው ተብሎ መወሰኑም ተሰምቷል። ድምጻቸውን ከፍ አድርገው መፈክር ማሰማት ግዴታም ነው ተብሏል።
"…በሌላ በኩል እነ አሕመድ ጀበል እና የኦሮሞ የወሀቢያ እስላሞች በሰልፉ አካባቢ ተገኝተው በአክሱም መስጊድ ይሠራ፣ ሂጃብ ይፈቅድልን ብለው ትግሬዎቹን እንዳይበጠብጡ ለፌደራል ፖሊስ ጥብቅ መመሪያ መውረዱም ተሰምቷል። ትግሬ አሁን የደከመ ስለመሰለ ቀስ በቀስ ትግሬን በትግሬ በማባላት ማጥፋት እንጂ እናንተ ጣልቃ ገብታችሁ እቅዳችንን እንዳታበላሹ ነው የሚለው አሉ ኦሮሙማ። ለትግሬ እና ለዐማራ ብዙ ወሬ፣ ብዙ ዜና ትንሽ ልማት፣ ለኦሮሞ ትንሽ ወሬ ብዙ ልማት። ትግራይ እስክትለማ ሌላው ክልል ይድማ ይባል የነበረውን የወያኔ መፈክር ኦህዴድ ኦነግ በአንደዜ ገልብጦ ኦሮሚያ እስክትለማ ሌላው ክልል በድሮን፣ በጀት፣ በቦንብ ይድማ ብሎ ሥራውን እየሠራ ነው። ለትግሬ እና ለዐማራ ባይራክተር ለኦሮሞ ትራክተር። እንዴዢያ ኖ።
"…ነገ የእኔ ሥራ የትግሬ ሰልፈኞቹን ሁኔታ ማየት ነው ሥራዬ። አደራ ኦህዴድ ሰልፍ የሚወጣ ትግሬ ቁጥሩ ያንሳል ብለህ ደግሞ እንደለመድከው እነ እትዬ ጫልቱን፣ እነ እማማ ዘርመጭን፣ እነ ኦቦ ጎንፋን፣ ፈይሳን ቀላቅለህ ሰልፍ ውጡ ብለህ እንዳትዋረድ። በቃ የትግሬን ጉዳይ ለትግሬ ነው መተው። መልካም ሰልፊ አሀት አሀወይታትና አቦታትና አዴታትና። የቀንኧለት።
• የምለው ገብቷችኋል ኣ…? | 28 702 |
| 15 | ማስታወቂያ !!
"…ነገ ጠዋት ትግሬዎች በራሳቸው አነሳሽነት ወያኔ ላይ የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ ሊወጡ ነው የሚል ዜና በኢሳት እና በኢቢሲ ባየሁ ጊዜ ከዚህ በታች የተሰማኝን ስሜት እንደሚከተለው ጻፍኩላችሁ። 👇 | 27 031 |
| 16 | "…ከትናንት ጀምሮ ብዙ ሰዎች ኧረ ምን ይሻለናል? አሁንም ይሄ አገዛዝ 5 ቢልዮን ብር ሊበደር ነው። እነሱም አበዳሪዎቹም ይሄ ማይም የሆነ ሰው ተመችቷቸዋል፣ ዶላሩን እየዛቁ እያነሱ ብድሩን በላይ በላዩ እየከመሩ እየሰጡት ነው። የአሁኑ ኑሮ ከበደን ስንል ወደፊት የባሰ ዘመን ሊገጥመን ነው? ኧረ እንደው ፈጣሪን ምን ብንበድለው ነው እንዲህ አሳልፎ ለዚህ ማይም አውሬ የብልፅግና ወንጌል እና ለኦሮሙማው የወሀቢይ እስላም አገዛዝ አሳልፎ የሰጠን ሲሉ እየሰማሁ ነው።
"…IMF እንደገለጸው ከሆነ እናንተ ብቻ 5 ቢልዮን ዶላር ብድሩን ልቀቁልኝ እና የጫካ ቤተ መንግሥት ፕሮጀክቴን ልገንባበት እንጂ
በነዳጅ ላይ ድጎማውን በማንሳት ሊትሩን 350 ብር አስገባዋለሁ። በሪል እስቴት፣ በአልኮልና በትምባሆም እና በኢንቨስትመንት ታክስ ነፃ መብቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦችን እጥላለሁ በማለት የብልግናው መንግሥት አዲስ የውጭ ብድር ለማግኘት ሲል እነዚህን ሰፊ የታክስ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑ ነው የተሰማው። ራብ አለ፣ ጦርነት አለ፣ በዚያ ላይ ኑሮው አሁን ካለው በላይ ሊጦዝ ነው ማለት ነው። በመንግሥት ድጎማ ሕዝብ ክፉ ጊዜን በሚሻገርበት ዘመን መንግሥቱ ራሱ ክፉ ሆኖ ከክፉው ጊዜ በላይ ከፍቶ ተገኘ።
"…አንዴ በጣልያን በኩል ሌላ ጊዜ በእንግሊዝ በቱርክና በግብፅ እያሉ ቅኝ ለመግዛት ብዙ የሕይወት እና የገንዘብ መስዋእትነት የከፈሉት ምእራባውያን ሎተሪ ነው የወጣላቸው። ሀገሪቷን ከቀጥተኛም ሆነ ከእጃዙር ቅኝ ግዛት ተፋልጠው ያስጠበቋት ኢትዮጵያውያን ብዙ ዋጋ ከፍለው ለዚህ ለእኛ ዘመኑ ከንቱ የከንቱ ከንቱ የሆነ ትውልድ ቢያስተላልፉም ምዕራባውያኑ ግን የቀድሞ መንገዳቸውን አካሄድ ገምግመው አዲስ መንገድ ተከትለው በሚፈልጉት ጊዜ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ወደ ቅኝ ግዛት ዘመን የሚመልስላት እና አሳልፎ የሚሸጣት ሰው አግኝተው ጮቤ ረገጣ ላይ ይገኛሉ።
"…ከኢጣሊያ ወረራ በኋላ ወደ አውሮጳ የተላኩት የትግሬና የኦሮሞ የባንዳ ልጆች በአውሮጳ ፀረ ኢትዮጵያ ትርክት ሲጋቱ ከርመው ከደርግ ጀምሮ የኢትዮጵያን ቋሚ ምሰሶዎች በማፍረስ፣ የኢትዮጵያዊነትን ዋና ዋና ምሰሶዎች በኦሮሞና በትግሬ ባንዳ የባንዳ ልጆች በመደብደብ፣ ሆዳም ዐማራውን በሆዱና በሴት በሥልጣን በመደለል አብሮ እንዲያፈርስ በማድረግ፣ ኦርቶዶክስን እና ዐማራን በማድቀቅ፣ የሀገር ፍቅር ስሜት፣ የሰንደቅ ዓላማ ፍቅር እንዳይኖር በማድረግ ዛሬ ላይ ለሀገሩ፣ ለወገኑ ደንታ የሌለው ሕዝብ እንዲፈጠር በማድረግ በገዛ ልጆቿ ኢትዮጵያን በማድቀቅ ዛሬ በጣር ላይ ያለች ሀገር ለማየት በቅተናል።
"…ለቅኝ ገዢዎች እንደ አቢይ አሕመድ አሊ ያለ ሀገሩን እና ሕዝቡን የሚጠላ መሪ እድሜልካቸውን ቢዞሩ፣ ቢለፉ አያገኙም። ትግሬዎቹም ቢሆን ትንሽ ኦርቶዶክሳዊ ደም ስለነበራቸው ለባርነት ራሳቸውን የፈቀዱ ቢሆንም ይሉኝታ ግን ነበራቸው። ይሄ ወዳጄ ፀረ ኢትዮጵያ የኦሮሞ የወሀቢያ እስላም ለምዕራባውያኑ የጌታ ልጅ ነኝ እያለ እየፎገረ፣ በተግባር ከዓረቦች የባሰ ጨካኝ ፀረ ኢትዮጵያ ሆኖ የገዛ ሀገሩን ፍርክስክሷን አውጥቶ አረፈው። አንድም ፋብሪካ፣ አንድም ትምህርት ቤት ሳይገነባ፣ መናፈሻና ሪዞርት እየገነባ፣ ቤተ መንግሥት እና የቡና ቤት ዲኮር የመሰለ ከተማ በቀለም ቅብ እየፈጠረ በአሰልቺ እና ሲደጋገም እውነት በሚመስል ውሸት ሕዝቡን አደንዝዞ ወደ መቃብር እየወሰደው ይገኛል።
