cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

Больше
Рекламные посты
11 358
Подписчики
+5524 часа
+6797 дней
+1 38630 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ፋኖ የታጠቀው ዘመናዊ መሳሪያ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ እጅግ ዘመናዊ መሳሪያዎችን ማርኮ መታጠቁን አስታወቀ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ በመዋቅር ደረጃ ራሱን እያደራጀና በትጥቅ እየበረታ መምጣቱን በቃል አቀባዩ በኩል ገልጿል፡፡ የእዙ ቃል አቀባይ ፋኖ አበበ ሙላት ፈጣን ተቋማዊ እድገት እያመጣን ነው ያለ ሲሆን ፣ በተጨማሪም የአገዛዙን ጦር የማፈራረስ ስራ እየሰራን እንገኛለን ብሏል፡፡ ፋኖ አበበ መሳሪያዎችን ገቢ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ስራዎችን እየሰሩ መሆኑንም ገልጿል፡፡ ከሰሞኑም እጅግ ዘመናዊ መሳሪያዎችን ጭምር ከአገዛዙ ጦር ማርከው መታጠቃቸውን አንስቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ከታንክ በስተቀር ሁሉም መሳሪያ እጃቸው ላይ እንዳሉ ተናግሯል፡፡ እንዲሁም የብልጽግናን ሰራዊት መማረክ የየእለት ስራችን ሆኗል ብሏል፡፡ በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች ለትግሉ አስተዋጽኦ ማድረግ እንፈልጋለን በሚል እየተቀላቀሉን ነው ያለ ሲሆን ከሰሞኑም የጀነራል አበባው ሰይድ ጠባቂ ከሁለት ጥርጥር ክላሽ ጋር ተቀላቅሎናል ብሏል፡፡ roha https://t.me/Moamediamoresh
Показать все...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

