ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍
کانال ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 11 688 مشترک است و جایگاه 16 913 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 2 858 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 11 688 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -226 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 9.31% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.83% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 088 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 798 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 4 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 14 ژوئن | +8 | |||
| 13 ژوئن | +4 | |||
| 12 ژوئن | +5 | |||
| 11 ژوئن | +3 | |||
| 10 ژوئن | +1 | |||
| 09 ژوئن | +5 | |||
| 08 ژوئن | +1 | |||
| 07 ژوئن | +4 | |||
| 06 ژوئن | +1 | |||
| 05 ژوئن | +6 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | +19 |
| 2 | በመጨረሻም USA እና ኢራን ተስማሙ፣ ኢስራኤል የለችም‼️
አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ለማቆም ከስምምነቱ ደረሱ።
በመጪው አርብ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ ሊፈራረሙ ቀጠሮ ይዘዋል።
ይህን ተከትሎ ሆርሙዝ ክፈት መደረጉን፣ በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ላይ እገዳ መነሳቱን ትራምፕ አስታውቀዋል።
ኢራንም ስምምነቱን መቀበሏን የገለፀች ሲሆን ሊባኖስን ጨምሮ ጦርነቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲቆም ተስማምቻለሁ ብላለች። ይህ የትራምፕ ስምምነት እስራኤልን ከጨዋታው ውጪ ማድረጉ አነጋጋሪ ሆኗል። | 141 |
| 3 | አመክንዮ አዘል ትችት አቅርቢ፣ በምክንያት የተቹትን በኡኡ ጥቅል አትፈርጅ።
አንዱን ፈርጆ ሌላውን በጭፍን ሽብሻቦ መደገፍ ይዞት የመጣውን የውድቀት ልክ አይተናል። አሁን ላይ አብዛኛው ቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች መልስ የሚሹ እና ትክክል ናቸው። ኡኡ በሚል አኩስሰሽ የምታልፊው አይደለም።
በህወሓት፣ በፋኖ እና ኦነግ መካከል የሚደረጉ ስትራቴጅካዊ ትብብሮች መርህ ዘለል ጥያቄ የሚያስነሱ ናቸው።
የስምምነቱ ማዕከል ምንድነው?
ህወሓት አሁን ላይ ከዐገዛዙ ጋር የምትታገለው፣ የተጋጨችውም፦
1ኛ. ወልቃይት ጠገዴ፣ ሰቲት ሁመራ፣ ዳንሻ ወልቃይት፣ በነሱ አጠራር ( ምዕራብ ትግራይ) ራያ አላማጣ እና መሰል የአምሓራ እርስቶች ይገቡኛል ወደ ቀደመ ቅኝ ግዛቴ ይመለሱ በማለት ነው።
2ኛ. መገንጠልን በአንቀፅ 39 የሚባርከው፣ በጎሳ ተኮር ፌደራሊዝሙ እና አምሓራን አግላይ ህገመንግስቱ ጠበቃነት
3ኛ. ሀገረ መንግስት ትግራይ ለመመስረት
4ኛ. ተቻይ ከሆነ… 4 ኪሎ ደርሶ የቀደመ ህወሓት መር ፀረ አምሓራ መንግስት ለማቆም ነው።
ፋኖ፣ በየትኛው የጋራ ትግል አላማ ላይ ነው፣ ከህወሓት ጋር የሚተባበረው?
ይህ ጥያቄን ያነሳ አምሓራ በሳል፣ ፖለቲካዊ ንቁ አምሓራ ነው።
ለነዚህ አንኳር ጉዳዮች ማብራሪያ የሚጠበቀው፣ ከፀረ አምሓራ ባለ አላማ ሰልፈኞች ጋር እየሰራ ከሆነ አካል እንጅ… በኡኡታ እና ፍረጃ ጠያቂዎችን ማኩሰስ ከፍትሓዊ አምሓራዊት ጋዜጠኛ ተጠባቂ አይደለም።
ይልቅ፣ ለከፋፋዮች እና ጥርጣሬውን አራጋቢ ሆነው ላሉት የለኦህዴድ አምሓሮች ግብዐት ላለመሆን እንጠንቀቅ! | 374 |
| 4 | بدون متن... | 326 |
| 5 | አመክንዮ አዘል ትችት አቅርቢ፣ በምክንያት የተቹትን በኡኡ ጥቅል አትፈርጅ።
አንዱን ፈርጆ ሌላውን በጭፍን ሽብሻቦ መደገፍ ይዞት የመጣውን የውድቀት ልክ አይተናል። አሁን ላይ አብዛኛው ቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች መልስ የሚሹ እና ትክክል ናቸው። ኡኡ በሚል አኩስሰሽ የምታልፊው አይደለም።
በህወሓት፣ በፋኖ እና ኦነግ መካከል የሚደረጉ ስትራቴጅካዊ ትብብሮች መርህ ዘለል ጥያቄ የሚያስነሱ ናቸው።
የስምምነቱ ማዕከል ምንድነው?