"…አሁን ምን ማድረግ ይቻላል ብሎ የሚጠይቅ ሰው እንኳ የለም። ጠፍቷል። ሆዳሙ በሙሉ ከሰውየው ጎን ተሰልፏል። ጥቂቶችን በሆድ ይዞ ሀገርን እንዴት ሀገርን መግደል፣ መቀመቅ መክተት እንደሚቻል አቢያ አሕመድ አሳይቷል። ከአይ ኤም ኤፍ መበደር ከእናት መቀነት እንደ መበደር ነው እያለ መንጋውን በሙሉ በማስጨብጨብ የሀገርን ማክሮ ኢኮኖሚ ያለ ግርግር፣ ያለ አንዳች ተቃውሞ አሳልፎ መሸጥ እንደሚቻልም አሳይቷል።
"…አሁን የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ነፃ እንዲሆን መተው በአስገዳጅ ውል ስለታሰረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከጨዋታው ወጥቷል አንድ ዶላር ስንት ብር እንደሚዘረዘር ማየት ነው። ለአበዳሪው የሚከፍለውን ብር ተበዳሪው አገዛዝ ሠርቆ፣ ዘርፎ እንጂ ሠርቶ፣ አምርቶ መክፈል የማይችል ሱፍ የለበሰ ሜካፓም ማጅራት መቺ ዱርዬ አደገኛ ዘራፊ ወንበዴ ስለሆነ በስሙ የተበደረው ሕዝብ አገዛዙ የተበደረውን እና ለቅንጡ ኑሮው ያወጣውን ወጪ ጨምሮ መክፈል ስላለበት አዳሜና ሔዋኔ ከፍተኛ የሆነ ታክስ ታክስና ቀረጥ አናቱ ላይ ይቆለላል ማለት ነው።
"…ይልቅ ድጎማዎች በሙሉ ስለሚነሱ ከወዲሁ አንድ ዳቦ 100 ብር፣ አንድ እንጀራ 200 ብር፣ አንድ ሊትር ዘይት፣ አንድ ኪሎ ሽንኩርት፣ አንድ ኪሎ ጤፍ፣ አንድ ኪሎ ስኳር፣ የታክሲ፣ የአውቶቡስ፣ የአውሮጵላን ዋጋ፣ የህክምና ዋጋ፣ የቤት ኪራይ፣ የመብራት፣ የውኃ፣ የትምህርት ቤት ክፍያ ወዘተ በእጥፍ ይጨምራል። ዚምቧቤ እና ሱማሌ ላይ ያሾፍን በሙሉ ከእነሱ በከፋ መንገድ ለአንድ ዳቦ የወደቀውን ብር በጋሪ ተሸከመን፣ ወዛደር ጠርተን በጆንያ አሸክመን እንንገላወዳለን። በዚያ ላይ ዝናቡ ከቀረ እና ራቡ የሚከተል ከሆነ፣ ጦርነቶቹ በአንዳች ምክንያት የማይጠናቀቁ ከሆነ መጪው 2019 ዓም ለዓለም ሁሉ መጥፎ ቢሆንም እንደዜጋ ለኢትዮጵያ ግን የከፋ የሚሆን ይመስላል።
"…አሁን አገዛዙ እያለ ያለው "አባቴ (ወያኔ) ቀንበር አክብዶባችሁ ነበር፥ እኔ ግን (ልጁ ኦህዴድ ብልፅግና) በቀንበራችሁ ላይ እጨምራለሁ፤ አባቴ (ወያኔ) በአለንጋ ገርፏችሁ ነበር፥ እኔ ግን (ልጁ ኦህዴድ ኦነግ ብልፅግና) በጊንጥ እገርፋችኋለሁ። 1ኛ ነገ 12:14። በቢሻን ቀበና እ ተዝናኑ መቻል ነው።
• ለማለት የፈለግኩት ገብቷችኋል አይደል? | 29 892 |
| 17 | መቻል ነው እንግዲህ…
"…አባቴ ቀንበር አክብዶባችሁ ነበር፥ እኔ ግን በቀንበራችሁ ላይ እጨምራለሁ፤ አባቴ በአለንጋ ገርፏችሁ ነበር፥ እኔ ግን በጊንጥ እገርፋችኋለሁ። 1ኛ ነገ 12:14
"…ራቡ አለ፣ ጦርነቱ አለ፣ በዚያ ላይ የመረጣችሁት የአድባር ዛፍ አለ። እናም ብልጽግና ይምራኝ ካልክ በኋላ ግብር በዛብኝ፣ ኑሮ ከበደኝ ምናምን አይሠራም። ልማታዊ መንግሥት ነው ብለህ አይደለ እንዴ የመረጥከው? የምን መንጫጫት ነው?
