ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
تُعد قناة ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 11 568 مشتركاً، محتلاً المرتبة 16 745 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 2 886 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 11 568 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 16 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -109، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.31%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.73% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 078 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 779 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 3.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 17 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 17 يوليو | 0 | |||
| 16 يوليو | +2 | |||
| 15 يوليو | +1 | |||
| 14 يوليو | +2 | |||
| 13 يوليو | 0 | |||
| 12 يوليو | +8 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | +2 | |||
| 09 يوليو | +2 | |||
| 08 يوليو | +4 | |||
| 07 يوليو | 0 | |||
| 06 يوليو | +2 | |||
| 05 يوليو | +1 | |||
| 04 يوليو | +6 | |||
| 03 يوليو | +4 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | +2 |
| 2 | የምትፃመደው በእርስትህ ላይ "የአማራ ወራሪ" እያለ ዐለም ዐቀፍ ክስ እና መግለጫ ከሚያወጣ፣ ሀገረ መንግስት ትግራይን ለማካለል የዐምሓራን እርስቶች ጎጆ መውጫ አድርጎ ለመውሰድ እየተሰናዳ ካለ ኃይል ጋር ነው።
አንዳች የትርክትም የዐላማም ለውጥ ሳያደርግ፣ የሚታገለው የአምሓራን እርስቶች ለመቀማት መሆኑን በኃላል እየቀሰቀሰ ካለ ኃይል ጋር የፋኖ ጥቅም ጋርዮሽ የቱ ጋ ነው? | 201 |
| 3 | ምክረ ዘመዴ…
እርስ በርስ ተጋደል
እርስበርስ ተላለቅ
አሸንፍ ወይ ተሸነፍ፣ የምን መመካከር የምን መወያየት ነው፣ ግደል ወንድምህን፣ አሳድድ ጓድህን እያለ ነው።
የአምሓራ ገና የመከራው መብዛቱ፣ በቅርብ የማይወጣው አረንቋ ውስጥ የመገኘቱ ምልክት ሌላ አይደለም። እንዲህ አይነቱን ውስጠ ሰርጎገብ አበጣባጭ እንደ ታጋይ ቆጥሮ ቁጭ ብሎ ምክር ይሰማል።
ይሔ ሰው፣ ጠቁሞ እና በሉት ብሎ ያላስገደለው፣ ያላስያዘው ፋኖ የለም።
ኮሌነል ጌታሁን
ሺ አለቃ ከፌን መሳዮች ፊት ለፊት የሚታወቁት ናቸው። | 66 |
| 4 | ኢራን የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤን በቋሚነት እንደምትቆጣጠር አስታወቀች
የኢራን ባለስልጣናት በአሜሪካ እና በእስራኤል የተጀመረው ጦርነት ከመነሻው አንስቶ የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤን "ቀይ መስመር" ወይም ሊጣስ የማይገባ ወሳኝ ጉዳይ አድርገው ሲገልጹት ቆይተዋል። ብሪጋዲየር ጄኔራል ኢብራሂም ዞልፋጋሪ በሰጡት መግለጫም ይህንኑ አቋም የሚያጠናክር ነው።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የኢራንን የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ መሰረተ-ልማቶች ስለማጥቃት በተደጋጋሚ መናገራቸው፣ ይህ መግለጫ የተሰጠዉ በወሳኝ ጊዜ እንዲሆን አድርጎታል።የወታደራዊው ዋና መስሪያ ቤት እንደገለጸው፣ አሜሪካ በኢራን መሰረተ-ልማቶች ላይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ብትፈጽም፣ ኢራንም በአካባቢው የሚገኙ መሰረተ-ልማቶች ላይ የአጸፋ ጥቃት ትሰነዝራለች። ኢራን እስካሁን ይህን ያላደረገችው አቅም ስለሌላት ሳይሆን፣ የመታቀብ ፖሊሲ ስላላት ነው ፤ ነገር ግን አሜሪካ እንደዚህ አይነት ጥቃቶችን ከፈጸመች ያ የመታቀብ ፖሊሲ ያበቃል ሲል መስሪያ ቤቱ አክሏል።
የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ እንደተናገሩት፣ የኢራን ብሔራዊ ደህንነት በሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤ ውስጥ "የኢራን አሰራሮችን" በመጠበቅ ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ "ጠላት" ይህንን በኃይል ለማዳከም እየሞከረ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።ኢራናውያን የሚያወሩት ስለ ሆርሙዝ ጊዜያዊ ቁጥጥር አይደለም፤ ይልቁንም ለዓለም የሚያስተላልፉት መልእክት ኢራን በዚህ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ ዘላቂ ቁጥጥር እና ሉዓላዊነት እንዲኖራት ነው። ይህ ደግሞ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ላለው ውጥረት ዋና ምክንያት ነው። | 378 |
| 5 | ታደሰ ወረደ ማሲንጋን እንዳያገኙ በደብረጺዮን ታገዱ ‼️
የቀድሞ የ #ትግራይ ጊዜያዊ ክልል አስተዳደር ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ ከ #አሜሪካው አምባሳደር ጋር እንዳይገናኙ መደረጋቸው ተገለፀ
የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በ #መቀለ ሊያደርጉት የነበረው ውይይት፤ የጸጥታ ኃይሎች ሌተናል ጄነራሉ ወደ ስብሰባው እንዳይጓዙ በመከልከላቸው ምክንያት መሰረዙን ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ገለጹ።
ይህ የሆነው አምባሳደር ማሲንጋ ለስራ ጉብኝት በዛሬው ዕለት መቐለ መግባታቸውን ተከትሎ ነው። ምንጮቻችን እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት የነበሩት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ከአምባሳደር ማሲንጋ ጋር ለመገናኘት የተያዘ ቀጠሮ የነበራቸው ቢሆንም፥ በደብረ ፂዮን የሚመራው የጸጥታ ኃይል ለጄነራሉ የተመደቡ ጠባቂዎች የጀነራሉን እንቅስቃሴ እንዲገድቡ መመሪያ ሰጥተዋል።
በአካል ሊደረግ የታቀደው ስብሰባ በደብረ ፂዮን ቀጥተኛ ትዕዛዝ ከተሰረዘ በኋላ፥ አምባሳደር ማሲንጋ እና ሌተናል ጄነራል ታደሰ በስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ምንጮቹ አክለዋል። | 1 026 |
| 6 | በዘረኛው እና ፋሽስቱ አብይ አህመድ የተካዱት የአርሲ ተጨፍጫፊ አምሓራ እና ኦርቶዶክሳውያን።
እነዚህን ይመስላሉ። ከተገደሉት መቶ በላይ ንፁሃን መካከል እናት እና ልጅ ህፃናት አረጋውያን ይበዙበታል። | 1 026 |
| 7 | የኬንያ፣ ጅቡቲ እና ሱዳን ከ40 እስከ 80 በመቶ የኃይል አቅርቦት የሚሰጠው ኢልፖ ለሀገር ውስጥ ግን "ድውይ ደካማ ነው" ተባለ።
ከአራት #ኢትዮጵያውያን መካከል አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚያገኘው አንዱ ብቻ መሆኑን አዲስ ጥናት አመለከተ
ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ላይ ለዓመታት ከፍተኛ መዋዕለ-ንዋይ ብታፈስም፥ ከአራት ኢትዮጵያውያን መካከል አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት የሚችለው አንዱ ብቻ መሆኑንና የገጠሩ ማኅበረሰብ በተመጣጠነ መልኩ ተጠቃሚ እንዳልሆነ አዲስ የወጣው የ«አፍሮባሮሜትር» ጥናት አመለከተ።
እ.ኤ.አ. ከግንቦት እስከ ሰኔ 2023 ባለው ጊዜ ውስጥ 2,400 ሰዎችን በማነጋገር የተጠናቀረው የአፍሮባሮሜትር ጥናት እንደሚያሳየው፤ ምንም እንኳ ግማሽ ያህሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀገር አቀፍ የኃይል መሰመር ዝርጋታ በደረሰባቸው አካባቢዎች የሚኖር ቢሆንም፥ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ አባወራዎች 43 በመቶ ብቻ ናቸው። ከዚህም በላይ «አብዛኛውን ጊዜ» ወይም «ሁልጊዜ» አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙት 26 በመቶ የሚሆኑት ዜጎች ብቻ መሆናቸውን ጥናቱ አመልክቷል። | 1 008 |
