cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Больше
Рекламные сообщения
411 214Подписчики
-37424 часа
-2 2967 дней
-7 07730 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

መልካም… ጠዋት ጠዋት እግዚአብሔር ይመስገን እያለ በማመስገን ቀኑን አሳምሮ የሚውለው የእኔ የቴሌግራም ቤተሰብ የሚፈለገውን ቁጥር አሟልቷል። እግዚአብሔር ይመስገን። እንግዲህ በመርሀ ግብራችን መሰረት ከምስጋናው በመቀጠል የምናልፈው እንደተለመደው ወደ ተወዳጇና ተናፋቂዋ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። "…በዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ስለ አህያ መጻፍ አማረኝ። አንዳንድ በንግግሬ፣ በጽሑፌ እና በአመለካከቴ የሚከፉብኝ የነፃ አውጪ ድርጅት አባላት ብዙ ጊዜ ጮክ ብለው የሚሰድቡኝ "አንት አህያ፣ ሀድጊ፣ ሃሬ" እያሉ ነውና ስለ አህያ ልጻፍላቸው ወደድኩ። "…አህያው ዘመዴ የሚጽፈውን ለማንበብ እናንት ሰው የሰው ዘሮች ዝግጁ ናችሁ? እስቲ አንድ መቶ ያህል ሰው ዝግጁ ነኝ ይበለኝማ። • ዝግጁ…?
Показать все...
“…እንዲህም አላቸው፦ በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርስዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ። ማንም አንዳች ቢላችሁ፦ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ፤ ወዲያውም ይሰዳቸዋል። ማቴ 21፥ 2-3 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
Показать все...
🙏 46 16👍 9
ደኅና እደሩልኝ…!
Показать все...
👍 1434 272🙏 151🏆 55😁 37🕊 12🤔 11👌 7🔥 5🤯 4
ጸሎት… "…እሺ… እንዴት አመሻችሁ…?  በወር ሁለት ቀን ከራየን ወንዝ ማዶ የምንኖር ስደተኞች ሰብሰብ ብለን የምንጸልይበት እለት ነው። እዚያ አምሽቼ አሁን ገና በኦቶቢሲ ማሞካቻ ተሳፍሬ ወደ ዋሻዬ እየተመለስኩ ነው። • ሰፈር መንደሩ እንዴት አመሸ? አማን ነው ቀዬው?
Показать все...
1186👍 437🙏 128😁 93🕊 34🏆 18🔥 14👌 12🤯 6😡 3
"…ጥሎብኝ ከድሮ ጀምሮ አንድ አጀንዳ ስጀምር ከቤተሰቦቼ አንስቶ ጫጫታ ይበዛብኛል። አላፊ አግዳሚው ሁሉ ይጮህብኛል። የእኔ ትልቁ ፀጋ ግን ጫጫታ አልሰማም። እኔ ጊዜ የሚወስድብኝ በአጀንዳው ማመኑ ላይ ነው። እስካምን ድረስ እቃትታለሁ፣ አምጣለሁ። እጨነቃለሁ። ከአመንኩበት በኋላ ግን ለምን መብረቅ አይጮህም ደንታዬም አይደለም። ማንንም አልሰማም። ኬሬዳሽ… "…ይሄ ከዘመነ ባህታዊ ገብረ መስቀል፣ ከዘመነ ተሃድሶ፣ ከእነ በጋሻው፣ ዘርፌ፣ ትዝታው ዘመን ጀምሮ ያየሁት ነው። በብፁዕ አቡነ ኤርምያስም፣ በቦለጢቀኛው ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራም፣ በሄኖክ ኃይሌም በወዘተረፈም የተረጋገጠ ነው። "…አሁንም ከዚያ የተለየ ነገር አይደለም። ትናንት የያዝኩትን አጀንዳ በስሱ ብልጭ ሳደርግ ጫጫታው አየሩን ሞላው። ወዳጄ የሆኑ ሰዎች ቤቴ ላይ መጥተው አስተያየት መስጠት ሼም ይዟቸው የለንደን ፋኖ ግሩፕ ጋር ሄደው ሲተነፍሱ አየኋቸው። ደግነቱ እዚያም ውስጥ እኔም አለሁ። "…አሁን ህመምተኛውን ትርፍ አንጀቱን ቆርጬ እንደምጥልለት ነግሬዋለሁ። ለቀዶ ጥገናም እንዲዘጋጅ አሳምኜዋለሁ። የትናንቱ የወዳጅ ዘመድ ጩኸት ዛሬ ላይ ቀንሷል። ኦፕራሲዮኑ የግድ ነው። ትርፍ አንጀት መጥፎ ነው። ካልተቆረጠ ሊገድልህ ሁላ ይችላል። "…ሪፖርቱን በነገው የመረጃ ቴሌቭዥን ዝግጅቴ ላይ ነው የምዘረግፈው። ሪፖርቱ የሚጠቅመው መሬት ላይ ላሉት ፋኖዎች ነው። የሚጎዳው ደግሞ በፋኖ ትግል ኢንቨስተር ለመሆን ለሚላላጡ ዘመናዊ የጎፈንድሚ ለማኞች ነው። ፋኖዎች ከታረቁ የእንጀራ ገመዱ የሚበጠስ የሚመስለውን ሌባን ሁላ ነው የማስተነፍሰው። ቀልድ የለም። "…አየሩ አሁን ተረጋግቷል። መንጋውም ሰከን ብሏል። ይሄ ችግር በድፍረት ከተፈታ ያለምንም ጥርጥር ፋኖ ባህርዳርም፣ ደሴም ጎንደርና አዲስ አበባም ሰተት ብሎ ይገባል። መጀመሪያ ትርፍ አንጀቶቹን እንቁረጥ።
Показать все...
👍 2085 242🙏 83🔥 43🏆 34😁 28👌 19🕊 15 9🤔 4🤯 1
"ርዕሰ አንቀጽ" "…የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችን ጥያቄአዊ ርዕሰ አንቀጽ ነው። ጠያቂ እኔ ዘመዴ ነኝ። ተጠያቂ ደግሞ እናንተ ዘመዶቼ። 😂 "…በመጀመሪያ ሰማይ ዝቅ፣ ምድር ከፍ ቢል የተጀመረው የዐማራ ፋኖ ትግል ከድል ደጃፍ ሳይደርስ አይቆምም። አይገታምም። መውደቅ መነሣት፣ መጓተት፣ መነታረክ ሊኖረው ይችላል። እሱ ደግሞ ተፈጥሮአዊ ነው። እንኳን በብዙ በደልና ግፍ ተገፍቶ የህልውና ትግል ውስጥ ተገድዶ የገባው ዐማራ ይቅርና ሀገር ለመገንጠል፣ ሕዝብ ለማፋጀት 7 ሆነው ጫካ የገቡት ወያኔዎችና የኤርትራ ሰዎች 17 እና 30 ዓመታትን ፈጅተው የልባቸውንም መሻት ፈጽመው የለም እንዴ? እናም ይሄም ንፁህና በሃቅ የተሞላው የዐማራ ፋኖም ትግል የፈጀውን ፈጅቶ፣ የወሰደውን ጊዜ ወስዶ ማሸነፉ እንደሁ አይቀርም። ይሄን እርግጠኛ ሆኜ ነው የምናገረው። "…የዛሬው ጥያቄ ለእናንተ ነው። የዐማራ ፋኖ ትግል ውሳጣዊ ሳይሆን ውጫዊ ነው። ይሄን ውጫዊ የሴራ ፖለቲካ ትግል በውስጥ ለመፍታት ለዓመታት ተሞክሯል። ነገር ግን አሁን ከአቅም በላይ ሆኗል። ይሄ ጉዳይ ወደ ሕዝብ መጥቶ ሕዝብ ካልተወያየበት ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ እልቂት በጀግኖች መካከል ይፈጠራል። እናስ ምን ታስባላችሁ? ይነገር አይነገር? "…ደፋር ሆነን ያበጠው ፈንድቶ ሰላም ማግኘት ይሻላል ወይስ እየተቋሰሉ የፋኖን እልቂት መጠበቅ? ከዚያ ኋላ ኘላይ ቀደም ብላችሁ ብትነግሩን ምን አለበት ብሎ ጓ ማለት ይሻላል ወይስ አሁን በጊዜ ሰምቶ በጊዜ መፍትሄ መፈለግ? ምርጫው የእናንተ ነው። "…በጥባጩን መክሮም፣ ዘክሮም፣ ገስጾም ልክ ማስገባት፣ መስመር ማስያዝ ነው የሚያስፈልገው ወይስ ከነ ፈንገሱ ሊጡን እንዲያቦካ መፍቀድ? የቱ ይሻላችኋል? ከሕዝብ በተዋጣ ዶላር የግል ፋኖ መግዛትስ ለዐማራ ትግል ምን ይረባዋል? •ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።
Показать все...
👍 1684 164🙏 65🤔 44🏆 26🔥 25🕊 16😁 12👌 12💔 12😱 9
መልካም… እንደተለመደው ጠዋታችንን እግዚአብሔር ይመስገን በሚል ነጎድጓዳማ፣ ብርሃናማ ድምጽ በሚያጥለቀለቁ 1ሺ ሰዎች ተሞልቷል። እግዚአብሔር ይመስገን። "…ከምስጋና ቀጥሎ በቀጥታ የምንሄደው እንደተለመደው ያው ወደ ቃሪያ በሚጥሚጣ ርዕሰ አንቀጻችን ነው። የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችንም ትናንት በጀመርነው "በፋኖዎች መሃል እጃቸውን ስለሚያስገቡ ሰዎች እና የእነዚያን ሰዎችም ሆነ ድርጅቶች እጅ እንዴት መቁረጥ" እንዳለብን ያነሣነውን ሓሳብ አንሥተን ስንወያይ እንውላለን። "…የእኔ ቤት ክፍት ነው። የሓሳብ መስጫ ሳጥን ሰንዱቁ አይዘጋም። እንደ ሌላው ሓሳብ ለጥፌ በር ዘግቼ አንጀት ጉበትህ እንዲቃጠል አላደርግም። በጨዋ ደንብ የተቃውሞ ሓሳብ መስጠትን አበረታታለሁ። እንድትተነፍስ አደርግሃለሁ። ከዚህ በላይ ዲሞክራትነት የለም። አስተያየት መስጫ ሳጥኑን የሚቆልፍ ደንቆሮ መሃይም ነው። አምባገነን። እኔ ግን ለመወቀስ፣ ለመሟገት ሁሌ ዝግጁ ነኝ። ጥይት እንጂ ሓሳብ አልፈራም። 😂 "…በፋኖዎች መሃል ስለነበረኝ የሽምግልና ቆይታ ግማሽ ሪፖርቴን ነገ ማታ በመረጃ ቲቪ መርሀ ግብሬ ላይ እዘረግፈዋለሁ። ማንም አያስቆመኝም። እኔ የምሰማው፣ የምከተለው፣ የማደምጠው፣ የምታዘዘውም በምድር ላይ ላሉት ፋኖዎች እና የፋኖ አለቆች፣ አዛዦች ብቻ ነው። አለቀ። "…ገና ምኑንም ሳልጀምረው ደግሞ መንበጫበጭ ጥሩ አይደለም። ግንቦቴዎች፣ በፋኖ ስም የተሰበሰበ ብር ቀፋዮች፣ ሌቦች፣ ፋኖ በተለመነ ዶላር ገዢዎች፣ መተዳደሪያችሁን የዐማራ ችግር ያደረጋችሁ ኮተታሞች፣ ጎጠኞች፣ መንደርተኞች፣ ፋኖ በመታረቁ ኤሌክትሪክ ካልጨበጥን፣ በረኪና ካልጠጣን ባዮች እናንተን በስም ዝርዝር ጠቅሼ አልፋታችሁም። እኔ ሓሳብ አነሣለሁ አንተ ደግሞ ሓሳቤን በጨዋ ደንብ ሞግት። ሓሳቤን በጨዋ ደንብ መሞገት ካልቻልክ ጮጋ በል። • ኣ… ዝግጁ ናችሁ…?
