ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
Канал ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (@ethiobooks) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 10 278 підписників, посідаючи 3 726 місце в категорії Книги та 3 243 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 10 278 підписників.
За останніми даними від 30 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 30, а за останні 24 години на -2, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 11.26%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 3.08% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 157 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 316 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 6.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 31 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Книги.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 31 липня | +2 | |||
| 30 липня | +2 | |||
| 29 липня | +3 | |||
| 28 липня | +2 | |||
| 27 липня | +3 | |||
| 26 липня | +5 | |||
| 25 липня | +3 | |||
| 24 липня | +1 | |||
| 23 липня | 0 | |||
| 22 липня | 0 | |||
| 21 липня | +1 | |||
| 20 липня | 0 | |||
| 19 липня | +4 | |||
| 18 липня | +4 | |||
| 17 липня | +4 | |||
| 16 липня | 0 | |||
| 15 липня | +2 | |||
| 14 липня | +2 | |||
| 13 липня | +5 | |||
| 12 липня | +1 | |||
| 11 липня | +9 | |||
| 10 липня | 0 | |||
| 09 липня | +4 | |||
| 08 липня | +9 | |||
| 07 липня | +2 | |||
| 06 липня | +3 | |||
| 05 липня | +6 | |||
| 04 липня | +1 | |||
| 03 липня | +2 | |||
| 02 липня | +6 | |||
| 01 липня | +4 |
| 2 | sticker.webp | 200 |
| 3 | ለ ፈ ገ ግ ታ
😁 😁 😁
የደሞዝ ጭማሪ
═════
ጋብሮቮው ሥራ ሊቀጠር ይሄድና ክፍያው ስንት እንደሆነ ይጠይቃል።
«መነሻ ሰባ ሌቭ እንከፍልሃለን። ጥቂት ጊዜ ከቆየህ ደግሞ እስከ መቶ ሌቭ መድረስ ትችላለህ።»
