የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ኢዜማ ኢትዮጵያ የሁሉም ዜጎች መብት የተከበረባት፣ ማኅበራዊ ፍትህ የሰፈነባት ሰላማዊ እና የበለፀገች ሀገር እንድትሆን የሚሠራ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ነው።
إظهار المزيد2 993
المشتركون
-324 ساعات
-57 أيام
-1930 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+2
في 0 قنوات
يونيو '26
+20
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+37
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+47
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+46
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+53
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+70
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+37
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+17
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+13
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+16
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+43
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+56
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+39
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+24
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+50
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+21
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+25
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+25
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+12
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+20
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+63
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+67
في 1 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+27
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+32
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+28
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+39
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '24
+49
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+99
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+217
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+170
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+24
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+24
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+17
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+16
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+21
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+17
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+37
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+86
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+82
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+26
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+48
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+46
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+49
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+10
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+127
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+35
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+47
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+33
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+30
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+20
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+30
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+9
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+18
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+8
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+12
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+25
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+8
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+7
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+17
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+328
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+294
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+1 308
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+205
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+166
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+47
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+3 745
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | +1 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | 0 |
منشورات القناة
ዛሬ ምሽት 3:00 ሰዓት
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ ኢዮብ መሳፍንት በ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) አንድ ዕድል ፕሮግራም ላይ ያደረጉትን ቆይታ ይመልከቱ።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
| 2 | የኢዜማ መሪ ኢዮብ መሳፍንት በተለያዩ ጉዳዮች በ EBC ወቅታዊ ፕሮግራም ላይ ያደረጉትን ቆይታ ይከታተሉ
https://youtu.be/ULHkENupbs8?si=TIiPX99y0jmZbYDu | 763 |
| 3 | لا يوجد نص... | 1 285 |
| 4 | የሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከኢዜማ የተሠጠ መግለጫ!!
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 መጠናቀቁን በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በማሣወቅ አረጋግጧል፤ ምርጫው ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ፓርቲያችን እንኳን ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
በተጨማሪም ፓርቲያችን ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ አጠናቋል። ይህንን ተጨባጭ ስኬት ላስመዘገቡ የፓርቲያችን ዕጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች እና በሂደቱ በቅንነት ለተሳተፉ አካላት ሁሉ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ፓርቲያችን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑን እየገለፅን፤ በነዚህ ዓመታት ከዚህ ቀደም ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንን እና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን።
በመጨረሻም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
#ምርጫ_2018 | 1 149 |
| 5 | የኢዜማ መሪ ኢዮብ መሳፍንት ምርጫውን እና ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከ NBC ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉትን ቆይታ ዛሬ ምሽት 3:00 ሰዓት ይከታተሉ።
https://youtu.be/q4kVabVLsrI?si=-NmZ6E2AHaPrSibB
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ | 1 112 |
| 6 | የ #ኢዜማ አዲስ አበባ ምርጫ ክልል 19 አባል እና የሴቶች መምሪያ ቋሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት ሊሊ ኃይሉ በትላንትናው ዕለት ሰኔ 11/ 2018 ዓ.ም. ባደረባቸው ሕመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ፓርቲያችን በአባላችን ሕልፈት የተሠማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው፣ ዘመድ እና ወዳጆቻቸው በቶሎ መጽናናትን ይመኛል። | 1 127 |
| 7 | ጦርነትን ሳይጀመር ማስቆም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል!!
