GION MEDIA
📈 Analytical overview of Telegram channel GION MEDIA
Channel GION MEDIA (@gion_media) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 55 502 subscribers, ranking 4 818 in the News & Media category and 597 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 55 502 subscribers.
According to the latest data from 05 May, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -643 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“▫ጥቆማ ለመስጠት➲ @HaimonAb”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 May, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 04 May | +13 | |||
| 03 May | 0 | |||
| 02 May | 0 | |||
| 01 May | 0 |
| 2 | ጎንደር ከተማ...!
ዛሬ መስከረም 19/2018ዓ.ም በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ገፎ ቁጭ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር የተደራጁ ሌቦች፦አደነ ተሾመ፣ ሙሉ ወንድሙ ባዘዘው፣ ይታየው ገቢያው፣ በረከት ይታያል እና ማርቆስ ተሻገር የተባሉ የተደራጁ ዘራፊዎች በአንድ እናት ቤት በመግባት የቤት ዕቃዎችን ዘርፈው ለማምለጥ ሲሞክሩ በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 16 349 |
| 3 | በነዳጅ ላይ የ30 በመቶ ግብር ሊጣል ነው!
የገንዘብ ሚኒስቴር ከ2018 የበጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ማረጋገጡ ተሰማ። ይህ አዲስ ግብር 15 በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15 በመቶ የኤክሳይዝ ቀረጥን የሚያካትት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ይህ እርምጃ በአገሪቱ የፋይናንስ ፖሊሲ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑና የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።
ሚኒስትሩ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ባቀረቡት አጠቃላይ የዜጎች በጀት ዉስጥ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የግብር አይነቶችን በዝርዝር አስቀምጠዋል።
በዚህ መሰረት፣ ከነዳጅ ላይ ከሚጣለው አጠቃላይ 30% የኤክሳይዝ ታክስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ በተጨማሪ፣ የንብረት ታክስ ይገኙበታል። እንዲሁም አማራጭ አነስተኛ ታክስ እና የቅድመ ግብር ክፍያ በተመሳሳይ መልኩ በ2018 በጀት ዓመት ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ካፒታል ጋዜጣ ለመረዳት ችሏል።
ነዳጅ በማዕከላዊነት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የግብር ጭማሪው የዋጋ ግሽበቱ እንዲባባስ ያደርጋል የሚል ስጋት ሲከሰት እንደነበር ይታወሳል። (ካፒታል)
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 18 347 |
| 4 | በአማራ ክልል ውጊያ ባለባቸው አካባቢዎች ታዳጊዎች ለሴተኛ አዳሪነት መጋለጣቸውን ጥናት አመላከተ!
በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት ዓመታት ውጊያ ባለባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው፣ ዕድሜያቸው ለጋብቻ ያልደረሱ ታዳጊዎች ወደ አዲስ አበባና ወደ ሌሎች የክልል ከተሞች በመሄድ በሴተኛ አዳሪነት እንደሚሰማሩ፣ ጀንደር ኤንድ አዶለስንስ ግሎባል ኤቪደንስ (Gender and Adolescence Global Evidence) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የጥናት ቡድን አስታወቀ፡፡
የተቋሙ ጥናት አማራ ክልልን ጨምሮ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በሶማሌና በአፋር ክልሎች ግጭትና ድርቅ ባሉባቸው አካባቢዎች በሚኖሩ 20 ሺሕ ሴቶች ላይ የተደረገ መሆኑንና የልጅነት ጋብቻን ጨምሮ ፆታዊ ጥቃት በከፍተኛ መጠን እንደጨመረ መረጋገጡ ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ የሴቶችን ማኅበራዊ ቅንጅት ‹‹ትመራለች›› በሚል መሪ ቃል ላለፉት አምስት ዓመታት በወጣት ሴቶች ላይ ትኩረቱን አድርጎ ሲሠራ የነበረው ፕሮጀክት የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ ጥናቱን ያቀረቡት፣ የምርምር ተቋሙ የኢትዮጵያ ተወካይ ወርቅነህ አበበ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን አምስት ወረዳዎች ውስጥ ካሉ 67 ቀበሌዎች ናሙና መወሰዱን የተናገሩት ወርቅነህ (ዶ/ር)፣ በቀበሌዎቹ ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተዘግተው መቆየታቸውንና ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ ለመሆን መገደዳቸውን ገልፀዋል። (ሪፖርተር)
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 15 639 |
| 5 | እስራኤል 🇮🇱
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔትኒያሁ የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ላይ ንግግር ለማድርግ መድረኩን ሲይዝ ከጋማሽ በላይ የሚሆኑት ልኡካኖች አዳራሹን ለቀው ወጥተዋል።
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 16 092 |
| 6 | እድለኛ ከሆናችሁ በየቀኑ እስከ 3000 ብር ድረስ ተሸላሚ ታደርጋችኋለች! ቁጥሮችን ያዙ! ያሸንፉና ይሸለሙ! ስለታማኝነቷ እኛ ኃላፊነቱን እንወስዳለን!