«መልካም፣ እንግዲያው ጥቂት ቆይቼ እመለሳለሁ።»
😂 😂 😂
ቁጭት
═•═
ጋብሮቮው ልጅ፣ መንገድ ዳር እየተንሰቀሰቀ ያለቅሳል።
«ለምን ታለቅሳለህ ማሙሽ?»
«እናቴ የሰጠችኝ አንድ ሌቭ ጠፋብኝ።»
«በል ተወው አታልቅስ፣ እንካ አንድ ሌቭ።»
ልጁ ታዲያ ገንዘቡን ከተቀበለም በኋላ ለቅሶውን ቀጠለ።
«አሁን ደግሞ ምን ያስለቅስሃል አንተ?»
«የመጀመሪያው ሌቭ ባይጠፋብኝ ኖሮ አሁን ሁለት ሌቭ ይኖረኝ ነበር።»
😂 😂 😂
"እንኳን ነገርከኝ"
═════
አንዱ ጋብሮቫዊ ለስሞታ ወደ ጎረቤቱ ይሄዳል። እንደደረሰም፦
«ውሻህ ዛሬም አንዷን ዶሮዬን በላብኝ።»
«እንኳን ነገርከኝ። ቀኑን ሙሉ ምንም የሚበላ ነገር አልሰጠውም።»
😂 😂 😂
════════
📔 ቀልዶች ከጋብሮቮ ምድር
✍ በአረፈዓይኔ ሐጎስ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 469 |
| 4 | sticker.webp | 462 |
| 5 | መውለድ
👩🍼 👩🍼
👩🍼
ወላድ፣ በድባብ ትሂድ።
👩🍼
ያልወለዱት ልጅ፣ ያልወቀሩት መጅ።
👩🍼
ወልደውት ያላሳረፈ፣ ነግዶ ያላተረፈ።
👩🍼
የወለደ ይልሳል፣ የበደለ ይክሳል።
👩🍼
ወልዶ አይሳምለት፣ ተናግሮ አይሣቅለት።
👩🍼
ያልወለዱ ሁሉ፣ ጊደሮች ይባላሉ።
👩🍼
የወለዱት ሁሉ ካደገ፣ የዘሩት ሁሉ በጸደቀ።
👩🍼
ወልዶ አይስም፣ ዘርቶ አይቅም የለም።
👩🍼
ያልወለደ፣ አጋድሞ አረደ።
👩🍼
ወልጄ አልላኩ፣ መንኩሼ አልጸደኩ።
👩🍼
ሲወልዱ አየሁ ብላ በጠጧን ጣለች።
👩🍼
ከተዛመዱ፣ የተዋለዱ።
👩🍼
የተወለዱት ይራባሉ፣ እንደገና ይወለዳሉ።
👩🍼
ወልደው ሳያበቁ፣ በሰው ልጅ አይስቁ።
👩🍼
የወለደውን ሲስሙለት፣ ያቀረበውን ሲበሉለት።
👩🍼
ያልወለድኩት ልጅ አባባ ቢለኝ፣ አፌን ዳባ ዳባ አለኝ።
👩🍼 👩🍼
ነገር በምሳሌ
@ethiobooks | 614 |
| 6 | sticker.webp | 541 |
| 7 | «ላገባ ነው»
━━•━━
✍ ሕይወት እምሻው
'
ገና ሲጋቡ አብሬያቸው ነበርኩ።
የቤት እቃዎቻቸው ከየተገዙበት ተግዘው ከመምጣታቸው በፊት የተከራዩትን ቤት ፍትግ አድርጌ አፅድቻለሁ። ወንበርና ጠረጴዛ፣ ሶፋና ቁምሳጥን፣ ኮመዲኖ እና የኩሽና ኮተት ቦታ ቦታ ለማስያዝ ጎንበስ ቀና ብያለሁ።
አዲስ አንሶላቸውን ከማሸጊያው አውጥቼ የባለትዳር አልጋቸውን አሳምሬ አነጥፌያለሁ። ልብሶቻቸውን ተኩሼና አጣጥፌ ወደየ ቁምሳጥናቸውና መሳቢያዎቻቸው ከትቻለሁ። የጋብቻቸው መሰረት በሰርግ ድግስ ሲጣል አብሬ ጨፍሬያለሁ።
ትዳራቸውን ሀ ብለው እንደጀመሩ ሶፋ ላይ ተቃቅፈው በተቀመጡበት የመጀመሪያውን ቡና ሳሎናቸው መሃል ቁጭ ብዬ አፍልቻለሁ። ዘመድ ጓደኞቻቸውን ከነ ቤት ለእምቦሳ ስጦታቸው የተቀበሉበትን የአዲስ ጎጆ ወጪ የመጀመሪያ ግብዣዎች ተጨናብሼና ተንደፋድፌ ደግሻለሁ።
የመጀመሪያ ልጃቸውን ማርገዝዋን ስታበስረኝ "እልል..." ብያለሁ።
ሁለተኛው ሲከተል "እንኳን ዳግም ተባረክሽ" ብያታለሁ።
ሦስተኛው ሲጨመር "ቤታችን ሞቀ" ብዬ አቅፌያታለሁ።
ሦስቱንም ልጆቿን ወልዳ በተኛች ጊዜ ሳልሰለችና ሳልደክም፣ አንድም ቀን ፊቴን ሳላጨፈግግ እናቷ የሉም ተብላ ከንፈር እንዳይመጠጥላት እንደ እናት አርሻታለሁ።