ሀገራችን በታሪኳ እስከአሁን ድረስ በተለያዩ የኃይል አማራጮች ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የመንግሥት ሥልጣንን ለመቀየር ስትባዝን አለች፤ ሆኖም የረጅም ዓመት ሀገረ መንግሥት ታሪኳን በማይመጥን መልኩ እስከአሁን ኋላቀር ከሚባሉት ሀገራት ግንባር ቀደም ከመሆን የዘለለ አንዳች ነገር አላገኘችም።
ላለፉት ከ 30 ዓመታት በላይ በሀገሪቱ ውስጥ ላሉ ችግሮች፣ ግጭቶች፣ ጥቃቶች እንዲሁም ሌሎች በርካታ ችግሮች በዋነኛነት ምክንያቱ ደግሞ ሕወሓት ሥልጣነ መንበሩን በኃይል ካረጋገጠ በኋላ ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ ነው። ይኽ የፖለቲካ ሥርዓት ከፍተኛ ችግር ያስከተለ ቢሆንም በሕወሓት ተንኳሽነት የተጀመረው እና ከሁለት ዓመታት በላይ የፈጀው የሰሜኑ ጦርነት ያስከተለውን የሰው ህይወትና የንብረት ውድመት በከፍተኛነቱ የሚስተካከለው የለም።
ከዚህ ጥፋት መልስ በፕሪቶሪያ ስምምነት ከጦርነት መውጣት የተቻለ ቢሆንም ይህ በዘላቂነት እንዳይቀጥል በተለይ ሕጋዊ ማንነቱን ባጣው ሕወሓት በኩል እንደሥምምነቱ እንዳይፈፀም የታዩ ዳተኝነቶች እና እንደ አጠቃላይ የፖለቲካ ሥሪቱ ላይ ውጤት ሊያመጣ የሚችለውን ሀገራዊ ምክክር፣ የ2018 ዓ.ም ምርጫ በትግራይ ክልል እንዳይከናውን በማድረግ፣ በክልሉ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዳይመለሱ በታጋችነት በመያዝ በአጠቃላይ በክልሉ ያለው ችግር እንዳይፈታ በማድረግ ይኸው ችግር መልሶ ይፈጠር ይሆን የሚል ስጋትን እንደያዘ አለ።
ለትግራይ ማኅበረሰብ እቆረቆራለሁ የሚለው ይህ ቡድን ከእሰጠዓገባ ውጪ መኖር የማይችል በሚመስል መልኩ የተለያዩ ችግሮችን ለመፍጠር እየሞከረ የከረመ ሲሆን ግንቦት 02/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እና በክልሉ አፀደቀ በተባለው አዋጅ ግልጽ የጦርነት አዋጅን ለፍፏል። በተለይም በአዋጁ ያካተተው አስገዳጅ የወታደር ምልመላ፤ የተለዩ ድምፆች በትግራይ እንዳይሰሙ ያስቀመጠው ልጓም፤ ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር የሚመስለው የፕሮፖጋንዳ ልፈፋ ይኽንን ተፈጥሯዊ ጠበኛ ባሕርዩን እና ፍላጎቱ አሁንም የትግራይን እና አጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ በስንት ልፋት ወዳስቆመው ጦርነት እና እልቂት መክተት መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው።
በመሰረቱ አዋጁን ማውጣቱ እና በተለይም ከወታደር ምልመላ እና ጦርነቱን ካለመደገፍ ጋር በተገናኘ የተካተቱት ቅጣቶች ማኅበረሰቡ በጦርነቱ ለመሣተፍ ፍላጎት እንደሌለው እና በዚህም ቡድኑ ስጋት ያደረበት መሆኑን በግልፅ የሚያሣይ ነው፤ ይህ ተስፋ የቆረጠ እድሜያቸው የገፋ የሥልጣን ጥመኞች ስብስብ አሁንም በግጭት ውስጥ አፍላ ወጣቶችን የመማገድ ዓላማ አድርጎ ከዚህ ቀደም ልጆቻቸውን ያጡትን እናቶች፤ በስለት ከጦርነቱ የተረፈ የቀረ ልጅ ያላቸውን ጧሪ ቀባሪያቸውን ሊነጥቃቸው አሰፍስፎ መምጣቱ ለትግራይ ህዝብም ሆነ ለሰው ልጆች ሁሉ እንጥፍጣፊ ርህራሄ እንደሌለው ያሳያል። ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል።
ኢዜማ የትኛውም ፖለቲካዊ ችግር በውይይት መፈታት አለበት ብሎ በጽኑ የሚያምን ሲሆን ይህንን ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆነን እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል፤ ማኅበረሰቡም አሁን ለጦርነት ዕያሣየ ያለውን እምቢተኝነት በተጠናከረ መልኩ እንዲገፋበት ጥሪ እናቀርባለን።
