ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
前往频道在 Telegram
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
显示更多📈 Telegram 频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 的分析概览
频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 55 344 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 932,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 587 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 55 344 名订阅者。
根据 27 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 707,过去 24 小时变化为 33,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.92%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.27% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 9 919 次浏览,首日通常累积 4 576 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 159。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
55 344
订阅者
+3324 小时
+957 天
+70730 天
帖子存档
55 344
ትንሿ ቤተክርስቲያን በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ
ባለትዳሮች በቤታቸው ውስጥ ማድረግ ያለባቸው ቤተ ክርስቲያን መጥተው ያዩትን ነው፡፡ ለምሳሌ፦
👉 ቤተክርስቲያን ውስጥ የጠዋትና የሰርክ ጸሎት እንዳለ ኹሉ እነዚህ ባለ ትዳሮችም የጠዋትና የሰርክ ጸሎት በቤታቸው ውስጥ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ያለው የኅብረትና የአንድነት ጸሎት እንደ ኾነ ኹሉ፥ ባልና ሚስት ልጆችም ሳይለያዩ አብረው መጸለይ አለባቸው፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ከቅዳሴ በኋላ ትምህርተ ወንጌል እንዳለ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም እራት ከበሉ በኋላ ቃለ እግዚአብሔር ሊማማሩ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ራሳቸውን ገዝተው የሚኖሩ ትጉሃን መነኰሳት እንዳሉ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ይህን ትግሃትና ምስጋና ወደ ቤታቸው ይዘዉት ሊኼዱ ይገባቸዋል፡፡
👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማታ ላይ ኅብስቱን አበርክቶ ሕዝቡን ከመገባቸው በኋላ ወዲያው ወደ መኝታ እንዲኼዱ እንዳላደረገ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ወደ መኝታቸው ከመኼዳቸው በፊት የቀን ውሎአቸውን መገምገም አለባቸው፡፡
👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሊት ሌሊት ሲጸልይ ያድር እንደ ነበረ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ሌሊት ላይ ነቅተው መጸለይ ይገባቸዋል፡፡ ሕፃናት ካሉም አብረዋቸው እንዲነሡ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ጾም እንደሚታወጅ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም በቤተ ክርስቲያን ከሚታወጀው ጾም በተጨማሪ ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር ተመካክረው በፈቃዳቸው ሊጾሙ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዳለው፥ ባልና ሚስትም የቤታቸውን ግድግዳ፣ መስኮትና በር በመስቀል ሊያስጌጡት ይገባቸዋል፡፡ ማማተብ በማይችሉ ልጆቻቸው ግንባርም አድገው ራሳቸው ማማተብ እስኪችሉ ድረስ እነርሱ ያማትቡላቸው፡፡ ቅዱሳት ሥዕላትም በቤታቸው ውስጥ ሊኖሩ ይገባል፡፡
ቤታቸው ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምትኾነው በዚህ መንገድ ነው፡፡
(ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 60 - 61)
55 344
ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር እንስጠው
