ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
تُعد قناة ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 11 634 مشتركاً، محتلاً المرتبة 16 683 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 2 874 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 11 634 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 10 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -66، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.19%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.87% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 069 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 799 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 4.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 11 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 10 يوليو | +2 | |||
| 09 يوليو | +2 | |||
| 08 يوليو | +4 | |||
| 07 يوليو | 0 | |||
| 06 يوليو | +2 | |||
| 05 يوليو | +1 | |||
| 04 يوليو | +6 | |||
| 03 يوليو | +4 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | +2 |
| 2 | ወደ አማርኛ ከመተርጎሜ በፊት ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያን ስለዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ? እውነት የኦሮሞን መሬት የያዘችው ኦርቶዶክስ ብቻ ናት ወይ? በአንድ ኪሎሜትር በማይሞላ ርቀት ሦስትና አራት ቤተ እምነት የተሠራው የኦርቶዶክስ ነው? ኦርቶዶክስ የኦሮሞን መሬት ወረረች ከተባለ እስልላሞች መስጊዶ ከሳዑዲ ዓረቢያ በመጣ አፈር ላይ ነው የተሠራው? ወይስ በአየር ላይ? ፕሮቴስታንት ቸርች ከጀርመን በመጣ አፈር ላይ ነው የተሠራው? የካቶሊኩስ ከቫቲካን በመጣ አፈር ላይ ነው የተሠራው?
እናንተስ ስለዚህ ጉዳይ ምንትላላችሁ? Yaada Keessan nuuf qoodaa | 645 |
| 3 | በ #ኢራን እና በ #አሜሪካ መካከል በተቀሰቀሰው አዲስ ውጥረት ምክንያት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የንግድ መርከቦች ጉዞ በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ
በኢራን እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል እንደገና ባገረሸው ወታደራዊ ግጭት ምክንያት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚደረገው የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን በ #እንግሊዝ የሚገኘው ሎይድስ ሊስት ኢንተልጀንስ «Lloyd’s List Intelligence» የተባለው የባሕር ትራንስፖርት መረጃ ተቋም አስታወቀ።
ይህ የእንቅስቃሴ መቀነስ የመጣው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ሦስት የነዳጅ ጫኝ መርከቦች የጥቃት ኢላማ መደረጋቸውን ተከትሎ በተቀሰቀሰው አዲስ ጥቃት ሲሆን፤ በዚህም አሜሪካ በኢራን 90 በሚደርሱ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት ሰንዝራለች።
በተጨማሪም ኢራን የአሜሪካ ጦር ኃይሎችን በሚያስተናግዱት እና የአሜሪካ አጋር በሆኑት እንደ #ባህሬን፣ #ኩዌት እና #ኳታር ባሉ የባሕረ ሰላጤው አገራት ላይ ጥቃቶችን የሰነዘረች ሲሆን፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል ተደርሶ የነበረው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ማብቃቱን ይፋ በማድረግ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ ማስጠንቀቃቸውን ሪፖርቱ ጠቅሷል። | 856 |
| 4 | ኦህዴድ ብልፅግና ለጭፍጨፋ ተጠቅሞበት እንደ በቅሎ አውጥቶ የጣለው የጦር መኮነን።
ለዚህ ስርዓት ወንበር ጠባቂነት የቆማችሁ በጊዜ አማራጭ ያዙ! | 935 |
| 5 | ግብፅ የአፍሪካን የኒውክሌር ዘመን ለመምራት መቃረቧ ተገለፀ
🗣 "ግብፅ በዚህ የኃይል ማመንጫ በአፍሪካ ትልቁ የኒውክሌር ኃይል ለመሆን ተቃርባለች" ሲሉ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ በኤል ዳባ የኒውክሌር ጣቢያ ሁለተኛ የኃይል ዩኒት ተከላ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተናግረዋል።
የሮሳቶም ኃላፊ አሌክሲ ሊካቼቭ በበኩላቸው፤ የዚህ ፕሮጀክት እጅግ ጉልህ ውጤት ለግብፅ ለኢኮኖሚ እና ለኢንዱስትሪ ልማት አዳዲስ እድሎችን ማምጣቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
✔️ የሁለተኛው የኃይል ዩኒት ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እየተከናወነ እንደሚገኝ የዩኒቱ የግንባታ ኃላፊ ሚካሂል ስያትኪን ለስፑትኒክ ተናግረዋል። | 768 |
| 6 | ሰውዬው የኦህዴድን ተልዕኮ ማሳለጥ ጀምረዋል።
ፊት ለፊት ቅጥር እና ዝውውር አግደው በውስጥ የኦህዴድ ሰዎችን እየሰገሰጉ ነው። | 698 |
| 7 | የኦህዴድ መራሹ ብልጽግና ታሪካዊ ቅርሶችን፣ የንግድ ተቃማትንና መኖሪያ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ መርካቶ ገባ!!!
