ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
Канал ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (@ethiobooks) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 10 269 підписників, посідаючи 3 708 місце в категорії Книги та 3 245 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 10 269 підписників.
За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 14, а за останні 24 години на 9, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 11.21%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 3.16% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 151 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 324 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 6.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Книги.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 09 липня | +1 | |||
| 08 липня | +9 | |||
| 07 липня | +2 | |||
| 06 липня | +3 | |||
| 05 липня | +6 | |||
| 04 липня | +1 | |||
| 03 липня | +2 | |||
| 02 липня | +6 | |||
| 01 липня | +4 |
| 2 | sticker.webp | 94 |
| 3 | 💿 ጋዜጠኛው 💿
══•══
🎤 ቴዎድሮስ ሞሲሳ
@ethiobooks
🎼🎵🎶🎵🎶🎵
ዓለም እንዴት አደርሽ እንደምን ከርመሻል
ረጋ ሰከን አልሽ ወይ ነውጡ ብሶብሻል
የነማን ቤት ቀና የነማን ፈረሰ
የት ቤት ፌሽታው ደራ የቱስ ማቅ ለበሰ
የምንሰማው ነቅተን የየዕለት ታሪክሽን
አጀብ የሚያሰኘው ጓዳ ጎድጓዳሽን
አሳምሮ 'ሚያቀርብ ክቡር ሰው መለኛ
ባይፈጠር ኖሮ ዕንቁ ጋዜጠኛ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
🎶🎶🎶
የቢሮክራቱን ግልምጫ
የባለስልጣኑን ጡጫ
የአድማ በታኙንም ዱላ
ቆሞ የሚጋፈጥ ተሟጋች
ሲሮጥ ሲወድቅ በየጎራው
አጋች ይዞ ሲያንገላታው
በበረሃ ረሃብ ሲቀጣው
አዛኝ የለው አይ ፈተናው
🎵🎶🎵🎶🎵
ከጦር ሜዳም አይቀር ነጉዷል ጓዜን ብሎ
ፍልሚያው መሀል ያድራል ድንኳን ቢጤ ተክሎ
ለዓለም ሕዝብ ሲደክም ምኑን አስተውሎ
ከእሳት ይማገዳል ልጅ ትዳሩን ጥሎ
የምድር ምስቅልቅል ምንጊዜም ላይጠራ
በቃኝ ማለት አውቆ ሰው ለሰው ላይራራ
እንባ ደም መፍሰሱ ላይገታ እሮሮ
መባከንህ ቆጨኝ ከፋኝ ያንተ ኑሮ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
🎶🎶🎶
የሹምሽሩን ትኩስ ዜና
የአዛዥ ታዛዡን ገመና
የፋሽን ኳስ የዘፈኑን
የጎርፍ የርዕደት ናዳውን
የምዕራብ ጥጋብ ቅብጠቱን
የአፍሪካን ረሃብ ጉዳቱን
ያ'ለምን ቀውስ ውጥንቅጡን
ይፋ አድራጊ ዘጋቢ ሁሉን
የባለ ፀጋ ምቾቱን
የድሃን ማጀት ምሬቱን
የንጉሥ እልፍኝ ምስጢሩን
በርብሮ የሚያሳየኝ ውስጡን
ፀሐይ ሳይመታኝ ሆኜ ቤቴ
ሁሉን መቃኛ መስኮቴ
ልቤ ከልብ ያከብርሃል
በ'ውነት ገብተሃል ካ'ንጀቴ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው...||
🎶🎵🎶
@ethiobooks | 361 |
| 4 | Немає тексту... | 360 |
| 5 | sticker.webp | 347 |
| 6 | #ዳሪዮስ_ሞዲ
“ለረጅም ዓመታት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ሲካሄድ የነበረው የርስ በርስ ጦርነት ያስከተለውን የኢትዮጵያዊያን ሕይወት መጥፋትና ከኑሮ መፈናቀል ለማስቀረት በልዩ ልዩ መልክ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል። ሆኖም ችግሩ ሊቃለል አልቻለም። ይልቁንም ወደ ባሰ ደረጃ እየተሸጋገረ በመሄድ ላይ ይገኛል።
