cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Ko'proq ko'rsatish
Advertising posts
411 064Obunachilar
-37424 soatlar
-2 2967 kunlar
-7 07730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Обуначиларнинг ўсиш даражаси

Ma'lumot yuklanmoqda...

አላችሁ አይደል…? "…ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር • ጀምረናል ገባ ገባ በሉማ "…ሻሎም !  ሰላም !
Hammasini ko'rsatish...
👍 814 150🙏 46🏆 26🔥 13🕊 9 6
"…ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር "…ዘወትር እሑድ በመረጃ ተለቭዥን በቀጥታ ስርጭት የሚተላለፈው “ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር” የተሰኘው ሳምንታዊው መደበኛ የቀጥታ ስርጭት መርሀ ግብራችን ከሁለት ወራት ቆይታ በኋላ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ ይጀምራል። • ዩቲዩብ 👉 https://www.youtube.com/watch?v=IoQqARsRDKo • ትዊተር 👉 https://twitter.com/MerejaMedia • በራምብል 👉 https://rumble.com/c/Mereja/live "…በተረፈ የእኔን የስልክ ወጪን ጨምሮ አገልግሎቴን ለመደገፍ የምትፈቅዱ። 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል መለገስ ትችላላችሁ። ሁላችሁም ተመስግናችኋል። "…ሻሎም !  ሰላም !
Hammasini ko'rsatish...
👍 460 78🙏 26🕊 14🏆 13🔥 10👌 2
"…ሁለቱም የጦር መሪዎች አነጋግረውኛል። የምሥራቹ ዜናውንም ለዓለም ሁሉ ንገርና አድርስም ብለውኛል። ለዐማሮችም መልእክት አላቸው። "…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በጉጉት በምትጠብቁትና ዘወትር ሳምንት እሁድ እሁድ በመረጃ ተለቭዥን በሚቀርበው "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር" በተሰኘው መርሀ ግብሬ ላይ ድምጻቸውንም፣ መልእክታቸውን አሰማችኋለሁ። የምሥራቹንም አበሥራችኋለሁ። "…ሳስበው፣ ሳስበው የኢትዮጵያንም ትንሣኤ በዚህ መልኩ የማበሥራችሁ ነው የሚመስለኝ። በድጋሚ እንኳን ደስስ አላችሁ…! • ሸዋ ሰምተሃል…!
Hammasini ko'rsatish...
👍 1977 287🙏 122🏆 60🕊 23🔥 19😁 12👌 8 6🤯 6
የምሥራች ሰበር ዜና ከወሎ ቤተ ዐምሓራ…! "…ረዘም ላሉ ወራት፣ ጊዜ ወስደው ሲነጋገሩ፣ ሲመካከሩ የቆዩት የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ እና የወሎ ዐማራ ዕዝ በዛሬው እለት ልዩነታቸውን ሁሉ አጥፍተው ወደ አንድ ዕዝ መግባታቸውን አብሥረዋል። "…እስከዛሬም ሲያጨቃጭቅ የነበረው የዕዙ መሪና የዕዙ ስምም መቋጫ፣ መደምደሚያ ማግኘቱ ነው የተነገረኝ። "…የምሥራቅ ዐማራ የሚለው የእነ ምሬ ስም በየዐማራ ፋኖ በወሎ ዕዝ የተተካ ሲሆን፣ የዕዙ መሪ ማን ይሁን የሚለውም ምላሽ አግኝቶ የአዲሱ የዐማራ ፋኖ የወሎ ዕዝ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ሲሆን የዕዙ ምክትል ዋና አዛዥ ኮረኔል ፋንታሁን ሙሐቤ ሆነው ዐማራ ፋኖ በወሎ ዕዝን በጋራ እንዲመሩ መመደባቸውን ከሥፍራው የደረሰኝ መረጃ አመላክቷል። • ጎጃም ፩ ሆኗል • ወሎም ይኸው ዛሬ ፩ ሆነ • ጎንደር ጣጣውን ጨርሶ ብሥራት እየጠበቅን ነው። "…የሚቀረው ሸዋ ብቻ ነው። ሸዋም እርቅ ጨርሶ የጎደለው አፈጻፀሙ ነው። እሱም ቢሆን የግዱን ይሳካል። 💪🏿💪💪🏿 "…እንኳን ደስስ ያላችሁ…!
