ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
Channel ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (@ethiobooks) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 283 subscribers, ranking 3 708 in the Books category and 3 231 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 283 subscribers.
According to the latest data from 17 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 26 over the last 30 days and by 4 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.97%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.16% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 1 128 views. Within the first day, a publication typically gains 325 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Books category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 17 July | +4 | |||
| 16 July | 0 | |||
| 15 July | +2 | |||
| 14 July | +2 | |||
| 13 July | +5 | |||
| 12 July | +1 | |||
| 11 July | +9 | |||
| 10 July | 0 | |||
| 09 July | +4 | |||
| 08 July | +9 | |||
| 07 July | +2 | |||
| 06 July | +3 | |||
| 05 July | +6 | |||
| 04 July | +1 | |||
| 03 July | +2 | |||
| 02 July | +6 | |||
| 01 July | +4 |
| 2 | sticker.webp | 269 |
| 3 | ጦ ጣ
🐒 🐒
🐒
የጦጣ ዘር አቀባይ፣ የዝንጀሮ ጎልጓይ።
🐒
ጦጣ በልታ፣ በዝንጀሮ አሳበበች።
🐒
ጦጣ፣ ባለቤቷን ታስወጣ።
🐒
የጦጣ ልጅ በዛፍ፣ የመናፍቅ ልጅ በመጽሐፍ።
🐒
ጦጣና ዝንጀሮ፣ ተኩላና ቀበሮ።
🐒
የለመደች ጦጣ፣ ሁልጊዜ ሽምጠጣ።
🐒
ከጦጣ የዋለ ጉሬዛ፣ እህል ፈጅቶ ገባ።
🐒
ጦጣ በዛፍ፣ ዝንጀሮ በአፋፍ።
🐒
ልጅና ጦጣ፣ ውሃ ይጠጣ።
🐒
ጦጣ አታላይ፣ እርኩም 'ጉድ' ባይ።
🐒
ጦጣ ተይዛ ትዘፍን።
🐒
የጦጣ ማኛሞኝ፣ የዝንጀሮ ብልጣ ብልጥ የለውም።
🐒
ጦጣ 'ምን ትወጃለሽ?' ቢሏት 'ከዛፍ ላይ ትግል።'
🐒 🐒
ነገር በምሳሌ
@ethiobooks | 521 |
| 4 | sticker.webp | 461 |
| 5 | ብልጥ ለብልጥ ...
━━ 🐒 ━━
ከዕለታት አንድ ቀን፣ እመት ጦጢት፣ ከዛፍ ዛፍ እየዘለለች ፍሬ ትለቅም ነበር። አያ ገበሬ ደግሞ ወደ እርሻ ሄዶ ዘር ዘርቶ መመለሱ ነው።
«እመት ጦጢት እንደምንድነሽ?» አላት።
«ደህና ነኝ፤ አንተስ እንደምንድነህ?» ጦጢት አፀፋውን መለሰች።
«እኔም በጣም ደህና ነኝ።»
«ሥራ እንዴት ነው?» አለችው።
«ምንም አይልም። ዝናቡ ብቻ ለዘር አልተመቸኝም።»
ጦጢት አሁን ወደ ጉዳይዋ ገባች።
«ለመሆኑ ዘንድሮ ምን ዘራህ?» ስትል ጠየቀችው።
ገበሬው በትክክል የዘራውን ቢነግራት ከእርሻው ውስጥ ልትቦጠቡጥበት ነው። ስለዚህ የዘራውን እና ለሷ የሚመቻትን ትቶ ለጦጢት የማይመቻትን ነው መጥራት ያለበት።
«እመት ጦጢት ዘንድሮስ ተልባ ነው የዘራሁት።» አላት እያስተዛዘነ።
ጦጢትም፦
«ይሁን እስቲ ወርደን እናየዋለን!» አለችው።
እመት ጦጢት ሌሊቱን ስትቦጠቡጥለት አደረች። ገበሬው ተናዶ ሲያሳድዳት ከረመ። ጦጢት ነቅታ ኖሯልና ደብዛዋን አጠፋች።
━ ብልጥ ለብልጥ፣ ዐይን-ብልጥጥ። ━
ይሏል ይኼው ነው!