በመርካቶ ጣና ገበያ ፊትለፊት ያሉ ከ200 በላይ የንግድ ሱቆች ስለሚፈርሱ ባለሱቆቹ በ20 ቀናት ውስጥ እቃቸውን ጣጥለው እንዲወጡ መዘዙ
መርካቶ በሚገኘው ጣና የገበያ ማእከል ፊት ለፊት የሚገኙ የንግድ ሱቆች በአፋጣኝ እንዲፈርሱ ተወስናል። ከ200 በላይ የንግድ ሱቅ ባለቤቶችም በ20 ቀናት ውስጥ ጓዛቸውን ሸክፈው በመውጣት ቦታውን እንዲያስረክቡ ቀጭን ደብዳቤ የደረሳቸው ሲሆን አገዛዙ በስፍራው የንግድ ማእከል እገነባለሁ በማለት በፌዴራል ቤቶች ኮሮፖሬሽን ኃላፊ በሆነው በአቶ አማኑኤል በኩል ምላሽ ሰጥታል።
የሚፈርሱት ሱቆች ጣና የገበያ ማእከል ፊት ለፊት ያሉትና ሲኒማ ራስ ተብሎ በተለምዶ አጠራር በሚጠራው ጎን ያሉ ቤቶች ናቸው ቦባልም ሲኒማ ራስ ከመፍረስ ስለመትረፉ የተገለጸ ነገር የለም።
ባለፈው እሁድ ለሊት ጨለማን ተገን አድርገው ያፈረሱት ሲኒማ ኢምፓየር በአደነች አቤቤ በኩል ለአንድ አመት በፊት የማይፈርስ የታሪክ ቅርስ ነው ተብሎና እድሳት ተደርጎለት ለሕዝብ ተገልጾ የነበረ ሲሆን ዛሬም ሲኒማ ራስ አጠገብ ያሉትን የንግድ ሱቆችን ብቻ አፍርሶ ሲኒማ ራስን ከማፍረስ ይታቀባል ብሎ ማሰብ የሚቻል አይደለም።
ከ 200 በላይ ሱቆች ባለቤት የተሰጣቸው 20 ቀን ብቻ ሲሆን ምትክ የመነገጃ ሱቅ ፈጽሞ አልተዘጋጀላቸውም። | 638 |
| 8 | የኦህዴድ መራሹ ብልጽግና ታሪካዊ ቅርሶችን፣ የንግድ ተቃማትንና መኖሪያ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ መርካቶ ገባ!!!