ህወሓት አሁን ላይ ከዐገዛዙ ጋር የምትታገለው፣ የተጋጨችውም፦
1ኛ. ወልቃይት ጠገዴ፣ ሰቲት ሁመራ፣ ዳንሻ ወልቃይት፣ በነሱ አጠራር ( ምዕራብ ትግራይ) ራያ አላማጣ እና መሰል የአምሓራ እርስቶች ይገቡኛል ወደ ቀደመ ቅኝ ግዛቴ ይመለሱ በማለት ነው።
2ኛ. መገንጠልን በአንቀፅ 39 የሚባርከው፣ በጎሳ ተኮር ፌደራሊዝሙ እና አምሓራን አግላይ ህገመንግስቱ ጠበቃነት
3ኛ. ሀገረ መንግስት ትግራይ ለመመስረት
4ኛ. ተቻይ ከሆነ… 4 ኪሎ ደርሶ የቀደመ ህወሓት መር ፀረ አምሓራ መንግስት ለማቆም ነው።
ፋኖ፣ በየትኛው የጋራ ትግል አላማ ላይ ነው፣ ከህወሓት ጋር የሚተባበረው?
ይህ ጥያቄን ያነሳ አምሓራ በሳል፣ ፖለቲካዊ ንቁ አምሓራ ነው።
ለነዚህ አንኳር ጉዳዮች ማብራሪያ የሚጠበቀው፣ ከፀረ አምሓራ ባለ አላማ ሰልፈኞች ጋር እየሰራ ከሆነ አካል እንጅ… በኡኡታ እና ፍረጃ ጠያቂዎችን ማኩሰስ ከፍትሓዊ አምሓራዊት ጋዜጠኛ ተጠባቂ አይደለም።
ይልቅ፣ ለከፋፋዮች እና ጥርጣሬውን አራጋቢ ሆነው ላሉት የለኦህዴድ አምሓሮች ግብዐት ላለመሆን እንጠንቀቅ! | 1 |
| 6 | ባላገሩ ቴሌቪዥን ተዘግቷል ወይ?
ይህ ጥያቄ በተለያየ አጋጣሚ ሰው ሲጠይቅ እሰማለሁ። ይዘጋ አይዘጋ እርግጠኛ ባልሆንም ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ እንዳለ ግን ይሰማኛል።
እኔ እስከማውቀው ድረስ ይህ ችግር የጀመረው ቀደም ብሎ ነው። አብርሃም ወልዴ የዶክተር አብይን ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ የሚል የሹመት ንግግር ከሰሙና ከተደሰቱ መሃል ነበር። ቤተመንግስት እየተጠሩ ውዳሴ ሲቀርብላቸውና ይህ ለውጥ የመጣው ለእናንተ ነው ከተባሉት ታዋቂ ሰዎችም አንዱ እሱ ነበር።
ጥበብ ነክ ነግሮች ሲዘጋጁም የእሱ እጅ እንዲነካው ይፈለግ እንደነበር አስታውሳለሁ። ለአንዳንድ የስራ ሃላፊነቶች ሲታጭ ግን ቀለል አርጎ አልፈልግም ሲል እንደነበረም አስታውሳለሁ፡፡ ነገር ግ ን ቀለል አርጎ አልፈልግም ማለት ችግር ውስጥ ሊያስገባው እንደሚችል የገባው አልመሰለኝም ነበር። በእርግጥ እኔስ ብሆን አቅሜ የፈቀደውን አገልግሎት ሰጥቼ ስልጣንን በሰላማዊ መንገድ ማስረከብ ይህን ያህል ተዘርዝሮ የማያልቅ ግፍ እንደሚያስከፍል መቼ ገምቼ?
