ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
前往频道在 Telegram
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
显示更多📈 Telegram 频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 的分析概览
频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 55 943 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 916,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 588 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 55 943 名订阅者。
根据 19 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 686,过去 24 小时变化为 43,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.17%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.98% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 9 602 次浏览,首日通常累积 4 466 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 114。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
凭借高频更新(最新数据采集于 20 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
55 943
订阅者
+4324 小时
+2507 天
+68630 天
帖子存档
55 943
ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ስታነቡ ዝም ብላችሁ ቃላትን ለመቁጠር ብቻ አይሁን። ነገር ግን በቃሉ ውስጥ ያለውን መንፈሳዊ ጣዕም ለማግኘት ጸልዩ። የምታነቡትን በተግባር ለመተርጎም ትጉ። 'ቃሉን የሚሰሙ ብቻ ሳይሆኑ የሚያደርጉት ይጸድቃሉ' ተብሏልና። አንድ ምዕራፍ እንኳ ብታነቡ ያቺ ለአንድ ቀን ስንቅ ትሆናችኋለች። ንስሐ የገባ ሰው ልቡ በቃለ እግዚአብሔር ካልታጠበ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ጭቃ መመለሱ አይቀርም። ቃሉ ግን ልባችሁን ይጠብቃል፤ አእምሮአችሁንም ያበራል።
ሰዎች ሆይ! መጻሕፍትን አትናቁ። እነርሱ ከሰማይ ወደ እኛ የተላኩ ደብዳቤዎች ናቸው። የሰማዩ ንጉሥ የላከልህን ደብዳቤ ችላ ብለህ እንዴት ሰላምን ታገኛለህ? በመጻሕፍት ውስጥ የታመሙት ፈውስን፣ ያዘኑት መጽናናትን፣ የወደቁት መነሳትን፣ ንስሐ የገቡት ደግሞ የተስፋን ብርሃን ያገኛሉ። በቃለ እግዚአብሔር የምትታጠብ ነፍስ ዘወትር ለምለም ትሆናለች።
ስለዚህ በቤታችሁ መጻሕፍትን ለማንበብ ጊዜ መድቡ። ልጆቻችሁንም በቃለ እግዚአብሔር ኮትኩቱ። ዓለማዊ እውቀት ለሥጋዊ ሕይወት ይጠቅም ይሆናል፤ መንፈሳዊ እውቀት ግን ለዘላለም ሕይወት ያበቃል። ንስሐችሁ ፍጹም ይሆን ዘንድ፣ ሕሊናችሁም ከክፉ ሐሳብ ይነጻ ዘንድ ዘወትር በመለኮታዊ መጻሕፍት ንባብ ተጉ። እግዚአብሔር ቃሉን በልባችን ይጻፍልን።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)
55 943
“በአውሎ ነፋስ መካከል ብትሆን እንኳ አትፍራ፤ መርከቧን የሚመራት ክርስቶስ እስካለ ድረስ ማዕበሉ አያሰምጥህም፤ እግዚአብሔር ፈተናውን ባያርቀው እንኳ ፈተናውን የምትችልበትን ኃይል ይሰጥሃል።’’
ሊቁ አውግስጢኖስ
55 943
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ
በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል።
በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ።
አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል።
ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን።
#በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ
ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ
1000513559821
#ለበለጠ_መረጃ፦
➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104
ሼር በማድርግ ይተባበሩ
55 943
ንስሐና ምጽዋት የነፍስ ሁለት ዓይኖች ናቸው። አንዱ ቢጠፋ ሌላኛው ብቻውን ሙሉ እይታ አይሰጠውም።