በመጨረሻም በዚህ ሒደት ውስጥ ፓርቲያችን ማኅበረሰቡ እያለፈበት ያለውን ጭንቀት እየኖረበት ያለውን አሰቃቂ ሁኔታ ለመቅረፍ ባለው አቅም ሁሉ በቀጥታ ለማገዝ ከማንኛውም ሀገራዊ ኃይል ጋር በጋራ ለመሥራትና የበኩሉን ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን ያረጋግጣል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 04/ 2018 ዓ.ም. | 1 533 |
| 8 | ኢዜማ እስካሁን በ5 የምርጫ ክልሎች ላይ ውጤትን የቀየሩ ችግሮች ተፈፅመዋል ብሎ ስለሚያምን በነዚህ ቦታዎች ላይ ውጤቱ ተሰርዞ በድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ አቤቱታ ያስገባ ሲሆን የቦርዱን ውሳኔ የሚጠባበቅ ይሆናል። አቤቱታ ያስገባንባቸው ምርጫ ክልሎች፤
1. ባኮ ጋዘር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል
2. ላስካ መደበኛ ምርጫ ክልል
3. ቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል
4. ፈለገ ሰላም ምርጫ ክልል
5. ማረቃ ጌና ምርጫ ክልል
በሌሎች ምርጫ ክልሎችም በተመሳሳይ አቤቱታዎችን እየመረመርን ሲሆን ሲጠናቀቁ ለቦርዱ የምናቀርብ ይሆናል።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
#ምርጫ_2018 | 1 943 |
| 9 | لا يوجد نص... | 1 686 |
| 10 | የምርጫው ሂደት ስኬታማ እንዳይሆን ካደረጉት ዋነኛ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች መካከል በመንግሥት አካላት የተፈጸሙ ሕጋዊ ጥሰቶች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። መንግሥት ለሕዝብ የጋራ አገልግሎት የሚውሉ ንብረቶችን ለገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ አሳልፎ ሰጥቷል። በምርጫው ዕለትም "የሰላም ሠራዊት" ተብለው የተደራጁ አካላትን፣ የወረዳ ሥራ አስፈጻሚዎችንና የመንግሥት ሠራተኞችን በሕግ ባልተሰጣቸው የምርጫ ተግባራት ውስጥ በማሳተፍ ግልጽ ጣልቃገብነት ፈጽሟል። በተለይም ደግሞ ከከተማ ርቀው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመንግሥት የጸጥታ አካላትና የገዢው ፓርቲ አመራሮች የተፎካካሪ ፓርቲ ታዛቢዎችን ሲያስፈራሩ፣ ሲያዋክቡና በጉልበት ከጣቢያዎች ሲያስወጡ ተስተውለዋል። ይህ ዓይነቱ አሠራር የመንግሥትን ገለልተኝነትና የሕግ የበላይነትን የገፈፈ እና ጭልጭል የሚለውን የዲሞክራሲ ጅማሮ ጨርሶ የሚያጠፋ አደገኛ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል፣ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኅን አቀራረብም ሌላኛው የሂደቱ ፈተና ነበር። የእነዚህ አካላት መመዘኛና መስፈርት በዋነኛነት በገዛ ራሳቸው ፖለቲካዊና ስትራቴጂካዊ ተጠቃሚነት ላይ ብቻ የታጠረ ነው። በዚህም ምክንያት የሀገሪቱን የምርጫ ሂደት እነርሱ ለዘመናት ካለፉበት የዲሞክራሲ ጎዳና አንጻር ከመመልከት ይልቅ፣ የምርጫ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ቅቡልነት እንዳይኖረው ለማድረግ ሲሰሩ ተስተውሏል። ይህም በምርጫ የሚመሠረት መንግሥት እንዳይኖረን በማድረግ በጎረቤት ሀገራት ጭምር እንደታዘብነው መንግሥት አልባ ሀገር የማድረግ የብሔራዊ ጥቅማችን ተቃራኒ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል።
ማጠቃለያ
ኢዜማ መንግሥታዊ ሥልጣን ሊያዝ የሚችለው በሰላማዊ መንገድ እና በምርጫ ሥርዓት ብቻ መሆኑን ያለማወላወል ያምናል። በምርጫው ሒደት ውስጥ ሰፊ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እና የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ስልታዊ የጥርነፋ ስልቶች በግልጽ የታዩ ቢሆንም፣ ፓርቲያችን በሰላማዊና በሰለጠነ የሐሳብ ክርክር የሕዝብን ልብ የማሸነፍ መርሆውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በድጋሚ ማረጋገጥ ይፈልጋል። በዚህ የምርጫ ተሳትፏችን ውስጥ ውስብስብ ችግሮችን በጽናት ተጋፍጠን ማለፋችን እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ፓርቲያችን ካለፉት የምርጫ ተሞክሮዎቹ በእጅጉ የተሻሉ ስኬቶችን ማስመዝገቡን በበጎ ጎኑ ገምግሟል። የሀገራችንን የዲሞክራሲ ባህልን ከዳዴ ጉዞው አውጥቶ በጠንካራ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ኢዜማ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት እያደሰ፣ ለዘላቂ ሀገር ግንባታ ከሕዝባችን ጋር በጽናት እንደሚቆም በድጋሚ ያረጋግጣል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ | 1 562 |
| 11 | 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ ከኢዜማ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫን በተመለከተ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ ውጤቶችን ካሳወቀ በኋላ እንደፓርቲ ዝርዝር ሪፖርት ወደፊት ማቅረቡ እንደተጠበቀ ሆኖ ምርጫውን በተመለከተ አጭር ግምገማ አድርጓል።
ፓርቲያችን ምርጫው በተካሄደባቸው አካባቢዎች ከሞላ ጎደል በሰላም መጠናቀቁን እንደ አንድ በጎ ክስተት ይገነዘበዋል። ፓርቲያችን በዚህ ሀገር አቀፍ ምርጫ ለመወዳደር ሲወስን የምርጫው ሂደት አልጋ በአልጋ ይሆናል ከሚል ተላላነት በመነሳት አይደለም። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት የዴሞክራሲ ባህላችን ገና በዳዴ ላይ ያለ በመሆኑ እና ይህንን ባህል ለማጎልመስ የሚወስደው ጊዜ ቀላል አለመሆኑን ከመረዳት የመነጨ ነው። ኢዜማ ምርጫውን ሂደት እና ውጤት ሊጎዱ የሚችሉ ሁኔታዎች የመኖር እድላቸው እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አምኖ፤ ነገር ግን የዴሞክራሲ ግንባታ በአስተሳሰብ፣ በመተማመን እና በተደጋጋሚ በማድረግ ጥረት የሚሳካ መሆኑን በመገንዘብ ነው በሂደቱ ውስጥ በሙሉ ልብ መሳተፉን የቀጠለው።
👉 የምርጫው ጠንካራ ጎኖች
ምንም እንኳ በምርጫው ሂደት ገዢው ፓርቲ ዜጎችን በማስገደድ የምርጫ ካርድ እንዲወስዱ ማድረጉ አግባብነት የሌለውና የሚኮነን ቢሆንም፣ በሂደቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው መራጭ ሕዝብ መመዝገቡ አንዱ መነቃቃትን ያሳየ ጠንካራ ጎን ነው። ከዚህም በተጨማሪ፣ የአሰራሩ አዲስነት እና የቴክኖሎጂ አፈጻጸም ክፍተቶች በስፋት ቢታዩም፣ መራጮችና እጩዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን (በኢንተርኔት) አማካኝነት መመዝገብ መጀመራቸው ለዲሞክራሲ ስርዓቱ መዘመን ትልቅ እመርታ ነው። በሌላ በኩል፣ ለሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰፊ የሚዲያ እድል፣ የጋራ የክርክር መድረክና የአየር ሰዓት በአግባቡ መመቻቸቱ የሂደቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ፓርቲያችን እነዚህን የታዩ በጎ ጅምሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የራሱን አስተዋጻኦ መወጣቱን ይቀጥላል።