ነገርን መሬት ወርዶ ማየት ብልህነት ነው!... ብዙ ሰዎች በንግግር ጥበብ ያምናሉ። ሆኖም የምላስ ወለምታ በቅቤ አይታሽም የሚለውን ተረት ልብ ቢሉ መልካም ነው።
━━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 650 |
| 6 | sticker.webp | 577 |
| 7 | «የኔ አበባ! ከእንግዲህ
የኔ ሚስት ነሽ፣ ሆድሽ አይባባ»
━━━━━✦━━━━━
እቤታቸው ድንገት ያልታሰበ ድግስ ሲደገስ ስትመለከት «የምን ድግስ ነው?» ብላ እናትና አባቷን ጠየቀች። በእድሜ ትንሽ በመሆኗ መልስ አልሰጧትም። ትንሽ ብትሆንም ነገሩ አላማራትምና እናቷን «እማማ!» ብላ አባብላ «ድግሱ የምንድነው?» ብላ ጠየቀች። እናቷም ልጃቸውን እቅፍ አድርገው «ልጄ! የገብርኤል ማኅበር ነው፤ የአባትሽ ተራ ስለሆነ ለዚያ ነው ድግሱ» ሲሏት ደስ አላት።
ለጓደኞቿ «እኛ ቤት ድግስ አለ!» ብላ ነገረቻቸው። እነሱም ደስ ብሏቸው ድግሱን የጋራቸው አድርገው ይጫወቱ ጀመር። ታዳጊዋ በቤቷ የሚደገሰውን ድግስ እያየች ስትቦርቅ፣ ስትደሰት ቆይታ ድግሱ ሁሉ ነገር ካበቃ በኋላ ተጣጥባ አምራና ተውባ አዲስ ልብስ ለበሰች። ለድግሱ ስለሆነ ደስ አላት። ጓደኞቿ አዲሱን ልብሷን አይተው «የጥቅምት አበባ መስለሻል፤ እንዴት ያምርብሻል» እያሉ አድናቆታቸውን ሲሰጧት ተከሻዋን ሰበቅ አድርጋ፣ ፈገግ ብላ አድናቆታቸውን ተቀበለች።
በማግስቱ ሌላ ልብስ ለብሳ ካማረች፣ ከተዋበች በኋላ «ዛሬ ሠርግሽ ነው ታገቢያለሽ» የሚለውን ቃል ስትሰማ አለቀሰች። ነገሩ ሁሉ ከጓደኞቿ ጋር የምታደርገው የዕቃ ዕቃ ጨዋታ መሰላት። «የገብርኤል ድግሱስ?» ብላ ጠየቀች። መልስ አላገኘችም።
በጊዜው ለልጆች ባል የሚያጩት ቤተሰቦች ነበሩና ምንም ማድረግ አልቻለችም። ደግሞ በርሷ እድሜ ጋብቻን የሚፈሩ ታዳጊዎች ነበሩ። ብዙዎቹ ጓደኞቿ ሳያውቁ እንዳገቡ ታውቃለችና ሁሉን ጥላ ቁጭ አለች። ድንጋጤዋ የልጅነት ውብ ፊቷን አዳመነው።
ባሏ እንዲሆኑ የታጩት በእድሜ ብዙ የሚበልጧት ሰው «የኔ አበባ! ከእንግዲህ የኔ ሚስት ነሽ፣ ሆድሽ አይባባ » ብለው እቅፍ አድርገው ታዳጊዋን ይዘው ሄዱ። ታዳጊዋ ለጊዜው ታግባ እንጂ ሁሌ ትጨነቅ ነበር። አስራ ሁለት ሰዓት በመጣ ቁጥር አልጋ ውስጥ ትደበቃለች። ቁም ሳጥን ውስጥ ትሸሸጋለች። ጓሮ ውስጥ ትሠወራለች። ሁሌም ተፈልጋ ነው የምትገኘው።
እንዲህ እየኖረች ሁለት ልጆችን ወለደች። ሦስተኛውን ልጅ አራስ ቤት ሆና ግን አልቻለችምና ቤቱን ጥላ ወጣች። ጭንቀቷ ለቀቃት። ፍርሃቷ ሲለቃት ከሰው መገናኘት፣ ከዘመድ መደባለቅ ጀመረች።
ይህ አስገራሚ ታሪክ የድምፀ መልካሟ፣ በአዘፋፈን ብልሃቷ የምትደነቀው የድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ታሪክ ነው። ራሔል ዮሐንስ በርካታ የሙዚቃ አልበም በማሳተም ዛሬም ድረስ የተወደደች ድምፃዊት ነች።
━━━━━━━━━━
📔 አዲስ 1879 / ፲፰፻፸፱
✍ ዳግማይ ነቅዓጥበብ
📄 44 - 45
📖 📖 📖 📖 📖
* ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
https://t.me/Ethiobooks | 862 |
| 8 | sticker.webp | 700 |
| 9 | ፒ. ኬ. ማሃናንዲያ | 1 021 |
| 10 | ▶ ፒ. ኬ. ማሃናንዲያ