ወርቅን የሚያነጥር ሰው አንዲትን የወርቅ ቅንጣት ወደ እሳት ውስጥ ጨምሮ እጅግ ንጹህ እስክትኾን ድረስ ይጠብቃታል፡፡ እግዚአብሔርም ልክ እንደዚሁ ሰዎች እስኪነጹ፣ እስኪለወጡና ባገኛቸው ነገር ጥቅም እስኪያገኙ ድረስ ፈተና ውስጥ እንዲቆዩ ይፈቅዳል፡፡ ይህ ደግሞ ከጥቅምም እጅግ ከፍ ያለ ጥቅም ነው፡፡
ስለዚህ ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም ተስፋ ሊቈርጥ አይገባውም፡፡ ያ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያኽል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኵሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንሔድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቈርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡
ይህን በማስመልከትም ጠቢቡ ሰው እንደዚህ ሲል መክሮናል፡- “ልጄ ሆይ! ለእግዚአብሔር ትገዛ ዘንድ ብትሔድ ሰውነትህን ለመከራ አዘጋጅ፤ ልብህን አቅና፤ ኹልጊዜ ታገሥ፤ አታወላውልም፤ በመከራ ብትጨነቅም አትጠራጠር” /ሲራ.2፥1-2/፡፡ “ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ስጠው፡፡” ለምን? እግዚአብሔር ከዚያ መከራ መቼ እኛን ማውጣት እንዳለበት ያውቃልና፡፡ ስለዚህ ኹሉንም ለእርሱ ልንሰጥ፣ ዘወትር እርሱን ልናመሰግን፣ ኹሉንም ነገር ጥቅምም ይኹን ቅጣት በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፤ ይህም ቢኾን ለእኛ ረብሕ የሚኾን ነውና፡፡
አንድ ሐኪም፥ ሐኪም የሚባለው ታካሚውን ገላዉን ሲያጥበውና ሲመግበው እንዲሁም ደስ ወደሚያሰኝ ስፍራ ሲወስደው ብቻ አይደለም፤ በእርሱ (በታማሚው) ሰውነት ላይ የቀዶ ጥገና ምላጭና ቢላ ሲያሳርፍም ጭምር ሐኪም ነው፡፡ አባትም አባት የሚባለው ልጁን ሲንከባከብ ብቻ አይደለም፤ የገዛ ልጁን ከቤት ሲያስወጣው፣ ሲገሥጸው፣ ሲገርፈውም ያው አባት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር ከሐኪሞችም በላይ ሰውን ወዳጅ እንደ ኾነ በማወቅ፥ ምን ዓይነት የሕክምና ዓይነት እንደሚሰጠን በጥልቀት አንጠይቅ፤ ወይም ደግሞ ለደረሰብን መከራ እርሱን ተጠያቂ አናድርግ፡፡ ከዚህ ይልቅ እርሱ የወደደውን ነገር ቅጣትም ይኹን ቅጣት የሌለው ነገር ብቻ ምንም ይኹን ምን በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፡፡
በየትኛውም መንገድም ቢኾን የእርሱ ፈቃድ እኛ እንድንድንና ከእርሱ ጋር አንድ እንድንኾን ነውና፡፡ የትኛው መንገድ ለእኛ እንደሚጠቅምም እርሱ ያውቋል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የትኛው መንገድ ወደ እርሱ እንደሚመልሰው ያውቃል፡፡ ኹላችንም እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ልንድን እንደምንችል ያውቃል፡፡ በመኾኑም የሚመራን በዚህ እኛ በምንድንበት መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ወደየትኛውም መንገድ ቢወስደንም ልክ እንደ መጻጉዑ እርሱ እንደሚያዘ’ን ተከትለን መሔድ እንጂ ትልቁ ጉዳያችን በለስላሳና በቀላል አልያም ደግሞ በከባድና በሸካራ ጎዳና እንድንሔድ የሚያዘ’ንን ትእዛዝ መኾን የለበትም (ልንሔድበት የሚገባ’ው መንገድ እርሱ ስለሚያውቀው እንዲሁ መታዘዝ እንጂ የመንገዱን ከባድነት ወይም ቀላልነት የእኛ አጀንዳ ሊኾን አይገባውም፡፡)
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልእክታት - በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
55 344
"ከራሳቸው ውጪ ደስታን የሚፈልጉ እንደምን ምስኪኖች ናቸው? ደስታን በባእድ ምድር በጉዞ የሚፈልጉ አሉ። በሀብትና በዝና መካከል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፤ በታላቅ ይዞታና በንብረት መካከል የሚፈልጉ አሉ፤ መራራ ፍፃሜ ባላቸው በውበትና በተቃራኒ ፆታ መካከል የሚፈልጉ አሉ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደስታን ከራሳችን ውጪ ለመገንባት መሞከር በተደጋጋሚ በመሬት ርእደት በሚናወጥ ሥፍራ ላይ እንደ መገንባት ነው።