👉 በምርጫው ሂደት ላይ የታዩ መዋቅራዊ ፈተናዎችና ተግዳሮቶች የገዢው ፓርቲ መዋቅራዊ ተፅዕኖዎች
ቀዳሚው ፈተና በገዢው ፓርቲ (ብልጽግና) የተፈጸሙ የተዛቡ አሠራሮች ናቸው። ፓርቲው እንደ ማኅበራዊ ጥበቃ፣ የትምህርት ቤት ምገባና መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብን የመሰሉ የመንግሥት የልማት ፕሮግራሞችን ለምርጫ ቅስቀሳ ፖለቲካዊ መጠቀሚያ አድርጓቸዋል። ዜጎች ለገዢው ፓርቲ ድምጽ ካልሰጡ እነዚህ አግልግሎቶችን እንደሚያጡ ስጋት ውስጥ በመክተት፣ ድምፅን በቁሳዊ ፍላጎት የመግዛት ስልት ተከትሏል። ይህንንም "ትስስር፣ የብልጽግና ቤተሰብ" በሚባል የዳቦ ስም በመጠረነፍ የምርጫ ውሳኔያቸው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሮባቸዋል። የመንግሥት መገናኛ ብዙኅንን የገዢው ፓርቲ የግል ንብረት አድርጎ የመጠቀም ሁኔታም ዐይን ባወጣ መልኩ በምርጫው ወቅትም ቀጥሏል።
በመራጮች ምዝገባ ወቅት የአካባቢው የመንግሥት አስተዳደር ሠራተኞችና የፓርቲው ካድሬዎች መራጮች ከምርጫ ጣቢያ ካርድ ይዘው ሲወጡ እና መረጃዎችን ቤት ለቤት በመሰብሰብ፣ ምርጫው በምስጢር የሚካሄድ በማይመስልበት ሁኔታ የሥነ-ልቦና ጫና ፈጥረዋል። ይህ ተፅዕኖ በምርጫ ቀኑም ቀጥሎ፣ ካድሬዎች በሕግ ተለይቶ ባልተሰጣቸው ኃላፊነት ሰልፍ እናስተናብራለን በሚል ሰበብ በምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በአካል በመገኘት መራጮች ላይ በተለያዩ መንገዶች ተጽእኖ አሳድሯል። ወደ ምርጫ ጣቢያ በሚወስዱ መንገዶች ላይ በመቆም "ስንዴን ምረጡ" የሚሉ ይፋዊ ቅስቀሳዎችን በማድረግ የመራጩን ማኅበረሰብ ነጻነት የሚገፍፍ ተግባራትን ሲፈጽሙ ተስተውለዋል። በተለይም ከከተሞች ውጪ የመንግሥትን የሕዝብ ሀብትና ንብረት ለፓርቲው የምርጫ ቅስቀሳ ሥራዎች በሠፊው አውሏል። ገዢው ፓርቲ ምርጫውን የሚያውኩ እነዚህን የመሰሉ መዋቅራዊ ጥሰቶች ለማስተካከል ቁርጠኛ ካልሆነ፣ በማኅበረሰቡ ዘንድ "በሰላማዊ ትግልና በምርጫ ሥልጣን መያዝ አይቻልም" ወደሚል ተስፋ መቁረጥ እንዳይገፋው ያሰጋናል። ይህ ደግሞ ከሰላማዊ ትግል ያፈነግጡ አማራጮችን በማበረታታት ሀገራችንን ወደ ሌላ ሊቀለበስ የማይችል አጠቃላይ ቀውስ ውስጥ የሚጥላት መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጋ አይገባም።
👉 በተፎካካሪ ፓርቲዎች የታዩ ጉድለቶች
አንዳንድ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የምርጫ ሂደቱን በሙሉ ልብ ተቀብለው የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማሻሻል ከመጣር ይልቅ፣ ከጅምሩ ለምርጫው ቅቡልነት ማጣት ምክንያት የሚሆኑ “ሁለት ልብ” አቋሞችን ከማንጸባረቃቸውም በላይ ከሰላማዊ ትግል ውጪ የሆኑ አቋራጭ መንገዶችን የመጠቀም ፍላጎት ተስተውሏል። በምርጫ ክርክሮች ወቅትም ተጨባጭ አማራጭ የመፍትሔ ሐሳቦችን ከማቅረብ ይልቅ ሁላችንም የምናውቃቸውን ሀገራዊ ችግሮች በማጉላት የሕዝብን ስሜት በመቀስቀስ መጠቀሚያ ለማድረግ ከመሯሯጥ በተጨማሪ እጩዎች በተወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች እንኳ ሂደቱን የሚከታተል የተሟላ የታዛቢ መዋቅር ማሠማራት አለመቻላቸው ሌላው ጉድለታቸው ነው።