Показать все...
👍 1424 148🙏 66🏆 29👌 25🕊 15🔥 10🤔 10😁 1
“…ክፉ ለማድረግ የሚያስብ ተንኰለኛ ይባላል።” ምሳ 24፥8 "…ተግሣጽን የሚወድድ እውቀትን ይወድዳል፤ ዘለፋን የሚጠላ ግን ደንቆሮ ነው። ደኅና ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስን ያገኛል፤ ተንኰለኛውን ሰው ግን ይቀሥፈዋል። ምሳ 12፥ 1-2 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
Показать все...
🙏 1481👍 219 153🕊 23🔥 19😡 9
ማስታወቂያ…! "…ይህ አዲሱ የኢትዮ 360 የሳታላይት ቴሌቭዥን ጣቢያን የምታገኙበት ማስታወቂያ ነው። ተከታተሉት። "…ምንሊክ የሚለውን ብቻ ምኒልክ በሚለው አስተካክሉት እንጂ ሌላው ልክ ነው። የሐረርጌ ቆቱ ነገር ለዐማሮች አማርኛ ላስተምር ብዬ እኮ መከራዬን በላሁ። ዐማራ ተሁኖ፣ ለዐማራ እየታገሉ ቢረሳ ቢረሳ የታላቁን ንጉሠ ነገሥት የእምዬ ምኒልክን ስም አስተካክሎ ያለ መጻፍ ልክ አይሆንም። "…ይሄን ማስታወቂያ ደጋግሜ በፔጄ አስተዋውቀዋለሁ። ይሄ አይደለም ቁም ነገሩ። ቁምነገሩ ምድር ላይ ያሉትን ፋኖዎች ከፋፍሎ ማጋደሉን ማስቆሙ ላይ ነው። እገሌ ስር ካልገባችሁ በቴሌቭዥን ድራሽ አባታችሁን ነው የማጠፋው ማለትን ነው ማስቆም። "…የሸዋም፣ የጎንደር የጎጃሞችም፣ የወሎም ፋኖዎች የሁሉም ችግር እርሱ ነው። በጥቂት የሥልጣን ጥመኞች ክፉ ሴራ ምክንያት በቅርቡ የሺዎች ፋኖዎች ደም በከንቱ ሲፈስ፣ እርስ በእርስ ሲጨራረሱ ታያላችሁ። አቅም ያላችሁ ሸዋዎች መሃል በቶሎ ግቡ። ጎንደር ትናንት ታርቀው በመታረቃቸው የተናደዱ ዛሬ ሲያታኩሱአቸው ነው የዋሉት። "…ግንቦት 7፣ ግንባሩ፣ ሠራዊቱ፣ በግል ወንድሜ ጋዜጠኛ ሀብታሙ አያሌው ከፋኖዎች መሃል ውጣ በሉት። እኔ የምመክረው ይመራችኋል ነገር ግን ደም እንባ ነው የምታለቅሱት። ተናግሬአለሁ። ያገባኛል የምትሉ በቶሎ ጣልቃ ግቡ። "…ባይገርምላችሁ እህተ ማርያም (ስንዱም) ሆነች ራዕይ 20ዎች የራሳቸው ጦር አላቸው ብላችሁስ። ስንዱ እንግሊዛዊ ናት አንዱን ትነግሳለህ ብላ ቀብታ አስቀምጣዋለች። 😂። ደብረ ኤልያስ መሽገው የነበሩት ደግሞ አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ እገሌ ነው መንገሥ ያለበት ብለዋል ብለው ፋኖ ሁሉ ለዚያ ሰው ይንበርከክ ይታዘዝ ብለው ጉድ አፍልተዋል። ይሄ ሁላ ቅዠት ግን ያልፋል። ዐማራም አሳምሮ ድብን አድርጎ ያሸንፋል። • እየኮመታችሁ…!