7👍 2
በይፋ በአምሓራ ላይ ኢንተርሃሞይ ታወጀ‼️ ሞዐ ሚዲያ - ሐ.3/2016) በኦሮሚያ ክልል ባሉ የአማራ ተወላጆች ላይ ዳግም ጭፍጨፋ ለማካሄድ በየቀበሌው መሳሪያ እንዲታደልና የፋኖ ሃይልን የክረምት ዘማቻ ያከሽፋል የተባለ መመሪያ በሰው በላው ቡድ ወረደ። በኦሮሚያ ዳግም በአማራው ህዝብ ላይ የዘር ጭፈጨፋ ለመፈጸም በመላው ኦሮሚያ በቀበሌ በተዋቀሩ ከሚቴዎች አማካኝነት መሳሪያ በገፍ እንዲታጠቁና የፋኖ ሃይልን የክረምት ዘመቻ ያጨናግፋል የተባለ አስቸኳይ መመሪያ መውረዱን የኢትዮ 360 የውስጥ ምንጮች አጋለጡ። እያንዳንዱ የኦሮሞ ተወላጅ አንድ ክላሽን በ35ሺ ብር ፣ ሽጉጥ በ3000 ብር  ሆኖ መክፈል ያልቻለ በግማሽ ክፍያ እንዲታጠቅ እየተደረገ መሆኑን የውስጥ ምንጮቹ ጠቁመዋል። የአማራን ፋኖ በእርቅ ፣በእድር፤በአገር ሽማግሌዎች እጅ እዲሰጡ በመላው አለም የሚድያ ዘመቻ ማድረግ የሚለውም ሌላኛው ከዘር ማጥፋቱ ዘመቻ ጎን ለጎን የሚካሄድ ዘመቻ መሆኑንም አጋልጠዋል። ለአማራ ሚድያዎች እና አክቲቪስቶች ብሎም ለፋኖ አመራሮች 4 ሚሊየን ብር በመስጠት መከፋፈል፣ እጅ እዲሰጡ በማድረግ የክረምቱን እቅዳቸውን ማጨናገፍ የሚለውም የአስቸኳይ መመሪያው ሌላኛው እቅድ መሆኑን አስታውቀዋል። ለዚህ ተግባር ማሳኪያ ደግሞ የክልሉ በጀት በቀጥታ ለዚህ ተግባር እንዲውል ማድረግ የሚለውም አንዱ መሆኑን አስቀምጠዋል። የፋኖ ሃይልን ትጥቅ ካስፈቱ በሁዋላ በወረደው መመሪያ መሰረት የተሰጣቸውን ብር፣ በዛ የገዙት ቤትም ሆነ መኪና ካለ በአዋጅ ምንጩ ያልታወቀ በማለት መውረስ  የሚለውም በአስቸኳይ መመሪያው ውስጥ ደመቅ ተደርጎ የተጻፈ መሆኑን የውስጥ ምንጮቹ አጋልጠዋል። ሌላው የጥፋት መመሪያ ደግሞ በሱዳን አማካኝነት የአማራን መሬት አልፋሽቃን ወልቃይትን በመፈራረም ለሰውዲ የጋራ ተጠቃሚነት መስጠት የሚለው መሆኑን አጋልጠዋል። በአማራ እና በትግራይ የተሰሩ ዘጋቢ ፊልሞችን በተመረጡ ግለሰቦች አማካኝነት በየሚዲያው ማራገብ የሚል ይገኝበታል ብለዋል የውስጥ ምንጮቹ። በነዚህ አካባቢዎች አጎራባች ቀጠናዎች ደግሞ የግጭት ትንኮሳ መፈጸም የሚለው በዚህ ሰው በላ ስብስብ የታቀደ መሆኑን የውስጥ ምንጮቹ ይናገራሉ። የመንግሥት ሚድያዎች ደግሞ የመከፋፈል፣የእጅ ሰጡና የአሸባሪነት ዘገባን እንዲራግቡ ማድረግም የእቅዱ አካል መሆኑን አስምረውበታል። የኦህዴኡ መከላከያ ጀነራሎች እና ሞኮንኖች በተሰጣቸው ተልዕኮ  ፈቃደኝነት ያላሳዩ የጀነራልነት ማረግ በፖለቲካ ሆናል ጡረታ እንውጣ የሉትን በአካውታቸው ብር በማስገባት ከፋኖ ደጋፊ ዲያስፕራ የተላከላቸው ነው በማለት መረሸን የሚለውም በመመሪያው ላይ መስፈሩን አመልክተዋል። የአማራ ተወላጅ የጦር አመራሮች እና ወታደሮችን ከፊት ለፊት ማሰለፍና እዳይከዱና ወደ ፋኖ እዳይቀላቀሉ መከታተል ይላል መመሪያው። ይሄንን እቅድ ለማሳካት ደግሞ ለኦሮሞና ለደቡብ  ተወላጅ የጦር ሞኮንኖች በሚስጥር የማበራቻ ጠቀም ያለ ብርና መሬት መስጠት፣ነገር ግን እቅዳቸውን ካሳኩ በሁላ የሰጡትን ዳጎስ ያለ ገንዘብ ምንጩ ያልታወቀ በሚል ይነጠቃሉ የሚለውም የሰው በላው ስብስብ ከፍተኛ ጄኔራሎቼ በሚላቸው ጭምር ያስወሰነው ጉዳይ መሆኑንም የውስጥ ምንጮቹ አጋልጠዋል። በኦሮሚያ ክልል ከዚህ በፊት የተሰሩ የተመረቁ ተቋማትን በማደስና ተጨማራ ግንባታ በማድረግ ማስመረቅ ፣ትራክተር የውሃ ፓንፕ ኮፓይነር በማደል የኦሮሞ ህዝብ የስራዓቱ ተጠቃሚ እንዲል ማድረግ የሚለውም የዚሁ መመሪያ አካል ነው ብለዋል። ስልጣኑ ከእጃችን እዳይወጣ የድጋፍ ሰልፋ ብቻ ሳይሆን መሰዋእትነት እዲከፈሉ መስበክ፣ ይህ እድል ከእጃችን የሚወጣ ከሆነ ካልደገፉኝ ለሺህ አመት ባራያ  እዲሚሆኑ ማሳመን የሚለውም በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲደረግ የወረደ መመሪያ መሆኑን የኢትዮ 360 የውስጥ ምንጮች አጋግጠው መረጃውን አድርሰውናል። #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Показать все...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

👍 28 3
👍 7 1😱 1
የችሎት ውሎን በተመለከተ ***** ዛሬ ሐምሌ 3/2016ዓ/ም በፌዴራል አራዳ ምድብ ችሎት ሁለት መዝገብ የቀረበ ሲሆን አንደኛው በእነ ዮርዴኖስ አለሜ መዝገብ 12 ሰዎች ሲቀርቡ በሁለተኛው መዝገብ በአነ ሰለሞን ፍቃዱ ጣሴ መዝገብ 14 ሰዎች የቀረቡ ናቸው። የመጀመሪያው መዝገብ በእነ ዮርዴኖስ አለሜ መዝገብ ስር በሽብር ወንጀል ተከሰው ከሚገኙት መካከል፦ 1. ዮርዴኖስ አለሜ 2. ረዳት ፕሮ ሲሳይ አውግቸው 3. ጫናያለው ዘየደ ትርፌ 4. ሐሊማ አህመድ መሀመድ 5. ዮሐንስ ተሻገር (በለሌበት) 6. ኮንስታብል ባዜ ቢተው 7. አሸናፊ መለስ ይዘንጋው 8. ዳኛ አበበ ተሰሜ 9. ዋና ኢስፔክተር አፍርዱ ታከለ አስረስ 10. ረዳት ኢንስፔክተር ትዛዙ ይትባረክ ወንድይራድ 11. ሳጅን ወረሰ ወጣት 12. ጥላዬ ይታየው ንጉሴ ሲሆኑ ከሁለት ሰዎች ውጭ 10 ሰዎች ችሎት ቀርበዋል ማለት ነው። እነዚህም ዛሬ ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ለሐምሌ 12/2016 መልስ ይዛችሁ ቅረቡ ተብለዋል። የበሰበሰው የኦህዴድ ስርአት ከ12ቱ ተከሳሾች መካከል ዳኛ አበበ አሸናፊ መለሰ እና ኮንስታብል ሳሙኤል ባዜ አፋር ክልል በሰመራ ከፍተኛ ግፍ የተፈፀመባቸው መሆናቸውን እንዲሁም ጫንያለው ዘየደ እና ሐለማ አህመድ በግፈኞች በአዲስ አበባ ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ የተፈፀመባቸው ናቸው መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታቸውን አቅርበዋል። የሁለተኛ መዝገብ ተከሳሾች በእነ ሰለሞን ፍቃዱ መዝገብ የቀረቡት ደግሞ፦ 1. ሰለሞን ፍቃዱ ጣሴ 2. አሸናፊ ይሁነው ሞላ 3. ገብረማርያም ተካ ይመኑ 4. መሰረት ወርቁ አለሙ 5. ተስፋዬ ብርቁ ይማሙ 6. አማኑኤል ያለው አየልኝ 7. ሳሙኤል ያለው አየልኝ 8. ስንታየሁ አያሌው ከልካይ 9. ብርሃኑ ምንውዬ ድንቁ 10. ሐብታሙ አንዳርጌ ተሰማ 11. ወመርቅ አለልኝ ገሰሰ 12. ኤልያስ አዳነ ገብረእግዚአብሔር 13. ገበየሁ ሁሴ ያደታ 14. ታያቸው ክፍሉ ሞላ ናቸው። 14ቱም ተከሳሾች ቀርበዋል። ለሐምሌ 19/2016ዓ/ም ለዋስትና ቀጠሮ ተሰጥተዋል። እነዚህም ተከሳሾች አዲስ አበባ ተከፍቶ በነበረው በጀግኖች በእነ አርበኛ ፋኖ ናሁሰናይ አንዳርጌ በተካሄደው ኦፕሬሽን ተጠርጥረው የተከሰሱት ነቸው። እግዚአብሔር ያስፈታችሁ እያልን በተመሳሳይ በእነ ቴዎድሮስ ጣምራይ 26 ተከሳሾች ያሉበት ቀርበው እንደነበርና ነገር ግን በስህተት ነው ዛሬ የቀረባችሁ ለነገ ማለትም ለሐምሌ 4 እንድትቀርቡ ተብለዋል። https://t.me/Moamediamoresh
Показать все...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

👍 7🔥 1
👍 5
8.47 KB
👍 9😭 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
👍 5😁 1
ቴሌግራም እንደ ቲክቶክ መክፈል ጀምሯል። 15 ሰው ኢንቫይት በማድረግ Wallet ላይ Ton coin ይስሩ። ወደ ዶላር መቀየር ይቻላል። አሁኑኑ ጀምሩት 🙏 👑Help me to become best of the best in @Major and get some Stars! 30⭐️ invite bonus for you 100⭐️ if you are Premium Major https://t.me/Moamediamoresh
Показать все...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