"…ያልመረጣችሁትን አልተናገርኩም። እኔ እየተናገርኩ ያለሁት መንግሥቴ ሺ ዓመት ንገሥልኝ ያሉትን በልጻጊዎች ነው።
• በሎም ‼ አለ ወያንቲቲው አሉላ ሰለሞን እንደ ዛሬው ሳይበለጽግ በፊት።
• የምልው ገብቷችኋል ኣ…? | 30 063 |
| 18 | • እንደምን አደራችሁ? | 29 309 |
| 19 | • አልዘነጋሁትም
"…የንክክር ኮሚሽኑን ጉዳይ አጀንዳዬ የማላደርገው አስቀድሞ የተባነነበትና የተበላ ዕቁብ ስለሆነ በማለት ነው። ይሄን ጨፍኑ ላሞኛችሁ የብልፄ የሴፍቲኔት እና የገጠር ካድሬ ስብሰባ ናቅ አድርጌ ነገር ግን ደግሞ በዚህ አጋጣሚ በሞኞች ትከሻ ላይ ተሰቅለው ከሰገነቱ ላይ ለመውጣት ያሰፈሰፉትን ምቹ ጊዜ ጠባቂዎችን መጨረሻቸውን ለማየት ስል በአይነ ቁራኛም ከስር ከስር እግር በእግር መከታተሌም አልቀረም።
"…በዚህ የንክክር ኮሚሽን ጉባኤ ጎልተው አድቫንቴጃቸውን አስጠብቀው፣ ፍላጎታቸውን ሕግ አድርገው ለመውጣት ያሰፈሰፉት ሁለት አካላት ናቸው። ሦስተኛዎቹ በአንደኛው ውስጥ ቦታ ስላላቸው ብዬ እንጂ በደረጃ ካስቀመጥናቸው 1ኛ፥ አቢይ አሕመድ፣ 2ኛ፥ የኦሮሞ ወሀቢያ እስላሞች ፫ኛ፦ የብልፅግና ወንጌል አማኞች ናቸው። እነዚህ ናቸው ከዚህ ጉባኤ በሰፊው ለማፈስ ያቆበቆቡት። ያሰፈሰፉት።
"…ትግሬ ወኪል የለውም። ዐማራም ጦርነት ላይ ነው። ከማን ጋር መክሮ፣ ተመካክሮ እንደሚወጣ ብቻ ማየት ነው። የሆነው ሆኖ ግን እኔ እንደ አንድ ግለሰብ ከጉባኤው ላይ አይኔን አላነሳሁም። ወፎቼ እና ርግቦቼም እዚያው ናቸው። በንቃት ሂደቱን እየተከታተሉም ነው። አይደለም ሌሎች ጋር እንደምንም የወሀቢይ እስላሞቹ ጋርም ወፎቼ ተመሳስለው ገብተው እየተሳተፉ ነው። ፍላጎታችን ካልተሟላ ጉባኤውን ረግጠን በመውጣት አገዛዙን ጭምር ማስደንገጥ አለብን ብለው በወሰኑት በሰሞኑ የመስጊድ ስብሰባም ላይ ነበሩ ወፎቼ።
"…እስከአሁን ባለው ሁኔታ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው ያለው። ጉባኤተኞቹ ምድብ ምድባቸውን ይዘው ተቀምጠው የሚያወያያቸው አጥተው ነው የዋሉት። ምሣ በልተው ብዙዎች መበተናቸውን ነው ወፎቼ ያደረሱኝ የዛሬውን ውሎ። የተፈራው የወሀቢያ እስላሙ አጀንዳ ሲሆን እሱ ብዙ የሚያነጋግርና ዱላም ሊያማዝዝ እንደሚችል ነው የሚናገሩት ወፎቼ። በተለይ ጅማዎቹ እና የጅማ የኦሮሞ የወሀቢያ እስላሞቹ በሙሉ ኃይላቸው ነው የሀገሪቷን መሪ ልጃቸውን አቢይ አሕመድ አሊን፣ የእስልምና ፕሬዘዳንታቸውን ኢብራሂም ቱፋን እና ሌላውን የጅማ እስላም አሕመዲን ጀበልን ከፊት አሰልፈው ለፍልሚያ የተዘጋጁት።
