Hasen Injamo
Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው:: https://telega.io/c/Haseniye
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Hasen Injamo
Канал Hasen Injamo (@haseniye) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 840 підписників, посідаючи 8 216 місце в категорії Економіка та фінанси та 2 272 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 840 підписників.
За останніми даними від 05 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 101, а за останні 24 години на 9, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 24.94%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 14.09% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 701 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 091 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 43.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“Main focus is Value Based Finance ዋነኛ ትኩረቱ እሴት ተኮር ፋይናንስ ነው::
https://telega.io/c/Haseniye”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 06 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Економіка та фінанси.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 05 липня | +9 | |||
| 04 липня | +2 | |||
| 03 липня | +8 | |||
| 02 липня | 0 | |||
| 01 липня | +3 |
| 2 | ሾፌርም እግረኛም
ሐኪም ቤትን ቢጎበኙ
==============
አሁን አለርት ሆስፒታል ነበርኩ:: አንድ የቤተሰብ ሕጻን ልጅ ትናንትና እግሩን መኪና ገጭቶት እየታከመ ዛሬ ልጠይቅ ሄጄ ለቅሶው ሲረብሸኝ ወጣሁ:: ተመልሼ መሪ እይዛለሁ አላልኩም ነበር:: በእርግጥ ከ20 ዓመታት በላይ መኪና ይዤ አደጋ አድርሼም ደርሶብኝም አላውቅም:: መብራት ላይ ከሗላ ተራ ኩርኩሞች አይጠፉም:: እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ሆኜ እየነዳሁ እንቅልፍ ከተጫጫነኝ ዳገት ላይ ጥላ ቦታ ፈልጌ ናፕ አደርጋለሁ:: ቁልቁለት ጋር ከቆምኩ ፍሬን የጣለ እንዳይወጣብኝ ነው:: ኦሪጅናል ነፍስ ይዤ ጭራሽ ቤተሰብ የምጭንበትን መኪና ስፔር በፍጹም ሎካል አልጠቀምም:: ሹፍርና 360 ዲግሪ ነው:: በ50 እየነዳህ ፍጥነትህ በ300 እንደሆነ አትዘንጋ:: ምክንያቱም በስድስቱም አቅጣጫ አደጋ አምጭ ነገር ሊኖር ይችላል:: በ4 አቅጣጫ የሚመጣ በ50 አብዛው:: 200 ኪሎሜትር በሰዓት ይሆናል:: ከከፍታ ቦታ የሚወድቅ ወይም የሚንከባለል, ኩርባ ላይ የሚቀነጠስ ተሳቢ, ዳገት ላይ የሚንሸራተት ኮንቴይነር ወይም የአጠና ጭነት, ከስር የሚቆረጥ ድልድይ ወይም የሚንሸራተት ገደል ሊገጥም ይችላል:: ከተማ ውስጥ ሁሌ 300 ኪሜ/በሰዓት እንደሆነ ማሰብ የግድ ይላል:: ከከተማ ውጭ በፍጥነትህ አብዛው:: በ80 እየነዳህ ነው ማለት 500 ኪሎሜትር ላይ ነህ::
እና ገና አንድ ፍሬ ጩጬ ልጅ አጥንቶቹ ተሰብረው ስጋው ተቦጭቆ, ገና የአጥንት ሕክምና ላይ ሲሆን ገጪ እስር ቤት, ቤተሰቦቹና ቤተሰባችን ሐኪም ቤት:: ሕጻኑ በለቅሶ ዓይኑ አብጦ ሲያላውሰኝ ወጣሁ:: አለርት emergency 🚨 7 ቁጥር ላይ:: ሕክምና ምን ያህል ክቡር ሥራ እንደሆነ ሆስፒታል ሄዶ ማየት ነው:: ሐኪሞችን አመሰግናለሁ:: ይህንን የምታነቡ ሐኪሞች ሕጻን ሙሐመድ ሳላህን ተንከባከቡትማ! | 1 167 |
| 3 | ፋይናንሻል ሲስተሙ ጨካኝ ነው:: ይዞ የተገኘ እንዲድን ተደርጎ ተዋቅሯል:: ሀብታም ደብ^ዳቢ እና ደሃ ተደብ^ዳቢ ለፍርድ ቢቀርቡ ፍርዱ ግልጽ ነው:: ባልናገረውም ታውቁታላችሁ:: እግር ዘርግታችሁ ተቀምጣችሁ ከጠበቃችሁት ኃይማኖታዊ እምነታችሁ ወይም ባሕላዊ ማንነታችሁ አይቋቋመውም:: እያያችሁት ትፈርሳላችሁ:: ሒጃብና ጺም መስቀልና ማእተብ አያድናችሁም:: ለብር ብላ ሂጃቧን ላለማውለቅ ወይም ከእነመስቀሏ ላለመባለግ ትንሽ ቀናት ብትታገል ነው:: ብር የሚያመጣ ከሆነ ሳታወልቃቸው ልትሸጣቸው ትችላለች:: ጺሙን ላለመላጨት ትንሽ ጊዜ ቢታገል ነው:: ቁርኣን ቢሃፍዝ እንኳ አይችለውም:: ቁርኣኑን እያየው ከልቡ ውስጥ ትቶት እየወጣ አቅም አንሶት ያለቅስ ይሆናል::
ይህንን የምጽፍላችሁ ላስጨንቃችሁ ወይም አጉል መካሪ ለመሆን አይደለም:: እየኖርንበት ያለነው ሲስተም ምን ያህል ከባድ እንደሆነ እኔም ዘግይቼ ነው የገባኝ:: ከ40ና 50 ዓመታት በፊት የገባቸው ሰዎች ለልጆቻቸው ተዘጋጅተውላቸዋል:: ዘና ብለው ሲኖሩና የሆነ የሚያስብላቸው ሰው ወይም መንግሥት ያለ ይመስላቸው የነበሩ ሰዎች ግን በልጆቻቸው ዕድሜ ቀልደዋል:: ዛሬ እነዚያ ልጆች እየኖሩ ያሉት የሕይወት ትግል በቃላት ለመግለጽ አይመችም:: ሲስተሙ ማስያዣ ፈልጓል:: ቤት ያልያዝክለት ልጅ ከሲስተሙ በ50% አርቀኸዋል:: ከተመሳሳይ ቤት ካገባና ልጆች ከደራረበ አረንቋ ውስጥ ወድቋል:: ተሰዶ እንኳ ወደ ሲስተሙ መቀላቀል አይችልም:: ስለዚህ ቆም ብላችሁ አስቡ:: የሲስተሙ ሪኳየርመንት ካጠናችሁ በአስር ዓመት ልትቀላቀሉ ትችላላችሁ:: | 2 250 |
| 4 | ኪሴ ባዶ:- ሲሆን ጸጉሬን ተከርክሜው የተንጨባረረ, አዲስ ጫማ አድርጌ የተንሻፈፈ, ጥሩ መኪና ይዤ እየገፋሁ የምሄድ ይመስለኛል::
ብር ሞላ ያለ ጊዜ ጸጉሬ ተንጨባሮ የተከረከመ, ሁለት የግራ አድርጌ ቢሆን እንኳ አዲስ ብራንድ ጫማ ያደረግሁ, ድክሞ መኪና ይዤ በትእዛዝ የተሰራ ኒች መኪና ይመስለኛል::
መኪና ያለኝ ወቅት ከኃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ቦሌ ድልድይ በእግሬ ሄጃለሁ:: ምንም አልደከመኝም:: መኪና የሌለኝ ወቅት ግን ለማኪያቶ ቅርብ ካፌ መሄድ እንኳ ይደክመኛል::
ዓለምን የሚቀይር ብልሃት የመጣልኝ ወቅት ኬሻ ላይ ቁጭ ብዬ እሠራለሁ:: ምግብ ትዝ አይለኝም:: እራሴን ለመቀየር ብልሃት የጠፋኝ ወቅት በቁርስና በምሳ መሃል መክሰስ መብላት ያምረኛል::