━━━━━━
«ከህንድ እስከ አውሮፓ
በሳይክል ለፍቅር»
@ethiobooks | 990 |
| 11 | sticker.webp | 951 |
| 12 | ወደ ነፈሰበት
══✦══
✍ አሳዬ ደርቤ
'
የኔ እኮ የጉድ ነው
ህዝብ ጋር የምነግሥ ህዝብ ጋር የምነፍስ
«ሃድድ ተነጥፈ፣ ጎዳኖች ተቃኑ፣ ሰዓታት አጠሩ
እንግልት ቀነሰ» እያሉ ሲያወሩ
አብሬ ስዘምር «ሃድድ» ስል ከርሜ
ከተጓዦች ጋራ ባቡር ጣቢያ ቆሜ
ባቡርና ሃድድ የተሰናዱ ዕለት
ተሳፋሪው እኔ 'ምሄድበት እጥት።
| አ ቤ ት |
አሁን በቀደም ዕለት ግድቡ ሲጀመር
ሀገራዊ ጥቅሙን ፋይዳውን ስናገር
«ፋብሪካ ብንተክል ጣውላ ቤት ብንከፍት»
«መስኖ ብናለማ አሳ ብናመርት»
«ዋናው ነገር ግድብ ዋናው ነገር መብራት»
እያልኩ እከርምና ...
አሁን በቀደም 'ለት አሁን ትናንትና
ለስንት የታቀደው መብራት የበራ ዕለት
አምፖሉን አጥፍቼው አዳፍኜው ትኝት።
| አ ቤ ት |
═══════
📔 እስኪነጋ ድረስ
🗓 መስከረም 2008 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 1 139 |
| 13 | sticker.webp | 915 |
| 14 | የሀገራችን
የአጭር አጭር አጭር ልቦለድ
✍ ደምሴ ጽጌ
'
ተገዳ ስትዳር የዘጠኝ አመት ልጅ ነበረች። አስራ ሰባት አመት ሲሞላት ነው ፍቅር ልቧን የዳሰሰው። አፈቀረችው፤ አፈቀራት፤ አወቀችው፤ አወቃት። አንድ ቀን ውሃ ልትቀዳ በሄደችበት ከፍቅረኛዋ ጋር እጥሻው ውስጥ ወደቀች። 'ባልየው' ወሬ ሰማ፤ ሽጉጡን ታጥቆ ተንደረደረ። ተዋህደው እንደተኙ ደረሰባቸው። ተኮሰ፥ እሷን ገደላት። ተኮሰ፥ ፍቅረኛዋን ገደለ፤ ተኮሰ፥ ራሱንም ገደለ። የማይሞተው ፍቅር ግን ከሶስቱም ልብ ውስጥ ወጥቶ ሌላ ጉብል ፍለጋ፤ ሌላ ጎልማሳ ፍለጋ እያዘነ ገሰገሰ...።
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 1 024 |
| 15 | sticker.webp | 829 |
| 16 | 💿 ጋዜጠኛው 💿
══•══
🎤 ቴዎድሮስ ሞሲሳ
@ethiobooks
🎼🎵🎶🎵🎶🎵
ዓለም እንዴት አደርሽ እንደምን ከርመሻል
ረጋ ሰከን አልሽ ወይ ነውጡ ብሶብሻል
የነማን ቤት ቀና የነማን ፈረሰ
የት ቤት ፌሽታው ደራ የቱስ ማቅ ለበሰ
የምንሰማው ነቅተን የየዕለት ታሪክሽን
አጀብ የሚያሰኘው ጓዳ ጎድጓዳሽን
አሳምሮ 'ሚያቀርብ ክቡር ሰው መለኛ
ባይፈጠር ኖሮ ዕንቁ ጋዜጠኛ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
🎶🎶🎶
የቢሮክራቱን ግልምጫ
የባለስልጣኑን ጡጫ
የአድማ በታኙንም ዱላ
ቆሞ የሚጋፈጥ ተሟጋች
ሲሮጥ ሲወድቅ በየጎራው
አጋች ይዞ ሲያንገላታው
በበረሃ ረሃብ ሲቀጣው
አዛኝ የለው አይ ፈተናው
🎵🎶🎵🎶🎵
ከጦር ሜዳም አይቀር ነጉዷል ጓዜን ብሎ
ፍልሚያው መሀል ያድራል ድንኳን ቢጤ ተክሎ
ለዓለም ሕዝብ ሲደክም ምኑን አስተውሎ
ከእሳት ይማገዳል ልጅ ትዳሩን ጥሎ
የምድር ምስቅልቅል ምንጊዜም ላይጠራ
በቃኝ ማለት አውቆ ሰው ለሰው ላይራራ
እንባ ደም መፍሰሱ ላይገታ እሮሮ
መባከንህ ቆጨኝ ከፋኝ ያንተ ኑሮ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
🎶🎶🎶
የሹምሽሩን ትኩስ ዜና
የአዛዥ ታዛዡን ገመና
የፋሽን ኳስ የዘፈኑን
የጎርፍ የርዕደት ናዳውን
የምዕራብ ጥጋብ ቅብጠቱን