Hammasini ko'rsatish...
👍 2371 286🙏 165🏆 50🔥 28👌 21😁 16🕊 10 9🤯 8 4
"…በኦሮሚያ ከሚሰለጥኑት ልዩ ኮማንዶዎች ብዛትና ጥራት የተነሣ መጪው ክረምት ለዐማራ ፋኖ እጅግ ሳይከብደው አይቀርም የሚሉ መተርጉማን አሉ። • ፋኖ ሆይ ምን ተሻለህ…? ወይ በጊዜ እጅ ትሰጥ ይሆን…? 🙏🙏🙏
Hammasini ko'rsatish...
😁 258👍 29🙏 11 7🤯 2🕊 1
የእኔ ሱቅ…! "…እኔ ኢንቬስተር ነኝ። ሰዎች ሓሳባቸውን የሚሸጡበትን ሱቅ፣ መደርደሪያ ሁሉ ሰርቼ፣ ክፍት ቦታም አዘጋጅቼ፣ በሩን ብርግድ አድርጌ ከፍቼ በነፃ ይጠቀሙበት ዘንድ ያበረከትኩ ዲታ ነኝ። የሰው ዲታ። "…የእኔ የሓሳብ መሸጫ ሰንዱቅ እንደ ዳንኤል ክብረት ሱቅ የተከረቸመ፣ የተዘጋ አይደለም። ጌትነት ዓልማው፣ መሳይ መኮንን እንኳ ሓሳብ እየሸጡ በር ይዘጋሉ። የደንበኛ አስተያየት አይቀበሉም። እንደ ነገረኛ የመንደር ሴት፣ ወይም እንደ አቅመቢስ ታማኝ የመንደር ውሻ በተዘጋ የሰፈራቸው ጊቢ ውስጥ ቆመው "ነጠላዬን አቀብዪኝ" ብለው ሲሳደቡ፣ ሲጮሁ ውለው የሰው ምላሽ እንደማይቀበሉ፣ እንደማያስወሩቱም አይደለሁም። "…ሓሳባቸውን የሚገልጹትን እጅግ አድርጌ አከብራለሁ። የሚያስቁኝ ተደብቀው ሲለይኩ የሚውሉት ሶዬዎች ናቸው። አትደበቁ፣ በአፋችሁ አትጸዳዱ እንጂ በተቃውሞም አስተያየት ለመስጠት አትቦዝኑ። "…የአያልነህ ላቀው "ምቀኛ ነገር ነህ" 12 ላይክ ካሰጠው፣ የሞጣ እና የብሪጅ ስቶን የሚኪ "ድራግ" ስድብማ ስንቶች ያስለይካቸው ይሆን…? • እየተመቀኛችሁ…!
Hammasini ko'rsatish...
👍 110😁 11 7🙏 7
መልካም… እሺ የዛሬውን የእኔ የአህያው የዘመዴን ርዕሰ አንቀጽ እንዴት አገኛችሁት…?
Hammasini ko'rsatish...