ስለዚህ ደም መፋሰስ እንዲቆምና ሰላምም እንዲሰፍን በልዩ ልዩ ወገኖች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ከስልጣን መውረዳቸው እንደሚበጅ የታመነበት ስለሆነ፣ ይህንኑ በማመዛዘን ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ከሥልጣናቸው ወርደው ከኢትዮጵያ ውጪ ሄደዋል።”
ይህ ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም. የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ከሀገር መውጣት የተገለፀበት መግለጫ ነው። በብዙዎች ጆሮና እዝነ ልቡና እስከ አሁንም የማይጠፋ ሆኖ ተቀርጿል። አንባቢው ደግሞ ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ።
ጋዜጠኛ ዳሪዮስ ሞዲ ለሬዲዮ የተፈጠረ፣ ተሰምቶ የማይጠገብ፣ እያነበበ ድምፁ የሚስረቀረቅ፣ የሬዲዮ ሞገድን የሚገዛ፣ ከዜና ባህሪው ተነስቶ አነባነቡን የሚከተል እንከን አልባ ዜና አንባቢ እና ጋዜጠኛ ነበር።
በትውልድ ፐርሺያዊ በዜግነት እንግሊዛዊ ከሆኑት ከአባቱ ከሚስተር ሞዲ ጉስታቭ እና ከእናቱ ከወይዘሮ አማረች መኩሪያ ታህሳስ 12 ቀን 1939 ዓ.ም. ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ አካባቢ ነው የተወለደው።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለው እንግሊዝ ትምህርት ቤት ሲሆን፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ነበር።
በመቀጠልም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርቱን በ"Political Science" መከታተል ቢጀምርም በወቅቱ በነበረው የተማሪዎች ንቅናቄ ሳቢያ የቅርብ ጓደኛውና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት የነበረው ጥላሁን ግዛው መገደልን ተከትሎ ትምህርቱን አቋርጦ ወጣ። ዘመኑም 1962 ዓ.ም. ነበር።
በወቅቱ በነበረው መንግሥት አመለካከቱ ያልተወደደለት ዳሪዮስ፣ ለሁለት ዓመታት ያህል ሥራ ለመቀጠር ባይችልም በግሉ የትርጉም ሥራዎችን ይሠራ ስለነበር በ1964 ዓ.ም. በብስራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያ ለመቀጠር ምክንያት ሆነው።
በብስራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያ የጀመረው የሬዲዮ ጋዜጠኝነት ሕይወቱ በኢትዮጵያ ሬዲዮ እስከ 1980ዎቹ መገባደጃ ድረስ በዜና አንባቢነት እና በፕሮግራም አዘጋጅነት የቀጠለ ሲሆን፣ ጡረታ እስከወጣበት 1994 ዓ.ም. ድረስ ያገለገለው በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የውጭ ቋንቋ ዴስክ ነበር።
ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ በተለይ የውጭ ቋንቋዎችንና ቃላትን በአማርኛ አቻ ትርጉም በመፍጠር የሕዝብ ቋንቋ ማድረግ የቻለ፣ የቋንቋ ምሁራንም ደግመው ደጋግመው የሚመሰክሩለት የትርጉም መምህር ነበር። አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ እንግሊዝኛ፣ ጀርመንኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣልያንኛ የመተርጎም ብቃቱም የመነጨው ካልተቋረጠ የንባብ ብቃቱ ነው።
ከቀደሙ የሙያ አባቶቹ ከእነ አሃዱ ሳቡሬ እና አሠፋ ይርጉ ብዙ እንደተማረ ሁሉ እሱም ያገኘውን ለራሱ ሳያስቀር ለተተኪዎቹ በማስተማር ምሳሌ መሆን የቻለ ድንቅ ጋዜጠኛ እንደነበር ብዙዎች ይመሰክሩለታል።
የዳሪዮስ ሞዲ የጋዜጠኛነት ሕይወት ለ30 ዓመታት ቢቀጥልም ይከፈለው የነበረው ደመወዝ የእርሱን አስደናቂ ችሎታና የሙያ ልቀት የሚመጥን ቀርቶ ለወር አስቤዛ የማይበቃ ነበር። ወር ጠብቆ በሚያገኘው አነስተኛ ደመወዝ ራሱን እና ቤተሰቡን ለማስተዳደር ቢቸገርም ያን ወርቃማ ድምፁን ለገንዘብ ማግኛነት ለማዋልና፣ ማስታወቂያ ሊሠራበት ፈቃደኛ አልነበረም።
"ዜና ላይ የሚሰማ ድምፅ እንዴት ሆኖ ሸቀጥ ይተዋወቅበታል? ይህ በራሱ የሙያውን ሥነ-ምግባር መጣስ ነው!"