የአፍሪካን ረሃብ ጉዳቱን
ያ'ለምን ቀውስ ውጥንቅጡን
ይፋ አድራጊ ዘጋቢ ሁሉን
የባለ ፀጋ ምቾቱን
የድሃን ማጀት ምሬቱን
የንጉሥ እልፍኝ ምስጢሩን
በርብሮ የሚያሳየኝ ውስጡን
ፀሐይ ሳይመታኝ ሆኜ ቤቴ
ሁሉን መቃኛ መስኮቴ
ልቤ ከልብ ያከብርሃል
በ'ውነት ገብተሃል ካ'ንጀቴ
ጋዜጠኛው... ጋዜጠኛው...
ጋዜጠኛው... ኑሮህ ልቤን ነካው
ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው - ጋዜጠኛው...||
🎶🎵🎶
@ethiobooks | 1 073 |
| 17 | No text... | 877 |
| 18 | sticker.webp | 951 |
| 19 | #ዳሪዮስ_ሞዲ
“ለረጅም ዓመታት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ሲካሄድ የነበረው የርስ በርስ ጦርነት ያስከተለውን የኢትዮጵያዊያን ሕይወት መጥፋትና ከኑሮ መፈናቀል ለማስቀረት በልዩ ልዩ መልክ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል። ሆኖም ችግሩ ሊቃለል አልቻለም። ይልቁንም ወደ ባሰ ደረጃ እየተሸጋገረ በመሄድ ላይ ይገኛል።
ስለዚህ ደም መፋሰስ እንዲቆምና ሰላምም እንዲሰፍን በልዩ ልዩ ወገኖች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ከስልጣን መውረዳቸው እንደሚበጅ የታመነበት ስለሆነ፣ ይህንኑ በማመዛዘን ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ከሥልጣናቸው ወርደው ከኢትዮጵያ ውጪ ሄደዋል።”
ይህ ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም. የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ከሀገር መውጣት የተገለፀበት መግለጫ ነው። በብዙዎች ጆሮና እዝነ ልቡና እስከ አሁንም የማይጠፋ ሆኖ ተቀርጿል። አንባቢው ደግሞ ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ።
ጋዜጠኛ ዳሪዮስ ሞዲ ለሬዲዮ የተፈጠረ፣ ተሰምቶ የማይጠገብ፣ እያነበበ ድምፁ የሚስረቀረቅ፣ የሬዲዮ ሞገድን የሚገዛ፣ ከዜና ባህሪው ተነስቶ አነባነቡን የሚከተል እንከን አልባ ዜና አንባቢ እና ጋዜጠኛ ነበር።
በትውልድ ፐርሺያዊ በዜግነት እንግሊዛዊ ከሆኑት ከአባቱ ከሚስተር ሞዲ ጉስታቭ እና ከእናቱ ከወይዘሮ አማረች መኩሪያ ታህሳስ 12 ቀን 1939 ዓ.ም. ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ አካባቢ ነው የተወለደው።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለው እንግሊዝ ትምህርት ቤት ሲሆን፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ነበር።
በመቀጠልም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርቱን በ"Political Science" መከታተል ቢጀምርም በወቅቱ በነበረው የተማሪዎች ንቅናቄ ሳቢያ የቅርብ ጓደኛውና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት የነበረው ጥላሁን ግዛው መገደልን ተከትሎ ትምህርቱን አቋርጦ ወጣ። ዘመኑም 1962 ዓ.ም. ነበር።