ሊንክ👇
https://t.me/+B3akD4Ruc2A0MDU8 | 7 543 |
| 7 | እህታችን እድለኛ ከሆኑ በየቀኑ እስከ 3000 ብር ድረስ ተሸላሚ ታደርጋችኋለች! ቁጥሮችን ያዙ! ያሸንፉና ይሸለሙ! ስለታማኝነቷ እኛ ኃላፊነቱን እንወስዳለን!
ሊንክ👇
https://t.me/+B3akD4Ruc2A0MDU8 | 667 |
| 8 | ይህ ውቢቷን ባሕር ዳር አይመጥንም!
የምትመለከቱት የባሕር ዳር አየር ማረፊያ ነው። በሀገራችን በቱሪስት ፍሰት ቀዳሚ ከሆኑት አንዷ ብትሆንም ሰሞኑን ወደ ከተማዋ በሄድሁበት ወቅት ያየሁት ግን የሚመጥናት አይደለም።
ምንም እንኳ ማስፋፊያ ላይ ቢሆንም ይህን መሰል ገጽታ የሚያበላሽ የቆሸሸ እና በእርጥበት ምክንያት የተበላሸ ጣሪያ ማየት አሳፋሪ ነው። ሚመለከተው አካል እንዲህ ያለውን ነገር ትኩረት ቢሰጠው።
ጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸው
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 23 553 |
| 9 | እህታችን እድለኛ ከሆኑ በየቀኑ እስከ 3000 ብር ድረስ ተሸላሚ ታደርጋችኋለች! ቁጥሮችን ያዙ! ያሸንፉና ይሸለሙ! ስለታማኝነቷ እኛ ኃላፊነቱን እንወስዳለን!
ሊንክ👇
https://t.me/+B3akD4Ruc2A0MDU8 | 5 322 |
| 10 | እህታችን እድለኛ ከሆኑ በየቀኑ እስከ 3000 ብር ድረስ ተሸላሚ ታደርጋችኋለች! ቁጥሮችን ያዙ! ያሸንፉና ይሸለሙ! ስለታማኝነቷ እኛ ኃላፊነቱን እንወስዳለን!
ሊንክ👇
https://t.me/+B3akD4Ruc2A0MDU8 | 4 123 |
| 11 | ኢትዮጵያ በ10.8 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ክፍተት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ አይኤምኤፍ እና የዓለም ባንክ አስጠነቀቁ!