👉 የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ክፍተቶች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ አሁንም ቢሆን በበቂ የሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ የዳበረ ጠንካራ ተቋም መሆን አለመቻሉ አሳዛኙ እውነታችን ነው። ከሁሉም በላይ አሳሳቢው ጉዳይ፣ በምርጫው ዕለት ሂደቱን እንዲያስተናብሩ የተመደቡ የቦርዱ አስፈጻሚዎች ሕጋዊ ኃላፊነታቸውን በሌሎች የመንግሥት አስተዳደር አካላትና ግለሰቦች ሲነጠቁ፣ ድርጊቱን ከማስቆም ይልቅ ዝምታን መምረጣቸው ነው። ተቋሙ ካለፉት ምርጫዎች በቂ ትምህርት በመውሰድ የተሻሉ፣ ገለልተኛና ለሕሊናቸው ታማኝ የሆኑ አስፈጻሚዎችን በጥንቃቄ መመልመል፣ ማሰማራት እና መቆጣጠር ሲገባው፤ በተመሳሳይ መልኩ በ"ይድረስ ይድረስ" ለማጋፈር መሞከሩ በምርጫው ገለልተኝነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሯል። በዚህም ምክንያት ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የቦርዱ አስፈጻሚዎች፣ በተግባር የገዢው ፓርቲ ታማኝ ጉዳይ አስፈጻሚዎች ሆነው ተገኝተዋል።
👉 የሲቪክ ማኅበራትና የማኅበረሰቡ ሚና
ሲቪክ ማኅበራት ባለፉት ዓመታት የዜጎችን መብትና ግዴታዎች የማስተማር ተቋማዊ ግዴታቸውን ከመወጣት አኳያ የረባ ተሳትፎ እንዳልነበራቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው። በምርጫው ዕለትም ተሳትፏቸው "አሉ ለመባል" እና ተምሳሌታዊ ከመሆን ባለፈ፣ የምርጫውን ነጻነትና ፍትሐዊነት በቅጡ አልተወጡም። በሌላ በኩል፣ ማኅበረሰባችን በምርጫ ሥርዓት "ለውጥ አመጣለሁ" የሚል የፖለቲካ እምነትና መተማመንን ገና በበቂ ሁኔታ ባለማዳበሩ ምክንያት፣ ምንም እንኳን ከቀደሙት ጊዚያት የተሻለ ቢሆንም በሂደቱ ላይ የሚጠበቀውን ያህል በንቃት ተሳትፏል ብለን አናምንም። በምርጫው ለመሳተፍ የምርጫ ካርድ የወሰደው የማኅበረሰብ ክፍል እንኳ ሳይቀር በገዢው ፓርቲ መዋቅራዊ ጫናዎችና ስጋቶች ውስጥ በቀላሉ የመውደቅ ዝንባሌ አሳይቷል።
በምርጫው ዕለት የታዩ የመስተንግዶ መጓተቶች ባስከተሉት መሰላቸት ምክንያት በርካታ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ማኅበረሰቡ አግባብ ባለው መልኩ ኃላፊነት ወስዶና ነቅቶ ከተንቀሳቀሰ፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት ላይ ፈጣንና ሥር ነቀል ለውጥ ማምጣት የሚችለው ቀዳሚው ኃይል ማኅበረሰቡ ነው። ይህንን ኃላፊነት አለመወጣት ግን በሂደቱ ላይ የሚመጣውን ከፍተኛ ጉዳት ቀድሞ የሚያስተናግደው ራሱ ማኅበረሰቡ መሆኑን አውቆ፣ በቀጣይ ዜጎች ፖለቲካዊ መብቶቻቸውንና ተሳትፏቸውን በንቃት እንዲወጡ አጥብቆ መሥራት ይጠበቅብናል፤ ማኅበረሰቡም ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል።
👉 የመንግሥት ዳተኝነት እና የዓለም አቀፉ ሚዲያ ጣልቃገብነት | 1 309 |
| 12 | በምሥራቅ አርሲ ማንነትን (ሃይማኖትን) መሠረት ባደረገ ጥቃት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆኑ ዜጎች እስከአሁን ማንነቱ ባልታወቀ አካል እንደተገደሉ እና ቤተክርስቲያን መቃጠሉ፣ ከጥቃቱ የሸሹ ዜጎችም ከቀያቸው መሰደዳቸው ከመገናኛ ብዙሃንና ከሀገረስብከቱ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።
ኢዜማ ሁሌም እንሚያስገነዝበው ለዚህ ዐይነቱ ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ምንጬ ፖለቲካችን በማንነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው ብሎ ያምናል።