በመርካቶ ጣና ገበያ ፊትለፊት ያሉ ከ200 በላይ የንግድ ሱቆች ስለሚፈርሱ ባለሱቆቹ በ20 ቀናት ውስጥ እቃቸውን ጣጥለው እንዲወጡ መዘዙ
መርካቶ በሚገኘው ጣና የገበያ ማእከል ፊት ለፊት የሚገኙ የንግድ ሱቆች በአፋጣኝ እንዲፈርሱ ተወስናል። ከ200 በላይ የንግድ ሱቅ ባለቤቶችም በ20 ቀናት ውስጥ ጓዛቸውን ሸክፈው በመውጣት ቦታውን እንዲያስረክቡ ቀጭን ደብዳቤ የደረሳቸው ሲሆን አገዛዙ በስፍራው የንግድ ማእከል እገነባለሁ በማለት በፌዴራል ቤቶች ኮሮፖሬሽን ኃላፊ በሆነው በአቶ አማኑኤል በኩል ምላሽ ሰጥታል።
የሚፈርሱት ሱቆች ጣና የገበያ ማእከል ፊት ለፊት ያሉትና ሲኒማ ራስ ተብሎ በተለምዶ አጠራር በሚጠራው ጎን ያሉ ቤቶች ናቸው ቦባልም ሲኒማ ራስ ከመፍረስ ስለመትረፉ የተገለጸ ነገር የለም።
ባለፈው እሁድ ለሊት ጨለማን ተገን አድርገው ያፈረሱት ሲኒማ ኢምፓየር በአደነች አቤቤ በኩል ለአንድ አመት በፊት የማይፈርስ የታሪክ ቅርስ ነው ተብሎና እድሳት ተደርጎለት ለሕዝብ ተገልጾ የነበረ ሲሆን ዛሬም ሲኒማ ራስ አጠገብ ያሉትን የንግድ ሱቆችን ብቻ አፍርሶ ሲኒማ ራስን ከማፍረስ ይታቀባል ብሎ ማሰብ የሚቻል አይደለም።
ከ 200 በላይ ሱቆች ባለቤት የተሰጣቸው 20 ቀን ብቻ ሲሆን ምትክ የመነገጃ ሱቅ ፈጽሞ አልተዘጋጀላቸውም። | 1 |
| 9 | ከወለጋ ዘር ፍጅት ከሞት አምልጠው በመኪና እና በእግር ተጉዘው የአዲስ አበባ መግቢያ አምቦ መውጫ ላይ በኦህዴድ አዲስ አበባ እንዳይገቡ የተከለከሉት የአምሓራ ተወላጆችን አስታወስኩ። በመጨረሻም በአዲስ አበባም እንዳይሰፍሩ ተከልክለው በሌሊት ወደ ደብረ ብርሃን እንዲያልፉ የተደረገው በነ አብይ አህመድ እና አዳነች አበቤ አዲስ አበባ ድርሽ እንዳይሉ ተከልክለው ነበር።
አምሓራ ጠልነት የስርዓቱ መለያ ቀለም ነው።
የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ መስተዳድር ለትግራይ ተወላጆች የሚያደርገው እንክብካቤ ድራማዊ ውስጠ ጩቤም ቢሆን መልካም ሆኖ… የደረሰብንን ግፍ ግን አስታወሰኝ። | 662 |
| 10 | ዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት፣ ኢትዮጵያ ለኢቦላ ወረርሽኝ የመጋለጥ እድሏ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል አለ።
ድርጅቱ፣ አገሪቱ ለበሽታው ከመጋለጥ አንጻር በከፍተኛ ደረጃ "ቅድሚያ" ከሚሠጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ላይ ገልጧል።
ድርጅቱ ኢትዮጵያ ለበሽታው በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ መኾኗን የገለጠው፣ ዓለማቀፍ ተጓዦች በብዛት የሚያልፉባት፣ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የመጓጓዣ ኮሪደሮች ያሉባትና በሽታው ከተከሠተባቸው አካባቢዎች ጋር ያላት ድንበር ክፍተት ያለበት መኾኑን በመጥቀስ ነው።
በድርጅቱ ሪፖርት መሠረት፣ ቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የድሬዳዋ፣ መቀሌ እና የባሕርዳር አውሮፕላን ማረፊያዎች፤ የሞያሌ፣ መተማ፣ ጋላፊ፣ ደዋሌ፣ ፓጋክ እና ኩርሙክ የድንበር መግቢያና መውጫዎች እንዲሁም የድሬዳዋ የባቡር ጣቢያ ቅድሚያ ትኩረት የሚሠጣቸው ቦታዎች ናቸው።
ድርጅቱ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ቀንድ፣ ምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ለ12 አገሮች በሽታውን ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የ55 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር እቅድ የነደፈ ሲኾን፣ ከድጋፉ ውስጥ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላሩ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓትና በድንበርናና ኮሪደሮች አካባቢ የጤና ተቋማትን ለማጠናከር እንደሚውል ገልጧል። | 727 |
| 11 | መነኮሳት ወደ መነኮሱበት ገዳም የሚመልሰው አዋጅ
[የኛ ሲኖዶስ የሄን ማድረግ የሚችል መንፈሣዊ ልብ ይኖረው ይሆን?