በተለይ ከጦርነቱ ጋር በተገናኘ የተሰሩትን አልበሞች በበላይነት እንዲያሰራ ሲጠየቅ የጦርነትን አስከፊነት እንጂ ጦርነቱን የሚመራ ዘፈን አልሰራም ጦርነቱ እንዳይጀመር የሰላም ፌስቲቫል ለማዘጋጀት አሁን ስሙን ከማላስታውሰው ጓደኛው ጋር ከአፍሪካ መሪዎች ጋር ቤተመንግስቶቻቸው ድረስ በመግባት ሲመካከሩና ለዝግጅቱ ሲጋብዟቸው የነበረበት ስራ በአንድ ቀጭን ትዕዛዝ እንዲያቆሙ ሲታዘዙ የተበሳጨው አብርሃም ጭራሽኑ ይሄ እንዴት ሆነ? ያ እንዴት እንዲህ ይሆናል? ለምን እንደዚህ ተባለ? እያለ ሲተች ሲወተውት ምን እንደሚፈጠርበት ያሰበ አይመስለኝም፡፡
ድምፃዊያን ለሰሜኑ ጦርነት ዘፈን አዋጡ ሲባል ለዳዊት ፅጌ የሰጠው "አንቺን ብዬ" ብሎ ለኢትዮጵያ የተቀኘላት ግጥም ውስጥ ጦርነቱን ይብቃ ቀና በይ! ሲልና
" በድህነቷ በወሬ ምትሃት፣
ተው አትፈትኗት የአድዋን እናት"
እያለ በግልፅ ለትግራይ እናቶች ሲቀኝ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የማያውቅ አይመስለኝም።
ሚዲያዎች በሃይማኖት ጉዳይ በተለይ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ እስካሁን ድረስ ለሚያደርጉት አስዋፅዖ ጀማሪ መሆኑ በብሮድካስት እና በመንግስት ውስጥ ጥርስ ያስነከሰበት ይመስለኛል።
ሌላው ስራ ፖለቲካ ነው ካልክ የገቢዎች አምባሳደር ሁን ተብሎ ሲጠየቅና እምቢ ሲል ቀጥሎ የሚመጣው ይምጣ ብሎ መሆን አለበት ስል ነበር። አብርሃምም እንደ ቴዲ አፍሮ ወጥመድ ውስጥ አልገባ ማለቱ ብቻ ሳይህን ሚዲያው ላይ የሚቀርቡት አብዛኛው ነገሮች የተወደደለት አይመስለኝም።
በአንድ ወቅት አብርሃም በባላገሩ ቴሌሺዥን ስለሚቀርበው ስለ ኢኤምኤስ ሲጠየቅ "እኛ እንደሚዲያ መንግስት ከፈቀደ ኢትዮ 360ም ሆኑ ርዕዮት ሚዲያ ቢመጡና የሃሳብ ነፃነት በጣቢያችን ቢታይ ደስ ይለናል" ሲል ምን ሊገጥመው እንደሚችል አስቤ እሰጋ ነበር።
ብቻ አሁን የምሰማው ባላገሩ አለ ወይስ ተዘግቷል የሚለው የሰው ጥያቄ መልስ የአብርሃምን የግል አመለካከትና ማንነትን ባልወደዱ የመንግስት ሃላፊዎች እጅ ያለ ይመስለኛል።
ገቢዎች ሚኒስቴር በልዩ ሁኔታ ኦዲት እንዲደረግ አዞበት ከፍተኛ የግብር እዳ ተጥሎበት በመዳከር ላይ የሚገኘው ባላገሩ ቴሌቪዥን ይቀጥል ይሆን?
