ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
کانال ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 11 639 مشترک است و جایگاه 16 698 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 2 871 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 11 639 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 07 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -77 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 8.81% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.74% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 025 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 784 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 3 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 08 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 08 ژوئیه | +4 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | +2 | |||
| 05 ژوئیه | +1 | |||
| 04 ژوئیه | +6 | |||
| 03 ژوئیه | +4 | |||
| 02 ژوئیه | +1 | |||
| 01 ژوئیه | +2 |
| 2 | بدون متن... | 66 |
| 3 | ሲስተሙ አምሓራን ማደህየት ተያይዞታል‼️
ከብልፅግና ጋር እጅና ጓንት ሆነው እየሰሩ ያሉት አቶ በላይነህ ክንዴን ኤክስፖርት ጭነት ከቡሬ ጭነት ይዘው ኬንያ ድንበር ሞያሌ የደረሱ ተሳቢዎች በኦሮሚያ ክልል አሻጥራዊ የድንበር ይለፍ ሴራ መሻገር አቅቷቸው " ዛሬ 1 ወር ሆነን የምግብ የአልጋ ወጭ አቃተን የባንክ እዳ የመክፈል ሀላፊነት ያለበት ንብረት ወር ለሚደርስ ጊዜስ አስጭኖ ማቆም የሚያደርሰው ግለሰባዊ ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ተረስቶ ነው ???" ሲሊ ሾፌሮች አቤቱታ እያሰሙ ነው። | 65 |
| 4 | #ጉና ተባብሶ የቀጠለው የአምሓራ ተወላጆች እና ኦርቶዶክሳውያን ፍጅት
በምሥራቅ አርሲ ዞን #ጉና ወረዳ ሬኤ አርባ ቀበሌ የአከባቢዉ ታዋቂ ገበሬ የሬኤ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ሰበካ ጉባኤ ሀላፊ አቶ አሰግደዉ የማሪያምወርቅ ትናንት ሰኔ 30 /2018 ከሌሊቱ 6 ሰአት በተኛበት የኦሮሞ አክሪሪ የእስልምና ታጣቂዎች በ10 ጥይት ገድለውት የወንድሙን ሚስት ከነልጆችዋ አግተው ወስደቸዋል። እንዲሁም የረኤ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የቄስ ሙሴ ቦጋለና የሌሎች ኦርቶዶክሳውያንን ከብቶቻቸውን በሙሉ ነድተው ሄደዋል።