ቀና ማለት ሲያቅታት ደግፌ፣ መነሳት ሲሳናት ምርኩዝ ሆኜ፣ ስትደክም አራስ ልጆቿን አቅፌ፣ ስታንቀላፋ ነቅቼ፣ ሰውነቷ እንዳይጎዳ አሁንም አሁንም መግቤያታለሁ፣ አእምሮዋ እንዳይቦዝን ቀን ከሌት አጫውቻታለሁ።
«ማርያም በሽልም ታውጣሽ!» ብለው የመረቋት ወዳጅና ዘመዶቿ በምርቃት እስኪያንበሸብሹኝ ተንከባክቤያታለሁ።
ወልዳ ወደ ሥራ በተመለሰች ቁጥር ልቧ ሳይከፈል እንድትውል ለልጆቿ ወደር የሌላት እናት ሆኛለሁ።
ሕይወት ስታጎሳቁላትና ባሏ ሲያስከፋት አብሬያት ተከፍቻለሁ፤ ሲሞላላትና ደስ ሲላት ከጎኗ ሆኜ ስቄያለሁ።
የጊዜ መርዘም እህትማማቾች አድርጎናልና ልጆቿን ያዘልኩትን ያህል አዝያታለሁ። የሕይወቴን አስራ አንድ ዓመታት እና የወጣትነት ጉልበቴን ያለ ስስት ሰጥቻታለሁ።
ዛሬ ጠዋት ቁርስ የበሉበትን እቃ ሰብስቤ ሳበቃ፣
«ቲጂዬ፣ ከሦስት ወር በኋላ ላገባ ነው» ስላት... በደስታ ልታቅፈኝ እየተንደረደረች፣
«እንኳን ደስ አለሽ እህቴ! ጥሩ ሚስት፣ መልካም እናት ትሆኛለሽ» ትለኛለች ብዬ ነበር።
በዚህ ፈንታ ለመጀመሪያዎቹ ሰከንዶች ከባድ ዝምታ ሰፈነ።
ከዚያ ምን አለችኝ?
«እንዴ... እኛን ለማን ጥለሽ ነው የምታገቢው...?»
የምናገረው ጠፍቶኝ ስደናገር እንዲህ ብላ ጨመረች።
«ወይኔ ጉዳችን ሙሉዬ... አንቺ አግብተሸ እኛ ምን ሊውጠን ነው?... ልጆቹስ?... እኔስ?... ተኬስ...? ... ባይሆን ተመላላሽ እንኳን ሆነሽ አትቀጥይም?»
እኛስ...። ልጆቹስ... ። እኔስ... ። ተኬስ... ።
ስለ እኔ አንዳች ነገር አላለችም።
ያን ጊዜ በደም ባትዛመደኝ አብሮ በመኖር እህቴ ሆናለች ያልኳት ትእግስት አሠሪዬ ብቻ ሆና ታየችኝ።
ለካ እኔ ለእሷ ሴት አይደለሁም።
የራሷ እጣ ፈንታ፣ የራሷ ሕይወት፣ የራሷ ታሪክ የሚኖራት ራሴን የቻልኩ ነጠላና ሙሉ ሰው አይደለሁም።
የሚሠሩ እጆችና እሺ የሚል አፍ ብቻ ያለኝ እድሜ ልኬን የእሷን ሕይወት ለማደላደል የተፈጠርኩ፣ የቤተሰብዋን ሕይወት ለማቃናትና ልጆቿን ለማሳደግ እንጂ የራሴን ጎጆ መስርቼ የራሴን ልጆች መውለድ ያልተፈቀደልኝ ጥላዋ ነኝ።
ይህንን እና ከሦስት ወር በኋላ ተመርቄ ለመሰናበት ያሰብኩትን የምወደውን ቤተሰቤን በቀናት መለየት እንዳለብኝ ሳስብ እንባ ቀደመኝና ወደ ኩሽና ሮጥኩ።
━━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 848 |
| 8 | sticker.webp | 680 |
| 9 | ይስሃቅ ራቢን - 2 የመጨረሻው! | 890 |
| 10 | ይስሃቅ ራቢን - 1 | 968 |
| 11 | ▶ ይ ስ ሃ ቅ ራ ቢ ን
━━━━━━━
«ለሰላም ሕይወቱን የከፈለው
ጠቅላይ ሚኒስትር»
@ethiobooks | 1 010 |
| 12 | sticker.webp | 948 |
| 13 | የሥጋ እዳ መዘዝ
═══•═══
✍ ሐዋዝ የሻነህ
'
አምላክ ጊደር አርዶ
ቅርጫ ሲያከፋፍል
ሠፊ ቅርጫት ይዤ በደስታ ተገኘሁ፣
እንደ ሥጋ ወዳጅ
እንደሰው እንደሰው
ሩብ ግማሽ ንቄ ሙሉ እጣ ተናኘሁ።
ልበላው ስስቴ፣
አዬ ሰውነቴ።
ቆረጥኩት ጮማውን፣
አቀለጥሁት ስቡን፣
ማልዶ ቁንጣን ያዘኝ፣
አርፍዶ ጨነቀኝ፣
የበላሁት ሥጋ
"ና ውጣ፥ ና ውረድ" እየተናነቀኝ።
ይኽን ኹነት ሰምተው፣
እውነቴን አድምጠው፣
የመጠየቅ አመል
ያለባቸው ሰዎች "እንዴት? ለምን?" ቢሉ፣
ምኑ ጤና ሊኾን?
የሥጋ እዳ ገብተው ሙሉ እጣ ቢበሉ።
════════
📔 ቊናማት
🗓 ፳፻፲፯ ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 1 084 |
| 14 | sticker.webp | 914 |
| 15 | 💬
❝እምነት ያለ ተግባር ፋይዳ ቢስ ነው። እምነት ተዓምራትን ይፈጥራል እንጂ እስኪፈጠሩ አይጠብቅም። እችላለሁም አልችልምም ብላችሁ ካሰባችሁ በሁለቱም በኩል ትክክል ናችሁ!❞
ሄንሪ ፎርድ
💬
❝የጋለ ፍላጎት ሳይኖር የተከናወነ አንድም ታላቅ ተግባር የለም።❞
ኤመርሰን
💬
❝ለማዕረግ ቀድመው የሚጨነቁ ሰዎች ማዕረጉ ለሚያስከትለው ጥቅም ትኩረት የሚያደርጉ ናቸው።❞
ሊሳ በቨሬ
💬
❝አንዱ ሰው በበታችነት ስሜትና ላለመሳሳት ማድረግ ያለበትን ተግባር ከመከወን ሲወላውል፣ ሌላኛው ስህተቶችን አብዝቶ በመሥራት የበላይነትን ይወዳጃል።❞
ሔንሪ ሲ. ሲንክ
💬
❝በራሱ ለራሱ አመኔታ ከሌለው ሰው ቁም ነገር መጠበቅ ሞኝነት ነው።❞
ጀምስ ራሰል ሉዌል
💬
❝አንዳንድ ጊዜ በሕይወትህ ሁለተኛ እድል የማይሰጡ ሁኔታዎች ያጋጥሙሃል፤ ሁለተኛ እድል ካገኘህ ግን ችላ ሳትል ተጠቀምበት።❞
ያልታወቀ
💬
❝ስዕል ቅኔ ነው፣ የማይ'ሰማ ግን የሚታይ፤ ግጥም ደግሞ የሚታይ ግን የሚደመጥ ስዕል ነው።❞
ሊዮናርዶ ዳቪንቺ
💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks | 1 228 |
| 16 | sticker.webp | 860 |
| 17 | አስገራሚ አሟሟቶች
━━━✦━━━
✍ ዶክተር ኬ.ኬ.