በኮፕት ቤተ ክርስቲያን ታሪኮች ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ካመጡት አዋጆች አንዱ በ ፓትርያሪክ ቅዱስ ቄርሎስ 6ኛ (እ.ኤ.አ. August 1960) የታወጀው ጠንካራ ትእዛዝ (አዋጅ) ነበር ፤ ትእዛዙም መነኮሳት እስከ September 30 ድረስ ምንኩስናን ወደተቀብሉበት ገዳም እንዲመለሱ ፣ ካልተመለሱ ግን ከማዕረጋቸው እንደሚሻሩና እንደ ተራ ምዕመን ሆነው እንዲኖሩ ፤ ምእመናንም ለነዚህ ትእዛዝ ጣሽ መነኮሳት ምንም ዓይነት የገንዘብ ድጋፍ እንዳያደርጉና እንዳያበረታቷቸው የሚያዝ ፤ በጊዜው እውቅ በተባሉት አል አህራምና ሚስር ጋዜጦችም ታትመው ለሕዝብ እንዲቀርቡ ተደርጎ ነበር፡፡
ቄስ ዳንኤል የቅዱስ ቄርሎስን ህይወት በዘገበበት A Silent Patriarch በተሰኝው ድንቅ መጽሐፍ አዋጁ ለምን እንዳስፈለገ ሲያረዳ አምስት መሰረታዊ ነገሮችን እንድንገነዘብ ያደርገናል።
1ኛ የምንኩስና ሥርዓትና ዲሲፕሊንን ማደስ (በከተማ አልለ ዘለል ና የ ሁካታ ኑሮ ተዳክሞ የነበርውን ምንኩስና ወደ ገዳማዊ ጽጥታ በመመልስ ገዳማት ወደ ቀደመ የጽሕፈትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶችነት መመለስ )
2ኛ ለተማሩ ካህናት የሥራ ዕድል መፍጠር (በወቅቱ በከተማ ያሉ ደብሮች በመነኮሳት ተይዘው ስለነበርና ከቴዎሎጂ ኮሌጅ የሚመረቁ ካህናት (married priests) የሚያገለግሉበት ቦታ አጥተው ነበር ፤ በመሆኑም መነኮሳቱ ወደ በአታቸው ሲመለሱ እነዚህ የተማሩ ካህናት ህዝብን በዕውቀት እንዲያገለግሉ ማስቻል)
3ኛ የገዳምት ህዳሴን ማፋጥን (ከመነኮሳት ወደ ከተማ መፍለስ ጋር በተያያዘ ገዳማት ባዶ እየሆኑ ስለነበር ሁሉም መነኮሳት ወደየ በአታቸው እንዲመለሱ መደረጉ ለገዳማቱ መጠናከር ፣ መልማትና ወደ ቅድስና ማዕከልነታቸው መመልስ)
4ኛ መጪውን ትውልድ ሚዋጁ የኤጲስ ቆጶሳትን መፍጥር (የቤተ ክርስቲያን የኤጵስ ቆጶሳት ከመነኩሴዎች እንደ መመረጣቸው ፤ በገዳማት ኖረው የተማሩና የተገሩ መነኮሳት ለጵጵስና ማዕረግ ሲጠሩ እውቀት ከቅድስና አስተባብረው ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገለግሉ ማስቻል )
5ኛ አስተዳደራዊና ፋይናንሳዊ ችግሮችን መፍታት። (መነኮሳቱ በከተማ ውስጥ ያለ ቁጥጥር መኖራቸው ለገንዘብና አያያዝ ጉድለት እንዲሁም ውሉ ለጠፋ አስተዳደራዊ ምስቅልቅሎሽ ምክንያት ሆኖ ስለነበር ያንን ለማረቅ ማስቻል።)
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ አምስት መሠረታዊ ሃሳቦች ቅዱስ አባታችን ላይ ብዙ ክስ ቢያስነሱም በመጨረሻ ግን በ አፈጻጽም ጥንካሬአቸው የተነሳ ለቤተክርስቲያንዋ አስተዳደራዊ ሥርዓትና ለልጆችዋ ነፍስ መዳንና ትሩፋትን ይዘው መጥተዋል ፤ ያኔ የተንቆጫቆጩም ቢሆኑ ዛሬ ውሳኔውን እያመሰገኑ ይኖራሉ፡፡ የኛው ቅዱስ ሲኖዶስ ይህን አይነት ውሳኔ የማሳለፍ ፣ የመከታተልና የማስፈጸም ልብና አቅም ይኖረው ይሆን??