👍 13 1🤯 1🙏 1
"…ርዕሰ አንቀጽ" • አህያ…! "… ዛሬ የሆሣዕና በዓል ነው። ታስረው የነበሩና በጌታ መፈታት ስለሆነላቸው አህዮች በዓለሙ ሁሉ የሚሰበክበትም ዕለት ነው። በሰልፍና በጦርነት በክብርም ዘወትር በአደባባይ የሚታዩት ፈረሶች ያልተመረጡበት። ኢየሩሳሌም ለመግባት መንገድ የጀመረው ጌታ ለጉዞው አህዮችን የመረጠበት ዕለትም ነው ዛሬ። "… ሳያቀምሷት ለአህያ ማር አይጥማትም እያሉ ሰዎች የሚያሟት አህያ መሃሪውን ጌታ የተሸከመችበት፣ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከእመቤታችን ቀጥሎ ጌታን በጀርባዋ ለመሸከም ልዩ ዕድል እና ፀጋን ያገኘችበት፣ ሐዋርያት ልብሳቸውን እያነጠፉ ሕዝቡም ሁሉ ዘንባባ እየነሰነሱ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ እየዘመሩ በደስታ በዝማሬም ታጅባ የከበረችበት ዕለት ነው አህያ… "… አህዮቹ በሌባ ተሰርቀው በመንደር በድብቅ የታሰሩ ነበሩና ይህን የሚያውቅ ጌታ ከእሱ በተላኩ ሐዋርያት ከእስራታቸው ተፈተው ጌታን ለመሸከም የተመረጡበትም ዕለት ነው የዛሬው እለት። በድሆች መንደር በቤተ ፋጌ የሆነውም ይሄው ነው። በልደቱ እለት በዚያ በብርድ ወራት በቤተልሄም ከተማ በከብቶች በረት እርሱ አምላካቸው መሆኑን አውቀው በእስትንፋሳቸው ያሞቁትን አህዮች ውለታ ከፋዩ ጌታ ቀን ጠብቆ ዘመን ቆጥሮ፣ ሲመሽ ወደ ማታ ዛሬ ብድራታቸውን ከፈለ። በበረት ውስጥ የገበሩለትን እስትንፋስ በአደባባይ አክብሮ አስከብሮ መለሰላቸው። ለአህዮች።  "… ጌታ ሲወለድ ከሰዎቹ ቀድመው አህዮቹ ናቸው ያወቁት። ከሰብዓሰገል ወርቅ ዕጣን ከርቤ በፊት እስትንፋሳቸውንም የገበሩለትም አህዮቹ ናቸው። በስደት ዘመኑም አህያ አልተለየችውም። ከእስራኤል እስከ ኢትዮጵያና ግብጽ ድረስ አብራው ደክማለች አህያ። የሚገርመው በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ አህዮች ከጀርባቸው ላይ የመስቀል ምልክት መኖሩ ነው። መስቀል ደግሞ መከራ ነው። እንደ አህያ በዚህ ምድር መከራንና ፍዳን የሚቀበል ማን አለ? አህያ ከጀርባዋ የተሣለላት መስቀል የማያስችለው የለምና መከራን እንድትታገስ አድርጓት ቢሆንስ? ባለቤቷ እስላም ይሁን ክርስቲያን፣ ሂንዱ ይሁን ቡድሀ፣ አይሁድ ይሁን ኢ አማኒ ብቻ አህያው ከጀርባዋ መስቀል አላት። መስቀል። "… ቤተ ፋጌ አህዮቹ ተሰርቀው እና ታስረው የተገኙበት የድሆች መኖሪያ መንደር ናት። በድሆቹ መንደር በሌቦች ታስረው የነበሩ አህዮች የነበሩበትን የድሆች መንደር ነው ጌታ የወደደው። ሐዋርያቱን ሂዱና በሌባ ተሰርቀው ታስረው የሚገኙትን አህዮች ፈታችሁ አምጡልኝ ብሎ አዝዞ አህዮቹን ከእስራታቸው አስፈትቶ አምጥቶ ሳያስቡት ክቡር የሆነው ጌታ አክብሮ አስከበራቸው። "… ቤተ ፋጌ ለእየሩሳሌም በጣም ቅርብ ናት፡፡ የተመሳቀለ መንገድ ላይ የምትገኝም መንደርም ናት። እዚህ መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆሞ ነው መስቀል ላይ ወደሚውልባት ኢየሩሳሌም ይወስዱት ዘንድ አህዮቹን የመረጠው። ብዙ ያልታሰሩ በሜዳው የሞሉ አህዮች ቢኖሩም ጌታ የመረጠው ግን በሌባ ተሰርቀው በድብቅ ተሸሽገው የነበሩትን አህዮችን ነበር። "… ጌታ ሐዋርያቱን ሲልካቸው እንዲህም ብሏቸው ነበር። የታሰረ አህያ ፈትታችሁ ይዛችሁ ስትመጡ "ምን ታደርጋላችሁ? የሚላችሁ ሰው ቢኖር "ጌታቸው ይሻቸዋል" በሉአቸው ነበር ያላቸው። ደግሞ ሌባ የሰረቀው አህያ ሁለት ብርቱ መጥቶ ሲፈታቸው እንደ ባለቤት አይንጫጫም። ሌባ ነውና ጣጣ ቢያመጣበትስ? ዝም፣ ጭጭ ከማለት ውጪ ምን አፍ ይኖረዋል? ምንም። "…ሐዋርያቱም እንደታዘዙት አደረጉለት። አህያዋንና የአህያዋን ውርንጫም አመጡለት። ከአህያዋ ጀርባም ሐዋርያቱ ልብሳቸውን አነጠፉለት። አህያ ዓለሟን አየች። የዘመናት መጨቆን፣ የዘመናት መወገር ለአንድ ቀንም ቢሆን ቀረላት። የሐዋርያትን ልብስ ለበሰች። ታድላ። በሐዋርያት ልብስ ላይ ጌታ ተቀመጠ። ታድላ።  ሕዝብና ሐዋርያቱ ዘንባባና ልብሳቸውን አነጠፉ። ለጌታ ቢሆንም አህያዋም ጌታን ተሸክማለችና በሐዋርያቱ ልብስ ላይ እየተረማደች እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ተጓዘች። የዚያን ቀን የመታት፣ የሰደባት አልነበረም። ታድላ። "…በዚህ ዕለት ፈረስም፣ ኮርቻም አልተመረጡም። ፈረስም ጦረኛ ነው። ኮርቻም ይቆረቁራል። ሁለቱም አልተመረጡም። ለስላሳ ሕግ ሊሠራልን እንደወደደ በኮርቻ ፈንታ ሐዋርያት ልብሳቸውን አነጠፉለት። አንተ ለስላሳ የፍቅር አባት ነህ ሲሉ ነው እንዲህ ማድረጋቸው፡፡ ለስላሳ ሕግ የተባለው ደግሞ ሕገ ወንጌል ነው። ወንጌል ፍቅር ናት። የሚረግማችሁን መርቁ ትላለችና፡፡ ልብስ የሰውነት ነውር እንዲሸፍን አንተም ነውር ኃጢአታችንን፣ በደል አበሳችንን የምትሸፍንልን አምላክ ነህ ሲሉ ልብሳቸውን አነጠፉለት። እወነትም ነውራችንን የሚሸፍንልን እሱ ነው፡፡ "…እንደ ሊቃውንቱ አስተምህሮ ጌታችን በሁለቱ አህዮች በአንድጊዜ በጥበብ ነው የተቀመጠው። በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የሚቻል ጥበበኛ፣ ሁሉን የሚችል አባት በመሆኑ እንዲያ አደረገ። አንድም ወንጌልን ኦሪት እና ሀዲስን ሁለቱ ኪዳናት አስታርቆ እና አስማምቶ አንዱ አንዱን እየመገበ እንዲሄድ አድርጓልና በሁለቱም ተቀመጠ። "…አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።” ዘካ 9፥9 የሚለውም የነቢዩ ትንቢት ፍጻሜውን ማግኘት ስለነበረበት በአህያ ላይ መቀመጡ ግድ ነበር። "… በበረት እንደተወለደ በአህያም ላይ ተቀምጦ ትህትናን አስተማረን። ፈረስ የጦር ምልክት ነው። መጪው የሰላም ዘመን ነው ሲል በአህያ ተቀመጠ። ፈረስ ሯጭ ነው። ሽምጥ ይጋለበብበታል። የበረታ ብቻ ነው ፈረሰኛ ላይ የሚደርሰው። እሱ ግን ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና እና በየዋህነት ለሚኖሩ መእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል ረጋ ብላ በምትጓዘው አህያ ላይ ተቀመጦ መሄድን መረጠ። ምክንያቱም አህዮች ትሁታን ናቸው። ረጋ ብለው ነው የሚሄዱት። አይሮጡም። በቀላሉም ይወጣባቸዋል። በቀላሉም ይያዛሉ። እንደፈለግንም እናዝዛቸዋለን። እኛስ? በቀላሉ ለጌታ እንታዘዛለን? "…ትልቋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ናት። ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት። ሕገ ኦሪትም የተለመደች ሕግ ናትና፡፡ በትልቋ አህያ ተቀመጠ። ትልቋ አህያ የእስራኤል ምሳሌም ናት። ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ሕግ ለመፈጸም በሕግ ለመራመድ የለመዱ ናቸውና፡፡ ትልቋ አህያ የአዳም ምሳሌ ናት። አባታችን አዳም ሸክም የበዛበት ነበር ሸክሙን ሊያራግፍለት። ከዲያብሎስ ከሠራቂ ሌባው ነፃ ሊያወጣው እንደመጣ ሊያጠይቅ በትልቋ አህያ ተቀመጠ። "…ውርጭላዋ በሕገ ወንጌል ትመሰላለች። ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት እና የሠራት አዲሲቱ ሕግ ናትና፡፡ ውርንጫይቱ በአህዛብም ትመሰላለች። ምክንያቱም ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች እንዳይደለች ሁሉ እንዲሁም አህዛብም ሕግን የመቀበል የለመዱ አይደሉም፡፡ ለሕጉም አዲስ ናቸውና፡፡ ውርንጭላይቱ የእመቤታችንም ምሳሌ ናት። የዓለምን ሸክም ለማቅለል የተመረጠች እናት ናትና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ናት። የዓለሙን ፈጣሪ እግዚአብሔር ወልድን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከንም ነውር ነቀፋም የሌለባት እናት ናትና፡፡ ህዝቡም ልብሳቸው እያወለቁ በጎዳና አነጡፉለት ለምን? እንኳን አንተ የተቀመጥክባት አህያም ክብር ይገባታል ብለው አነጠፉለት። እስራኤላውያን ጌታ የተቀመጠባትን አህያ አከበሩ፡፡ ጌታ የተቀመጠባትን አህያ ያከበረ ሰው ጌታን
Hammasini ko'rsatish...
568👍 305🙏 65🏆 12👌 11🔥 6🕊 6😁 1😱 1
ያስገኘች እናቱን ሲሰድብ፣ ሲያንቋሽሽ ስታይ ትሸማቀቃለህ። "…ከአህያማ አንነስ። አህያ የሚል ቃል ለስድብ የሚጠቀሙ ይፈሩ። ይደበቁም። አህያ ያገኘችውን ክብር ያላገኘ የሜዳ አህያ ብቻ ነው። በሌባው በዲያብሎስ ታስረን በጫት፣ በሺሻ፣ በዝሙት፣ በዘረኝነት፣ በሴሰኝነት፣ በአምቡላ፣ በሐሺሽ፣ በሌብነት፣ በአጋንንት መንደር የተደበቅን እኛ መፈታት ይሁንልን። አሜን። "…እኔ አህያው ዘመዴ ሰናይ ቀን ተመኘሁላችሁ።
Hammasini ko'rsatish...
👍 1009 173🙏 125🕊 43👌 18🤔 13🏆 11😁 10🔥 8🤯 1
መልካም… ጠዋት ጠዋት እግዚአብሔር ይመስገን እያለ በማመስገን ቀኑን አሳምሮ የሚውለው የእኔ የቴሌግራም ቤተሰብ የሚፈለገውን ቁጥር አሟልቷል። እግዚአብሔር ይመስገን። እንግዲህ በመርሀ ግብራችን መሰረት ከምስጋናው በመቀጠል የምናልፈው እንደተለመደው ወደ ተወዳጇና ተናፋቂዋ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…በዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ስለ አህያ መጻፍ አማረኝ። አንዳንድ በንግግሬ፣ በጽሑፌ እና በአመለካከቴ የሚከፉብኝ የነፃ አውጪ ድርጅት አባላት ብዙ ጊዜ ጮክ ብለው የሚሰድቡኝ "አንት አህያ፣ ሀድጊ፣ ሃሬ" እያሉ ነውና ስለ አህያ ልጻፍላቸው ወደድኩ። "…አህያው ዘመዴ የሚጽፈውን ለማንበብ እናንት ሰው የሰው ዘሮች ዝግጁ ናችሁ? እስቲ አንድ መቶ ያህል ሰው ዝግጁ ነኝ ይበለኝማ። • ዝግጁ…?
Hammasini ko'rsatish...