ኃጢአትህ እንዲፋቅልህ ትፈልጋለህን? እንኪያስ የምሕረት በርን በምጽዋት አንኳኳ። 'የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና' ተብሏል። አንተ ለባልንጀራህ ካልራራህ እግዚአብሔር እንዲራራልህ እንዴት ትጠይቃለህ? ምጽዋት ሰጪውን ከኃጢአት እስራት ትፈታዋለች፤ ተቀባዩንም ከችግር ታሳርፈዋለች።
ወንድሞቼ ሆይ! አትሳሳቱ፤ ገንዘባችሁ እዚህ ምድር ላይ ይቀራል። ይዛችሁት የምትሄዱት ምጽዋታችሁን ብቻ ነው። በሕይወት እያላችሁ ለነፍሳችሁ ስንቅ አዘጋጁ። ድሆች የእግዚአብሔር መሠዊያዎች ናቸው። በቤተክርስቲያን ያለውን መሠዊያ እንደምታከብሩ ሁሉ፣ እነዚህን ሕያው መሠዊያዎች (ድሆችን) አክብሩ። በድሃው እጅ ላይ የምታስቀምጠው ስጦታ በቀጥታ ወደ እግዚአብሔር እጅ ይደርሳል። ስለዚህ ንስሐችሁ ፍሬ እንዲያፈራ፣ ጸሎታችሁም እንዲሰማ ዘወትር በምጽዋት ትጉ።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)
55 943
+2
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ
በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል።
በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ።
አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል።
ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን።
#በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ
ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ
1000513559821
#ለበለጠ_መረጃ፦
➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104
ሼር በማድርግ ይተባበሩ
55 943
ሰይጣን ኃጢአት እንድትሠራ ሲገፋፋህ 'ድፍረትን' ይሰጥሃል። 'እግዚአብሔር መሐሪ ነው፣ አንድ ጊዜ ብትሠራው ምን ይልሃል? ቆይተህ ንስሐ ትገባለህ' እያለ በኃጢአት ላይ እንድትደፋፈር ያደርግሃል። አንተ ተሸንፈህ ኃጢአቱን ከፈጸምክ በኋላ ግን ሰይጣን ስልቱን ይቀይራል። ያን ጊዜ ደግሞ 'እፍረትንና ተስፋ መቁረጥን' ያመጣብሃል። 'እንዲህ ያለ ኃጢአት ሠርተህ እንዴት እግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ? አንተ ረክሰሃል፣ ንስሐህ ተቀባይነት የለውም፣ ሞትህም ለገሃነም ነው' እያለ በልብህ ይጮኻል።
አንተ ግን የሰይጣንን ተንኮል አሸንፈው። ኃጢአት ልትሠራ ስትል 'እፈር'፤ ንስሐ ልትገባ ስትል ግን 'ደፋር ሁን'። ሰይጣን ግን ኃጢአት ስትሠራ እንድትደፍር፣ ንስሐ ስትገባ ደግሞ እንድታፍር ያደርግሃል። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ኃጢአት ቍስል ነው፣ ንስሐ ግን መድኃኒት ነው። ቍስል ያለው ሰው ቍስሉን ለሐኪም ለማሳየት አያፍርም፤ ካሳየው ይፈወሳል፣ ከሸሸገው ግን ይበሰብሳል። አንተም ኃጢአትህን ለእግዚአብሔር ንገረው፤ እርሱም ይፈውስሃል።
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)
55 943
አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ! በዓይንህ ውስጥ ጉድፍ እንዲገባ የማትፈቅድ ኾነህ ሳለ በነፍስህ ላይ እልፍ ወትእልፊት የጉድፍ ክምሮች እንዲገቡ ቸለል ትላለህን? ታዲያ ዕለት ዕለት በነፍሳችን ብሌን ላይ እያከማቸነው ያለነውን ቆሻሻ የምናጸዳው መቼ ይኾን? እሾኾቹን የምንቆርጣቸው መቼ ይኾን? አረሞችን የምንነቅላቸው መቼ ይኾን? እንግዲህ ወዲህ መከሩ እንደ ቀረበ አታውቅምን? እኛ ግን እርሻችንን እንኳን ገና አላረስንም፣ አላለሰለስንም፡፡ እንግዲህ ገበሬው (የወይኑ ባለቤት) በመጣ ጊዜ ስሕተት ቢያገኝ ምንድን ነው የምንለው? እኮ የምንመልሰው ምን ይኾን? ዘር የሚሰጠንን ሰው አጥተን ነው ብለን ነው የምንለው? በፍጹም! ዘሩ'ማ ዕለት ዕለት እየተዘራ ነው፡፡ እሾኾቹን የሚቆርጥ ሰው አጥተን ነው የምንለው? ኧረ በጭራሽ! ዕለት ዕለት ማጭዱን እንደ ሳልን ነው፡፡ የዚህ ዓለም ሕይወት ውጣ ውረድ ይዞህ ነውን? ለምን ታዲያ ይህ ዓለም በአንተ ዘንድ ስቁል አልኾነም? የተበደረውን ዕጥፍ ሳያደርግ ያንኑ ብቻ መልሶ የሚከፍል እርሱ ክፉ አገልጋይ ከኾነ ይህቺውን ብትኾን የሚያጠፋስ ምን ብለን ነው ልንጠራው የምንችለው? ያ ሰው እጁና እግሩ ታስሮ ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ከተጣለ፥ ሠናያትን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ የሚያነሣሡን እልፍ ምክንያቶች እያሉ ወደ ኋላ የምንልና የማንፈቅድ እኛ ታዲያ እንደ ምን ያለ መከራ ይገባን ይኾን?