ሲል ለሙያው መርህ እና ልዕልና አጥብቆ ይከራከራል። ይህን አቋሙንም እስከ ሕይወቱ ፍፃሜ ድረስ ሳይለውጥ ቆይቷል።
ለዳርዮስ በተለይ የመጨረሻዎቹ ሦስት ዓመታት ጥሩ አልነበሩም። ለዘመናት ማልዶ ከሥራ ገበታው የማይታጣው ዳሪዮስ ሕመም ደጋገመው። እንደ ልብ መተንፈስ ስለተሳነው በኦክሲጅን እየተረዳም ቆይቷል።
ባለትዳርና የሰባት ልጆች አባት የነበረው ዕንቁው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ሰኔ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ሕይወቱ አልፏል። የቀብር ሥነ-ሥርዓቱም ሰኔ 14 ቀን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በፈረንሳይ ጉራራ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተፈጽሟል።
━━━━━━━━━━━━
ምንጭ ➢ ዊኪፔዲያ እና ሌሎች
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 559 |
| 7 | ━━ ጋዜጠኛ ዳሪዮስ ሞዲ ━━
1939 - 2007
@ethiobooks | 486 |
| 8 | sticker.webp | 447 |
| 9 | ╔══ 💚💛♥️ ══╗
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
👉 የደራሲያን፣ ገጣሚያን፣ ከያኒያን እና የተለያዩ ግለሰቦች የሕይወት ታሪክና ሥራዎች፤
👉 ወጎች፣
👉 ግጥሞች፣
👉 ልብ ወለዶች፣
👉 የፍልስፍናና የስነ-ልቡና ፅሁፎች፣
👉 ተረትና ምሳሌዎች
«ነገር በምሳሌ»
👉 ተረኮች
"የቅዳሜ ተረክ"
👉 የዘፈን ግጥሞች
(ከሙዚቃ ጋር)
👉 ጥቅሶች
(ከታዋቂ ሰዎች እንደበት)
እና ልዩ ልዩ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል
❤️ ከስነ-ፅሁፍ ዓለም ❤ ️
ቻናላችንን
👇👇👇
https://t.me/Ethiobooks
ለወዳጅ ጓደኞችዎ 'share' ያድርጉ።
📖 📖 📖 📖 📖
ለማንኛውም አስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ን ተጠቀሙ።
በአክብሮት እንቀበላለን።
🙏 አብረን እንዝለቅ። 🙏
@ethiobooks
╚═══💚💛♥️═══╝ | 569 |
| 10 | sticker.webp | 507 |
| 11 | ንጉሥ ፋይሳል አብዱልአዚዝ - 2 የመጨረሻው! | 816 |
| 12 | ንጉሥ ፋይሳል አብዱልአዚዝ - 1 | 804 |
| 13 | ▶ ንጉሥ ፋይሳል አብዱልአዚዝ
━━━━━━━━━
«መ ለ ኛ ው ን ጉ ሥ»
@ethiobooks | 783 |
| 14 | sticker.webp | 697 |
| 15 | 📔 ርዕስ የለውም
፷፰
═══════
ደስ ባለሽ ቀን ነይ፤ ነይ ደስ ባለሽ ቀን፤
ተፈጥሮ ይሰበር፤ ዶፍ ሰኔ ይሙቀን።
አቦ!
ነይልኝ ዝም እንዳልሽ፤ ወረኛን ስበሪው፤
ዙፋን ሰልችቶታል፤ አፍቃሪሽን ምሪው።
አቦ!
ነይ ደስ ባለሽ ቀን፤ በፈለግሽው ሰዓት፤
አንቺ የኔ ጸሎት፤ የጠላቴ መዓት።
ከየትም አልሄድኩም፤ መጠበቅ አርቆኝ፤
በተፋቀርንበት ጊዜ ቀርቻለሁ፤ ናፍቆትሽ አጣብቆኝ፤
ወገን ተሰብስቦ፤ ሂድ ቢለኝም እንኳ፤ አልሄድም የምለው፤
ድንገት የሄድኩ ቀን፤ ብትመጪ ብዬ ነው።
ነይ ደስ ባለሽ ቀን!