ለእውነት ለአላማቸው ዋጋ የሚከፍሉ ሙያተኞች ሊከበሩ ይገባል። ይህ አቋሙ አሁንም አብሮት እንዳለ የሚያሳየው ደግሞ ለቴዲ አፍሮ ወገንተኝነቱን ባሳየበት መልዕክቱ
"የአሁኑ ጠበል ነው መሰለኝ ልክፍት ያለባቸውን የነካቸውን ሁሉ ማስለፍለፍ ጀምሯል" ያለውን ፅሁፉን በምንም አይነት ተፅዕኖ እስካሁን ሳያጠፋው ማኖሩ ነው።
ለእውነት እና ለፍትህ የሚቆም አርቲስትን ማወደስ ማለት ጥበቡን ከትርፍና ከስልጣን በላይ ለሰው ልጅ ክብር ማዋሉን ማክበር ማለት ነው፡፡
ታሪክ እንደሚያስረዳን እንደ ፓብሎ ፒካሶ በሥዕሉ የጦርነትን ጩኸት ቀለም አድርጎ ያሳየ እንደ ፍሪዳ ካሎ፤ እንደ ቶልስቶይ ፤እንደ ሂክሜት፤ እንደ ቤትሆቨን በሙዚቃ እና በቃላቸው ጸጥታን ፈታኝ ያደረጉ ሁሉም በአንድነት ለዘመናቸው ህሊና ነበሩ ማለት ይቻላል። ብሩሽቸው እግር ነበረው ሲራመድ ፍትህ ይከተለው ነበር፡፡ ሙያቸው እንደ ወንዝ የእውነት እና የፍትህ አለቶች እንዲከፈቱ ያደረጉ ነበር፡፡
አንድ ቀን "እውነት" ልትሞት ስትቀመጥ ሁላችንም ሸሸናት፡፡ ነገር ግ ን ቀለም ብቻ ቀረች
ቀለም፡ "እኔ አልሸሽም ልቀለምሽ? " አለቻት እውነትን
"እውነትም" አለቻት ቀለምን አንቺ ብቻሽን ብትቀሪ ሰዎች ውበትሽን እንጂ ህመሜን አያዩም
ቀለሟ ግን አለቀሰች እንባዋ በራሷ ላይ ወደቀ እና ከዚያ ቀን ጀምሮ ያቺ ቀለም ስትቀባ "እውነት" ትባላለች
ያቺ ቀለም ስሟ ነው አርቲስት።
አርቲስት ለእውነት እና ለፍትህ የዘመን ህሊና ነው፡፡ እንደዚህ ያለ አርቲስት ሲያልቅ ዘመን አያልቅም ዘመኑ ግን እሱን ማለፍ እንደማይችል ይማራል፡፡
ተው አትፈትኗት "የአድዋን እናት"
ቅኔው በሚዲያ የተላለፈ አይመስለኝም። | 315 |
| 7 | بدون متن... | 253 |
| 8 | "ሚዲያ በአግባቡ ካልተመራ፣ የራስህን ወንድሞች ጠላት፣ እውነተኛ ጠላቶችህን ደግሞ ወዳጅ አድርገህ እንድታስብ ያደርግሃል”‼️
የሲቪል መዋቅሮችን «ከዜሮ መጀመር» የሚለውን ስልታዊ ጽንሰ-ሐሳብ አጣመውና አዛብተው የሚረዱ አካላት፣ በትግል ምህዳር ውስጥ ተቋማዊ ብስለት እና የስራ ክፍፍል ምን ያህል ወሳኝ እንደሆነ ካለመገንዘብ የተነሳ ታላቅ የትርጉም ስህተት ላይ ወድቀዋል።
«ከዜሮ መጀመር» ማለት ነባሩን ትግል፣ የሕዝብን የደም ውለታ እና እስካሁን የተከፈለውን መስዋዕትነት ማፍረስ ወይም መበተን ሳይሆን፤ በትግሉ አካል ላይ የተሰገሰጉትንና ለውስጥ መጠራጠር ምክንያት የሆኑትን የተበታተኑ፣ ግለሰባዊና ልምዳዊ አሠራሮችን በቁርጠኝነት ፈትቶ ሁሉንም የሚያግባባና የሚያስተሳስር አዲስ የጋራ ፕሮፌሽናል መዋቅር መዘርጋት ማለት ነው። ታላቁ ፈላስፋ ሶቅራጥስ “ለውጥ ማለት አሮጌውን መዋጋት ሳይሆን፣ አዲሱንና ጠንካራውን ነገር በሙሉ ኃይል መገንባት ማለት ነው” እንዳለው ሁሉ፣ የሲቪል ክንፎችን (ፋይናንስ፣ ስለላ፣ ሚዲያ፣ ዲፕሎማሲ) በአንድ ወጥ መመሪያ ስር መሰብሰብ የትግሉን መሠረት ይበልጥ የማጽዳትና የማጠናከር ታሪካዊ ግዴታ ነው።