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (የአይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ በጋራ ባወጡት አዲስ ሪፖርት መሠረት፣ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ በተደረጉ ማሻሻያዎች እና ድርድሮች ቢኖሩም አሁንም በከባድ ዕዳ አጣብቂኝ ውስጥ እንደምትገኝ ተጠቆመ።
ሪፖርቱ ሀገሪቱ በ2024–2028 ባለው ጊዜ ውስጥ 10.8 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የገንዘብ ክፍተት እንዳለባት አብራርቷል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ ዘላቂነት የሌለው ሲሆን ይህም በዓለም አቀፍ የገንዘብ ቀውሶች፣ የዩሮቦንድ ዕዳ ክፍያ ባለመፈጸሟ እና ከኤክስፖርት ገቢ ጋር ተመጣጣኝ ባልሆነ የዕዳ መጠን ሳቢያ ነው።
ኢትዮጵያ በታህሳስ 2023 የወለድ ክፍያና በታህሳስ 2024 የ 1.1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ዕዳ ክፍያ መክፈል ያልቻለች ሲሆን፣ ምንም እንኳን ከኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር በመጋቢት 2025 የመርህ ስምምነት ላይ ብትደርስም፣ ሁኔታው አሁንም አሳሳቢ እንደሆነ ተጠቅሷል።
የዕዳ ዘላቂነትን ለመመለስ ኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ አያያዝ፣ የአይኤምኤፍ ድጋፍ እና ከልማት አጋሮች የሚገኝ ፋይናንስን ማጣመር ይኖርባታል። ፕሮግራሙ እኤአ ከ 2024 ጀምሮ ለ4 ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ 10.8 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ ክፍተት እንዳለ አስቀምጧል።
ይህ ክፍተት ከ3.4 ቢሊዮን ዶላር ከአይኤምኤፍ፣ 3.8 ቢሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ የሚገኝ የበጀት ድጋፍ፣ እና 3.6 ቢሊዮን ዶላር ከሁለትዮሽ እና የንግድ አበዳሪዎች የሚገኝ የዕዳ እፎይታ እንደሚሸፈን ይጠበቃል።
አይኤምኤፍ በ2024/25 የሀገሪቷ የጂዲፒ ዕድገት 7.2% እንደሚሆንና የመካከለኛ ጊዜ ትንበያውም ወደ 7.5–8% እንደሚያድግ ገልጿል።
የአይኤምኤፍ እና የዓለም ባንክ ሪፖርት አገሪቱ ከገበያ ውጭ የሆኑ ፋይናንስን በማስወገድ፣ የግብር መሠረትን በማስፋት እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን አስተዳደር በማጠናከር ላይ እንድትሰራ መክሯል።
ሆኖም የዕዳ መልሶ ማዋቀር መዘግየቶች፣ የፀጥታ ችግሮች እና ዓለም አቀፍ የሸቀጦች ዋጋዎች ሊያስከትሉ የሚችሉ ተግዳሮቶች እንደ ዋና ስጋቶች ተጠቅሰዋል። (ካፒታል)
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 21 457 |
| 12 | No text... | 18 821 |
| 13 | በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ለአንድ ሰዓት ያህል ተቋርጦ የቆየው የመብራት አገልግሎት መቋረጥ አሁን ላይ በአብዛኛው አካባቢዎች ተመልሷል።
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 20 473 |
| 14 | እውነተኛ የመረጃ ምንጭ ፈልገው ያውቃሉ⁉️
ከዚህ በፊት ያልተሰሙና ያልተነገሩ መረጃዎችን፣ ያለምንም ወገንተኝነት፣ ስለ ህዝብ ጥቅም ብቻ የሚያቀርብ ቻናል ተከፍቷል። ወቅታዊና አስተማማኝ መረጃዎችን ለማግኘት ይቀላቀሉ።
👉join👈 👉join👈 👉join👈 | 15 476 |
| 15 | "አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የክልል ከተሞች መብራት ተቋርጧል!"
-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል!
ከሰበታ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ፤ ከጥቁር አንበሳ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ አዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋዉ 132 ኪ.ቮ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ መደበኛ የጥገና ሥራ ሲከናወን ውሏል፡፡
ይሁንና ጥገናው ተጠናቆ መስመር በሚሞከርበት ጊዜ በተፈጠረ የመስመሮች መነካካት በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡
የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ በመሆኑ መስመር በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን፡፡
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 13 247 |
| 16 | የቀድሞው የወልድያ ከተማ ከንቲባ የነበሩት መሐመድ ያሱን ስለ ግዕዝ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ያሰፈሩት!