ይህንን ነገር ብዙ ሰዎች ላይ አየሁት:: ለመታየት መከራቸውን የሚበሉ, ውድ ውድ ነገሮችን የሚገዙ ሰዎች ውስጣቸው ላይ የሚታገላቸውና የሚያሯሩጣቸውን ነገር ለማሸነፍ የሚታገሉ እንደሆኑ ነው:: ውስጡ ያለው ረብሻ በዝነጣ ለመሸፈን ይታገላል:: መዘነጥ መልበስ ጥሩ ነው:: ከውስጡ ጋር ትግል የገጠመ ሰው ዝነጣና ታይታ ግን ያስታውቃል::
መሠረታዊ ፍላጎቶቻችንን ብናሟላ አስተሳሰባችን ሁላ ይቀየር ነበር:: ጸቦቻችን ሁሉ ማለት ይቻላል ከለት ጉርስና መሠረታዊ ፍላጎት ጋር የተያያዙ ናቸው:: መኖሪያ ቤት ማግኘት እንደ ሰማይ እያዩት የራቀ ጉዳይ ነው:: እድር እና በራስ ቤት መታወቂያ ማውጣት የሀገሪቷን ግሪን ካርድ እንደ መያዝ ነው:: ሀገር ውስጥ ሆኖ ሀገር የራቀው እልፍ አዕላፍ ምእመን አለ:: | 2 364 |
| 5 | በዚህ ዘመን ስለአምላክም ስለጣዖትም በቀላሉ ለማስረዳት ከገንዘብ የተሻለ ምሳሌ ማግኘት ይከብዳል:: ፈጣሪ አይታይም, አይዳሰስም, አይቀመስም ግን ሁሉንም ነገር ይገዛል:: የኃይማኖት መሪዎች የተለያዩ ምስሎች ቀርጸው ያመልኩታል:: በኪሳቸው ይዘውት ይዞራሉ::
ገንዘብም አይታይም, አይዳሰስም, አይቀመስም:: ግን ሁሉንም ነገር ይገዛል:: የሀገር መሪዎች የተለያዩ ስዕሎች እየሳሉ ለሕዝቡ ሰጥተው በኪሳቸው ይዘውት ይዞራሉ:: ይንከባከቡታል:: በዚህ ዘመን ትልቅዬ ጣዖት የቤንጃሚን ፍራንክሊን ፎቶ ነው::
ፈጣሪን በትክክል define ካላደረግህ የባከነ ሕይወት እንደ ምትመራው ሁሉ ገንዘብንም በትክክል define ካላደረግህ የባከነ ሕይወት ትኖራለህ:: ይህንን በትክክል define ካላደረገ ሰው ጋር መቼም አትግባባም:: | 2 394 |
| 6 | ትምህርት ቤት ጎበዝ ተማሪ ሥራና ሕይወት ላይ የማይሳካለት ትምህርት ቤት ውስጥ አይኮርጅም:: አያስኮርጅም:: ክልክል ነው:: ሥራና ሕይወት ላይ ግን ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በመኮረጅና በማስኮረጅ ነው የምትኖረው:: ኩረጃ በትምህርት ቤት chea^ting ሲባል ሕይወት ላይ ግን cooperation ነው:: ጎበዝ ተማሪ ሆኖ ወጥቶ ሳለ መጠየቅ ያፍራል:: አታውቅም የሚባል ይመስለዋል:: ለዚያም ነው በንግድም በሌላ ሥራም የሚወድቀው:: ስለዚህ ዩኒቨርሲቲ ደሴት ውስጥ ሳትኮርጁ በአሪፍ ውጤት የተመረቃችሁ Welcome to the land of the masses of ኩረጃ! | 2 809 |
| 7 | ቻይና ለመጓዝ ቪዛ የምትጠይቁ ሚመናን በኢ ^ቦላ ምክንያት የአፍሪካ ቪዛዎች ያዝ እየተደረጉ ናቸው:: ፕሮግራማችሁ ላይ ይህንን ከግምት አስገቡ:: ከመደበኛው 10 ቀን እየቆየ ነው:: መልካም ጉዞ! | 2 670 |
| 8 | አሜሪካ ሙ^ስሊሙን ነው በቦ^ምብ የምት^ፈጀው:: ያው ትምህርት ሀራም ነው ብለህ ምርምርን ትተህ ዝም ሊሉህ ነው? የተማረ ማይምን ሁሌ ይወቅጣል:: ያለና የሚኖር ነው:: ወቀጣው ሙስሊም ስለሆንክ አይደለም:: ማይም ስለሆንክ ብቻ ነው:: ምክንያቱም የዕውቀት ደረጃህ ወቀጣውን የመከላከል አቅም የለውም::
በቀላል ምሳሌ:-
አልአሙዲ ዳሽን ባንክን ሲከፍት ሙስሊሙ ሆዬ አልአሙዲ የነካውን ነገር ሁሉ ውሻ የነካው አድርጎ ገጀረ:: ፍልውሐ መስጂድን በሸራተን ጥራት ልሥራው ሲል "አትነጅሰን" ተባለ:: በሗላ ግን ለመጅሊስ ግልበጣ የት ተመረጠ? ሸራተን:: ፍልውሐና ሌሎች መስጂዶችም ጭምር የሚሠራው ማን ሆነ? አልአሙዲ:: ምንድነው ልዩነቱ ካልክ ምእመኑን ድህነት ወቅጦ አሳምኖት ነው:: ድህነት ያሳምናል::