ደስታ የሚገኘው በእኛው ውስጥ እንጂ ከእኛ ውጪ አይደለም። ምስጉን ማለት ይህን ሁኔታ የተገነዘበ ሰው ነው። ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው፤ እንዲህ አይነቱን ልብ እግዚአብሔር ማደሪያ ያደርገዋልና። ስለዚህ ንፁህ ልብ ያላቸው ወገኖች ክርስቶስ እንዲህ ይላቸዋል፦ በእነሱ እኖራለሁ፣ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸው እሆናለሁ እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 2ኛ ቆሮ. 6፥16 እንዲህ አይነት ወገኖች ምን ይጎድልባቸዋል? ምንም። "
(አባ ሳራባሙን - የበረሃ ፈርጦች መጽሐፍ ገጽ 14 በመምህር ምትኩ አበራ)
55 344
ሦስቱ ጠቢባን
ልጄ ሆይ እነርሱ ይጠብቁህ ዘንድ፤ ሕግጋትን ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ በኃያላንና በጠቢባን ዘንድ ክብር ይሆንልህ ዘንድ በወጣትነት ዘመንህ ታገሥ፡፡ ልጄ ሆይ ሞገስን ይሆንህ ዘንድ የሰማኸውን ነገር ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ መንፈሳዊ አባትህን ጠይቀው፡፡ እርሱም ጽድቅንና እውነትን ይነግርሃል።
ልጄ ሆይ በተሾምክበት ወራት ለድኾች ፍርድ አታጉድል፤ ሰውን ባለጸጋ ነው ብለህ አትፍራው ለዘመዶችህም ፍርድ አታድላ፡፡ ለባለጸጎችም ቢሆን የሰው ሀብቱ ንብረቱ መብዛቱ እያስፈራህ፡፡ እሰከ ዕለተ ሞትህ ድረስ እውነትን ተናገር ጠቢብ ሲራክ እንዲህ አለ፦ ለሰነፍ ራስህን ዝቅ አታድርግ፡፡ እንደ ሀብቱ ብዛት ኃጢአቱም ብዙ ነው፤ በንግግሩ ብዛት ሐሰቱ ይበዛልና፡፡
ከእግዚአብሔር እንዳትለይ ድኻውን አትግፋው፡፡ ሦስት ጠበብቶች አሉ፥ አንዱ እንደተቻለው የሚተው የሚታገሥ ነገር ኃላፊ ልበ ሰፊ ነው፡፡ ሁለተኛው እያወቀ ዝም የሚል ሦስተኛው ጠቢብ ሲሆን የዋህ ነው፡፡ ልጄ ሆይ ቸኩለህ አትናገር። ነቢይ "ቀባጣሪ አንደበት ሞትን ትጠራለች" ብሏልና፡፡ ወንድሜ ሆይ በአንደበትህ በነገር እንዳትሰናከል ተጠንቀቅ፡፡ በአንደበትህ ከምትወድቅ ወደ ገደል ብትወድቅ ይሻልሃልና፡፡ ቀባጣሪ አንደበት ብዙዎችን አወከቻቸው ከትዳራቸውም ለየቻቸው፡፡ ብዙዎችም ከቤታቸው ወጡ፤ ከሀገራቸው ተሰደዱ ከክብራቸው አነሱ፡፡
(አባ ገብረ ኪዳን - መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 86-84)
55 344
በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
55 344
“የምትበላውን ምግብ እንደምትመርጥ ሁሉ፣ የምትናገረውንም ቃል ምረጥ፤ መጥፎ ምግብ ሥጋን እንደሚመርዝ፣ መጥፎ ቃልም ነፍስን ይመርዛል።’
አባ ጴሜን
55 344
ሰላም
አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል።
ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ።
ለበለጠ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይቻላል
55 344
ሰላም እንደምን ዋላችሁ/አደራችሁ?
አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል።
ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ።
55 344
"ለበጎ ነው"
"አንድ ንጉስ ከአጃቢው ጋር በመሆን ለአደን ይወጣል። ለአደን ሲወጡ ንጉሱ ወጥመድ እያጠመደ እያለ ወጥመዱ አምልጦት እጁን ቆረጠው። በዚህም አጃቢው በማዘን "አይዞህ ንጉስ ሆይ ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!" ይለዋል። በዚህም ንጉሱ በንዴት እየጦፈ "የኔ እጅ መቆረጥ ነው ለበጎ?" ይለውና እስር ቤት አሳሰረው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ ንጉሱ ብቻውን ሀገሩን ሲዞር ሰው አርደው ለጣዖት መሰዋት የሚያደርጉ ጨካኝ ሰዎች ያዙትና አርደው መሰዋት ሊያደርጉት ሲሉ ቆራጣ እጁን አዩት። በእነሱ ህግ መሰዋት የሚያደርጉት ሰዉ ሙሉ ጤነኛ መሆን ስላለበት ለቀቁት።
ንጉሱ አጃቢው 'ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!' ያለው ትዝ አለውና እስር ቤት ሄዶ ስላሰርኩህ ይቅርታ አርግልኝ! ብሎ ታሪኩን አጫወተው። አጃቢውም "ማሰርህ ለበጎ ነበር! እኔም መታሰሬ ጠቅሞኛል።" አለው። ንጉሱ "እንዴት?" አለው አጃቢውም "ባልታሰር ኖሮ ከአንተ ጋር እሄድና አንተ ቆራጣ መሆንህን ሲያውቁ ይለቁህና አኔን ይገሉኝ ነበር" አለው።
ስለዚህ ሁላችንም ስለተደረገልንም ሆነ ስላልተደረገልን እንዲሁም ስለሆነውም ሆነ ስላልሆነው ነገር ሁሉ "ለበጎ ነው" ማለት ይልመድብን፡፡
55 344
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።"
(ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)
55 344
እኔን ያስደነቀኝ...