'
•✦••✦••✦•
ሊ ፖ የተባለ በአስረኛው ምዕተ ዓመት የኖረ ቻይናዊ ገጣሚ እና ፈላስፋ ለጨረቃ ካለው ፍቅር የተነሳ «በሕይወቴ ውስጥ ጨረቃን ስሜ ብሞት አይቆጨኝም!» ይል ነበር። ታዲያ አንድ ቀን በምሽት ጀልባ ላይ ሆኖ ጉዞ ሲያደርግ የደማቋን ጨረቃ ነፀብራቅ ፍንትው ብሎ በባህሩ ላይ አንፀባርቆ ያያል። ፈላስፋው ሊ ፖም በደስታ ብዛት ከጀልባው ላይ ተዘቅዝቆ ጨረቃዋን ሊስማት ሲል በአፍጢሙ ተደፋና ውሃ ውስጥ ሰጥሞ ሞተ። ይህ ሰው ልክ እንደ አሟረተውም ጨረቃዋን ስሞ ሞተ።
•✦••✦••✦•
በ1063 እ.ኤ.አ. ቀዳማዊ ቤላ የተባለው የሃንጋሪ ንጉሥ ዙፋኑ ላይ ዘፍ ብሎ ሊቀመጥ ሲል ድንገት የዙፋኑ እግር ስለተሰበረ፣ ወደ ኋላ ተንጋልሎ ጭንቅላቱ ከመሬቱ ጋር በመላተሙ ምክንያት ሕይወቱ አለፈች።
•✦••✦••✦•
በ1387 ዳግማዊ ቻርለስ የተባለ የናቫሬ ንጉሥ ሌሊት ላይ ብርድ በሽታዬ ተነሳብኝ በማለት ወፍራም ብርድ ልብስ በመከናነብ ኩሽና ውስጥ እሳት እየሞቀ ማዕድ አጠገብ ተኝቶ እንቅልፉን ሲለጥጥ በአጋጣሚ ሌሊት በጨለማ ለሥራ የተነሳችው የማዕድቤቱ ሠራተኛ ዓይኗ ተጨናብሶ በደንብ አልታያትም ነበርና «እንዴት ያለ ደፋር ሌባ ቤተ መንግሥት ውስጥ ገባ!» በማለት በግዙፍ መጥረቢያ አናቱን ለሁለት ገመሰችው። ንጉሡም በዚሁ ባልታሰበ አደጋ እስከ ወዲያኛው አሸለበ።
•✦••✦••✦•
በ1771 አዶልፍ ፍሬድሪክ የተባለ የስዊድን ንጉሥ የሞተው ራሱ ባዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ 17 ሳህን ምግብ በመብላቱ በደረሰበት የአንጀት መተርተር ሰበብ ነበር!! ከዚያን ጊዜ በኋላ «ሆዳሙ ንጉሥ ራሱን በቁንጣን ገደለ!» ተብሎ ለዘመናት ተፌዘበት።
•✦••✦••✦•
በ1814 እ.ኤ.አ. ለንደን ውስጥ በጎርፍ አደጋ ሰባት ስዎች ሞተው ነበር። ይህ አደጋ የደረሰው ግን በውሃ ሳይሆን በቢራ ጎርፍ ነበር። ይኸውም 'ማውክስ ቢር ካምፓኒ' ከተባለ የቢራ መጥመቂያ ግቢ ውስጥ አንድ ግዙፍ ጋን ይፈነዳና አካባቢው በ323,000 ጋሎን ፍሳሽ ቢራ ተጥለቀለቀ። ብዙ ንብረት ወደመ፣ በርካታ ሰዎችም ለአካል ጉዳት ተዳረጉ። ሰባቱ ሰዎች ግን የቢራ ሰማዕት ሆኑ።
•✦••✦••✦•
ጀምስ ኦቲስ የተባለ የ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አሜሪካዊ የነፃነት ታጋይ «ምንጊዜም ምኞቴ በሰው እጅ ሳይሆን በመብረቅ ተመትቼ መሞት ነው!» እያለ ለጓደኞቹ ይናገር ነበር። ታዲያ አንድ ቀን ምሽት ጀምስ ከዝናብ ሊጠለል ወደ ጓደኛው ቤት ሊገባ ሲል፣ ድንገት ከሰማይ በወረደ መብረቅ ተመትቶ ሕይወቱ አለፈች።
ምኞቱ ተሳካ ወይስ አልተሳካም?
>>>
━━━━━━━━━━
📔 የዕውቀት ማኅደር - ፫
📄 26 - 28
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 1 206 |
| 18 | sticker.webp | 868 |
| 19 | ማርያም ሚርዛክሃኒ - 2 የመጨረሻው! | 1 229 |
| 20 | ማርያም ሚርዛክሃኒ - 1 | 1 216 |