| 8 | #አምባሳደሩ መቀሌ ገቡ‼️
ቀጠናዊ ትስስር በመፍጠር የመደራደር ሐቅሙን ያሳደገው ህወሓት የአሜሪካ አምባሳደር መቀሌ ድረስ እንዲገኙለት እድል አግኝቷል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር አርቪን ሆሴ ማሲንጋ የተመራ ከፍተኛ የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድን ዛሬ ጠዋት መቀሌ ከተማ ገብቷል።
ልዑኩ በመቀሌ ቆይታው በአገዛዙ እና ህወሓት መካከል የተፈጠረው ልዩነት ለመፍታት እንደሚሞክርና ግጭት በቀጠናው እንዳይከሰት ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
አሜሪካ በቅርቡ በህወሃት አመራሮችና ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ መጣሏ ይታወሳል።
| 899 |
| 9 | "የምክክር ኮሚሽን" የተባለው የኦህዴድ ብልፅግና የድራማ አዛውንት ቡድን እየፈራረሰ ነው‼️
3ኛዋ ኮሚሸነር ሥራቸውን ለቀቁ🤔
ከ11 የምክክር ኮሚሽነሮች ከዚህ ቀደም 2ቱ የለቀቁ ሲሆን ምስጢር አወጣች ተብላ ከኮሚሽኑ ከታገደች ከዓመታት ቦኃላ ዶክተሬቷን ለመጨረስ የምክክር ኮሚሽኑ ሥራ ረጅም ጊዜ እንዲፈጅብኝ አሉታዊ አስተዋጽኦ አሳድሯል በሚል ምክንያት ሰሞኑን በይፋ ሥራ የለቀቀት ወ/ሮ ብሌን ገ/መድህን 3 ኛዋ ሆናለች። | 830 |
| 10 | #ቢያፍራ እና የኦህዴዱ አንበል ዛቻ‼️
#ፋሽስቱ እና የዘረኛው ኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ አንበሉ ዐብይ አህመድ ዛሬ ቢያፍራን አንስተው የሆነ ጽሑፍ ጽፈዋል።
ቢያፍራ ማነች?
የቢያፍራ ታሪክ በናይጄሪያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ታሪክ ውስጥ እጅግ አስከፊ እና ልብ ሰባሪ ከሆኑት ምዕራፎች አንዱ ነው። የቢያፍራን ታሪክ፣ በሕዝቡ ላይ የደረሰውን መከራ እና ዓለም ስለ ጉዳዩ የሚያውቀውን እውነት በሚከተለው መልኩ በዝርዝር እንመልከተው።
የቢያፍራ ታሪክ በአጭሩ
እ.ኤ.አ. በ1967 በናይጄሪያ ምስራቃዊ ግዛት የሚኖሩት የኢግቦ (Igbo) ብሔረሰብ አባላት በሀገሪቱ ውስጥ ይደርስብናል ያሉትን መድልዎ፣ ግድያና ጥቃት በመቃወም ራሳቸውን የቻሉ ሉዓላዊት ሀገር መመስረታቸውን አወጁ።
ይህቺ አዲስ የተመሰረተች ሀገር "የቢያፍራ ሪፐብሊክ" (Republic of Biafra) ተባለች። ይህንን ተከትሎ የናይጄሪያ ፌደራል መንግስት ግዛቱ እንዳይገነጠል ጦርነት በመክፈቱ ከ1967 እስከ 1970 የዘለቀው አስከፊው የናይጄሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት ተቀሰቀሰ።
በቢያፍራውያን ላይ ምን ተከሰተ?
በጦርነቱ ወቅት በቢያፍራ ሕዝብ ላይ እጅግ አሰቃቂ ሰብአዊ ቀውስ ደርሷል፦
የአየርና የባህር እገዳ (Blockade)፦ የናይጄሪያ መንግስት ወደ ቢያፍራ የሚገቡ ማናቸውንም የምግብ፣ የመድሃኒትና የዕርዳታ መስመሮች ሙሉ በሙሉ ዘጋ። ይህም በቢያፍራ ምድር ላይ ታይቶ የማይታወቅ ረሃብ አስከተለ።
የረሃብ እል ቂት (Kwashiorkor)፦ በጦርነቱ ከመሞተው በላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የቢያፍራ ህጻናት እና ንጹሃን ዜጎች በረሃብና በፕሮቲን እጥረት በሽታ (ኳሺዮርኮር) እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ አልቀዋል።
የህይወት መጥፋት፦ በሦስት ዓመት የጦርነት ጊዜ ውስጥ ከ500,000 እስከ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ የቢያፍራውያን ሕይወት መጥፋቱ ይገመታል። አብዛኞቹ የረሃብ ሰለባዎች ነበሩ።
የቢያፍራ መሸነፍ፦ ቢያፍራውያን በታላቅ ጀግንነት ቢከላከሉም፣ በረሃቡና በወታደራዊ የበላይነት በመሸነፋቸው እ.ኤ.አ. በጃንዋሪ 1970 እጃቸውን ሰጡ። ክልሉም በድጋሚ በናይጄሪያ ስር ተጠቃለለ።
ዓለም ስለ ቢያፍራ የሚያውቀው እውነት ምንድን ነው?
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ ቢያፍራ ያለው እውነት እና ትዝታ በሁለት ዋና ዋና ነጥቦች ይከፈላል፦
1. የመጀመሪያው በቴሌቪዥን የታየ የረሃብ እልቂት
ቢያፍራ በዓለም ታሪክ ውስጥ የረሃብ ምስሎች በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ለዓለም ሕዝብ የቀረቡበት የመጀመሪያው ክስተት ነበረች። የቢያፍራ ህጻናት አጥንታቸው ወጥቶና ሆዳቸው አብጦ የሚያሳዩ ፎቶግራፎች በመላው ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ልብ ሰብረዋል። ይህም በዓለም ታሪክ ትልቁን የሰብአዊ እርዳታ እንቅስቃሴ ቀስቅሷል።
2. የ"ድንበር የለሽ ሐኪሞች" (MSF) መፈጠር
በቢያፍራ የነበረው አስከፊ ሁኔታ እና በወቅቱ የነበረው የቀይ መስቀል ማህበር የፖለቲካ ገደቦችን በመፍራት እርዳታ በፍጥነት ማድረስ አለመቻሉ፣ ጥቂት ፈረንሳውያን ዶክተሮችን አስቆጣ። እነዚህ ዶክተሮች በጦርነትና በረሃብ ለሚሰቃዩ ወገኖች ያለ ፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ለመርዳት ዛሬ ዓለም የሚያውቀውን ታዋቂውን "የድንበር የለሽ ሐኪሞች ማኅበር" (Médecins Sans Frontières - MSF) እንዲመሰርቱ ምክንያት ሆኗል።
3. የዓለም ኃያላን ፖለቲካዊ አቋም
ስለ ቢያፍራ ያለው ሌላው እውነት የዓለም ኃያላን ሀገራት የገዛ ጥቅማቸውን ለማስከበር ያደረጉት ሴራ ነው።
ናይጄሪያን የደገፉ፦ የታላቋ ብሪታንያ መንግስት (ለነዳጅ ጥቅሟ ስትል) እና የሶቪየት ህብረት የናይጄሪያን የፌደራል መንግስት በጦር መሳሪያ በከፍተኛ ሁኔታ ደግፈዋል።
የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ ቢያፍራን ሲያስታውሱ የትኛውን ህዝብ ለማስፈራራ ለመጠቀም ነው?
ዶሮ ሲያውቅ ሆኖ ቅሉ… ከጦርነቱ የሚገኘው ውጤት ግን፣ የዲያፍራ ሳይሆን የሮም ሞሶሎኒ ድምሰሳ እንደሚሆን አናጣውም!
.
.
. | 813 |
| 11 | لا يوجد نص... | 786 |
| 12 | لا يوجد نص... | 868 |
| 13 | ልዑል አስፋወሰን አሰራት ከ1966ቱ አብዮት እስከ ወቅታዊው የብሔር ፌዴራሊዝም፣ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እና የፋኖ ሕዝባዊ ተጋድሎ በጥልቀት የተነተኑበት ልዩ ቃለ-መጠይቅ ሰጥተዋል!
(ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ 251 ሚዲያ)
የአውሮፓ የሕግና ፍትሕ ማዕከል (ECLJ) ከቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የልጅ ልጅ፣ ታዋቂው ደራሲና የንጉሣዊው ቤተሰብ አባል ልዑል አስፋወሰን አሰራት ጋር ያደረገውን ልዩና እጅግ ግልጽ የሆነ ቃለ-መጠይቅ ይፋ አድርጓል። ይህ ውይይት የ1966ቱን ታሪካዊ የአብዮት ውድቀትና ተያያዥ አሳዛኝ ክስተቶችን ከወቅታዊው የብሔር ፌዴራሊዝም መዋቅር፣ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ካለው ስልታዊ ጥቃት፣ ከፋኖ ሕዝባዊ ተጋድሎ እና ከአፍሪካውያን የስደት ቀውስ ጋር እያሰናሰለ በጥልቀት የዳሰሰ ነው።
አብዮቱ በፈነዳበት ወቅት የዘውድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የነበሩት የልዑሉ አባት የፈረንሳይን ፕሬዝዳንት የቀብር ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ፓሪስ ይገኙ እንደነበርና ልዑሉ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለሱ በአስቸኳይ መልዕክት በወቅቱ ቢያስጠነቅቋቸውም፣ አባታቸው ግን በችግር ጊዜ በዕድሜ ከገፉት ንጉሠ ነገሥት ጎን ለመቆም ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ መወሰናቸውን ያስታውሳሉ። ይህንን ተከትሎም አባታቸውን ጨምሮ 60 የንጉሣዊው ሥርዓት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ያለ ምንም ፍርድ በደርግ መረሸናቸውን በሐዘን አስታውሰዋል። ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ስለሞቱበት ሁኔታም ሲያብራሩ፣ የንጉሠ ነገሥቱ የግል አገልጋይ የሰጠውን እምነት የሚጣልበት ምስክርነት በመጥቀስ፣ ንጉሡ የሞቱት በተፈጥሮአዊ ምክንያት ሳይሆን በአልጋቸው ላይ በትራስ ታፍነው መሆኑን በግልጽ ተናግረዋል።
አያይዘውም፣ መላው የአገሪቱ የተማረ ክፍል እንዴት በወቅቱ ወደ ማርክሲስት-ሌኒኒስት ጽንፈኝነት ሊያዘነብል እንደቻለ አሁንም ድረስ ግራ የሚያጋባ ትልቅ እንቆቅልሽ መሆኑን ጠቁመው፣ የሚገርመው ግን በሞስኮ የተማሩት ሳይሆኑ በለንደን፣ በርሊንና በበርክሌይ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሩት ምሁራን ይበልጥ ጽንፈኛ ኮሙኒስቶች ሆነው መመለሳቸውንና ይህ ጽንፈኝነት ከ600 ሺህ በላይ ወጣቶችን ሕይወት ለቀጠፈው "ቀይ ሽብር" ሰበብ መሆኑን ገልጸዋል።
በቃለ-መጠይቁ ላይ ልዑል አስፋወሰን ካነሷቸው እጅግ ስሜት ቀስቃሽ ነጥቦች መካከል አንዱ የአገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካ መዋቅር ነው። ከደርግ ውድቀት በኋላ በ1991 ዓ.ም የተዘረጋውን ሕገ-መንግሥት "የአፓርታይድ ሕገ-መንግሥት" ሲሉ በጽኑ የኮነኑት ልዑሉ፣ ይህ መዋቅር ዜጎችን በጋራ ብሔራዊ ማንነት ሥር ከማስተሳሰር ይልቅ በብሔር እንዲከፋፈሉ ሆን ተብሎ የተቀረጸ ነው ብለዋል።
በልጅነታቸው ወቅት የክልል ወይም የብሔር አመጣጥ ለአብሮነታቸው ምንም ዓይነት ዋጋ እንዳልነበረውና ሁሉም ራሱን በኢትዮጵያዊነት ብቻ ይገልጽ እንደነበር በማስታወስ፣ እርስ በርስ በጋብቻና በደም በተሳሰረ ማኅበረሰብ ላይ የብሔር ፌዴራሊዝምን መጫን "ከፋፍለህ ግዛ" የሚለውን ስልት ለማስፈጸም የተደረገ ኢ-ሰብዓዊ ሙከራ መሆኑን አስረድተዋል። ታሪካዊው እውነታም ቢሆን፣ በአገሪቱ ታሪክ አልፈው የሄዱት ነገሥታት በሙሉ ከአንድ ወገን ብቻ የተገኙ "ንጹሕ" ብሔር ያላቸው እንዳልነበሩና የዘመኑ የብሔር ክፍፍል አባዜ ታሪካዊ መሠረት የሌለው መሆኑን አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ ሦስቱ የታላላቅ ሰማያዊ ሃይማኖቶች መገኛና ለዘመናት የዘለቀው ልዩ የሃይማኖቶች መቻቻል የነገሠባት አገር መሆኗን ልዑሉ በኩራት ገልጸዋል። ለዚህም ማሳያ እንዲሆን የመጀመሪያውን የስደት ጉዞ (ሂጅራ) በማስታወስ፣ የክርስቲያኑ የአክሱም ንጉሥ ከመካ የደረሰባቸውን ስደት ሸሽተው የመጡትን የመጀመሪያዎቹን ሙስሊም ስደተኞች እንዴት በጥበቃው ሥር እንዳስጠጋቸውና የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር የሚዘክረውን የሱረቱል መርየም የቁርዓን አንቀጽ በሰማ ጊዜ አልቅሶ በሃይማኖቶቻቸው መካከል ያለው ልዩነት የአንዲት መስመር ያህል ብቻ መሆኑን የተናገረበትን ታሪካዊ ክስተት አውስተዋል።
ይሁን እንጂ ይህ ታሪካዊና ውብ የአብሮነት መዋቅር በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ አደጋ ላይ መውደቁን ያስጠነቀቁት ልዑሉ፣ ወቅታዊው የፖለቲካ አየር ሁኔታ በተለይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ ስልታዊና ሆን ተብሎ የሚፈጸም ጥቃት እንዲበረታ ማድረጉን ጠቁመዋል። ይህ ጥቃት አገሪቱን አንድ አድርገው ያቆዩትን ሁለቱን ዋና ዋና ምሶሶዎች ማለትም ቤተክርስቲያንንና ዘውዱን በማዳከም አገረ መንግሥቱን ለማፍረስ ያለመ ስትራቴጂካዊ ሴራ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የአገሪቱን የወደፊት እጣ ፈንታ በተመለከተ ልዑል አስፋወሰን ሲናገሩ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እስካሁን ድረስ የሚመራበትን የሥርዓት ዓይነት በተመለከተ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የማድረግ ዕድል አግኝቶ እንደማያውቅ ገልጸዋል። በመሆኑም ሕዝቡ በሕገ-መንግሥታዊ ንጉሥ፣ በፓርላማ ሪፐብሊክ ወይም በፕሬዝዳንታዊ ሥርዓት መካከል መርጦ የሚመራበት ብሔራዊ ሕዝበ-ውሳኔ ሊዘጋጅ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ሕልውና ራሱ አደጋ ላይ መውደቁን የገለጹት ልዑሉ፣ የአሁኑን አምባገነን አገዛዝ ለመቋቋም እና ከብሔር ፌዴራሊዝም ሥርዓት ለመውጣት በአማራ ክልል እየተንቀሳቀሰ ላለው የፋኖ ሕዝባዊ ኃይል ያላቸውን ጠንካራ ድጋፍ ገልጸዋል። የፋኖ ሕዝባዊ ኃይል ከደቡብና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ካሉ አጋሮቹ ጋር በመሆን ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ግንባር በመፍጠር አገሪቱን ወደ አንድነትና ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ጎዳና ይመልሳታል የሚል ጽኑ ተስፋ እንዳላቸውም አመልክተዋል።
በቃለ-መጠይቁ ማጠቃለያ ላይ ልዑሉ እ.ኤ.አ በ2018 ያሳተሙትን "የአፍሪካ ስደት፦ ፍልሰትና የአውሮፓ የወደፊት ዕጣ ፈንታ" የተሰኘውን መጽሐፋቸውን መሠረት በማድረግ በዓለም አቀፉ ጂኦ-ፖለቲካ ላይ ሰፊ ትንታኔ ሰጥተዋል። እ.ኤ.አ በ2050 የዓለም ሩብ ሕዝብ አፍሪካዊ እንደሚሆንና የናይጄሪያ ሕዝብ ቁጥር ብቻውን ከመላው አውሮፓ አህጉር እንደሚበልጥ በመጠቆም፣ የጅምላ ስደት ዋነኛው መንስኤ በአፍሪካ ያለው የመልካም አስተዳደር እጦትና የአምባገነን መሪዎች መበራከት መሆኑን አስረድተዋል።
አውሮፓውያን እንደ ኮልታን ያሉ ማዕድናትን ለማግኘት ሲሉ ዲሞክራሲያዊ እሴቶቻቸውን በመተው ከአፍሪካ አምባገነኖች ጋር የሚያደርጉትን "ሪልፖሊቲክ" የተባለ ግብዝ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሊያቆሙ እንደሚገባም አሳስበዋል። በተጨማሪም የተለመደው የልማት እርዳታ ሙሰኛ የሆኑ የአፍሪካ ባለሥልጣናት ገንዘቡን መልሰው ወደ አውሮፓ ባንኮች እንዲያሸሹ ከማገዝ ውጭ ምንም ዓይነት ለውጥ አለማምጣቱን ጠቅሰዋል።