የአባቶች አባባል “በበሰበሰ ጠንካራ ቤት አይሰራም” እንደሚለው፣ የቆዩትንና ለውስጥ ክፍፍል ምክንያት የሆኑትን አሠራሮች በድፍረት ፈትቶ በአዲስ መሠረት ላይ ማቆም የትግሉን ዕድሜ ረጅም ያደርገዋል።የየግንባሩ አዛዦች ወይም የየዳያስፖራ ማኅበራት የየራሳቸውን የገንዘብ ከረጢት የሚይዙበት አሮጌ አሠራር በንቅናቄው ውስጥ የአጥቢያ አበጋዝነት በሽታን ስለሚወልድ፣ የፋይናንስ መዋቅሩን ከዜሮ መጀመር ይህንን የግልና የአጥቢያ ስሜት አጥፍቶ ሁሉንም ሀብት በአንድ ማዕከላዊ የድርጅት ቋት (Single Treasury) ስር የማሰባሰብ ብቸኛው መንገድ ነው። ታላቁ መሪ ማህተማ ጋንዲ “ቁጥጥር እና ፍጹም ግልጽነት በሌለበት ምድር ላይ፣ የፈለገው ታላቅ ዓላማ ቢኖር እንኳ በገንዘብ ሩጫና በትናንሽ ስግብግብነቶች ይፈርሳል” እንዳለው፣ ገንዘብ በአንድ ቋት ስር ሲመራ ለአንድ አካባቢ ብቻ ሳይሆን ለጠቅላላው ግንባር ፍላጎቶች በስትራቴጂካዊ ፍትሐዊነት ይከፋፈላል። የአባቶች ጥበብ “አምስት ፍሬ ከሆኑ ነብር አይበላቸውም” እንደሚለው፣ የፋይናንስ ምንጮች በአንድ ቋት ስር ሲዋሃዱ በአባላት መካከል ፍጹም እኩልነትና ድርጅታዊ መተማመን ይሰፍናል።
በተመሳሳይ መልኩ፣ በፋኖ ስም የሚንቀሳቀሱት ማለቂያ የሌላቸው የየግል አፈ-ቀላጤዎች የሚመሩት ለትግሉ ድል ሳይሆን የግል የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት በመሆኑ፣ የሚዲያ መዋቅሩ ከዜሮ በአንድ ማዕከላዊ የሚዲያ ቦርድ እና ወጥ በሆነ የአርትዖት መመሪያ (Editorial Policy) ስር መሰብሰብ ይኖርበታል። ማልኮም ኤክስ “ሚዲያ በአግባቡ ካልተመራ፣ የራስህን ወንድሞች ጠላት፣ እውነተኛ ጠላቶችህን ደግሞ ወዳጅ አድርገህ እንድታስብ ያደርግሃል” እንዳለው፣ ይህ ሽግግር ሚዲያውን በጥቃቅን አለመግባባቶች ጎራ እየለዩ ከመነቋቆር አውጥቶ፣ የጠላትን ሰራዊት ሞራል የሚሰብር እውነተኛ የስነ-ልቦና ጦርነት መሣሪያ ያደርገዋል። የአባቶች አባባል “የወሬ ማገር ቤት አይቀስርም” እንደሚለው፣ የግል ጥቅም አሳዳጅ አጋፋሪዎች ወሬ ከትግሉ መሪ መስመር ሲወገድ፣ የጠላት የከፋፍለህ ግዛ ፕሮፓጋንዳ የሚረጭበት ማገዶ ያጣል።
የወታደራዊ ክንፍን ታክቲክ ከሲቪል መዋቅር ቀጣይነት ጋር ማቀላቀል ደግሞ ሌላው ሐሳቡን አጣሞ የመረዳት መገለጫ ነው። ተዋጊው ኃይል የአየር ንብረቱን (የደመና ከበባንና ወንዞች መሙላትን) በቀጥታ ወታደራዊ ታክቲክ ለማስፈጸሚያነት እና የጠላትን የአየር ላይ የበላይነት (የድሮን ጥቃት) ለመመከቻነት የሚጠቀምበት ቢሆንም፣ የሲቪል መዋቅሮች ግን ወቅታዊ የአየር ሁኔታን ጠብቀው የሚንቀሳቀሱ ሳይሆኑ፣ ጦርነቱ ያመጣውን ወታደራዊ ድል በየሰዓቱ ወደ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ የበላይነት ለመቀየር የ24 ሰዓት ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ ዝግጅት የሚያደርጉ የትግሉ ሞተሮች ናቸው። ዊንስተን ቸርችል “ጦርነት በመሬት ላይ በሚደረግ ውጊያ ይጀመራል፤ ፍጻሜውና ድሉ ግን የሚወሰነው በፖለቲካ፣ በሀብትና በዲፕሎማሲ ተቋማት ጥንካሬ ነው” እንዳለው፣ ወታደሩ መሬት ላይ ጠላትን ሲመታ፣ ዲፕሎማሲው፣ ፋይናንሱና ስለላው ያንን ድል በስትራቴጂ ደግፈው ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ወዳለው ፖለቲካዊ ትርፍ የመቀየር ተቋማዊ ኃላፊነት አለባቸው። የአባቶች አባባል “ሰው ይሞታል ታሪክና ሀገር ግን ይቀጥላሉ” እንደሚለው፣ የሲቪል መዋቅሮች በጋራ ርዕዮተ-ዓለምና በተቋማዊ ልዕልና ላይ አዲስ ሆነው ሲገነቡ፣ የትግሉ ዕድሜ የማያረጅ ወጣት ሆኖ የነገውን ዘላቂ መንግሥታዊ ድል በእርግጠኝነት ይጨብጣል። ስለዚህ ይህንን ሁሉንም የሚያግባባ፣ የሚያስተሳስርና ወደ አንድ የጋራ ግብ የሚመራ የጋራ መዋቅር የመዘርጋት ሐሳብ የትግሉ ዋና ጋሻ ነው።
መላው የአፋብን አመራር አሁን ከአለው ሀሰተኛ ብልጭልጭ ወጥተው ትክክለኛው ሀዲድ ላይ መገኘት ይኖርባቸዋል። የጋራ ጀግና፣ የጋራ ራዕይ፣ የጋራ መግባቢያ አጀንዳ፣ በሀገር ውስጥም በውጭም የጋራ ሰው የሌለን አደረጃጀቶቻችን የጋራ ስላልሆኑ ነው። ስለዚህ ይሄ መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑ መረሳት አይኖርበትም። በእርግጥ የገነገነ ስር ሲቆረጥ ሊያም ይችላል። ግን ህመሙን ጥርስን ነክሶ መቻል ነው። ስር ሰዶ የኖረ፣ ሲበዘብዝና በተልዕኮ ሲያናክስ የነበረ ከውጪ እስከ ሀገር ቤት የደም ስሩ ሲነካ ጉዳት ለሜድረስ መንፈራገጡ ረይቀርም ፤ ግን ይሄ ለጥሩ ነገር ነውና ሁሉም ዐማራ በእምነትና በመተማመን ተጋግዞ መሻገር ይችልላል። እንዲህ ብቻ ነው የምናሸንፈው።
ከዚያ ውጭ ከዜሮ ይጀመር ማለትን "ክረምቱ እንዲያልፍ" የየሚለው የአንድ አንድ ወዳጆቻችን ስጋት ከክረምቱ ጋር የማያገናኘው ወታደራዊው ኃይል እንጅ የሲቪል መዋቅሩ እንዳልኮነ ይገለጥላችሁ።
@Yidneqkachew Shewangizaw | 257 |
| 9 | بدون متن... | 355 |
| 10 | በወልቃይት ዙሪያ በመላው አለም የሚኖሩ የትግራይ ሪፐብሊክ ደጋፊዎች ሰሞኑን ስብሰባ ተቀምጠው ነበር። የስብሰባው ሰመሪ፥ በባሌም በቦሌም ብለን ጎንደሮቹን ከወልቃይት ገፈትን ( ህገ ወጥ ጎንደሬዎችን ነው የሚለው ) አገራችንን ኦንመሰርታለን፥ ያንን ለማድረግ ግን ያልተቀደሰ ጋብቻውን መፈጠም ግድ ይላል በሚለው ተስማምተዋል።
እነሱን ዐደንቃለሁ። አላማቸውን ለማስፈጠም የትም ጥግ ይሄዳሉ። ጀግኖች ናቸው በዚህ ጉዳይ። ