cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

Show more
Advertising posts
8 563
Subscribers
+1724 hours
+3587 days
+1 22230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Ashara Media - አሻራ ሚዲያ: የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ መግለጫ!!                                    ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም የሰሞነ ህማማት ሳምንት ክፉዎች ክፉ ምክርን የመከሩበት ነው። ምክራቸውን ያፀኑበት በምክራቸው ይሆን የወሰኑትን የፈጸሙበትና ያስፈፀሙበት ነው። በዚህ ምክር ውስጥ ከእውነት ይልቅ ሀሰት  ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ ከፍትሐዊነት ይልቅ ኢ-ፍትሐዊነት ከርሕራሔ ይልቅ ጭካኔ ከአድናቆት ይልቅ ቅናት ቅድሚያ ተሰጥቷቸዋል። ከሳምንቱ ዕለታት መካከል ሐሙስ ማምሻውን ሴራው በክርስቶስ ላይ በተግባር መገለጥ ጀመረ። ይልቁንም አርብ የሴረኞቹ አስከፊነት ጨካኝነት ነውረኝነትና ክፋት በግልጽ የታየበት ዕለት ሆነ። የወቅቱ አርብ የመከራና የሞት ዕለት ሆነ። መከራውን ለየት የሚያደርገው ክብር በሚገባው ምስጋና በሚገባው በርካቶችን በመገበው ለብዙዎች ተስፋ በሰጠው በእውነተኛውና በሀያሉ ላይ የተፈጸመ መሆኑ ነው። ሀያሉና እውነተኛው ይሞት ዘንድ የሚሰቅሉትን አልተቃወማቸውም ታገሳቸው ይቅርም አላቸው፡፡ እነሱ ግን የይቅር ባዩን ርህራሄ አይተው ጭካኒያቸውን አልተውም። ይልቁንም ዝም በማለቱ የሀሰት ታሪክ ፈጥረው ሀሰተኛ ምስክር አቁመው በደለኛ ስለመሆኑ ያለመሰልቸት አስተጋቡ እንጅ። ጥቂቶች የእውነተኛውን መሰቀልና መገደል ቢቃወሙም ሰሚ አላገኙም እንደ ወንጀለኛ ተቆጠሩ። በሀሰተኛ ማህበር ውስጥ እውነተኞች በሰላም ይኖሩ ዘንድ አይችሉምና። አርብ ዕለት እውነተኛው በሀሰተኞች ሞት ተፈረደበት። ጌታችንም ሞት ተቀበረ ቅዳሜ ዕለትም ከመቃብር አልወጣም ሞቱን አጥብቀው የሚሹት በእርግጥም እንደሞተ አመኑ ነገር ግን ሞት አይገባውም ነበርና አሑድ ዕለት በመንፈቀ ሌሊት ከመቃብር ተነሳ። ድቅድቁ ጨለማ ትንሳኤውን አላስቀረውም መተተኞችም አንቀላፍተው ሳለ በሆነው ትንሳኤ  ደነገጡ አፈሩም። አርብ ለቅዳሜ ቅዳሜም ለእሑድ መዳረሻ ናት። አርብ ስላለ ቅዳሜ፤ ቅዳሜ ስላለ ደግሞ እሁድ አለ። አርብ ጽኑ መከራና ሞት ቢኖርም እሑድ ትንሳኤ አለ። አርብ ዕለት ሀሰተኞች ደስ ተሰኙ። ከእሑድ ጀምሮ ግን እውነተኞች ፍስሀ አደረጉ። አርብ እሑድ ለመቅረቡ ምስክር ነው። የአርብ ያልተገባ ሞት ለእሑድ የተገባ ትንሳኤ መሰረት ነው። የአርብ ሀሰተኛ ፍርድ የእሑድን እውነተኛ ትንሳኤ አላስቀረውም። ክርስቶስ የእሑድ ትንሳኤ እውን ይሆን ዘንድ የአርብን መከራ በትግስት ተቀበለ። ይህ ዓለም የሚያወቀው የክርስቶስ ታሪክ ነው። የአማራ ሕዝብ ዓመታትን በወለዱ ብዙ ሳምንታት ከተመከረበት፣ ከተፈረደበትም በኋላ በሀሰት ክስና ሀሳውያን ምስክርነት የተበየነውን የአርቡን መከራ እየተቀበለ ይገኛል። በእርግጥም አርብ አጭር ቆይታ ቢኖረውም መከራው ጽኑ ነው። የአማራ ሕዝብ አርብን ለማሳለፍ በመከራው እንደፀና ይገኛል። የአርብ ስሁት ፍርድ ካለ ምንጊዜም የእሑድ ፍትህና ትንሳኤ ይኖራል፡፡ ነገር ግን የእሑድን ፍትህ ማየትም ሆነ ማመን የማይፈልጉ ክፉዎች ለረጅም ጊዜ አርብ ላይ መቆየትን ይሻሉ። ነገር ግን አርብ ከልኩ አያልፍምና እሑድ ይመጣል። የአርብን ኢ-ፍትሐዊነት ያልተረዳና ያላወገዘ የእሑድን ትንሳኤና እውነት በቅጡ አይገነዘብም፡፡ የአማራ ጠላቶች ሕዝባችንን እነሱ በፈጠሩት አርብ ላይ ለማዘግየት የሚደረገው ሁሉ ግን በአርብና በእሑድ መካከል ያለውን ተፈጥሯዊና ሚስጥራዊ ትስስር ካለመረዳት የሚመነጭ ከንቱ ድካም ነው። ከአርብ ግፍ ጋር መተባበር የእሑድ ትንሳኤ ዕለት የሚያሳፍር አንገትን ለዘላዓለም የሚያስደፋ ድርጊት ነው። የአማራውን አርብ እሑድ አድርጎ ማቅረብም ሆነ ተቀበሉ ብሎ መከራከር እሑድን ከመናፈቅ ሳይሆን እሑድን ከመጥላት የሚመጣ መጥፎ በሽታ ነው። እኛ ግን እሑድን ስለምንናፍቅ አርብን በጽናት እያለፍነው እንገኛለን። በአርብ ውስጥ እሑድን ስለምናይ በመከራችን እንጽናናለን። በወቅቱ የክርስቶስ እናት ድንግል ማርያም ከአርብ እስከ እሑድ በመራራ ሀዘን ውስጥ ቆይታ በኋላም በትንሳኤው ሀዘኗን እንደረሳች ሁሉ ዛሬ የአማራ እናቶች የሚጽናኑበት የትንሳኤ ጊዜ ቅርብ መሆኑ አይቀርም። በእለተ አርብ በስቅለቱ እና በመከራው ዕለት የሰማይ ክዋክብት እንደረገፉት ሁሉ የአማራን ህዝብ መከራ ለመግፈፍም ብርካታ ጀግኖች በየ ግምባሩ ረግፈዋል። በእነሱ ክቡር መስዋዕትነትም የአማራው አርብ (ቅዳሜ) ተራውን ለእሑድ እያስረከበ ይገኛል። የአማራ ህዝብን ተጋድሎ በነጠረ ዓላማ፣ በጋለ ስሜት፣ በጥድፊያ፣ በቆራጥነት እና በፅናት መምራትን ታሳቢ አድርጎ እንደ አዲስ የተቋቋመው የአማራ ፋኖ በጎጃም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ ለሰማዕታት ቤተሰቦች፣ ለመላው የድርጅቱ አመራር እና አባላት እንዲሁም ደጋፊዎቻችን እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዚህ አጋጣሚ የመከራ ዘመንን አልፎ ትንሳዔው ላይ ለመድረስ የሚደረገውን የአማራ ህዝብ ተጋድሎ በመምራት ታሪካዊ ሚናውን እየተወጣ ያለው የፋኖ ኃይል በዚህ ወሳኝ የታሪክ መታጠፊያ ወቅት በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን ጭፍጨፋ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚመጥን ምላሽ በመስጠት ላይ መሆኑን በድጋሚ እናረጋግጣለን፡፡ ጸኃፍት ፈሪሳውያን እና ሰዶቃውያን በህማማቱ ሳምንት በእለተ ሰኞ እና ማክሰኞ በክርስቶስ ላይ የክፋት ምክር እንደመከሩበት ሁሉ የፈጠራ ሰነዶችን በግልብ ንባብ ያነበበ ጥራዝ ነጠቅ ትውልድ የአማራን ህዝብን እንደ ጨቋኝ በመፈረጅ፤ እንዲጠፋ በመቀስቀስና ጠላቶቹን በማስታጠቅ ለግማሽ ምዕተ-ዓመት ያህክል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሀ ሁ እንዲሆን አድርጓል፡፡ ስለሆነም የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ የዘመኑ ፈሪሳውያን እና ሰዶቃውያን የመከሩበትን እና መዋቅራዊ ቅርፅ የሰጡትን ስሁት ብያኔ መሻር ቁልፍ ተግባር እንደመሆኑ መጠን የትውልድ ልህቀትን የሚያመጣ ሁነኛ ተግባር ማከናወን ያስፈልግ ነበር፡፡ የአማራ ፋኖ በጎጃም ከተደራጀበት ግዜ ጀምሮ ባሉት አጭር ግዜ ውስጥ የፖለቲካ ልሂቃንን ማዋለድን፤ በአማራ ህዝብ ፖለቲካዊ እጣ ፋንታ ላይ የመወሰን እድል ያገኘውን ትውልድ የህዝባችን ሁለንተናዊ አቅም፣ የሞራል ልዕልና፣ የሀገረ- መንግስት ግንባታ ተሳትፎ ታሪክ የሚመጠን ፖለቲካዊ አቋም እና ወታደራዊ ቁመና ማስጨበጥን ታሳቢ ያደረጉ ተከታታይ የስልጠና ተግባራት አከናውኗል፡፡ በዕለተ እሮብ የክርስቶስ ቤሰተብ የሆነው ይሁዳ ከፊሪሳውያኑ ጋር በክርስቶስ ላይ ክፉ እንደ መከረው ሁሉ ከአማራ ህዝብ አብራክ የወጣው እና ከኢህዴን እስከ አማራ ብልፅግና ስሙን የለዋወጠው፣ ግብሩ ግን ያው እና አንድ ዓይነት የሆነው ሰብስብ መብታችንን በመለመን እና ጠላቶቻችንን በማባበል ምላሽ ለማግኘት 3 አስርት ዓመታትን እንድንጠብቅ በማድረግ ትልቅ የታሪክ ጠባሳን ትቶ አልፏል፡፡ ይሁን እንጅ ከዚህ  ያልተገባ መንገድ ወጥተን ጠላቶቻችንን በመተናነቅ እና አጥፊውን ስርዓት በማፈራረስ ወሳኝ የታሪክ እጥፋት ላይ ደርሰናል፡፡ ወደዚሕኛው የታሪክ ምዕራፍ እንደርስ ዘንድ ያስቻለንም የዘመኑ ይሁዳ የሆነውን የአማራ ብልፅግና የነበረውን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ አቅም ቀናትን በወሰደ ህዝባዊ ተጋድሎ እንደ ጨው ማሟሟት መቻላችን ነው፡፡
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ለማንኛውም መስዋእትነት በተዘጋጁ ልጆቹ እጅ ላይ በመውደቁ ምክንያት በአሁኑ ሰዓት ከባድ ትንቅንቅ እያደረግን ያለነው ከአማራ ብልፅግና ጋር ሳይሆን የብአዴን ሞግዚት ከሆነው የአብይ አህመድ ቡድን ጋር ነው፡፡ ባስመዘገብናቸው ወታደራዊ ድሎች እና ሰፊውን የአማራ ህዝብ ለተመሳሳይ ግብ እና ዓላማ በማሰለፍ ባከናወንናቸው ፖለቲካዊ ተግባራት የፋኖ ኃይል በምስራቅ አፍሪካ እና አካባቢው መልክዓ- ፖለቲካ ውስጥ ወሳኝ ሚና ያለው የፖለቲካ ተዋናይ መሆን በመቻሉ ከፍ ያለ ኩራት ይሰማናል፤ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በጎጃም ውስጣዊ አንድነቱን የሚያስጠብቁ እና ጓዳዊ ግንኙነቶችን የሚያጠናክሩ ተግባራትን ከማከናወን ጎን ለጎን የፋኖ ትግል በታወቀ መስመር እንዲራመድ፣ ትውልዱን በአንድ ረድፍ እንዲሰለፍ፣ ትክክለኛው የትግል ዘዴ እንዲቀየስ እና እንዲተገበር በማድረግ እንዲሁም ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ኃይላችን የተደራጀ እና የጠበቀ የእዝ ሰንሰለት እንዲኖረው በማድረግ በኩል ታሪካዊ ሚናውን በሚገባ እየተወጣ ይገኛል፡፡ ለዚህ ቁልፍ ተግባር ስኬትም የድርጅታችን መሪ አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ተገቢ ጥረት እያደረጉ መሆኑን እና አጠናክረውም እንደሚቀጥሉ ማረጋገጥ እንፈልጋለን፡፡ ከተላላኪው የአማራ ብልፅግና ጋር ያደረግነው ትግል በድል ቢጠናቀቅም ከወራሪው የአብይ አህመድ ሰራዊት ጋር የምናደርገው ትግል ቢያንስ ሶስት ድርብ ኃላፊነቶችን መወጣት እና በዚህ ቁመና ልክ መገኘትን የሚሻ መሆኑን በአግባቡ እንረዳለን፡፤ ጠላትን ፊት ለፊት መዋጋት እና ስርዓቱን መገርሰስ፣ ትግሉን የሚሸከም አንድ ታላቅ ድርጅት መውለድ እንዲሁም ነጻ የወጣውን ቀጠና ማስተዳደር ቁልፍ ኃላፊነቶቻችን ናቸው፡፡ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ ርዳታ ሰጭ ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል መደላድል በመፍጠር በኩልም በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንገኛለን፡፡ ይህ ትግል መራር መስዋዕትነትን፣ ትዕግስትን እና ጥበብን እንዲሁም ያልተቋረጠ የማደራጀት ስራን እና ስትራቴጅክ ድሎችን የሚጠይቅ መሆኑን በማያወላዳ መልኩ የተረዳው ድርጅታችን ባህርዳርን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ከ15 ግዜ በላይ የታቀዱ ውጊያዎችን በማድረግ በርካታ ስትራቴጅክ ድሎችን ተጎናፅፏል፡፡ በቀጠናው ያለውን ኃይል በክፍለ ጦሮች እና በሌሎች ወታደራዊ አደረጃጀቶች አደራጅቷል፡፡ ከወታደራዊ አደረጃጀቶች ትይዩ ፖለቲካዊ ሚናቸውን የሚወጡ የአመራር አባላት ምደባ እና ስምሪት በመስጠት የትግሉን እድገት የሚመጥን የአደረጃጀት ስራ ለመስራት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ የአማራ ህዝብ የህልውና ጥያቄ ያለበት መሆኑ ላይ ጥርት ያለ አቋም የያዘው ድርጅታችን እና በየግምባሩ እየተዋደቀ ያለው ኃይል