ለዚህም መፍትሔ ይሆን ዘንድ፣ የተለመደውን እርዳታ በማስቀረት የአምስት ዓመት ውል ያለው ስልታዊ የስደት ፕሮግራም (Circular Migration) ተግባራዊ እንዲሆን መክረዋል። በዚህም አውሮፓውያን ወጣቶችን በጤናና በተለያዩ የሰው ኃይል እጥረት ባለባቸው ዘርፎች አሠልጥነው ከቀጠሩ በኋላ፣ የውል ዘመናቸው ሲያበቃ የሠለጠኑት ዜጎች ወደ አገራቸው ተመልሰው የራሳቸውን የንግድና የኢኮኖሚ መዋቅር እንዲገነቡ በማድረግ ሁለቱንም ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ ዘላቂ አጋርነት መፍጠር እንደሚቻል ልዑሉ በሰፊው አብራርተዋል።
M | 830 |
| 14 | لا يوجد نص... | 646 |
| 15 | የወንድማችን ትንግርቱ ብሩህ የፖለቲካ ትንተና አዳምጡለት። በዋናነት በጎንደር ፋኖ ወቅታዊ አቋም ጉዳይ ላይ የሰጠው ትንተናን የጎንደር ፋኖ አመራሮች ታዳምጡ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
የፋኖ አመራሮች ወደ ፊት እየወጣችሁ ህዝብን አስቆጭ እና ከድጋፍ ነጣይ ንግግሮችን ማቆም ትችሉ ዘንድ ከTPLF መልከ ብዙ አካሔድ ልምድ ውሰዱ።
https://www.youtube.com/live/sXgOubMBU0U?si=7QxnzfXHVRmPcn0Q | 726 |
| 16 | https://www.facebook.com/profile.php?id=61571637893418
ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም
ሞዐ ሚዲያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
https://t.me/Moamediamoresh | 558 |
| 17 | አከራዮች ላይ ከተማ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ እወስዳለሁ አለ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያን 11.5 በመቶ ማድረጉን ተከትሎ፣ ሕግን በመጣስ በህገ-ወጥ መንገድ የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ አከራዮች ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
በተለይም ተከራዮችን “ቤቱን ለራሴ ወይም ለዘመዴ እፈልገዋለሁ” በሚል ሐሰተኛ ምክንያት በማስለቀቅ፣ በምትኩ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ በመጫን፣ የ11.5 በመቶውን ጭማሪም ሕጋዊ አስመስለው የመጫን ተግባራት በስፋት እየተስተዋሉ ነው።
በተጨማሪም፣ አከራዮች በውል ሰነድ ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ11.5 በመቶ ጣሪያ በመጥቀስ በሕጋዊ መንገድ እየተስማሙ፣ በተግባር ግን በአፍ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ በመደራደር ተከራዩን ለከፍተኛ የገንዘብ ጫና የሚዳርጉበት የ”ድርብ ውል” አሰራር የተለመደ እየሆነ መምጣቱን የተሰጡ ጥቆማዎች ያመለክታሉ። ይህ ድርጊት በግልጽ ሕግ ተጠያቂ የሚያደርግ ሕገ-ወጥ ተግባር መሆኑን ቢሮው አስገንዝቧል።
በዚህ ረገድ ተከራዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል። በተለይም በአፍ የተጠየቀው ከፍተኛ የክፍያ ዋጋ በውል ሰነድ ላይ ካልተቀመጠ፣ ተከራዮች ክፍያቸውን ሁልጊዜ በባንክ በኩል ብቻ እንዲፈጽሙ በማድረግ ሕገ-ወጥነቱን በማስረጃነት እንዲይዙ መክሯል።
ቢሮው አክሎም፣ አከራዮች መተሳሰብና ሰብአዊነትን እንዲያስቀድሙ ጥሪ በማቅረብ፣ ሕግ ተላልፈው በሚገኙት ላይ ከባድ አስተዳደራዊና ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ በጥብቅ አስጠንቅቋል። ማህበረሰቡም ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር በጋራ ለመከላከል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል። | 754 |
| 18 | لا يوجد نص... | 755 |
| 19 | የአብይ ጦር አስገድዶ መድፈር ፈፀመ‼️
በፍላቂት ከተማ በታዳጊ ህጻናት ላይ አሰቃቂ ተከታታይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ ተሰማ፤ ጥቃቱን የፈጸሙት ወታደሮች መሆናቸው ተገልጿል
ፍላቂት (ሰሜን ወሎ) — በሰሜን ወሎ ዞን መቂት ወረዳ ፍላቂት ከተማ ውስጥ ባለፉት ጥቂት ቀናት በታዳጊ ህጻናት ላይ ተከታታይነት ያለውና አሰቃቂ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙን ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች አጋለጡ። ወንጀሉ የተፈጸመው በአካባቢው ስምሪት ላይ በሚገኙት የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት መሆኑን የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል።
የመጀመሪያው ጥቃት (ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም)፦ በፍላቂት ከተማ “ጮጓሬ መስክ” ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ አንዲት የስምንት ዓመት ታዳጊ ልጅ በአንድ የመከላከያ አባል አስገድዶ መድፈር ተፈጽሞባታል። ታዳጊዋ በጥቃቱ ሳቢያ ለከባድ የጤና ቀውስ የተዳረገች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በሸደሆ መቄት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ራሷን ስታ በሕክምና ላይ ትገኛለች።
የሁለተኛው ጥቃት (ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም)፦ በአራት ቀናት ልዩነት (በዛሬው ዕለት) ፍላቂት ከተማ “የድሮው ሐሙሲት” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተመሳሳይ መልኩ ሌላኛዋ የዘጠኝ ዓመት ታዳጊ ልጅ በሌላ የመከላከያ አባል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈጽሞባታል። ይህችም ታዳጊ በተመሳሳይ መልኩ በሸደሆ መቂት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለሕክምና ገብታለች።
(ከቦታው በቀጥታ የተላከ መረጃ) | 935 |
| 20 | የ #ሱዳን ጦር በኤል ኦቤይድ አቅራቢያ #ቻይና ሰራሽ ድሮን መትቶ መጣሉን አስታወቀ
የሱዳን መደበኛ ጦር ከፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ጋር የሚያደርገው ውጊያ በበረታበት በዚህ ወቅት፣ በሰሜን ኮርዶፋን ግዛት በኤል ኦቤይድ (El Obeid) ከተማ አቅራቢያ ዘመናዊና የቻይና ምርት የሆነች ድሮን መትቶ መጣሉን አስታወቀ። ጦሩ በአንድ ወር ውስጥ ተመሳሳይ የድሮን ምርት መቶ ሲጥል የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑ ተመልክቷል።
የሱዳን መከላከያ ትላንት ሰኞ ዕለት ባወጣው መግለጫ፥ የአየር መከላከያ ሥርዓቱ «ኤፍኤች-95» (FH-95) የተሰኘች ስልታዊ ድሮን ከኤል ኦቤይድ በስተሰሜን ምዕራብ አቅራቢያ መትቶ መጣሉን ገልጿል። ወታደራዊ ተቋሙ ድሮኗን የጠላት ሰው አልባ አውሮፕላን ሲል የገለጻት ቢሆንም፥ ስለ ኦፕሬሽኑ ዝርዝር ሁኔታ ግን ተጨማሪ ማብራሪያ አልሰጠም።
እንደ ሱዳን ጦር ገለጻ፥ ይህ በአንድ ወር ውስጥ የተመታች ሦስተኛዋ የኤፍኤች-95 ድሮን ናት። የመጀመሪያዋ ድሮን በሰኔ 25 ቀን በኋይት ናይል ግዛት በቴንደልቲ አካባቢ የተመታች ሲሆን፥ ሌላኛዋ ደግሞ በሚቀጥለው ሳምንት ካርቱምን እና ሰሜን ኮርዶፋንን በሚያገናኘው አውራ ጎዳና ላይ መመታቷን ጦሩ አስታውቋል። | 797 |