የጌሙ ፕሮግራመር ካልሆንክ የነጻ ርካሽ ጌም ፍለጋ ትባዝናለህ::
አንዳንዱ ስለወለድ እኔን ሊያስጠነቅቅ ሲመጣ እስቅና እቦልከዋለሁ:: ምንም የሚያውቀው ነገር ስለሌለው ችግር እስኪያሳውቀው ትተወዋለህ:: ዞሮ መጥቶ በተማሪ አደብ "ሀጂ እስቲ አስረዳኝ" ይላል::
አንዳንድ ኃይማኖተኛ ባይ የባንክ ብድር-ተራ ማን አድርሶት? ባንኮች ለደሃ አያበድሩም እኮ:: በፍጹም:: አበድሩኝ ስትላቸው እስቲ የንግድህን ትርፍና ቤትህን አሳየን ይሉሃል:: በቃ ትጠፋለህ:: ሲስተሙን ሲዘረጉት ሸሽተህ እና እግርህን ዘርግተህ በቦ^ምብ ሲፈጁህ "ዋ ኢስላማ" ትላለህ:: እዚህ ጋር የምጽፈውን ነገር በታላቅ ስነሥርዓት አንብብ:: ተወያይ:: ጻፍ:: አሠራጭ:: ንቃ:: አንቃ:: | 2 608 |
| 9 | አሜሪካ ሙ^ስሊሙን ነው በቦ^ምብ የምት^ፈጀው:: ያው ትምህርት ሀራም ነው ብለህ ምርምርን ትተህ ዝም ሊሉህ ነው? የተማረ ማይምን ሁሌ ይወቅጣል:: ያለና የሚኖር ነው:: ወቀጣው ሙስሊም ስለሆንክ አይደለም:: ማይም ስለሆንክ ብቻ ነው:: ምክንያቱም የዕውቀት ደረጃህ ወቀጣውን የመከላከል አቅም የለውም::
በቀላል ምሳሌ:-
አልአሙዲ ዳሽን ባንክን ሲከፍት ሙስሊሙ ሆዬ አልአሙዲ የነካውን ነገር ሁሉ ውሻ የነካው አድርጎ ገጀረ:: ፍልውሐ መስጂድን በሸራተን ጥራት ልሥራው ሲል "አትነጅሰን" ተባለ:: በሗላ ግን ለመጅሊስ ግልበጣ የት ተመረጠ? ሸራተን:: ፍልውሐና ሌሎች መስጂዶችም ጭምር የሚሠራው ማን ሆነ? አልአሙዲ:: ምንድነው ልዩነቱ ካልክ ምእመኑን ድህነት ወቅጦ አሳምኖት ነው:: ድህነት ያሳምናል::
የጌሙ ፕሮግራመር ካልሆንክ የነጻ ርካሽ ጌም ፍለጋ ትባዝናለህ::
አንዳንዱ ስለወለድ እኔን ሊያስጠነቅቅ ሲመጣ እስቅና እቦልከዋለሁ:: ምንም የሚያውቀው ነገር ስለሌለው ችግር እስኪያሳውቀው ትተወዋለህ:: ዞሮ መጥቶ በተማሪ አደብ "ሀጂ እስቲ አስረዳኝ" ይላል::
አንዳንድ ኃይማኖተኛ ባይ የባንክ ብድር-ተራ ማን አድርሶት? ባንኮች ለደሃ አያበድሩም እኮ:: በፍጹም:: አበድሩኝ ስትላቸው እስቲ የንግድህን ትርፍና ቤትህን አሳየን ይሉሃል:: በቃ ትጠፋለህ:: ሲስተሙን ሲዘረጉት ሸሽተህ እና እግርህን ዘርግተህ በቦ^ምብ ሲፈጁህ "ዋ ኢስላማ" ትላለህ:: እዚህ ጋር የምጽፈውን ነገር በታላቅ ስነሥርዓት አንብብ:: ተወያይ:: ጻፍ:: አሠራጭ:: ንቃ:: አንቃ:: | 2 317 |
| 10 | ከትልቁ አዋሽ እስከ ታችኞቹ አዳዲስ ባንኮች በሙሉ በብ^ሔርና በኃይማኖት የተዋቀሩ ናቸው:: ይህንን የሚበጥሰው የመንግሥት ግብርናና ኢንደስትሪ ባንኮች ሲመጡ ነው:: ማንም ግለሰብ ከመቶ ሺህ ብር በላይ መያዝም ይሁን ማዘዋወር አይችልም:: ግን ግለሰቦች በባንክነት ከመጡ ግን በቢሊዮን ብሮች ማከማቸና መያዝ እንዲሁም ማዘዋወር ይችላሉ:: ከዚያም ያንን ክምችት ማበደር የሚችሉት ትርፋማ ቢዝነስ እና የሚያዝ ቤት ላለው ዘመዳቸው, ወዳጃቸው, የብሔ^ራቸው ወይም የኃይማኖታቸው ቅርብ ሰው ነው:: የማያውቁት ሰው ፎርማሊቲ ቢያሟላም ይታሻል:: ይህንን አሠራር በፖሊሲ ደረጃ ይዘነው, ሕግና መመሪያ አበጅተንለት ግን ልናድግ እንሟሟታለን:: ታድጊያታለሽ::