«#ግእዝ is not OLD it’s GOLD. በተሳሳተ ስሌት ልጆችን ከትምህርት ገበታ አናርቃቸው!
ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ህጋዊ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ለወደፊት ህይወታቸው ሊሰጧቸው የሚችሉት ምርጥ ስጦታም ነው።📚
ከግእዝ አንፃር ግን:-
❶ ግእዝ ለኢትዮጵያዊያን የማንነታችን ስርና መሰረት ነው። A people who forget their heritage lose their future. Let’s value Ge’ez not as the past, but as power for Tomorrow.
❷ ግእዝ ሙዚየም ላይ የሚቀመጥ ጌጥ አይደለም፤ የሕያው ኃብታችን አካል እንጂ። ስለሆነም Whoever honors their roots grows stronger for the future.
❸ ያለ ግእዝ ነባር ታሪካችን ሁሉ ድምጽ አልቦ ነው። እናም Keeping it alive means keeping ourselves alive.
ስለሆነም ግእዝን ከ3ተኛ-8ተኛ ክፍል ማስተማር የተፈለገው ልክ እንደ ማንኛውም ቋንቋ ተማሪዎች የግእዝን ቋንቋ የመስማት፣ የማንበብና የመናገር ክህሎቶችን እና እውቀቶችን ለማስጨበጥ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን በቢሮው በኩል የተዘጋጀውን የመማሪያና የማስተማሪያ መፀሀፎችን አግኝቶ ዝርዝር ይዘቱን በማየት መረዳት ይቻላል።
ምክኒያቱም Ge’ez is not a BURDEN, it’s a BRIDGE between generations.
ከዚያም በአመዛኙ በሙከራ ትግበራ ላይ ያለና በመምህራንና መሰል የግብዓት እጥረቶች ሳቢያ በሁሉም የክልሉ የመንግስት ትም/ት ቤቶች 100% እየተሰጠ የሚገኝ ባለመሆኑ በቀጣይ ስርዓተ ትምህርቱ እየዳበረ እንዲሄድ ለማሻሻያነት ግብዓት የሚሆኑ ጉዳዩችን በተደራጀ ሁኔታ ለሚመለከተው ተቋም ማድረስ ጠቃሚ ይመስለኛል።
ምክኒያቱም Ge’ez is the KEY, without it the door to our history stays CLOSED.
ነገር ግን ከዚህ ቀደም በቤተ ክርስቲያን በኩል ለሰንበትና ለአብነት ትም/ት ቤቶች፣ ለመንፈሳዊ ኮሌጆችና ተቋማት ላይ በማስተማሪያነት ከተዘጋጁት የመማሪያ መፀሃፎች ውስጥ ከፊል ገፆችን እያቀረቡ እንዲሁም አበው ለመንፈሳዊ ተማሪዎች ስለ ግእዝ ያስተማሩበትን ተንቀሳቃሽ ምስል በአስረጂነት በማቅረብ ነገርየውን የእምነት አጀንዳ እንዲይዝ ማድረግ ተገቢነት የለውም።
ምክኒያቱም ግእዝ ለቀድሞው እኛነታችን የጀርባ አጥንት ነው። ስለሆነም Cut the root and the tree cannot stand በሚል መነሻ እየተዘመተበት ያለው።
በመጨረሻም አዕምሮ የሚያውቀውን እውነት ልብ እስኪቀበል ጊዜ ይፈልጋል። This is my #last word on Ge’ez. ሰላም በሰላም።»
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 12 969 |
| 17 | No text... | 15 364 |
| 18 | የደመወዝ ጉዳይ!
መንግስት ከመስከረም 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ የደመወዝ ጭማሪ ተደርጓል ቢልም እስካሁን ድረስ ወደየትኛውም መስሪያ ቤት የተላለፈ የደመወዝ ጭማሪ ሰርኩላር እንደሌላ አረጋግጠናል። የደመወዝ ጭማሪ ተደርጓል መባሉን ተከትሎ ያለ ምንም ምክንያት በሸቀጦች እና በፍጆታ እቃዎች ላይ የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
የደመወዝ ጭማሪው ከመስከረም ወር ጀምሮ ቢሆንም የመስከረም ወር ደመወዝ ክፍያው የሚፈፀመው ግን በጥቅምት ወር መሆኑን የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አሳውቆ ነበር። ሆኖም እስካሁን ድረስ የደመወዝ ጭማሪውን አስመልክቶ ዝርዝር የደመወዝ ጭማሪ እና አፈፃፀም መመሪያ አልወጣም፣በርካታ ሰዎችም መረጃ እየጠየቁ ይገኛሉ።
የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ በቅርቡ ይወጣል፣አሁንም በርካታ የውሸት መረጃ እየተሰራጩ በመሆኑ የሚመለከተው አካል በዚህ ዙሪያ መረጃ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 19 473 |
| 19 | አንጋፋዉ ጋዜጠኛ ወደ ቴሌግራም መጣ፡፡ መረጃዎችን ጎልጉሎ በማዉጣት የመንግስት እራስ ምታት ሆኖል ፡፡
ተቀላቀሉት Join👇👇
"በዚህ ሊንክ ግቡ 👇👇
https://t.me/+MMg_t9-xdF05Zjhk
https://t.me/+MMg_t9-xdF05Zjhk
https://t.me/+MMg_t9-xdF05Zjhk | 14 136 |
| 20 | #አዲስአበባ
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የጥበቃ ሠራተኛ አቅራቢያ ኤጄንሲዎች የጥበቃ ሠራተኞችን ከኦሮሚያ ክልል እንዲቀጥሩ እየተገደዱ መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለፁ
በከተማዋ የጥበቃ ሠራተኞችን ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚያቀርቡ በርካታ ኤጄንሲዎች የሚገኙ ሲሆን፣ እነዚሁ ኤጀንሲዎች የጥበቃ ሠራተኞችን ከኦሮሚያ ክልል እንዲወስዱ የክልሉ መንግሥት እያስገደደ ነው ተብሏል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የጥበቃ ኤጄንሲዎች ለስራ ቅጥር ዝግጁ የሆነ የሰው ኃይል መልምሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ ምንጮች አያይዘው ገልጸዋል።
የጥበቃ ሠራተኛ አቅራቢ ኤጄንሲዎች በንግድ ተቋማት፣ በሲቪልና ግለሰብ ድርጅቶች፣ እንዲሁም በመኖሪያ አፓርታማዎች በጥበቃ ስራ የሚሰማሩ ሠራተኞችን ለደንበኞቻቸው እንደሚያቀርቡ ይታወቃል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥትም የጥበቃ ሠራተኞችን በማሰልጠን እና ለቅጥር ዝግጁ በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ በስፋት አገልግሎት የሚሰጠውን ይሄንኑ ዘርፍ ለመቆጣጠር በስፋት አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል ተብሏል።
በተያያዘ ዜና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት “ገዳ ልዩ የኮማንዶ ኃይል” የተሰኘ ራሱን የቻለ ልዩ ስልጠና የሚሰጠው ወታደራዊ ኃይል በአዲስ አበባ ከተማ ሊያሰማራ እንደሆነ ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል።
አሁን ደግሞ በከተማዋ የሚገኙ የሲቪል ጥበቃ ኤጄንሲዎች የኦሮሚያ ክልል የሚያሰለጥናቸውን የጥበቃ ሠራተኞች እንዲቀጥሩ ግዳጅ እንደተጣለባቸው ዞብል ፖስት ከመረጃ ምንጮቹ ያገኘው መረጃ ያሳያል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ እና በዙሪያዋ በሚገኙ ወረዳዎች የሚያካሂደው የፀጥታ ኃይል ስምሪት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ስለመምጣቱ መሰል እንቅስቃሴዎች እንደ ሁነኛ ማሳያ ተደርገው ሊወሰዱ ይችላሉ። (ዞብል ፖስት)
መረጃዎችን በቪዲዮ ለማየት➲ tiktok.com/@haimon_abi | 15 684 |