እመቤቴ ሆይ! እኔን ያስደነቀኝ ከሙታን መካከል ተለይተሽ መነሣትሽ አይደለም፤ ትንሣኤና ሕይወትን በመውለድሽ ነው እንጅ። ሞት በሠለጠነበት ማኅፀን የሕይወት መገኘት እንደምን ይደንቃል?!
ድንግል ሆይ! ወደ ሰማይ ከመውጣትሽ ይልቅ የሰማይ ሁለተኛ ተብለሽ መጠራትሽ ይደንቀኛል። ማሕደረ መለኮት በመሆኑ ምድርን ሰማይ ሰማይን ምድር ያደረገ ሰውነትሽ በምድር ተወስኖ ሊኖር እንደምን ይቻላል?!
እመብርሃን ሆይ! ልጅሽ የጽድቅ ብርሃን ነው አንች ደግሞ የብርሃኑ መገኛ የፀሐይ ክበብ ነሽ፤ የፀሐይ ክበብ ለጊዜው በተራሮች ራስ ቢጋረድ መልሶ ላይወጣ ኖሯልን? ያንችም ትንሣኤ እንደዚያ ነው።
ለጊዜው ሰውነትሽ በመቃብር ውስጥ አደረ ነገር ግን በምሽት የጠለቀችው ፀሐይ በማለዳ እንድትወጣ ያንችም ሰውነት ከመቃብር ወጣ።
እመ አምላክ ሆይ! አምላክን የዳሰሱ እጆች፣ መለኮት የተቀመጠባቸው ጉልበቶችሽ፣ ጌታዬ የጠባቸው ጡቶችሽ በመግነዝ እንደታሰሩ ሊቀር ይገባልን? ገፀ መለኮቱን ያዩ ዐይኖች በሞት እንደተከደኑ ትንሣኤ ዘጉባኤን ይጠብቃሉን? ይህስ አይደለም እመቤቴ በሞት ሥልጣን ሥር አይደለችም።
የጌታዬ እናት ሆይ! ጥንቱንስ ቢሆን የታቦት ማደሪያው በመቃብር ውስጥ ነውን? ቃሉ የተጻፈባትን የሙሴ ጽላት በመቃብር ውስጥ አለች ብሎ የሚያምን የተረገመ ነው። የአሮን በትር የዘለዓለም የክህነቱ ምልክት ሆና በመቅደስ ልትኖር ከተገባት የሐዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህናት የ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህናት ንጉሠ ነገሥት ተብሎ የተሾመባት አማናዊቷ በትረ አሮን በሰማዩ መቅደስ በሕይወት ልትኖር አይገባምን?
በነገራችን ላይ ይህንን ታሪክ አምኖ ለመቀበል ከሐዋርያት በጥምቀት መወለድና የሰማዩ የቅዱሳን ኅብረት አባል መሆን ግድ ይላል። ቤተ ክርስቲያናችን የሰማዩ የቅዱሳን ጉባኤ አባል ስለሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተነሥታለች፣ ወደ ሰማይ ዐርጋለች ብላ ታምናለች። በሰማይ ያሉ ቅዱሳን እያሸበሸቡ እየዘመሩ ተቀብለዋታል። ይህ በዓል በታቦተ ጽዮን ፊት ሲዘምር ያየነው ዳዊት የዘመረበት ዕለት ነው። ያኔ የበፍታ ኤፉድ ለብሶ የዘመረውን መዝሙር 2 ሳሙ. 6፥14ዛሬ የጽድቅ ካባ ደርቦ ዘመረው። ያኔ የድንግል ማርያም ምሳሌ ለነበረችው ታቦት የዘመረውን መዝሙር ዛሬ በአማናዊቷ ታቦት ፊት አቀረበው።
እኔን የሚያስደንቀኝ የእመቤታችን ምሳሌ በነበረችው መቅደስ ሲያገለግሉ የነበሩ ካህናት ሁሉ ዛሬ በአማናዊቷ መቅደስ ፊት ለፊት ቆመው ለማገልገል መብቃታቸው ነው። ሊያዩአት ይመኙ ለነበሩ ሁሉ ዛሬ ተነሥታ በግልጥ አዩአት። ለ እመቤታችን ከተደረገው ይልቅ ለቅዱሳን የተደረገላቸው ብዙ ነው።
የእናቱን ትንሣኤ እንደ ልጇ ትንሣኤ አድርጋችሁ የምታከብሩ የጥምቀት ልጆች ሁላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ወላዲተ አምላክ ማርያም ዐርጋለች።
ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ!