@Kaleb berhanu | 620 |
| 12 | በቅርቡ በአርሲ የተፈፀመውን ጭፍጨፋ በካደ መልኩ ሪፖርት ያደረገው ኢሰመኮ ስጋቱን ሪፖርት አደረገ‼️
" የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ "የታጠቁ አካላት መበራከት"፣ "ሕገወጥ የሲቪሎች ግድያ"፣ "የዘፈቀደ" እና "የተራዘመ" እስር፣ "አስገድዶ መሠወር"፣ "ጠለፋ" እና "የጾታ ጥቃት" ለአዲሱ የአምስት ዓመት እቅዱ ትግበራ እንቅፋት ሊኾኑበት እንደሚችሉ ስጋቱን ገለጠ። ማሰቃየት፣ ኢሰብዓዊ አያያዝ፣ የጦርነት ስጋቶች፣ ሰብዓዊ ጥሠት በሚፈጽሙ አካላት ላይ የተጠያቂነት ጉድለት፣ በነጻ መገናኛ ብዙኀንና ጋዜጠኞች ላይ እየጨመሩ የሄዱ ገደቦች እንዲሁም በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ርምጃዎች ጭምር በእቅዱ መሳካት ላይ እንቅፋት ሆነው ሊቀጥሉ ይችላሉ ብሎ መለየቱን ኮሚሽኑ ጠቅሷል። ኮሚሽኑ እነዚህን ስጋ የገለጠው፣ ከ2019 እስከ 2023 የሚተገበረውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱን ዛሬ ይፋ ባደረገበት መድረክ ላይ ነው። ኮሚሽኑ፣ የስትራቴጂክ እቅዱ ትግበራ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ አስታውቋል። | 620 |
| 13 | "የምንተማመነው በራሳችን ኃይል ብቻ ነው፣ ከማንም ጋር ፅምዶ የለንም"
TPLF
"ለአምሓራ ከትግራይ በላይ ወዳጅ የለውም" ጄ/ተፈራ ማሞ
♨️ #ሕወኃት #ኤርትራ እና #ሱዳንን እንዲሁም ፋኖን ያካተተ ጥምረት ፈጥሯል በማለት ፋሽስቱ ዐቢይ ያቀረቡበትን ክስ ውድቅ አደረገ፤ «እኛ በራሳችን ኃይል ነው የምንተማመነው ከማንም ፅምዶ የለንም» ብሏል
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወኃት)ከኤርትራ እና ከሱዳን ጋር በጋራ እየሠራ ነው በማለትጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሰነዘሩበትን ክስ ውድቅ አደረገ። ቡድኑ ከየትኛውም የውጭ አካል ወታደራዊ ድጋፍ እንደማይፈልግ እና «በራሱ ኃይል እንደሚተማመን» ገልጿል።
ይህ ምላሽ የተሰጠው ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ ባለፈው ማክሰኞ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ፥ ሱዳን፣ ሕወኃት እና ኤርትራ እና ፋኖ በጋራ እየሠሩ መሆኑን በመጥቀስ፤ ይህንን ሁኔታ እ.ኤ.አ. በ1991 የደርግ ሥርዓት እንዲወድቅ ካደረገው ጥምረት ጋር በማመሳሰል ከሰጡት አስተያየት በኋላ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የተባለው ጥምረት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚያመጣው አደጋ የለም ቢሉም፥ ስማቸውን ያልጠቀሷቸው የውጭ አካላት ከጀርባ ሆነው እየመሩት መሆኑን ጠቁመዋል።
ለእነዚህ ክሶች ምላሽ የሰጡት የሕወኃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አስገዶም፤ ድርጅታቸው አብረውት ተሰልፈው እንዲዋጉለት የውጭም የውስጥም አካላትን በፍጹም ጋብዞ አያውቅም፣ የምንተማመነው በራሳችን ኃይል ነው ብለዋል።
https://addisstandard.com/Amharic/?p=13260 | 628 |
| 14 | ብዙ ያልተወራለት አነጋጋሪው 'የስራ አጡ' ማሞ ምህረቱ ቃለ-ምልልስ!