በተጠቀሰው ስፍራ በተደጋጋሚ የሚደርሰው መሰል ጥቃትን የመከላከል ኃላፊነት የአካባቢው የመንግሥት አስተዳዳር እና የጸጥታ ተቋማት መሆኑ የታወቀ ነው። በዚህ ረገድ የአካባቢው አስተዳደርና የኦሮሚያ ክልል መንግሥት በተደጋጋሚ ተፈትኖ እንደወደቀ ማየት ይቻላል።
ስለሆነም አስፈላጊውን ማጣራት ተደርጎ ኃላፊነት የሚወስዱ አካላትን በመለየት አስተማሪና ሕጋዊ የእርምት እርምጃ መንግሥት እንዲወስድ እናሳስባለን።
በዚህ ኢሰብአዊ ጥቃት ለተገደሉት ዜጎች የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለሟች ቤተሰቦችና ዘመዶች እንዲሁም ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን እንመኛለን።
በማንነት ላይ የተመሠረተው ፕለቲካችን ጨርሶ አንድ በአንድ ሳያጠፋን መፍትሔ ማበጀት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የቤት ሥራ መሆኑንም ኢዜማ ማስገንዘብ ይወዳል።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ | 1 365 |
| 13 | لا يوجد نص... | 1 551 |
| 14 | ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሠጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 07/2018 ዓ.ም. "ዴሞክራሲያዊ መብቶች በብሔር ማንነት እና በመንግሥት አሉታዊ ተፅዕኖ ውስጥ መውደቃቸው ምርጫውን ችግር ውስጥ ይከታል" ሲል ባወጣው መግለጫ፤
የሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ለሐረሪ ክልል ም/ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች የሐረሪ ብሔረሰብ ተወላጅ መሆን ለመመረጥ እንደ አስገዳጅ መስፈርት መቀመጥ በኢፌዴሪ ሕገመንግስት የተደነገገውን ዜጎች ያለምንም ዘር፣ ሐይማኖት እና ሌሎች ማንነት ልዩነቶች ሊጎናፀፉት የሚገባን የመምረጥ እና መመረጥ መብትን የሚጥስ መሆኑን ገልፆ መቃወሙ ይታወሳል።
በተጨማሪም በዚሁ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች ለሐረሪ ም/ቤት እንደሚወዳደሩ ዕጩዎች የሐረሪ ብሔረሰብ ተወላጅነትን እንደ አስገዳጅ መስፈርት ባያስቀምጥም በክልሉ ኢዜማን ወክሎ ለሕ/ተ/ም/ቤት እንዲወዳደር ያቀረብነው እጯችን በሐረሪ ጠ/ፍ/ቤት የወንጀል እና ፍትህ ብሔር ችሎት መዝገብ ቁ 08916 ከሕግ አግባብ ውጪ የሐደሬ ብሔር ተወላጅ አይደሉም በሚል ፓርቲያችን ባልተሣተፈበት እና ባላወቀው ክርክር እጩው እንዳይወዳደሩ ወስኗል።
የውሳኔው ይዘት ምንም እንኳን ስለ ሐረሪ ክልል ም/ቤት ተወዳዳሪዎች የተሰጠ ቢሆንም ለሕ/ተ/ም/ቤት ያቀረብነው አባላችን ስም ተካቶ የተሠጠው ውሳኔ ሕጋዊ ባለመሆኑ ምርጫ ቦርድ ለፍ/ቤቱ ማብራሪያ ቢጠይቅም እንዲሁም ፓርቲያችን በሌለበት የተሠጠው ውሳኔ ተገቢ አለመሆኑንና የክርክሩ አካል እንድንሆን ያቀረብነውን ጥያቄ ከፍትሕ ይልቅ ፖለቲካዊ ውሳኔ ተጭኖት ሳይቀበል ቀርቷል።
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ የፓርቲያችንን እጩ ተወዳዳሪ ሕጋዊ ባልሆነ/ባልተሠጠ ውሳኔ ላይ በመመሥረት ከእጩነት ማገዱ ተገቢ አለመሆኑን በመጥቀስ እንዲታረም ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አቤቱታችንን ያቀረብን ሲሆን ክርክሩ ውሳኔ እስከሚያገኝ ድረስ የምርጫ ቦርድ እጯችንን ለመሠረዝ የሠጠው ውሳኔ እንዲታገድ የፍ/ቤቱን ውሳኔ የጠየቅን ቢሆንም ፍ/ቤቱ ግን ተከሳሽ የሆነውን ምርጫ ቦርድን ሳያስቀርብ በእራሡ የተከሳሽን የመከራከርያ ነጥቦች በማንሳት ውሳኔ አሳልፏል።