የህልውና ትግላችን የሚመለሰው በወታደራዊ አቅም ብቻ መሆኑን በማመን እየታገለ ያለ እንደመሆኑ መጠን የአማራ ህዝብ ህልውና አደጋ ላይ የወደቀው ፖለቲካዊ ይዘት ባላቸው ሴራዎች መሆኑንም በአግባቡ ይገነዘባል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ መላው የትግሉ ደጋፊ እና ህዝቡ ሊረዳው የሚገባው ነጥብ ትግሉ የደረሰበት ደረጃ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አቅሞችን ያዋሃደ እና ያጣመረ ወጥ ድርጅት የሚፈልግ እንጅ የፖለቲካ እና ወታደራዊ ክንፍ በሚል የሚደረግ ተናጥላዊ አካሄድ ተገቢ አለመሆኑን እና በታሪክም ውጤታማ የሆነው ትግል የተዋሃደ አመራርን የተከተለ መሆኑን ነው፡፡ በነገራችን ላይ ፋኖ በቅጥረኝነት የሚዋጋ የሰራዊት ኃይል ሳይሆን ጠመንጃ ያነገበ የፖለቲካ ኃይል መሆኑ ላይ ግልፅ አቋም ሊኖረን ይገባል፡፡ ትግሉ ግዙፍ የሆነ ኢኮኖሚ የተሸከመ ኃይልን የመገርሰስ ጉዳይ በመሆኑ የብዙ ባለድርሻዎችን ተሳትፎ ይጠይቃል፡፡ ይህንን ከግብ ለማድረስም ትግሉን በውስጥ አርበኝነት የሚደግፉ ግለሰቦችን እና ቡድኖችን ማደራጀት እና ለትግሉ አስተዋፅኦ  አስተዋፅኦ የሚያበረክቱበትን ምቹ አውድ ለመፍጠር የሚያበቃ አደረጃጀት ከመፍጠር ጎን ለጎን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ እና የተለያዬ ሙያ እና ዝንባሌ ያላቸው ግለሰቦች በዲፕሎማሲ፣ በኮሚኒኬሽን፣ በወታደራዊ፣ በሎጅስቲክስ እና በኢንተለጀንስ እና በስትራቴጅክ ጉዳዮች ላይ ወጥነት ያለው ሚና እንዲኖራቸው የሚያስችሉ ግብረ-ኃይሎችን በማቋቋም የትግሉን አሳታፊት ከፍ ማድረግ እና የህዝባችንን እምቅ አቅም መጠቀም እንደሚገባን እናምንበታለን፡፤  በሌላ በኩል በዋናነት የአማራን ህዝብ ለከፍተኛ እልቂት፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድቀት የዳረገው ጦርነት መሰረታዊ ምንጭ ህገ-መንግስታዊ ዋስትና ያለው ሀገር አፍራሽ ስርዓት ሲሆን የቅርብ ምክንያቱ ደግም በቡድኖች መካከል የተፈጠረ የስልጣን ሽኩቻ እንዳልሆነ ሁሉ ደቡብ አፍሪካ-ፕሪቶሪያ ላይ ሁለቱን የኢህአዴግ ቡድኖች በማስማማት ብቻ ጦርነቱን ለመቋጨት የተሞከረበት ሂደት ትልቅ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን እንረዳለን፡፡ የፕሪቶሪያው ስምምነት ቁልፍ ነጥብ የአማራን ህዝብ ህልውና አደጋ ውስጥ በሚጥሉ ፖሊሲዎች እና የፖለቲካ መሰረተ-ሃሳቦች ላይ ተመርኩዞ የተረቀቀውን እና የችግራችን ዋነኛ ምንጭ የሆነውን ህገ-መንግስት ገቢራዊነት ማፅናት መሆኑ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ዘላቂ ሰላም የሚመጣበትን እድል እና መልካሚ አጋጣሚ ዘግቶታል:: የአማራ ህዝብ የህልውና ጥያቄ አካል የሆኑት የአማራው የማንነት እና የአፅመ-ርስት ባለመብትነትን በሚገፋ መንገድ አስተዳደራዊ ክልሎች የተዋቀሩትም ሆነ ህጋዊ ሽፋን ያገኙት አሁን በስራ ያለው ህገ-መንግስት ከመውጣቱ አስቀድሞም ጭምር ነው፡፡ ይሁን እንጅ ራሳቸውን የህገ-መንግስቱም ሆነ የፕሪቶሪያው ስምምነት አወዳሽ እና ጠባቂ አድርገው የሚገልፁት ሁለቱ የኢህአዴግ ቡድኖች በራያ እና ወልቃይት አካባቢዎች ያለውን የአማራ ህዝብ የማንነት ጥያቄዎች መነሻ አድርገው አዲስ የጦርነት ነጋሪት መጎሰም ጀምረዋል፡፡ የራያ እና የወልቃይት አካባቢዎችን ጨምሮ በሁሉም አካባቢዎች ያሉ የአማራ ህዝብ እና የሌሎች ኢትዮጵያውያን የማነንት እና የወሰን ጥያቄወች የሚመለሱት ከህገ-መንግስቱ ማዕቀፍ ውጭ በሆነ ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይት (Extra-Constitutional Dialogue) እንጅ የጦርነት ምንጭ የሆነውን ህገ መንግስት በመተግበር አይደለም፡፡ ይህ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው ደግሞ የመፍትሔው ደንቃራ በሆነው ብልፅግና መቃብር ላይ ብቻ እንደሆነ በፅኑ እናምናለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እና ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች የምናስተላልፈው መልዕክት መጠፋፋትን በሚያፋጥን መንገድ በተቀረፀው ስርዓት ምክንያት በገዛ ሀገሩ ባይተዋር የሆነው እና በስርዓቱ አገልጋይ ጠመንጃ ያዦች እየተጨፈጨፈ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን ስርዓት ግርስሶ በመጣል በምትኩ በህዝብ ይሁንታ እና ፈቃድ ላይ የተመሰረተ ስርዓተ- መንግስት ማንበር የሚችልበት ወሳኝ ወቅት ላይ ይገኛል፡፡ በንፁሃን ደም የጨቀየ ወንበሩን እስካልተነጠቀ ድረስ የብልፅግና ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች፤ ሀገሪቱ ከጎረቤት ሀገሮች እና ከቀጠናው መልክዓ-ፖለቲካ ሃይሎች ጋር ስለሚኖራት ሚናም ሆነ ሰለ ህዝብ አንድነት ደንታ እንደሌለው በተግባር የተረጋገጠ የአደባባይ ሃቅ ነው፡፡ ስለሆነም መላው ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵ የፖለቲካ ኃይሎች በሁሉም ማህበረ-ፖለቲካዊ  ጉዳዮች ህልውናው አደጋ ላይ መውደቁን ተከትሎ የአፈሙዝ ተጋድሎ በመጀመር ስርዓቱን እያሽመደመደ ያለው የአማራ ህዝብ የሚያደርገውን ተጋድሎ ትቀላቀሉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን፡፡እንዲሁም የአማራ ብልፅግና በሚል ስም የሚነግዱ ጥቂት የብአዴን ቅሪቶች በጥቂት
Show all...
ከተሞቻችን ውስጥ በፍርሃት እና በቅዠት ተውጠው ከመኖራቸው እና አለን ለማለት ያህክል በአገልጋይ ሚዲያዎቻቸው በኩል ከመተንፈሳቸው በስተቀር ኢህአዴግ የአማራ ሲል የከለለውን ክልል የሚያስተዳድረው መንግስት ጥቂት ቀናትን በወሰደ ፋኖ መር ህዝባዊ ተጋድሎ እንደ ጨው ሟሙቷል፡፡ ይህንን የተረዳው የቡድኑ ቅሪት አካል የነበረውን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ጉልበት መልሶ ማግኘት እንደማይችል ሲረዳ በአንድ በኩል የአማራ ህዝብ እና የአማራ የፖለቲካ ኃይሎች ያልተወከሉበትን እና አንዱንም የአማራ ጥያቄ አጀንዳ ያላደረገውን የፕሪቶሪያ ስምምነት ለመተግበር እየተጋሁ ነው እያለ በሌላ በኩል ደግሞ ህወሃት ጋር ጦርነት ውስጥ ሊገባ እንደሆነ አስመስሎ ህዝቡን በማደናገር እንደገና እግር ለመትከል የሚያደርገውን መፍጨርጨር የአማራ ህዝብ በውል ሊረዳው ይገባል፡፡ በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ሽፋን የአማራ ህዝብ ላይ ግልፅ ወረራ እና ጦርነት ይፈፀምበት ዘንድ ይፋዊ ጥሪ በማቅረብ ህዝብን በወራሪ ጦር እያስመታ ያለው ይህ ስብስብ የአማራን ህዝብ ለጦርነት የሚጋብዝበት እና የአማራ ህዝብ መብቶች ተቆርቋሪ የሚሆንበት አመክንዮ ሊኖር አይችልም፡፡ የጦርነት ነጋሪቱ የቡድኑን የቆየ የተላላኪነት ሚና የበለጠ የሚያሳይ፤ ጸረ-ህዝብነቱን በይፋ የሚያረጋግጥ እንዲሁም በህዝብ እልቂት ተጠቅሞ ስልጣኑን ለማቆየት የሚያደርገውን መፍጨርጨር በግልፅ የሚያላክት መሆኑን መላው የአማራ ህዝብ ሊረዳው ይገባል፡፡ በመሆኑም ስርዓቱ ላይ የተቀዳጀናቸው ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ድሎች የበለጠ ይሰምሩ እና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ውድ ዋጋ እየከፈለበት ያለው ተጋድሎ በአጭር ግዜ ውስጥ ይቋጭ ዘንድ መላው የአማራ ህዝብ የፋኖው መዋቅር የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል በመደገፍ እና በሁሉን አቀፍ ተጋድሎ የትግሉ አካል እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የስርዓቱ መለዮ ለባሾች እና መስመራዊ መኮንኖች በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ስም በተደራጀ የአንድ ቡድን ፍላጎት ማስፈፀሚያ በሆነ ሰራዊት ውስጥ ተቀላቅላችሁ በራሳችሁ ህዝብ ላይ በታወጀ ጦርነት ላይ እየተሳተፋቸሁ መሆኑን መላው ህዝብ በውል የሚረዳው ሃቅ ነው፡፡ በአማራ ህዝብ ላይ አፈሙዝ እንድታዞሩ እና ህዝብ እንድትጨፈጭፉ ያሰለፏችሁ የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የብልፅግና ቡድን ዓላማ ህዝብን በባርነት መያዝ ከዛ አለፍ ሲልም ኢትዮጵያን መበታተን መሆኑን መገንዘብ ይገባችኋል፡፡ አውዳሚ እና ግብ-አልባ ጦርነትን መገለጫው ያደረገው ቡድን በሰጠው አመራር ሰራዊቱ እና ህዝቡ የከፈለውን መራር መስዋዕትነት በማራከስ ትላንት ጠላት ካደረገው ኃይል ጋር ሻምፓኝ የሚከፍት እና ውስኪ የሚራጭ ከሃዲ ቡድን የሚሰጠውን ወታደራዊ ስምሪት መቀበል ሀገር እና ህዝብን መካድ እንደሆነ ልትረዱት ይገባል፡፡ ስለሆነም በርካቶች ጓዶቻችሁ እንዳደረጉት ሁሉ የፋኖ አደረጃጀቶችን በመቀላቀል ስርዓቱን የመታገል ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እና በህዝብ እልቂት ለሚነግደው የብልፅግና ቡድን ከማገልገል እንድትቆጠቡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የኦሮሞ እና የትግራይ ህዝብም በስማችሁ የሚምሉ የፖለቲካ ኃይሎች በተደጋጋሚ ጦርነት እንዲጎሳቆል ከማድረግ አልፈው ህዝብ የእነሱን ሃጢዓት እና ጥፋት ተሸክሞ የቆሸሸ ታሪካቸውን እንዲጋራቸው የሚያደርጉትን ጥረት ማክሸፍ እንደሚገባ እናሳስባለን፡፡ በየትኛውም የሀገራችን ኮርነር ያለው ህዝብ የሚያነሳቸው የህልውና፣ የማንነትም ሆነ የወሰን ጥያቄዎች በህገ መንግስቱ ምላሽ የማያገኙ ይልቁንም በሀቀኛ የህዝብ ልጆች በሚመራ ብሔራዊ ውይይት እና ሽግግር ብቻ ዘላቂ መፍትሔ የሚሰጣቸው መሆኑን በድጋሚ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የችግሮቻችን ሁሉ ትብታብ የሆነውን የብልፅግና ሰርዓት በመገርሰስ ወደ ሃቀኛ ብሔራዊ ውይይት እና ዘላቂ ሰላም ሊመራን የሚችልን የአማራ ህዝብ ሃቀኛ ተጋድሎ እንድትቀላቀሉ እና የፖለተካ ትንሳኤያችንን እውን እንድናደርግ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ አዲስ ትውልድ! አዲስ አድተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! የአማራ ፋኖ በጎጃም https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

👍 1
በአምሓራዊቷ ምዕራብ ግዛት ገነተ ጎጃም፣ ከአባይ ግድብ ቀጥሎ ለአምሓራው ሌላ በረከት በምስራችነት መጥቷል። መተከል ውስጥ ከ20 ትሪሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ ወርቅ እንደተገኘ ማዕድን ሚኒስትር ለፌደራል ባለስልጣን በሚስጥር  ይፋ አድርጎላቸዋል። የአማራ ወጣት ይህንን ለትውልድ የሚበቃ ሀብትና እሪሶርስ ማወቅ አለበትና ማጠበቅ አለበት። መተከል የጎጃም አማራ አምደ-ርዕስት ነው። https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን ሁሉ… አምሓራ ላይ በፋሽስቱ አገዛዝ ለሆነበት፣ እየሆነበትም ላለው ሁለ ሰቆቃ ተጠያቂ ናቸው። https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

በአንድ ወረዳ በተመሣሣይ ቀን የአስራ ሁለት ሚሊሺያ አባለት የቀብር ስነ ሥርዓት ተፈፀመ። በሰሜን ወሎ ዞን አሁን ተገኝ ወረዳ ተረፌ በተባለ ቦታ በተደረገ ውጊያ በርካታ የሚሊሺያ አባለት ሲገደሉ። በርካታ ቁጥር ያላቸው በፋኖ ኃይሎች ተይዘው ተወስደዋል። ከሁለት ቀናት በፊት  ተረፌ በተባለች ቦታ በፋኖ ኃይሎች እና በሚሊሽያ አባላት መካከል በተደረገ ውጊያ 11 የሚሊሺያ አባላት ሲሞቱ የተረፌ ቀበሌ ሊቀመንበር እንዲሁ በውጊያ ላይ መሞቱ ተሰምቷል። 19 የሚሊሺያ አባላት በፋኖዎች ተይዘው ተወስደዋል። ፋኖዎች በዚህ ውጊያ 41 በላይ የነፍስ ወከፍ መሣሪያ መውሰዳቸውን አረጋግጠዋል። ሚያዝያ 28/2016 ዓ.ም https://t.me/Moamediamoresh
Show all...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

🏆 2👍 1
👍 14 1