"…እስላሞቹ ተወካዮች፣ የጴንጤዎቹም ተወካዮች ጥንቅቅ ብለው ተዘጋጅተው ከቁጥር ሳይጎድሉ በጉባኤው የተገኙ ሲሆን ከኦርቶዶክስ የተወከሉት ግን አብዛኛዎቹ እንዳልተገኙ ወፎቼ መረጃውን አድርሰውኛል። በተለይ ከክፍለ ሀገር የተመደቡት ቀኑ ረጅም ነው። ይሄን ያህል አንድ ወር አዲስ አበባ አንቆይም። እዚያው አዲስ አበባ ያሉት ከቻሉ ይገኙ በሚል ምክንያት ሳይገኙ እንደቀሩ ሰምቻለሁ። የቤተ ክህነቱን የሕግ ክፍል ጨምሮ እነ ፕሮፌሰር ግርማ ባቱ፣ እነ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤልን የመሳሰሉ ልጆች በጉባኤው ላይ መሰየማቸው ተረጋግጧል።
"…ለማንኛውም የእኔ አጀንዳ ራቡ ላይ፣ ዝናቡ በመጥፋቱ ሊመጣ ስላለው ጠኔ ላይ፣ ስለ ቸነፈሩ ማውራት፣ ሕዝቡ ካህናቱ እምቢ ቢሉ ራሱ ምህላ እንዲያደርስ፣ እንዲጸልይ መወትወቱ ላይ ነው የማተኩረው። አሁን አይታችሁ ከሆነ እኔ ድርቅ ብዬ ዋይ ዋይ ማለት ከጀመርኩ በኋላ የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ሳይቀር በሸገር ራዲዮ " ትንሽ ሽግር ይኖራል" የሚል መግለጫ ሲያስነብብ አይቻለሁ። አንዳንድ የመንግሥት አካላትም በወረዳና በዞን ደረጃ የድርቁን አስከፊነት ከወዲሁ መግለጽ ጀምረዋል። እናም አጀንዳዬን እዚያው ላይ ነው ማተኮር ያለብኝ ብዬ እዚያው ላይ እዬዬ ማለቱን ተያይዤዋለሁ።
"…በመሃል የከተማ መነኮሳትን እና አባ በርገሮችን በተመለከተ ጣል በማድረግ እንወያያለን። ርእሰ አንቀጾችም ይኖራሉ። ድርቁን በተመለከተ ባለፈው ለሊቃውንተ ኢትዮጵያ የቀረበው የኤልኒኖ ጉዳይን በተመለከተ ክፍል ሁለትም በሚገባ ተዘጋጅቷል። በወሎዬዎቹ እና በጎጃም ቅባቶች እየተመሰረተ ስላለው የዐማራ ሲኖዶስም ጥናቱ እያለቀ ስለሆነ ሊቃውንቱ ለሕዝብ ይቅረብ ሲሉ ወዲያው አቀርብላችኋለሁ። አዚህ ፔጅ ላይ የምንነጋገራት፣ የምንወያያት ጉዳይ ሁላ በንቀት የሚመለከተው እንደሌለ አስረግጬ ነው የምነግራችሁ። ከባድ ሚዛኖች መሆናችንን መዘንጋት የለባችሁም።
"…በነገራችን ላይ የኦሮሞ የወሀቢይ እስላሞቹም ሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለቱም ተቋማት ለንክክር ኮሚሽኑ ያስገቡትን አጀንዳ ሳልቆራርጠው፣ ሳልሸራርፈው ሙሉውን ከፈለጋችሁ በርእሰ አንቀጽ መልክ አቅርቤ ለታሪክ ማስቀመጥ ከፈለጋችሁ ልለጥፍላችሁ እችላለሁ። የሁለቱም ተቋማት አጀንዳዎች ከነማኅተማቸው አለኝ። ከፈለጋችሁ ነው ታዲያ።
"…ለማንኛውም ትኩረታችን መጪው አስከፊ ድርቅ ላይ ይሁን። ባለሙያዎች ሕዝቡ ምን ዓይነት ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት ጽፋችሁ ብትልኩልኝ እኔ ከወዲሁ ለሕዝቡ ለማሳወቅ እጥራለሁ። እተጋለሁ።
• ሰምታችኋል አይደል? | 31 228 |
| 20 | "…በሰይፍ የሞቱ በራብ ከሞቱት ይሻላሉ።" ሰቆ ኤር 4፥9
• ሰይፍ ፋታ አይሰጥም። ጉምድ ጭጭ ነው። ጣር፣ ጋር፣ ስቃይ የለውም እና በሰይፍ መሞት ተመሰገነ።
• ራብ ግን ክፉ ነው። ወዲያው አይገድልም። አለዝዞ፣ አመንምኖ፣ አሰቃይቶ ነው የሚገድለው። ራብ ክፉ ነው።
"…በተለይ ሕፃናት ይዞ ራብ አያድርስ… | 31 195 |