55 344
#ድንግል_ሆይ የአንቺ ሥጋ ይገርመኛል ከሔዋን ተገኝቶ ከመላእክት ይልቅ ንፁህ ሆኗአልና፣ አፈር ነህ ከተባለው ከአዳም ተወልደሽ በሰማይ በአባቱ ቀኝ በተቀመጠው ንጉሥ በክርስቶስ ክቡር ሰውነት ላይ በተለየ ክብር ሆኖ በሰማያት ታይቷልና። ባለ ራዕይው ዮሐንስ ከአንቺ በነሳው ሥጋ ከተወጋው ቁስለቱ ጋር ወደ ሰማይ እንደወጣ ቢያየው እንዲሁ ይመጣል ብሎ በመጽሐፍ ነገረን። የወጉትም ሁሉ ያዩታል ተብሎ ተጻፈ። የታናሿ የአንቺ ገላ ሰማይ ለሚጠበው አምላክ ልብስ ሆነ። መሰወሪያው ከዚህ ነው የማይባለው ልዑል ሥጋሽን ለብሷልና ሥጋ ሆነ ተባለለት። ከባሕሪው እሳት የሆነውን እርሱን ሁሉ ዳሰሰው ሁሉ አቀፈው። መለኮታዊ ክብሩን በአንቺ ሥጋ ውስጥ ቢሰውረው የወደቀው ሰውም አምላክ ሆነ ተባለ። ይደንቃል።
#ደንግል_ሆይ መላእክት በቤተልሔም በአንቺ ላይ የሆነውን ቢመለከቱ ስብሐት ለእግዚአብሔር አሉ። ሌላ ምን ይባላል? የማይወርደው ከከፍታው ወርዶ ሲታይ በአድናቆት ስብሐት ነው እንጂ። ሰማይ ከክብሩ የተነሳ የምትጠበውን በአንቺ ክንድ ላይ ሲያዩት ምን ይበሉ? ኦ ማርያም በአንቺ የሆነውን ለመጻፍ የሚያስብ ቃለ ጸሐፊ ከፍቅሩ የተነሣ ብዕሩ በእንባ ስለሚርስ ስለ አንቺ እንዲህ ነው ለማለት ቃልና እቅም በማጣት ሠአሊ ለነ ብሎ ጽሑፉን ይዘጋዋል። አይችልምና።
#ልዑሉን_የወለድሽ_ልዕልት_ሆይ የአንቺ ሥጋ ከአቤል ይልቅ ተወደደ፤ ከደገኛው አብርሐም ይልቅ ከፍ አለ፤ ከንጉሡ ከዳዊት ይልቅ ሥጋሽ የተለየና የተመረጠ ሆነ ...ዳዊትም፦ ንጉሥ ደም ግባትሽን ወደደ ብሎ ጻፈልሽ። ከእስራኤላውያን አባት ከያዕቆብ ድንኳን ይልቅ የአንቺ ሥጋ ተመረጠ። ሎጥ፦ መላእክትን ወደ ቤቴ ግቡ ቢላቸው በአደባባይህ እንሆናለን እንጂ አንገባም አሉት። ድንግል ሆይ የአንቺ ሥጋ ግን መላእክትን ለፈጠረ ጌታ ማደሪያ ሆነ። ለዚህ ቃል የለም ዝምታና አንክሮ እንጂ።
#ድንግል_ሆይ የአንቺን ሥጋ በመቃብር የለም በአብ ቀኝ እንጂ። አንዳንዶች #ተነሥታለች ለማለት ከበዳቸው። ለመሆኑ ልጅሽ አልዓዛርን ከመቃብር ያስነሣ መሆኑን አላነበቡ ይሆንን? የኢያዒሮስ ልጅን ታሪክ አልተመለከቱ ይሆን አንቺ ግን ወደ ሰማያት ከተነጠቁት ከሄኖክና ከኤልያስ ትበልጫለሽ። #ትንሣኤሽን_የሚያምን_ሁሉ_አሜን_ይበል።
#ምልጃሽ #ኢትዮጵያን #ይታደግ። ለዓለም ምሕረት ይሁን ።
(Memher abunu mamo መ/ር አቡኑ ማሞ )