የተላለፈው ውሳኔ አግባብነት ያለው እና ፍትሐዊ ነው ብለን የማናምን መሆኑን እየገለጽን ኢዜማ የዚህ ዓይነት ኢፍትሐዊ አሠራሮች ከሀገራችን እስከሚጠፉ ድረስ እስከመጨረሻው ድረስ እንደሚሞግት ለመግለጽ ይወዳል።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ | 1 603 |
| 15 | ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) | 1 395 |
| 16 | لا يوجد نص... | 1 361 |
| 17 | የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የቅስቀሳ መዝጊያ መርሐግብርን በሚመለከት የተሰጠ ማብራሪያ
በቅድሚያ ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የመተሣሠብ እንዲሆንላችሁ እየተመኘን የቅስቀሳ መዝጊያ መርኃግብራችን ላይ የሚከተለውን ማብራሪያ ለመሥጠት እንወዳለን።
ፓርቲያችን ኢዜማ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 ምርጫ ቅስቀሳ መጀመሩን ካወጀበት ቀን ጀምሮ በተለያዩ መንገዶች ለማኅበረሰቡ ያዘጋጃቸውን አማራጭ የፖሊሲ ሀሳቦች አቅርቦ ለመመረጥ ሲቀሰቅስ መቆየቱ ይታወቃል።
ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የቅስቀሳ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ፓርቲያችን ያዘጋጀውን የመዝጊያ መርኃግብር አስመልክቶ ሚዲያዎች እንዲዘግቡ ጥሪ ያቀረበበትን ደብዳቤ በማያያዝ መርኃግብሩ በበዓሉ ቀን መደረጉ ግርታ የፈጠረባቸው ወገኖች በቀናነት ማብራሪያ እንድንሰጥበት ጠይቀውናል።
የምርጫ ቅስቀሳ ማጠቃለያችንን በዚህ ዕለት ማድረግ የተመረጠበት ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው
1. ከበዓሉ ማግስት አንስቶ ማንኛውም ከቅስቀሳ ጋር የተያያዙ ተግባራት የማይፈጸምበት የጽሞና ጊዜ በመሆኑ፤
2. በሥራ ቀናት አባላቱን (ሁሉንም የእምነት ተከታዮች) የማሣተፍ እድሉ ዝቅተኛ በመሆኑ፤
3. መርሐግብሩን አመሻሽ ላይ ማድረግ ያስፈለገው የእስልምና እምነት ተከታይ አባላት እና ደጋፊዎቻችን በበዓሉ የሚደረጉት የሶላት ስግደት እና ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚያሳልፉትን የበዓል ጊዜ ታሣቢ በማድረግ ምሽት ላይ መርሐግብራችንን እንዲካፈሉ በማሰብ፤
4. የመርኃግብሩ ይዘት ሰላማዊ ሰልፍ ሳይሆን የፓርቲው ቅስቀሳውን ማገባደዱን የሚገልጽበት መሆኑን ለማሣወቅ እንወዳለን።
አስተያየታችሁን በቀናነት የገለፃችሁልን ወገኖቻችንን ሁሉ ከልብ እያመሰገንን በድጋሚ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
#ምርጫ_2018 | 1 589 |
| 18 | የኢዜማ የሐረሪ ክልል ሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ም/ቤት ዕጩዎች
ኢዜማን ይምረጡ!!
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
#ምርጫ_2018 | 1 300 |
| 19 | መፈፀም የማንችለውን ቃል አንገባም፤ ለገባነው ቃል ተጠያቂ የሚሆን መንግሥት እንገነባለን!!
#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ
#ምርጫ_2018 | 1 675 |
| 20 | لا يوجد نص... | 1 708 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