👍 5
======አውደ ፋኖ====== አንዳንዴ… የምሰማቸው ፋኖን ያስመለከቱ የዳያስፖራ ወገኖቼ ንግግር በጥልቅ ሀዘን እንዲሰማኝ ያደርገኛል። ፋኖ፣ በቁጭት ለህልውናው ክብር ጠመንጃ ያነሳ የገበሬ ጦር አድርገው የሚያዩ፣ ፖለቲካ እና የቀለም እውቀት ያልዘለቀው ለሚመስላቸው እና ትግሉን ጠልፈው ባሻቸው መንገድ ለሚፍገመገሙ እርባና ያለው ሀሳብ የማካፍል ቢሆንስ ብዬ እንዲህ አሰብኩ። በቅርብ የማውቃቸውን የፋኖ አመራሮች ፈቃዳቸውን እየጠየቅሁ፣ "# በአውደ ፋኖ" ገፅ ማስተዋወቅ። ለዛሬም፣ ዝምተኛው ገዳይ The "#Silent Killer" በመባል የሚታወቅ አንድ ብርቱ ፋኖን በማስተዋወቅ የአውደ ፋኖን ገፅ ስራ እጀምራለሁ። ታደገ ይሁኔ ማን ነው⁉️ =የትውልድ ቦታ በቀድሞው አጠራር በጎጃም ክፍለ ሐገር በደብረ ማርቆስ አውራጃ በማቻ ስናን ወረዳ በአሁኑ በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ኤልያስ ወረዳ ልዩ ስሙ #ሙዛ በምትባል ትንሽዬ ቀበሌ ተወለደ። ==የት ተማረ? የአንደኛ ደረጃ ትቤቱን ትግል ፍሬ አንደኛ ደረጃ ትቤት ሁለተኛ ደረጃ ትቤቱን ደብረ ኤልያስ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃና መሠናዶ ትቤት የመጀመሪያ ደረጃ ትቤቱን ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ በተፈጥሮ ሳይንስ ስነ ስሪት(ኬሚስትሪ) የመምህርነት ስነ ሙያ ትምህርቱን በደብረ ብርሐን ዩኒቨርስቲ የማስተርስ ትምህርቱን በአዲስ አበባ የግል ኮሌጅ ሰሌክት የቢዝነስና ቴክኖሎጅ ኮሌጅ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ተማረ ==የትግል ሁኔታው ምን ይመስላል? ከ2002ዓም ጀምሮ የወያኔ  ስርዓትን አምርሮ በመጥላት ብዙ ትግል ሲያደርግ ከቆዬ በኃላ በ2009 ዓ.ም ደብረ ማርቆስ ላይ በነበረው ወያኔን ለመጣል የተደረገ ትንቅንቅ ብዙ የስቃይ ቀናትን አሳልፏል። በ2011ዓ.ም የአማራ ወጣቶች ማህበር እንደ አዲስ ሲዋቀር ብዙ ተግባራትን ሰርቷል። ወደ አዲስ አበባ በመምጣትም በመምህርነት ሙያ በማስተማር ተግባር አንቱታን አትርፏል። በ2013 ዓም አብንን በመወከል አዲስአበባ ላይ ከባልደራስ ጋር ጥምረት በመፍጠር ቃሊቲን ወክሎ ተወዳድሯል። በ2014 እና በ2015ዓም አብን በባንዳዎች መሸጡን ሲሰማ ካለማንም ደጋፊነት ለአማራ ህዝብ በአማራ ሚዲያ ማዕከልና በሚኒሊክ ቲሊቭዥን ተከታታይ ፖለቲካዊ ትንተናዎችን በመስጠት መረጃ ቲቪ ላይ እንዲቀርብ በማስደረግ ከጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ ጋር ብዙ ስራ ሰርቷል። ከ2015ዓም ሐምሌ ወር ጀምሮ ደግም የአማራ ህዝብ ጥያቄ እና የህልውና አደጋው  በእስክርቢቶ እንደማይቀለበስ ሲገነዘብ… በቀጥታ ከአዲስ አበባ በመውጣት ነፍጥ አነግቦ ወደ ጫካ ገብቷል። በአሁኑ ሰአት በጎጃም ክፍለ ሐገር የአማራ ፋኖ በጎጃም በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። ታደገ ይሆን፣ የአምሓራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ…  ለዘመናት ያስተዋልከው ጭቆና ወደ ጫካ የሸኘህ የነፃነት ስብከት ፊት አውራሪ ነህ። የፖለቲካ ንቃትክን እና ጥንካሬህን የምናውቅልህ እናውቃለን። የአምሓራ ህዝብ፣ የትውልዱ ኩራት እና ባላደራ ነህ። አንተ የትውልድ ምልክት ጓዳችን ሆይ!  ምልክታችን አድርገን እንከተልሃለን! እስከ ድል አጥቢያ፣ ከጎንህ የማንጠፋ የህዝብ ልጆች ነን!! 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Показать все...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

👍 19😁 1
👎 1
Выберите другой тариф

Ваш текущий тарифный план позволяет посмотреть аналитику только 5 каналов. Чтобы получить больше, выберите другой план.