የአብይ ብሔራዊ ባንክ የቀድሞ ገዢ የነበሩት አቶ ማሞ ምህረቱ የዛሬ ወር ገደማ የሰጡትና ፣ የሰሩትን ግፍ ሁሉ የተናዘዙበት ቃለ-ምልልስ አነጋጋሪ ሆኗል።
አቶ ማሞ ምህረቱ VoxDev ከተሰኘ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ በስፋት የሚሰራ ሚዲያ ጋር ባደረጉት የ50 ደቂቃ ቆይታ ፦👇
''ኢህአዴግ ኢኮኖሚውን በሁለት ዲጅት አሳድጎት ነበር ፣ ኢንቨስትመንት አድጎ ነበር ፣ ትልልቅ ካምፓኒዎች ገብተው ነበር... መለስ የውጭ ባለሃብቶችን ለመቀበል በለሊት ኤርፖርት ይሄዱ ነበር ፣ የኢንዱስትሪ ፓርክ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል"
''አብይ ደግሞ በትግራይ ጦርነት ምክንያት ኢኮኖሚውን ለIMF ሽጦታል ፣ የአግዋ የታክስ ነፃ ተጠቃሚነት ተቀምተናል ፣ በኢህአዴግ ዘመን የገቡ በተለይ በአዋሳ ኢንዱስትሪ ካምፕ የነበሩ ካምፓኒዎች ለቀው ወጥተዋል ፣ ብዙ ወጣቶች ስራ አጥተዋል ፣ ኤክስፖርት ቀንሷል የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ተዳክሞል''
'' ምን አይነት ፖሊሲ እንደሚከተል አይታወቅም ፣ ግልፅ መመሪያ የለም ፣ በዚህ ውጥንቅጡ በወጣ የኢኮኖሚ ተግባር ላይ በመሳተፌ እፀፀታለሁ"
"እኔ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆኜ ስሾም ... #ብልፄ ኢኮኖሚውን ከማሽመድመዱ የተነሳ አንድ ሺ ዶላር ለመስጠት ሁለት አመት ሙሉ ቀጠሮ ይሰጥ ነበር ... በዚህ ሁኔታ #ኢትዮጵያን ለIMF ከመሸጥ ውጪ አማራጭ አልነበረም!" በማለት ከአብይ ጋር ሆነው መቀመቅ ያወረዱትን የሀገር ኢኮኖሚና የሸጧትን ሀገር አጠቃላይ እውነታ አፍረጥርጠውታል!
አቶ ማሞ የጨቅላውን ትእዛዝ ለመፈፀም ሲሉ ከሙያዊ ክህሎታቸው አፈንግጠው በሰሩት እጅግ አሳፋሪ ተግባር ሲቪአቸው ተበላሽቶ ''የቀጣሪ ያለህ!'' እያሉ የሚገኙ ቢሆኑም ፣ ከረፈደም ቢሆን ለአመታት ስንወተውተው የነበረውን ጉዳይ አደባባይ ማስጣታቸው ለአድማጩ መልካም ነገር ነው!
ሙሉ ቃለ-ምልልሱን ከስር ያለውን ሊንክ ተጭነው ይከታተላሉ!