እንዲህ እንዳታደርግ አንተን ለማሳመን የማይበቃው እስኪ የትኛው ነው? የዓለሙን ርኵሰት አላየህምን? የዚህን ዓለም ሕይወት ርግጠኛ ያለመኾን አልተመለከትክምን? የዚህን ዓለም ድካም፣ በዚህ ዓለም ለሚቀር ደመወዝ የሚወጣውን ላብ አላየህምን? እኮ እስኪ ንገረኝ! ምግባር ሲሠራ ላብ ጠብ ርግፍ የሚያደርግ ክፋት ሲሠራ ግን ምንም ምን ድካምና መከራ የሌለው ነውን? በፍጹም! ታዲያ በኹለቱም ዘንድ ውጣ ውረድ ካለው ይህን ያህል ትርፍ ያለውን ለምን አትመርጥም?
እንዲያውም አንዳንድ ሠናያት ድካምን የሚጠይቁ አይደሉም፡፡ እስኪ ንገረኝ! የስድብ ቃልን ላለመናገር፣ በባልንጀራህ ላይ ላለመቈጣት፤ ላለመዋሸት፤ ላለመማል የሚፈልግብህ ድካም እንደ ምን ያለ ድካም ነው? ምንም ድካምን አይጠይቅም! ይልቅስ እጅጉን ድካም ያለውና ብዙ የሚያስጨንቀው እነዚህን ለማድረግ ነው፡፡
እንግዲህ እነዚህን እንኳን ላለማድረጋችን ልናቀርበው የምንችል ሰበብ እንደ ምን ያለ ሰበብ እንደ ምን ያለ ምክንያት ይኾን? ከስንፍናችንና ከልል ዘሊልነታችን የተነሣ ድካም የሚጠይቁትንም እንደማንሠራቸው በዚህ ግልፅ ነውና፡፡
ስለዚህ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ ክብርና ኃይል የባሕርይገንዘቡ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነቱና ሰውን መውደዱ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ለዚህ የበቃን እንኾን ዘንድ ይህን ኹሉ ልብ ብለን አስተውለን፥ ከክፉ እንሽሽ፤ ሠናያትንም እንምረጥ፡፡ አሜን!
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ቅጽ 2 ድርሳን 42 ገጽ 368-370 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
55 943
ሁለቱን ሐሳቦች ተረዷቸውና ተጠንቀቋቸው አንደኛው "አንተ ቅዱስ ነህ" የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "መቼም ቢሆን ልትድን አትችልም" የሚለው ነው፡፡
ሁለቱም ሐሳቦች ከጠላት ናቸው፤ በትዕቢትና ተስፋ በመቁረጥ የተሞሉ እውነት የሌላቸው ናቸው፡፡
አንተ ግን ለራስህ ይህን በለው "እኔ ታላቅ ኃጢአተኛ ነኝ ሥራዬ በፊቴ ነው ግን አምላክ መሐሪ ነው! ሰዎችንም በጣም ይወዳል፤ ስለዚህ ኃጢአቴን ይቅር ይለኛል፡፡"
አባ ስልዋኖስ ዘአምድ
55 943
#ከንስሐ_ርቀን_ይቅርታን_አናገኝም
ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት፡፡ ይህንንም የሚያስረዳ ነገር በጥምቀት ከእግዚአብሔር ከምትገኝ ልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግስተ ሰማይ መያዣ ከናት፡፡
በንስሐ ምክንያት የእግዚአብሔርን ቸርነት እናገኛለን፡፡ ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን፡፡ መከላከያ ከሚሆን ከንስሐ ርቀን ይቅርታን አናገኝም፡፡
አምላክ የጻፈው መጽሐፍ እንደተናገረ ሁላችን በድለናልና ያለ ዋጋ በይቅርታው ከኃጢአት እንነጻለን፡፡ ንስሐ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በሃይማኖትና በልቡና የምትገኝ ሁለተኛ ጸጋ ናት፡፡ ሀብታተ ምስጢራት ከሚገኙበት ከመንፈሳዊ ፍቅር እስክንደርስ ድረስ የሚጠብቀን መንፈሳዊ ዕውቀት ነው፡፡
(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ)
55 943
“እግዚአብሔር የሚወዳችሁ አንድም እግዚአብሔርን የምትወዱት ወንድም እኅቶቼ ሆይ! እግዚአብሔር በሥጋ ከባረከን በላይ በነፍስ የባረከን ይበልጣልና ስለዚሁ ልናመሰግነው ይገባናል፤ ምድራዊ መጠጥን አንድም ምድራዊ መብልን ከመስጠት መንፈሳዊ መጠጥንና መብልን መስጠት ይበልጣልና፡፡
እግዚአብሔር አስቀድሞ ለእሥራኤላውያን መናውን የሰጣቸው በኋላም እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ለእኛ ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን የሰጠንም ስለዚሁ ነውና በሥጋ ከሰጠን ይልቅ በነፍስ የሰጠን ስለሚበልጥ እግዚአብሔርን እጅግ ልናመሰግነው ይገባናል፡፡
እግዚአብሔር በሥጋ ሲባርከን በዚያው (በሥጋዊው ነገር ላይ ብቻ) እንድንቀር አይደለም፤ የበለጠ ወደርሱ እንድንቀርብ ነው እንጂ፡፡ ሥጋዊውን ስጦታ ይዘን የምንቀር ከሆነ ግን ዓላማውን ስተናልና ልናስተካክል ይገባናል፡፡
ተወዳጆች ሆይ! በአፍአ ከተባረክነው ይልቅ በነፍስ የተባረክነው ይበልጣልና ስለዚያ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ለምን? መንፈሳዊው ነገር ከእኛ ዘንድ ካለ፥ ሥጋዊ ነገር ቢቀርም ምንም አናጣምና፡፡ መንፈሳዊውን ካጣን ግን ከእኛ ዘንድ ምን ተስፋ፥ ምንስ መጽናናት ይቀርልናል? አስቀድመን መንግሥቱንና ጽድቁን እንድንሻ የተፈለገውም ስለዚሁ ነው፡፡
የምወዳችሁ ልጆቼ! አስቀድመን እውነተኛውን ሀብት ይኸውም ሰማያዊውን ሀብት እንለምን፤ ርሱንም ለማግኘት እንጣጣር ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሌላው ከዚያ በኋላ ይቀጥላል፡፡ እኛ ስለለመንን ሳይሆን ልቡናችን ዋናውን ስለፈለገ፡፡ ጸሎታችንን የምናገላብጠው ከሆነ ግን በነፍስ በሥጋ የተጐዳን እንኾናለን፡፡”
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ- የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ገጽ 27)
55 943
እግዚአብሔር የሚወዳችሁ እናንተም የምትወዱት ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የእውነት አዲስ ዓመት እንዲኾንላችሁ ካሻችሁ ነፍሳችሁን ከኀጢአት ቀንበር አላቋት እንጂ ድጋሜ በኀጢአት ሸክም አትጫኗት፡፡ አሮጌው ዓመት እንዳለቀ ስታዩ እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ወደሌላ ዘመን አሸጋግሯቸዋልና እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ልቡናችሁንም ውቀሱት፡፡ በዕሜአችሁ ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰባችሁም ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁት፡- “ቀናት እየሮጡ ነው፡፡ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፡፡ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፡፡ ታዲያ ምን በጐ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፡፡ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፡፡ ታዲያ ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውም የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንዳቅሜ እያደረግኩ ነውን?”
ተወዳጆች ሆይ! አዲስ ዓመት ሲመጣ እነዚህን ነገሮች በጥንቃቄ ልናስብባቸው ይገባናል፡፡ ይህን እያደረግንም ስለ ቀጣዩ ዓመት እናስብ፡፡ ይህን የምናደርግ ከኾነ “ቀኖቻቸውም በከንቱ አለቁ፤ ዓመቶቻቸውም በችኰላ” አይባልብንም (መዝ.78፡3)፡፡ ዕለት ዕለት በዓልን እናድርግ ብዬ የገለጥኩላችሁም ይኸው ነው፡፡ የእኛ በዓል ዘወትር መኾን ይገባዋል፡፡ የክርስቲያኖች በዓል በዓመታትና በቀናት ብቻ መወሰን የለበትም፡፡ ቤተ ክርስቲያንም በሳምንት፣ በወር፣ በዓመት የሚከበሩ በዓላት እንዲኖሩ ማድረጓ ዘወትር ከዚሁ ልንርቅ እንደማይገባ ማሳሰቧ እንጂ ሌላ አይደለምና፡፡ ይህን በዓል በየዕለቱ ማድረግም ለኹሉም ይቻላል፤ ለድኻውም ለባለጸጋውም ይቻላል፡፡ በዓልን ለማድረግ (የጽድቅ ሥራን ሠርቶ ሐሴት ለማድረግ) የሚያስፈልገው ቅን ልቡና እንጂ ገንዘብ አይደለምና፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሰማዕትነት አያምለጣችሁ ገጽ 13-19 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመው)
55 943
“ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።”
ኤፌ 4፥22
55 943
#የአዲስ_ዓመት_ጸሎት_በአቡነ_ሺኖዳ
አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ዓመቱን የተባረከ አድርገው። አንተን ደስ የሚያሰኝ ንጹሕ ዓመት ይሁን። መንፈስ የሚገለጥበት ዘመን ይሁን፣ ከእኛ ጋራም ይሥራ፤ እጆቻችንን ያዝና አሳቦቻችንን ከዓመቱ መጀመሪያ እስከ ማብቂያው ድረስ አንተ ምራቸው። አንተ ደስ ያሰኝህ ዘንድ ይህ ዓመት የአንተ ይሁን፡፡ ይህ አመት አዲስ ዓመት ስለሆነ በኃጢአታችንና በበደላችን አናርክሰው።
እግዚአብሔር ሆይ፦ በዚህ ዓመት ልንሠራው ባቀድነው በማንኛውም ሥራ ውስጥ አንተ ከእኛ ጋር ሁን፤ እኛ ዝም እንላለን አንተ ሁሉንም ነገር ታደርጋለህ፡፡
አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ይህ ዓመት መልካም ይሁን።
በእያንዳንዳችን ላይ ፈገግታን ግለጥ፤ የሁላችንንም ልብ አስደስት፤ በችግራችን ውስጥ ጸጋህ ይገለጥ፤ የተፈተኑትንም አንተ እርዳቸው፤ የአሳብ ሰላምንና ጸጥታን አድለን፡፡ ለተቸገሩት ስጣቸው፤ የታመሙትን ፈውሳቸው፣ ያዘኑትን አጽናናቸው፡፡
ጌታችን ሆይ፦ ለራሳችን ብቻ አንጠይቅህም ያንተ ስለሆኑት ስለሁሉም እንጠይቃለን የፈጠርኻቸው ባንተ ደስ እንዲሰኙ ነው ይህ ከሆነ በአንተ ደስ እንዲሰኙ አድርጋቸው ቃልህ ለሁሉም ልብ ይደርስ ዘንድ ስለ ወንጌል አገልግሎትና ስለ ቤተ-ክርስቲያናችን እንጠይቅሃለን፤ ስለሃገራችንም እንጠይቅሃለን፡፡
መንግሥትህ በሁሉ ስፍራ እንድትመጣም ስለ ዓለም ሰላም እንጠይቅሃለን፡፡ ዓመቱ ፍሬያማና በመልካም ነገሮች የተሞላ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ ቀንና ሰዓት የራሱ የሆነ ስራ አለው አንተ የሚባክን ጊዜ ይኖርህ ዘንድ አትፍቀድ፡፡ ሕይወታችንን በእንቅስቃሴ በሥራና በምርት የተሞላ አድርግ፤ ለምርታማና ለተቀደሰ ልፋታችን በረከትህን አድለን፡፡ በተግባራችን ውስጥ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት ከእኛ ጋር ይሁን።
አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ እስከዚች ሰዓት ድረስ ጠብቀህ ስላቆየኸንና ይህንን ዓመት ስላደልከን እናመሰግንሃለን፣ እንባርክህማለን፡፡