በዚሁ ላይ ትላልቅ ታክሶች አሉ:: ታክስ እና ኢንተረስት ቀጥተኛ ግንኙነት ነው ያላቸው:: ብዙ በተበደርክ ቁጥር ትንሽ ታክስ እና ትንሽ ግሽበት ነው የሚነካህ:: በብድሩ ንብረት ትገዛበታለህ:: ወለዱን ለታክስ ማቀናነሻ ወጪ ታደርገዋለህ:: በ20% ወለድ እና ወርሃዊ አከፋፈል የተበደረ ሰው ትክክለኛ ወለዱ 11% ነው:: የትም ባንክ ብትሄዱ ይኸው ነው:: በ20% ተበደርክ ማለት አሞርታይዝ ስለሚደረግ 11% ትከፍላለህ:: ወለዱ ገቢዎች ላይ እንደ ወጪ ስለሚያዝልህ ወደ 7% ይወርዳል:: መቶ ሚሊዮን ብር የተበደረ ድርጅት የሚከፍለው ወለድ 7% ነው:: መ-ገንዘብን ስታነቡ በደንብ ይገባችሗል:: ከዚህ አሠራር እንውጣ ብንል IMF አይሰጠንም:: ከIMF እንውጣ ብንል "ዲሞክራሲ ያስፈልጋል" ብለው ድፍን ሀገራችንን በቦ^ምብ ያስጋዩታል:: ለዚህ የተዘጋጀ ጀማዓ አላቸው::
የመጀመሪያው መፍትሔ ከመደበኛ ትምህርት ቦርሳ ውስጥ ወጥቶ ማሰብ ነው:: | 2 459 |
| 11 | በሀገራችን መሬት የመንግሥት ነው:: ከዚያ ግን ኢኮኖሚክስ ተምሬያለሁ የሚለውም መንግሥትም ቤት የማቅረብ እና በርካሽ ዋጋ የማከራየት ኃላፊነት የግለሰቦች ነው ብለው ያምናሉ::
ብዙ ሕዝብ ያለበት ሀገር ሶሻሊዝም የግድ ነው:: ካፒታሊዝም የካፒታል ፒራሚድ ነው የሚሠራው:: አንድ ቀን በነጋ ቁጥር የሀብታምና የድሃ ክፍተት እየሠፋ ይሄዳል:: የካፒታል ውድድር የማያባራ ሩጫ ውስጥ ይከታል:: በለት ተለት የሚፈለጉ መሠረታዊ ፍላጎቶች ቅንጦትና የጭቆና ምንጭ ይሆናሉ:: ስለዚህ እነዚህን በፍጹም ለግሉ ሴክተር አለመተው ነው:: መድኃኒት ለግሉ ሴክተር ከተተወ ከመድኃኒት ይልቅ በሽታ ይመረታል:: ሕዝቡ መድኃኒት ቃሚ ሆኖ ይኖራል::
ቤት ሁሌ አስፈላጊ ነው:: መሬትን አንቆ መያዝ ቤትን አስወድዷል:: መሬትን የያዘ ክፍል ቤት ግዴታው ነው:: የቤት ባሕሪው ብዙ ካፒታል ስለሚልግ እና Payback period ከ20 ዓመት በላይ ስለሚሆን ግለሰቦች አይችሉትም:: ቤትን በማከራየት ዋጋውን በ5 ዓመት መመለስ አይቻልም:: ግለሰብ መቶ ሚሊዮን እና ቢሊዮን ብር አውጥቶ ገንብቶ 30 ዓመት ሊጠብቅ አይችልም:: ያወጣውን ለመመለስ የግድ በውድ መሸጥ አለበት:: ቤት በውድ መሸጥ ማለት ከግሽበት ውጭ ሌላ ምክንያት የለውም:: ቤቱ እያረጀ, ወደላይ ሳያድግ, ወደ ጎን ሳይሰፋ, ኩሽና ሳይወልድ በውድ የሚሸጠው የዲማንድ ጋፕ ወይም ግሽበት ነው:: ይህ በግለሰብ በፍጹም የማይሳካ ሴክተር ነው:: ቻይና ቤት 96% አዳርሳለች:: ሕዝቡ ስለሥራ እንጂ ስለቤት አያስብም:: እኛ ሀገር የቤትና የመሬት ጉዳይ ግልጽ ነገር የለውም:: መሬት የባለሥልጣናት ሀብት ከሆነ 30 ዓመታት አልፎታል:: | 2 586 |
| 12 | ከተወሰኑ ቀናት ዠምሮ ሁሉም ስልኮቼ ስግ ናቸው:: እራሴን ከምዘጋ ብዬ ስልኮቼን ዘግቼ ነው:: ከሰሞኑ ወደ አየር እመለሳለሁ:: (እና ምን አገባን? የሚል ምእመን መብቱ ነው):: | 2 802 |
| 13 | መ-ገንዘብ 2 መጽሓፍ የጠያቂ ቁጥር በግሌ ላስተናግደው ከምችለው በላይ ነው:: 4ኛ 5ኛ ወዘተኛ እትም የግድ እንደሚል ግድ ሆኗል:: ያሰላም ጊዜ ከየት ይምጣ? የባለፈው ሥርጭት ጊዜዬን እኝክ አድርጎ በላው:: አክብሮህ ለከፈለ ሰው ደግሞ ማክበር የግድ ነው:: መጽሐፍ ገዢዎች እንዴት እንደተባበሩኝ ሳስበው:: መልስ ሳልሰጣቸው እቆያለሁ:: ምንም አይበሳጩም:: ችግሬ Active ቴሌግራም ብቻ 4 አሉኝ:: በአራቱም በሺህ የሚቆጠር መሴጅ ይገባል:: ለሁሉም መልስ መስጠት አለብኝ:: መልስ ላልሰጥ ከከፈትኩት ኻላስ! ሄደ ወደ ተነበበው ሄደ!