በወቅቱ በነበረው መንግሥት አመለካከቱ ያልተወደደለት ዳሪዮስ፣ ለሁለት ዓመታት ያህል ሥራ ለመቀጠር ባይችልም በግሉ የትርጉም ሥራዎችን ይሠራ ስለነበር በ1964 ዓ.ም. በብስራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያ ለመቀጠር ምክንያት ሆነው።
በብስራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያ የጀመረው የሬዲዮ ጋዜጠኝነት ሕይወቱ በኢትዮጵያ ሬዲዮ እስከ 1980ዎቹ መገባደጃ ድረስ በዜና አንባቢነት እና በፕሮግራም አዘጋጅነት የቀጠለ ሲሆን፣ ጡረታ እስከወጣበት 1994 ዓ.ም. ድረስ ያገለገለው በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የውጭ ቋንቋ ዴስክ ነበር።
ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ በተለይ የውጭ ቋንቋዎችንና ቃላትን በአማርኛ አቻ ትርጉም በመፍጠር የሕዝብ ቋንቋ ማድረግ የቻለ፣ የቋንቋ ምሁራንም ደግመው ደጋግመው የሚመሰክሩለት የትርጉም መምህር ነበር። አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ እንግሊዝኛ፣ ጀርመንኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣልያንኛ የመተርጎም ብቃቱም የመነጨው ካልተቋረጠ የንባብ ብቃቱ ነው።
ከቀደሙ የሙያ አባቶቹ ከእነ አሃዱ ሳቡሬ እና አሠፋ ይርጉ ብዙ እንደተማረ ሁሉ እሱም ያገኘውን ለራሱ ሳያስቀር ለተተኪዎቹ በማስተማር ምሳሌ መሆን የቻለ ድንቅ ጋዜጠኛ እንደነበር ብዙዎች ይመሰክሩለታል።
የዳሪዮስ ሞዲ የጋዜጠኛነት ሕይወት ለ30 ዓመታት ቢቀጥልም ይከፈለው የነበረው ደመወዝ የእርሱን አስደናቂ ችሎታና የሙያ ልቀት የሚመጥን ቀርቶ ለወር አስቤዛ የማይበቃ ነበር። ወር ጠብቆ በሚያገኘው አነስተኛ ደመወዝ ራሱን እና ቤተሰቡን ለማስተዳደር ቢቸገርም ያን ወርቃማ ድምፁን ለገንዘብ ማግኛነት ለማዋልና፣ ማስታወቂያ ሊሠራበት ፈቃደኛ አልነበረም።
"ዜና ላይ የሚሰማ ድምፅ እንዴት ሆኖ ሸቀጥ ይተዋወቅበታል? ይህ በራሱ የሙያውን ሥነ-ምግባር መጣስ ነው!"
ሲል ለሙያው መርህ እና ልዕልና አጥብቆ ይከራከራል። ይህን አቋሙንም እስከ ሕይወቱ ፍፃሜ ድረስ ሳይለውጥ ቆይቷል።
ለዳርዮስ በተለይ የመጨረሻዎቹ ሦስት ዓመታት ጥሩ አልነበሩም። ለዘመናት ማልዶ ከሥራ ገበታው የማይታጣው ዳሪዮስ ሕመም ደጋገመው። እንደ ልብ መተንፈስ ስለተሳነው በኦክሲጅን እየተረዳም ቆይቷል።
ባለትዳርና የሰባት ልጆች አባት የነበረው ዕንቁው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ሰኔ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ሕይወቱ አልፏል። የቀብር ሥነ-ሥርዓቱም ሰኔ 14 ቀን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በፈረንሳይ ጉራራ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ተፈጽሟል።
━━━━━━━━━━━━
ምንጭ ➢ ዊኪፔዲያ እና ሌሎች
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks | 1 245 |
| 20 | ━━ ጋዜጠኛ ዳሪዮስ ሞዲ ━━
1939 - 2007
@ethiobooks | 917 |