═══════
✍ ኤልያስ ሽታኹን
🗓 ፳፻፲፫ ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 935 |
| 16 | sticker.webp | 737 |
| 17 | 📔 ሲ ቫ ና
📖 📖 📖
«የሕይወትህን ጉዞ በጊዜ ሰሌዳ ብቻ ቀፍድደህ አትያዘው፤ በዚህ ፋንታ ህሊናህና ልብህ የሚያምኑበት ነገሮች ላይ አትኩሮትህን አድርግ። በራስህ ላይ ስትዘምት አዕምሮህንና አካልህን የተሻሉ እንዲሆኑ ከልብህ ስትጥር፤ ከውስጥህ አንድ አቅጣጫ ጠቋሚ ነገር እንዳለ እየተረዳህ ትመጣለህ። በእጅህ ላይ ስላለው የእጅ የሰዓት መቁጠሪያ መጨነቁን ታቆምና ሕይወትህን ማጣጣም ትጀምራለህ።»
📖 📖 📖
«ሁልጊዜም አንብብ። በቀን ለ30 ደቂቃዎች ማንበብ በአስተሳሰብህ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ይፈጥራል። ቢሆንም ግን አንድ ነገር ላስጠነቅቅህ ግድ ይለኛል። ያገኘኸውን ሁሉ አታንብብ። በውበት በተሸለመው የአዕምሮህ አፀድ ውስጥ ስለምታስቀምጣቸው ነገሮች በጥንቃቄ ማሰብ አለብህ። የአንተን ማንነትና ብሎም የሕይወትህን እርከን የሚያሻሽል ሊሆን ይገባል።»
📖 📖 📖
«የምትችለውን ያህል መጻሐፍት አታንብብ ብዬ አልመክርህም። ሆኖም ዘወትር ማስታወስ ያለብህ፤ አንዳንድ መጻሐፍት የሚቀመሱ ሲሆኑ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ የሚታኘኩ ናቸው፤ ሌሎቹ ተላምጠው የሚዋጡ ናቸው። ልነግርህ የምፈልገው ቢኖር ታላላቅ መጻሕፍት ውስጥ ያለውን ጭብጥ ለማግኘት ማንበብህ ብቻ በቂ አለመሆኑን ነው። መጻሕፍቱን መርምረህ ልታጠና ይገባል።»
📖 📖 📖
«በሕይወት ዘመንህ ሁሉ ለገጠሙህ ጥያቄዎች ምላሽ በመጻሕፍት ውስጥ ተቀምጦ ታትሞ ይገኛል። በማንነትህ ውስጥ የሚያስደስት ልዩነትን ይፈጥራል። ያኔ በውስጥህ አንተን ለማገልገል የተቀመጠውን የዕውቀት ክምችት በጨረፍታ ማየት ትጀምራለህ። ከቀድሞው የተሻልክ ለመሆን፣ ወደ መልካም ስብዕናዎች መዳረሻ የሚያስወነጭፉህ መጻሕፍት ብቻ ናቸው።»
📖 📖 📖
«በሕይወት ዘመንህ የሠራሃቸው ስህተቶች፣ የፈተኑህ አጋጣሚዎች እንኳን ቢሆኑ፣ ከአንተ በፊት በምድር ላይ በተራመዱት ሁሉ ተፈጽሟል። በሕይወትህ አስፈላጊው ጥያቄ እና ምላሽ በመጻሕፍት ገፆች ላይ ይገኛል። ትክክለኞቹን መጻሕፍት በሚገባ አንብብ። ሰዎች ችግራቸውን የፈቱበትን ብልሃት ተጠቀምበት። ያኔ በሕይወትህ ላይ በሚፈጠረው መሻሻል ትደነቃለህ።»
>>>
━━━━━━━━━
✍ ሮቢን ሻርማ
ትርጉም ➢ የእዮብዘር ዘውዴ በቀለ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 981 |
| 18 | sticker.webp | 744 |
| 19 | 📔 ፍ ካ ሬ
>>>
ኮሶ የተባለው ዛፍ በጫካው ውስጥ እድሜ ጠገብ ከሚባሉት በሳል ዛፎች አንዱ ነው። እውነትን እውነት፣ ውሸትን ውሸት ብሎ ፊት ለፊት የሚናገር ስለሆነ ‹ኮሶ መራራ ነው› ይባላል።
በመድኃኒት ጥበቡ እጅግ የተመሰከረለት ሲሆን ለጥገኞችና አስመሳዮች አይመችም። ምሬቱን ተጋፍጠው ለሰሙት ግን ነገሩ መሬት ጠብ የማይል እውነተኛ ማርከሻ ነው።
ይህን ጠባዩን የሚያውቀው የሰው ልጅ ባለቅኔ የሆነው ከበደ ሚካኤል፦
«ኮሶና ቁም ነገር ይመሳሰላሉ
ያለማጣፈጫ እጅግ ይመራሉ፤
ኮሶን ለሰው መስጠት በማር ጠቅሎ ነው
ማሩ እያጣፈጠ ኮሶ እንዲያድነው።»
ብሎለታል።
>>>
════════
✍ ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ (ዶ/ር)
🗓 2017 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 986 |
| 20 | sticker.webp | 836 |