በዚህ ላይ
መ-ገንዘብ የልጆች ቨርዥን እየሠራሁ ነው:: የጽሑፍ ሥራ ከፍተኛ ኮንሰንትሬሽን ይፈልጋል:: በዚያ ላይ ለኤዲት ለልጆች ሰጥቼ እያነበቡት ቆዩ:: ከ12 ዓመት በላይ ብዬ ያዘጋጀሁት ግን ስንገመግመው ከ16 ዓመት በላይ ሆነብኝ:: ለካ ለአዋቂ መጻፍ ቀላል ነው:: አባባ ተስፋዬ አጉል ጊዜ ቀድመው ሞ^ቱ:: አሁን ያስፈልጉኝ ነበር::
በባለፉት መጻሕፍት እስከ ማስትሬት ያልተማርነውን ነው የጻፍኩት:: ልጆች ጋር ሳይ አሁንም እየተማሩት አይደለም:: ግን የሞት ሽረት ዕውቀት ነው:: ብቻ ማተሚያ ቤት ደጃፍ ላይ ነኝ::
በባለፈው ያልወሰዳችሁ ጥቂት ምእመናን ከሰሞኑ ትወስዳላችሁ::
የሕጻናት ቨርዥን ስርጭት ግን ሰው ይመደባል:: | 3 286 |
| 14 | ይህ ደግሞ ጉድ ያለው ዜና ነው:: ከእኛ የሚጠበቀው የትኛውንም የማዕድን ስምምነት በዶላር አለማድረግ ነው:: ካልሆነ ግን የልጅ ልጆቻችንም ከድህነት አይወጡም:: አስረዳን የምትሉ ባለሥልጣናት ቀጠሮ ያዙ:: | 3 364 |
| 15 | ስለገንዘብ በጻፍኩ ቁጥር የማስታውሳቸው ሰው አጼ ምኒልክ አንዱና ዋነኛው ናቸው:: 1896 ላይ ነጻነታችንን ብናስከብርም ከአድዋ ድል 48 ዓመታት በሗላ 1944 ላይ ግን በቅኝ ግዛት ስር ገብተናል:: በዚህ ወቅት ቢኖሩ ኖሮ የብሬተን ውድስን ስምምነት ይፈርማሉ ተብሎ አይታሰብም:: ነጻነታችንን ታሳቢ በማድረግ 1944 ላይ በልዩ ክብር (VIP) ተጠርተን ግን የአሜሪካን ዶላርን የዓለም መገበያያ የሚያደርገው ስብሰባ ላይ የወከልናቸው አሜሪካውያን ነበሩ:: የሚያስቀው ዛሬም ላይ ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ የምንማረው በአሜሪካ መጻሕፍት ለያውም እንደወረደ መሆኑ ነው:: ከድንበር የማይወጣ ብር ይዘን በዶላር ቦታ ተክተን ሀገራዊ ጥናት እንሠራለን:: እከክ በእከክ ሆንን:: | 3 509 |
| 16 | Немає тексту... | 4 436 |
| 17 | ዜናው:- ዶላር ጉዱ ፈላ ይላል
ወዴት ነው የሚፈላው?
===============
በእርግጥ ባለበት የማይቀየር ፈጣሪ ብቻ ነው:: ዶላር የሆነ ወቅት ጉዱ መፍላቱ አይቀርም:: ጀምሮታል:: ግን በጣኣኣኣኣኣም ሩቅ ነው::
ይህንን የምንመልሰው በማቲማቲክስ ነው:: ምላሹ ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ ለተማረም ላልተማረም በሚገባ መንገድ ይቀርባል።
ኢትዮጵያ 1 ቢሊዮን ብር አትማ ከናይሮቢ ዕቃ ብትገዛ... ብሩ ናይሮቢ ውስጥ ምንም ስለማይሠራ ኬንያውያን መልሰው አዲስ አበባ ይዘውት መጥተው እቃ ይገዙበታል። 1 ቢሊዮን ብራችን ሄደ፤ 1 ቢሊዮን ብራችን መልሶ መጣ፤ ስለዚህ ተጣፋ። ኬንያውያንም ሽሊንግ ይዘው መጥተው እቃ ገዝተው ቢሄዱ፣ እኛም ሽልንጋቸውን ይዘን ሄደን እቃ ገዝተን እንመጣለን። ሁሉም የየራሱን መገበያያ እየያዘ ድንበር ቢያቋርጥ ኖሮ ንግዱ "ውኃ ቅዳ ውኃ መልስ" በሆነ ነበር።
ሒሳቡ (ማትሱ) የሚጀምረው እዚህ ጋር ነው፦ የአሜሪካ ዶላር ከድንበር ይወጣና እቃ ይዞላት ይመጣል። መልሶ ግን ወዲያው አሜሪካ ገብቶ እቃ ይዞ እንዳይወጣ ስሌት መሥራት እና ይህንን ሁሉ የገንዘብ ፍሰት ማኔጅ ማድረግ አለባት። ጨዋታው ማቲማቲክስ ላይ ነው (ትራዲሽናል ኢኮኖሚክስ በደንብ አይፈታውም፣ ፍላጎቱ ያላቸው Triffin Dilemma የሚለውን ጽንሰ-ሀሳብ ማንበብ ይችላሉ)።
ለመሆኑ ከአሜሪካ የወጣው ዶላር ወዲያው ተመልሶ እንዳይገባ ምን ይደረጋል? ውድ ውድ እቃ ወደ አሜሪካ ስለሚገባ አሜሪካ ውስጥ መግዛት አያዋጣም። ዶላር ጠንካራ ስለሚሆን ማምረቻም ውድ ነው:: ስለዚህ ዓለም ዶላሩን ይዞ ቻይና ይሄዳል። ከዚያ በርካሽ ይገዛበታል። ቻይና ደግሞ ዶላር በሀገሯ ውስጥ ምንም ስለማይሠራ ለደሃ ሀገራት ታበድረዋለች፤ አልያም ውጭ ሀገር ሄዳ ኢንቨስት ታደርገዋለች። በምትኩ ከውጭ ሀገር ዶላር ሳይሆን ጥሬ እቃ (ማዕድን) ይዛ ትገባለች። ጥሬ እቃውን እያቀለጠች መልሳ እቃ አምርታ ትሸጣለች። የራሷን እቃ በራሷ ዩዋን (Yuan) መሸጥ ግን አያዋጣትም፤ የገንዘቧ ዋጋ ከፍ ሲል ምርቷ ውድ ስለሚሆን ይጥላታል። ለዚህም ነው እኛ ብራችንን እንድናረክስ (Devalue እንድናደርግ) ስንገደድ፣ ቻይና ደግሞ በተቃራኒው ዩዋንን እንድታጠናክር ጫና የሚደረግባት። ጉዳዩ ማቲማቲክስ ነዋ!