የእነዚህ የኦሮሞ አክራሪ እስልምና ታጣቂዎች ዋና ካምፓቸው ከወረዳው ከተማ የ50 ደቂቃ የእግር ጉዞ ቢሆን ነው።ቦታው አርጀኦ ጫካና ኦሳ ጫካ ይባላል። ይኽንን የ ወረዳዉ፤የዞንና የክልሉ ባለሥልጣናት በደንብ ያቁታል ነገር ግን እርምጃ ሊወስዱ ፈቃደኞች አይደሉም።ምክንያቱም እልቂቱን የሚመሩት እነርሱ ስለሆኑ ። ባለሥልጣናቱ ከትናንተ ወዲያ በውድቅት ሌሊት አምሓራ ኦርቶዶክሳውያንን ሰብስበው ከዚህ የተሰደዱት ወደ ቦታቸው ካልተመለሱ ቀን እያረሱ ሌሊት ወደ ሌላ የሚሄዱ ከሆነ በቀን እርምጃ እንወስድባቸዋለን መሬታቸውንም እንወስዳለን እያሉ ሲዝቱባቸው እንደነበር የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
በዚሁ ቀበሌ ሰኔ 24/2018ዓ.ም መ/ ር ተስፋዬ ተሾመ አጋና ወ/ሮ ሚሚ ግርማ የተባሉ አምሓሮች ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው። | 61 |
| 5 | ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ከቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ።
ባለፉት 5 ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠንካራ ተቃዋሚነታቸውና በደፋር ተናጋሪነታቸው የሚታወቁት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)፣ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋ አስታወቁ።
በትላንትናው ዕለት የፓርላማ ቆይታቸውን ያጠናቀቁት ደሳለኝ (ዶ/ር)፣ ከማንኛውም ፓርቲ አባልነትም ሆነ ደጋፊነት መውጣታቸውን ገልጸዋል።
ደሳለኝ (ዶ/ር)፤ "በትናንትናው የምክር ቤቱ ጉባዔ ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ 'አብረን እንስራ' በማለት ላቀረቡልን ጥሪና ላሳዩን አክብሮት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል።
" ከጉባዔው መጠናቀቅ በኋላ ጥያቄ ያቀረብን የተቃዋሚ የምክር ቤት አባላት ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበረን የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ላይ፣ በ7ኛው ዙር ምርጫ በባሕር ዳር ከተማ ለመወዳደር ተመዝግቤ ቢሆን ኑሮ እጩ ላለማቅረብ ወስነው እንደነበር ገልጸውልኛል " ያሉት ደሳለኝ (ዶ/ር)፤ " በምክር ቤቱ ሳነሳቸው የነበሩ ሀሳቦች ጠቃሚ እንደነበሩ፣ በትኩረት እንደሚወስዷቸው እና በምክር ቤቱ ብቀጥል ፍላጎታቸው እንደነበር የገለጹልኝን ሀሳብም በበጎ ጎኑ እና በቅንነት ተመልክቼዋለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
ደሳለኝ (ዶ/ር) ላለፉት 10 ዓመታት የሕዝብን አደራ ለመወጣት ካደረጉት ከፍተኛ ጥረትና ድካም በኋላ፣ አሁን ላይ ትኩረታቸውን በሙያቸው ሀገራቸውን ማገልገል፣ ጎን ለጎን ወደ ግሉ ዘርፍ በመግባት በፈጠራ ሥራዎች (Startups) ላይ መሰማራት እና ለቤተሰባቸው ጊዜ መስጠት ላይ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
ቀጥተኛ ፖለቲካውን ቢሰናበቱም፣ የአማራን ሕዝብ አንድነትና ከሌሎች ወንድም ሕዝቦች ጋር ያለውን አብሮነት በሚያጠናክሩ ማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በሙያቸው ማገዛቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋግጠው፤ አዲሱ የ2019 ዓ.ም ለኢትዮጵያ የእውነተኛ ሰላምና የተስፋ ዘመን እንዲሆን ተመኝተዋል።
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ወደ ፖለቲካው ከመግባታቸው በፊት በነበራቸው የዩኒቨርሲቲ መምህርነት ሕይወታቸው እንዲሁም የጣና ሐይቅን ከእንቦጭ አረም ለመታደግ በአክቲቪዝም እና የሀገር በቀል ሲቪክ ማኅበራትን በግንባር ቀደምትነት በመምራት ሰፊ የማኅበረሰብ አገልግሎት በማበርከት ይታወቃሉ። | 125 |
| 6 | بدون متن... | 121 |
| 7 | ፖርላማው እና የክልል ም/ቤቱ በተሳትፎ እና ዝምታ ሽፋን የሰጠው ዘር ፍጅት በአርሲ ቀጥሏል‼️
በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ከትናንት ጀምሮ ዳግም በተቀሰቀሰ ጥቃት በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑ ታወቀ
"ትናንት ምሽት ጀምሮ በአካባቢው ያለው የኔትወርክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ተደርጓል። አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ የወረዳው ካድሬዎች በየቀበሌው እየዞሩ የሰዎችን ስልክ በመንጠቅና በማስፈራራት መረጃ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ነው"
በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ከትናንት ጠዋት ጀምሮ ከፍተኛ ጥቃት እና አለመረጋጋት መከሰቱን የአካባቢው ነዋሪዎችና የዓይን እማኞች ገለጹ።
ከሳምንታት በፊት በአካባቢው በደረሰው ጥቃት ሳቢያ የሚዲያ ትኩረት ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ትናንት ጠዋት 3:00 አካባቢ ጀምሮ በነዋሪዎቹ ላይ አዲስ የተቀናጀ ጥቃት መከፈቱ ታውቋል።
እስካሁን ከተለያዩ የዓይን እማኞች በተገኘው መረጃ መሠረት ግጭቱ መጀመሪያ የተቀሰቀሰው በቢዮ ቀበሌ ሲሆን በአጭር ሰዓታት ውስጥ ወደሚከተሉት አካባቢዎች ተስፋፍቷ።
ጨፌ ቀበሌ፣ እሬቻ ሚካኤል ቀበሌ፣ ሌንጫ ኦዳ፣ በበራርቲ ጫካ ውስጥ፣ ኳስ ድሬ፣ ዲቡ፣ ሱንቴ ማርያምና ወራንቡስ ውስጥ በተከፈተው ተኩስ እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ቢያንስ የ4 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ጥቃቱ የተሰነዘረው ከፍተኛ ቁጥር ባላቸው ታጣቂዎች ሲሆን ቁጥራቸውም ከሺዎች በላይ ሊገመት እንደሚችልና ዓላማውም በአጭር ቀናት ውስጥ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ በማፈናቀልና ንብረት በመዝረፍ ቀውሱን በፍጥነት መቋጨት እንደሆነ ነዋሪዎች በከፍተኛ ስጋት ገልጸዋል።
ከወር በፊት ታሪካዊው የጠለታ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በተቃጠለበት ስፍራ ላይ ወደ 75 የሚጠጉ የፌደራል ፖሊስ አባላት ካምፕ ሰርተው ቢቀመጡም ታጣቂዎቹ የፀጥታ ኃይሉን አልፈው በመሄድ ጥቃት ሲፈጽሙ እንደታዩ ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።
በተጨማሪም ነዋሪዎች የወረዳው አመራሮችና ካድሬዎች ሆን ብለው የነዋሪዎችን መከላከያ መሣሪያዎች በመንጠቅ ሕዝቡን ባዶ እጁን እንዲቀር ማድረጋቸውንና ከታጣቂዎቹ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን ይገልጻሉ።
"ትናንት ምሽት ጀምሮ በአካባቢው ያለው የኔትወርክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ተደርጓል። አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ የወረዳው ካድሬዎች በየቀበሌው እየዞሩ የሰዎችን ስልክ በመንጠቅና በማስፈራራት መረጃ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ነው" በማለት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሚድያችን ተናግረዋል።
በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ በመሆኑና የጸጥታ ኃይሎች በአስቸኳይ ጣልቃ ገብተው ጥቃቱን ካላስቆሙ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት እልቂት ሊከሰት እንደሚችል ነዋሪዎች ድምጻቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።
መሠረት ሚዲያ | 665 |
| 8 | ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከጊዮርጊስ ፖፒረስ ያለን የመንገድ አካፋይ አትክልት ሲያፈርስ ተው ይህ ልክ አይደለም ብለን ተቃውመን ነበር።
አስፖልቱ ምንም አይነት ተጨማሪ ስፋት በማያገኝበት የአካፋይ አትክልት እግረኞች ባሻቸው እንዳይሻገሩ በሚከላከልበት የከተማ ውበት በሆነበት እንዴት አካፋዩን ታፈርሳላችሁ በርሀማነትን ታስፋፋላችሁ አረንጓዴ አሻራ ተብሎ በሚነገርበት አረንጓዴ ቦታን ማጥፋት ለምን ብለን ነበር።
አሽከርካሪው ዝግ መስመር ይረግጣል ባሻው ይዞራል ሰው ባሻው ይሻገራል ትርምስምስም የሚቆጣጠር ቀለም ረገጥክ ያለ ማቋረጫህ አቋረጥክ የሚል የለም።
አሁን ይህ መንገድ መኪና እግረኛ ባሻው የሚዞርበት የሚያቋርጥበት ትርምስምሱ የወጣ ውበቱ የጎደፈ መንገድ ሳይሆን ገብያ ነው የሚመስለው ተው ያልን ለዚህ ነበር።
ከተማ አስተዳደሩ በደመነፍስ በወሰነው ውሳኔ የመንገዱን ውበት በመግፈፍ አካባቢውን የትርምስ ቀጠና አድርጎታል።
#የሹፌሮች አንደበት | 637 |
| 9 | መረጃ‼️
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተርን የጊዜ ቆይታ በ23 የድጋፍ ድምጽ በድጋሚ ላንድ ዓመት አራዘመ።
የምክር ቤቱ አባል የኾነችው ኢትዮጵያ፣ የልዩ ራፖርተሩን የጊዜ ቆይታ ለማራዘም የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ደግፋ ድምጽ ሠጥታለች።
ኬንያንና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ 17 አገራት ድምጸ ተዓቅቦ ሲያደርጉ፣ ግብጽ፣ ቻይና፣ ቡሩንዲ፣ ፓኪስታን እና ሕንድ የውሳኔ ሀሳቡን ተቃውመዋል።
ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡን ያቀረቡት የአውሮፓ አገራት ነበሩ።
ኤርትራ፣ ከእንግዲህ በልዩ ራፖርተሩ ዙሪያ ከአጋር አገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደማታደርግ በቅርቡ ማሳወቋ አይዘነጋም። | 919 |
| 10 | بدون متن... | 866 |
| 11 | በዝንጀሮው ፖርላማ ነጥሮ የወጣው አንበሳ! | 784 |
| 12 | بدون متن... | 837 |
| 13 | የፓራጓይ ሴናተር ምባፔ ፈረንሳዊ እንደሆነ ያስመስላል እንጂ ቅኝ የተገዛ ካሜሮናዊ ማለቷን ተከትሎ ተቃውሞ ገጠማት
የፓራጓይ ሴናተር ሴሌስቴ አማሪላ ኪሊያን ምባፔ ላይ ያስተላለፉት የዘረኝነት ንግግር ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። "ወይዘሮ ሴሌስቴ አማሪላ፣ እፕንቺ እጅግ የተናቅሽ ሴት ነሽ፤ ለያዝሽውም ቦታ አትመጥኝም" ሲሉ ምባፔ በኤክስ ገፁ ላይ ጽፏል።
ከፓራጓይ እና ፈረንሳይ ጨዋታ መጠናቀቅ በኃላ ሴናተሯ ምባፔን አስቀያሚ በማለት “ ሙሉ ጨዋታውን ተረብሾ እና ፈርቶ ነው የጨረሰው “ ብላለች። ኪሊያን ምባፔ በበኩሉ “ የፓራጓይን ህዝብ አትወክይም ፣ በግንዛቤ ማነስ እና ባልተገደበ የዘረኝነት ዝንባሌሽ ምክንያት፣ መላው ዓለም የፓራጓይን ሩጫ እና በዚህ የዓለም ዋንጫ ያሳዩትን ታሪካዊ ጥረት ረስቶታል" ሲል አክሏል።
የሴናተሯ አስተያየ በፈረንሳይ ቁጣ ቀስቅሷል፤ የአገሪቱ የስፖርት ሚኒስትር ማሪና ፌራሪ “አሳፋሪ እና ተቀባይነት የሌላቸው” ሲሉ ገልጸዋቸዋል።የፈረንሳይ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አምበላቸው ላይ የደረሰውን የስም ማጥፋት ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ሚመለከተው የህግ አካል መወሰዱን አሳውቋል። የፓራጓይ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር መንግስትን ወክሎ የሴናተሯ ጉዳይ ውስጥ እንደሌለበት በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገፅ አጋርቷል።
Via_dagu | 1 036 |
| 14 | የጊዜ ጉዳይ ነው የገደለ ብቻ ሳይሆን ያስገደለም ዋጋ የሚከፍልበት ጊዜ ይመጣል (ከ ቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግሥት)። እየተጨፈጨፈ ያለው ቲማቲማ አይደለም ክርስስቶስ ዋጋ የከፈለለንት የሰው ልጅ ነው። አዎ ደግሜ እናገራለሁ የጊዜ ጉዳይ ነው ገዳይም አስገዳይም የዘራውን ያጭዳል ብቻ ሳይሆን ከዘራው በ50 እጥፍ ያጭዳታል። እነዚህ በግፍ የተጨፈጨፉት ከዚህ በፊት በሽርካ ወረዳ በአክራሪ የኦሮሞ እስላሞች በግፍ የተጨፈጨፉ ናቸው።ለዚያውም በአብሮ አደጎቻቸው በጎረቤቶቻቸው። አብረው በልተው ጠጥተው ሌሊት በተኙበት ገብተው ነው የጨፈጨፏቸው። 8ኦርቶዶክሳውያን ናቸው ያኔ የተጨፈጨፉት ስምንቱም ከአንድ ቤተሰብ ናቸው። ከተማ ተቀምጠህ የምታላዝን ኦርቶዶክስ ነገ የአንተም እጣፋንታ ይኽ እንደሆነ አስብ። | 1 112 |
| 15 | የኖርዌ ህዝብ ያህል ተፈናቃይ እና የምግብ እጥረት ያጋጠማት ኢትዮጵያ መረጃ ባለማቅረቧ ምክንያት በዓለም አቀፉ የምግብ ቀውስ ሪፖርት ውስጥ ሳትካተት ቀረች
ኢትዮጵያ የቴክኒክ መስፈርቶች የሚያሟላ ወቅታዊና ትክክለኛ የምግብ ዋስትና እጥረት መረጃ ማቅረብ ባለመቻሏ ምክንያት ከ2026ቱ ዓለም አቀፍ የምግብ ቀውስ ሪፖርት (GRFC) ውጭ ተደረገች። ይሁን እንጂ ሌሎች ትንበያዎች፤ አገሪቱ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2026 አጋማሽ ድረስ በዓለም ላይ ከፍተኛ የሰብአዊ ምግብ ቀውስ ካለባቸው አገራት መካከል አንዷ ሆና እንደምትቀጥል ጠቁመዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በጋራ ባወጡት ሪፖርት እንደተገለጸው፤ ኢትዮጵያ ወሳኝ የሆኑ የምግብ ዋስትና እጥረት መረጃዎች ካልተገኙባቸው ወይም የቀረቡት መረጃዎች የጋራ ስምምነት ግምገማዎችን ጨምሮ የሪፖርቱን የቴክኒክ መስፈርቶች ማሟላት ካልቻሉ 18 አገራት እና ግዛቶች መካከል አንዷ ሆናለች። | 1 173 |
| 16 | የህወሓት በሱዳን ግጭት ጉዳይ ጣልቃ ገብነት አሜሪካን ክፉኛ አሳስቧል
በሱዳን የሚገኘው የህወሓት አርሚ 70 ሰራዊት አባላት ትናንት ሰኔ 28/2018 ዓ. ም ከሱዳን ተነስተው ትናንሽ ጀልባዎችን ተጠቅመው ወደ ተከዜ ወንዝ ሲያመሩ ታይተዋል።
ከፍተኛ የጦር አዛዦችም አብረው ይታያሉ።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከብሔራዊ መረጃ ዳይሬክተር ጋር በመተባበር የህወሓት አርሚ 70 ጦር በሱዳን ጦርነት ውስጥ ስላላቸው ቀጥተኛም ሆነ ቀጥተኛ ያልሆነ ተሳትፎ፣ እያደረጉት ስላለው ድጋፍ ወይም ስለፈጸሟቸው ጥሰቶች ጥብቅ ክትትል በማድረግ በየ6 ወሩ ለኮንግረሱ ሪፖርት እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ማሳለፉ ይታወሳል። | 1 118 |
| 17 | ዜና፡ #ሂዩማን_ራይትስ ዎች የ #ትግራይ ባለሥልጣናት ሲቪሎችን በግዳጅ ለውትድርና እየመለመሉ ነው ሲል ከሰሰ፤ ምልመላው «የፍርሃት ድባብ» መፍጠሩንም ገልጿል
የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ሂዩማን ራይትስ ዎች፤ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ባለሥልጣናት ዕድሜያቸው 16 የሆኑ ሕፃናትን ጨምሮ በሲቪሎች ላይ ያነጣጠረ የግዳጅ ውትድርና ምልመላ ዘመቻ እያካሄዱ ነው ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ የክልሉ ኃይሎች ቢያንስ ከሚያዝያ 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀድሞ ተዋጊዎችን፣ ወንዶችንና ታዳጊዎችን እያገቱ መሆኑን ገልጿል።
ዛሬ የወጣው የድርጅቱ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፤ ይህ የምልመላ ዘመቻ በክልሉ ውስጥ «የፍርሃት ድባብ» የፈጠረ ሲሆን፥ ሲቪሎች ከጎዳናዎች፣ ከሥራ ቦታዎች፣ ከመኖሪያ ቤቶች እና ከባህላዊ ወርቅ ማውጫ ሥፍራዎች እየተያዙ ወደ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ካምፖች እየተወሰዱ ነው።
በሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሌቲሺያ ባደር «የትግራይ ባለሥልጣናት ወንዶችንና ታዳጊዎችን በግዳጅ ለመመልመል የሚያካሂዱት ዘመቻ በክልሉ ውስጥ የፍርሃት ድባብ እየፈጠረ ነው» ያሉ ሲሆን፤ የክልሉ ባለሥልጣናት ዘመቻውን በአስቸኳይ እንዲያቆሙና ያለፍላጎታቸው የተመለመሉትን ወደ ቤታቸው እንዲመልሱ ጥሪ አቅርበዋል። | 1 017 |
| 18 | 🚨 አጣዳፊ የሰብአዊ እርዳታ ጥሪ ለአርሲ ተፈናቃዮች! 🚨
#ይድረስ፦
* በአሜሪካ እና አውሮፖ ግዙፍ ገዳም እንገነባለን ብላችሁ ሚሊኖች ዶላር ላከማቻችሁ
* በየከተማው ግዙፍ ካቴድራል ለመገንባት ቢሊዮኖችን ለምትሰበስቡ አድባራት
* በመላው ዓለም ለተበትናችሁ ወገኖቼ ዳያስፖራሬዎች ለሳይበር ወሬኞች ቲክቶከሮች እና ዩትዩበሮች ኪስ መድለብ ምክንያት ለሆኖችሁ
* ለመላው ህዝበ ክርስቲያን
በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በደረሰው ጥቃት የወገኖቻችን ህይወትና ንብረት መውደሙ ይታወሳል። አሁን ላይ ከቀያቸው ተፈናቅለው በከባድ ችግር ውስጥ የሚገኙትን ወገኖቻችንን ወደ ቀደመ ሰላማዊ ኑሯቸው ለመመለስና የወቅቱን አጣዳፊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የእናንተን ድጋፍ ይሻሉ።
ምዕመናን፣ ባለሀብቶችና በጎ አድራጊዎች ሁሉ በሀገረ ስብከቱ እውቅና በተከፈተው በዚህ አካውንት የተቻላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉ በቅዱስ ገብርኤል ስም እንማጸናለን።
📌 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦
👉 ቁጥር፦ 1000772136394
👉 ስም፦ ጠለታ ቅ/ገብርኤል ተፈናቃዮች ገቢ ማሰባሰቢያ
የተሰደዱትን ማጽናናት የሁላችንም ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው! | 1 044 |
| 19 | #አሳዛኝ ዜና ‼️
በአምሓራ ምድር ጎንደር ዳባት 21 ንፁሃን ገበሬዎች ተጨፈጨፉ‼️
በዳባት ወረዳ ከአንድ ሙሉ ቤተሰብ ላይ በአገዛዙ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ፈፅሟል።
በጦር ሜዳ ሽንፈትን ያስተናገደው የጠላት ኃይል የተለመደው የብቀላ እርምጃውን በንጹሃን ዜጎች ላይ አሳርፏል። ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ ልዩ ስሙ "13" በተባለው አካባቢ በተደረገው ከባድ ውጊያ የፋኖን ክንድ መቋቋም ያቃተው ይኸው የገዢው ሥርዓት ግሪሳ ጦር መከላከያ የሌላቸውን ንጹሃን አርሶ አደሮች ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ ፈጽሟል። በተለይም "ዘና ጎዴ ማርያም" በተባለችው ልዩ ቦታ 19 ወንድ ገበሬዎችን እና 2 ሴቶችን ጨምሮ በአጠቃላይ 21 ንጹሃንን በአሰቃቂ ሁኔታ ረሽኖ አልፏል።
ይህን የጭካኔ ድርጊት ይበልጥ አሳዛኝና ለየት የሚያደርገው የአንድ አባወራ አባላትን ለይቶ ማጥፋቱ ነው። በዚህ የሰሞኑ እረሸና ጫቅሉ አማረ፣ አምባቸው አማረ፣ ሞላ አማረ እና ደስታ አማረ የተባሉ አራት ወንድማማቾች በአንድ ላይ የተገደሉ ሲሆን በተጨማሪም የአምባቸው አማረ እና የደስታ አማረ ልጆች ጭምር ተለይተው ተረሽነዋል። በአጠቃላይ ከአንድ ቤተሰብ ብቻ ከ8 በላይ አባላት በጠላት የጭካኔ በትር ያለጥፋታቸው ተቀጥፈዋል። ይህ የጠላት የሰሞኑ ግፍና ሰቅጣጭ ድርጊት የፋኖን ኃይል ይበልጥ የሚያስቆጣና ለህልውና ለፍትህ ለነፃነት የሚደረገውን ትግል የሚያፋጥን መሆኑን እናሳውቃለን።
✅ድል ለመላው አምሓራ ህዝብ!!!
ለተሰው ቤተሰቦች ነፍሳቸውን በአፀደገነት ያሳርፍልን | 1 130 |
| 20 | ልብ በሉ፦
ይኽ የግፍ ግፍ የሚፈጸመው፦
👉አልቃይዳ በሚንቀሳቀስባቸው በኢራቅ በረሃና ኮርብቶች አይደለም
👉ቦኮሃራም በሚንቀሳቀስባቸው በናይጄሪያ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉 መንግሥት በማይደርስባቸው ISIS በሚንቀሳቀሱባቸው በሊቢየ በረሃ አይደለም
👉ISIS በተቆጣጠራቸው በፑንትላንድ ተራሮችና ኮረብቶች አይደለም
👉አልሸባብ በሚንቀሳቀስባቸው በሶማሊያና በሶማሊንድ ኮረብቶች አይደለም ፦
እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ እስላሞች ነው።ሥርዐቱስ ኦርቶዶክሳውያን ማጽዳት የተቋቋመበት ዋና ዓላማው ነውና ዝም ቢል አያስገርምም የእኛ ዝም ማለት ግን ያናድዳል።
ወያኔ ወያኔ እያሉ እሬሳውን የጎተቱትም ሆነ በግድ ማዕተባቸውን በጥሰው እንዲሰልሙ የተደረጉ ኦርቶዶክሳውያን በነፍስ የሚጠብቃቸው፦
👉 ቤተ ክህነት የሚባል መዋቅር አላቸው
👉ሲኖዶስ የሚባል የጳጳሳት ጉባኤ አላቸው
👉ፓትርያርክ አላቸው
👉የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ አለ
👉የወረዳው ቤተ ክህነት አለ
👉የአጥቢያው አስተዳዳሪ አለ
👉ወንጌል የሚያስተምራቸው መምህር አላቸው
👉የንስሐ አባት አላቸው
👉 በጥምቀት የሚመስለው ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ አለ
ከእነዚህ ሁሉ ግን ለምን ብሎ የጠየቀ የተቆጣም የለም።እኛም ምዕመናን መከራን ተለማመድነው። አትግደሉን ማለትን እንደ ፖለቲካ ቆጠርነው። | 1 198 |