Показать все...
👍 30 18 3🙏 1
"…ገና በሽታውማ አትስከሩ…! "…ሲጀመር ገና ምኑንም አልተናገርኩም። አላወራሁም። አላሳየሁም። ነገር ግን ወዴት እንደምሄድ የገባው ፀረ ዐማራ፣ ፌክ ኢትዮጵያኒስት ምድረ ግንቦቴ ሁላ መስቀል እንዳየ ፀበም እንደነካው አጋንንት እምቧእሪቁቀምበጭ ማለት ጀምሯል። ምኑ ተያዘና ነው የምትለፈልፈው። "…በእርቁ ሰዓት ዋነኛው የፋኖዎች ችግር የነበረው ሁሉ በድምጽ የተቀዳ፣ ሽማግሌዎቹ ሁሉ ያዘኑበት፣ በመሬት ላይ ያለው ፋኖ የሚያደርገው የሚሠራው የጠፋበት፣ በእስክንድር በኩል ተጠግተው የመጡት ፌክ ኢትዮጵያኒስቶች ገና ለገና ብልፅግና መውደቁ አይቀርምና እኛ ከአሁኑ የራሳችንን ፋኖ ገዝተን አዘጋጅተን ቦታ ሥልጣን መያዝ አለብን በማለት በማወክ ፋኖን በጋዜጠኝነት ስም አሸማቀው መድረሻ ለማሳጣት የተኬደበትን ርቀት ይፋ አወጣዋለሁ። "…ለሽምግልና የተጠራን ሽማግሌዎች በምንችለው ሁሉ ፋኖዎችን ተማጽነን በስግብግቦች ሴራ ምክንያት ደም እንዳይፋሰሱ አድርገናል። "…እኔ እዳ የለብኝም። በኋላ ከተጠያቂነት ለመዳን አሁኑኑ የችግሩን ሰንኮፍ ውልቅ አድርጎ ማውጣት ያስፈልጋል። ሽመልስ ለገሰን እጅግ አድርጌ አመሰግነዋለሁ። ተናግሮ እንድናገር ስላደረገኝ አመሰግነዋለሁ። "…በተረፈ ቀንተህ ነው፣ ምናምን ለእኔ አይሠራም። በምኑ ነው የምቀናው? የዐማራ ፋኖን መከራና ሙጀሌ ግን በመረጃ እና በማስረጃ ሰንኮፉን ነቅለን እናወጣዋለሁ። "…ሺ ሆነህ ና፣ ተደራጅተህ ና፣ ተሰባስበህ ና እኔ ዘመዴ የሥላሴ ባርያ የድንግል አሽከር ዱቄት ነው የማደርግህ። ምድረ መኒ ላውንደሪ፣ ገንዘብ አጠባ ላይ የተሰማራህ የደም ነጋዴ የዶላር ቀበኛ ሁላ አሁን ነው የሚለይልን። "…እኔ አንድም አጋዥ ሰው አልፈልግም። ግንቦቴዎች ልትሞግቱኝ ትችላላችሁ የሰው አይን የሚያቆሽሽ የተለመደ ነውረኛ ስድባችሁ ግን ያስቀስፋችኋል። • ሰምተሃል…!
Показать все...
1202👍 641🙏 63😁 34👌 30🤔 26🏆 21🔥 14 12🕊 12🤯 9