"ታዲያ ተመልሶ አሜሪካ የገባው ዶላርስ ምን ይሆናል?" ከተባለ በሁለት መልኩ ይቃጠላል። አንደኛው በእሳት... ሁለተኛው ደግሞ በኢንተረስት (ወለድ)፣ በታክስና እዚያው በአሜሪካ ገበያ በመበላት ይቃጠላል። እዚህ ጋር ልብ በሉ፦ ታክስ ለአሜሪካ መንግሥት የሚከማች ገቢ ሳይሆን፣ በገበያው ውስጥ የተረፉ ትርፍ ዶላሮችን ማቃጠያ ምድጃ ነው።
ከብዙዎች ጋር ቶሎ የማንግባባው ለዚህ ነው። እኛ በአሜሪካ መጻሕፍት ተምረን የእነሱን የታክስ ፖሊሲ ስንኮርጅ፣ ያንን አውዳሚ ምድጃ አብረን እንደኮረጅን አናስተውልም። በዚህ በተሳሳተ መንገድ ታክስን በሰበሰብን ቁጥር የሥራ እንቅስቃሴን ገድበን ሙስናን ነው የምንጨምረው። ይህ ሃሳብ ትንሽ ጠጠር ማለቱ ስለማይቀር በቅርቡ በቪዲዮ በሰፊው ይዤው እመጣለሁ።
ስናጠቃልል:- ቻይና ዶላርን በዩዋን ልተካ ካለች ብዙ ፈንጂዎችን ትረግጣለች። ሚሊቴሪዋ እጅግ ጠንካራ መሆን የግድ ይለዋል። በዶላር የተዋዋለቻቸውን ብድሮች በሙሉ በእቃ (በማዕድን) ማስፈረም ይጠበቅባታል። ካልሆነ ለማያቋርጥ ጸ^ብ እና ጦ^ርነት እራሷን ማዘጋጀት አለባት:: ምክንያቱም አሜሪካ የምትዋ^ጋው ለግዛት ሳይሆን ለፋይናንስ ሥርዓቷ ማረጋጊያ ጭምር ነው። እኛም ደሃዎቹና ማይማን ሀገራት መሞ^ት ይጠበቅብናል:: ባይሆን ለምንሞ^ትለት ጉዳይ አስቀድመን ሒሳብ (ማትስ) መሥራት አለብን:: 1944 ላይ ዶላር ይምራ ብሎ የፈረመ ሀገር በቀላሉ የማይወጣው ቅርቃር ውስጥ ገብቷል:: እዚህ ጋር የምጽፈውን ነገር እና መሰል ትምህርቶች በየቦታው መውሰድ አለብን::
(መ-ገንዘብን ያነበበ ይበራለታል) | 3 940 |
| 18 | ትምህርት አያስፈልግም እያስባለ ያለው ድህነት ነው:: ምክንያቱም እየተማርንበት ያለነው ካሪኩለም ድህነትን ከሀገር እንዴት እንደምናባርር አያሳይም:: ሀገርም መንግሥትም ደሃ ሆኖ አንተ በየት በኩል ልትከብር ነው? መፍትሔው አለመማር ሳይሆን ያልተማርነውን ጨምረን በመማር ብቻ ነው:: ካልተማርክማ ሌላውን ተወውና ዳቦ ለመግዛት በቴሌብር ማን ሊከፍልልህን ነው?
ምን እንማር?