https://youtu.be/qGRvUOb0kr4?si=tPi6TAFVtKCyKOvT
#ሼር | 737 |
| 15 | لا يوجد نص... | 744 |
| 16 | በሱዳን ኤል ፋሽር የፈጥሮ ደራሽ ኃይል አማጺያን እንደ የዘር ማጥፋት የሚቆጠሩ ወንጀሎችን እንደፈጸሙ ተመድ በምርመራው አረጋገጠ
📌 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሱዳን እውነታ አውጪ ተልዕኮ ባወጣው አዲስ ሪፖርት መሠረት፤ ታጣቂ ቡድኑ በኤል ፋሽር ጅምላ ግድያዎች፣ ስልታዊ አስገድዶ መድፈር፣ እገታዎች እና ሆን ብሎ በረሃብ የመቅጣት ድርጊቶችን ፈጽሟል።
ዋና ዋና ግኝቶች፦
📌 ከጥቃቱ የተረፉ ሰዎች የገዛ የቤተሰቦቻቸውን አባላት ጨምሮ በቅርብ የተገደሉ ንጹሃን አስከሬኖች መሬት ላይ በተዘረሩባቸው ክፍሎች ውስጥ አስገድዶ መድፈር እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።
📌 ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ለረጅም ጊዜ ከበባ በማድረግ የዕርዳታ አቅርቦቶች እንዳይገቡ ማገድ እንዲሁም በረሃብ ለመቅጣት የምግብ ማምረቻ ሥርዓቶችን በከባድ መሣሪያ ደብድበዋል።
📌 ሪፖርቱ በኤል ፋሽር አረብ ባልሆኑ ማኅበረሰቦች ላይ የተፈጸሙት መጠነ ሰፊ ግድያዎች "የዘር ማጥፋት ወንጀል መገለጫዎች" የታዩባቸው እንደነበሩ በየካቲት ወር የተደረሰው ግኝት የሚያጠናክር ነው።
የተልዕኮው ሰብሳቢ መሐመድ ቻንዴ ኦትማን፤ "ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከነዚህ ክስተቶች ትምህርት መውሰድና ተጨማሪ ጥፋቶችን ለመከላከል አስቸኳይ እርምጃ መውሰድ አለበት" ብለዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ፤ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ጦር በብዛት እየተሰባሰበበት በሚገኘው በሰሜን ኮርዶፋን ‘ኤል ኦቤይድ’ ዙሪያ ተመሳሳይ "ጥፋት" እየተከሰተ መሆኑን ባለፈው ሳምንት አስጠንቅቀዋል። | 1 009 |
| 17 | لا يوجد نص... | 971 |
| 18 | መረጃ‼️
የግብጽ መንግሥት ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የምሥራቅ አፍሪካ ስደተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን "በዘፈቀደ" እያሠረና ከአገሪቱ "እያባረረ" ይገኛል ሲል ሂውማን ራይትስ ዎች ከሠሠ።
የግብጽ ባለሥልጣናት ስደተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ከተያዘው ዓመት ጀምሮ እያሠሩ ያሉት፣ የመኖሪያ ፍቃዳቸውን እድሳት በማዘግየት መኾኑን ተቋሙ ገልጧል።
ፖሊስ ሕጋዊ የስደተኞች ሠነዶችን እንደሚነጥቅ መረዳቱን ተቋሙ ጠቅሷል።
ዘለግ ላለ ጊዜ እስር ከሚፈጸምባቸው ስደተኞች መካከል፣ ከኢትዮጵያዊያን በተጨማሪ ኤርትራዊያን፣ ደቡብ ሱዳናዊያንና ሱዳናዊያን ይገኙበታል ተብሏል።
ተቋሙ፣ የአገሪቱ ባለሥልጣናት ከመኖሪያ ፍቃድ እድሳት መዘግየት ጋር በተያያዘ በስደተኞች ላይ የሚፈጽሙትን "የዘፈቀደ እስር" እና "ከአገር የማባረር" ድርጊት እንዲያቆሙ ጠይቋል። | 1 119 |
| 19 | لا يوجد نص... | 941 |
| 20 | ሲስተሙ አምሓራን ማደህየት ተያይዞታል‼️
ከብልፅግና ጋር እጅና ጓንት ሆነው እየሰሩ ያሉት አቶ በላይነህ ክንዴን ኤክስፖርት ጭነት ከቡሬ ጭነት ይዘው ኬንያ ድንበር ሞያሌ የደረሱ ተሳቢዎች በኦሮሚያ ክልል አሻጥራዊ የድንበር ይለፍ ሴራ መሻገር አቅቷቸው " ዛሬ 1 ወር ሆነን የምግብ የአልጋ ወጭ አቃተን የባንክ እዳ የመክፈል ሀላፊነት ያለበት ንብረት ወር ለሚደርስ ጊዜስ አስጭኖ ማቆም የሚያደርሰው ግለሰባዊ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ተረስቶ ነው ???" ሲሊ ሾፌሮች አቤቱታ እያሰሙ ነው። | 899 |