1ኛ) የቀለም ትምህርት
2ኛ) የልምድና የሙያ ትምህርት
3ኛ) የፋይናንስ ትምህርት
የፋይናንስ ትምህርት መማር ያለባቸው የአካውንቲንግና ፋይናንስ ተማሪዎችም ጭምር ነው:: ኮሌጆች ውስጥ የሚማሩት የቀለም አካውንቲንግና ፋይናንስ ነው:: አብዛኞቹ ደሃ ናቸው:: ብር ሲቆጥር ከሚውል የባንክ ሠራተኛና ኮብልስቶን አንጣፊ ይሻለዋል:: አብዛኞቹ ባንከሮች ሲስተሙ እንዴት እንደሚሠራ የእኔን መጽሓፍ ነው የሚያነቡት:: ከሚልኩልኝ ምስጋና በመነሳት ነው:: ኢኮኖሚክስ ስለተማር ስለኢኮኖሚ ታውቃለህ አይባልም:: የግድ የፋይናንስ ዕውቀት ሊኖርህ ይገባል:: ካልሆነ ሀገርንም ጭምር ትገ^ድላለህ:: በዶላር ቦታ ከሞያሌ የማያልፍ ብር ተክተህ ብትጠበብ ሀገር ታበላሻለህ:: የእነርሱ ዶላር ካፒታል K ከየትም ሀገር ይገዛል:: የእኛ ብር ግን Capital K መሆን አይችልም:: ስለዚህ ይህንን ቫሪያብል ዜሮ ሲሆንብህ ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል አስበው:: | 3 698 |
| 19 | አንድ ሀገር ውስጥ ታክስ ካለ ... የሚያበድር ካለ ... የድርጅታችሁን የሀብት መዋቅር 100% ብድር አድርጉት ይላሉ ባለኖቤሎቹ ሞጂሊያኒ እና ሚለር:: ሙሉ ለሙሉ በሞኝ ቆጣቢዎች ብር ሥሩ እንደማለት ነው:: ብዙ ምሁራን የአሜሪካና እንግሊዝን መጽሓፍ አንብበው ይሸወዳሉ:: በአክሲዮን የሚታደግና ትልቅቅቅቅዬ ኩባንያ የሚቋቋም ይመስላቸዋል:: እስቲ ሀገራችን ውስጥ ካሉ ትላልቅ ኩባንያዎች ምን ያህሉ አክሲዮን ናቸው? ብትል አንድ ብለህ ለመቁጠር ትቸገራለህ:: የሉም:: ባንኮች እንኳ የግድ ሆኖባቸው, ብሔራዊ ባንክ ከላይ እየተቆጣጠራቸው, የሕዝቡ ሁሉ ብር እነርሱ ጋር እየተቀመጠ, ለ22 ሺህ ሆነው ከፍተው, 5 ቢሊዮን ብር ለመሙላት መከራቸውን ይበላሉ:: እዚህ ጋር ሲደርሱ ይደግሳሉ ሁላ:: ወንድሜ ሁለት ባልና ሚስት የከፈቱዋቸው ፋብሪካዎች በቢሊዮን ብር ይተመናሉ:: ለ22 ሺህ ሆነህ የከፈትከው አክሲዮን ትርፍ ሲያመጣ ለ22 ሺህ ሆነህ ነው የምትካፈለው:: ሁሉንም ታክስ ተቆርጦለት ትርፍ ስትከፋፈል ሁላ 15% ዲቪደንድ ታክስ አለው:: ፍኖተ ካርታውን በመ-ገንዘብ 2 ቁልጭ ብሏል:: ገንዘቡ እራሱ እዳ (credit) ነው:: Credit ሌላው ስሙ debt ነው:: Debit እንዳታምታታ:: በጣም የተለያዩ ናቸው:: እና ዋናው ብሔራዊ ባንክ ብር ነው ብሎህ ቁጥር ያለው ቦኖ ነው የሚያትመው:: ጭራሽ ቦኖ የማያትም ንግድ ባንክ ከየት ያመጣል? ሁለቱም ባንኮች ገንዘብ የላቸውም:: እዳ (debt) ነው የሚያጫውቱት:: ስለዚህ አክሲዮን እያልክ ከምትሟዘዝ እንደ ካፒታሊስቱ debtን አጫውት:: ትንሽ ታክስ ከመክፈል legally ምንም ታክስ ወደ አለመክፈል የሚያሻግረው ብቸኛው መንገድ በእዳ መነገድ ነው:: መንገዱ አስማት ነው ስልህ! | 3 637 |
| 20 | ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ችግር አለ ማለት ብዙ ሥራ አለ ማለት ነው:: ጦ^ርነት አለ ማለት ሌላው ይቅና ጥ^ይት በደንብ ይሸጣል:: ማስታረቅ እራሱን የቻለ ቢዝነስ ነው:: ዳቦ ተወደደ ማለት የስንዴ እጥረት አለ:: በቀጭን ምሳሌ ቤት ሲቀየር ጫኝና አውራጅ ካስቸገረ የፓኪንግ ኤንድ ሙቪንግ ሥራ ተከፍቶልሃል:: ችግር ካለ ችግር ብቻ አታውራ:: በእርግጥ ችግርም ማውራት ቢዝነስ ነው:: የገቢ እናቱም አጎቱም ችግር ናቸው::
መጽሓፍ አሳትሞ መደህየት ትልቅ ችግር ነበር:: እኔ ቅድመ ሕትመት በፖስታ ቤት ጀመርኩት:: በአራት ዓመት የማያልቅ ጣጣ በአራት ወር ጥንቅቅ አድርጌ ጭጭ አደረግሁት:: ሽሽት አያዋጣም::
ወንድ ልጅ እንዴት ገቢዎችን ፈርቶ ፈቃድ ይመልሳል? መባጠስ ነው እንጂ! እነርሱ ሲያስቸግሩ ኮራ^ፕሽን ይጦፋል:: ይህ ደግሞ በአቋራጭ ከባሪ ድግሱ ነው:: ገቢዎች አሪፍ ከሆኑማ ምኑን ነገድከው? | 4 174 |
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
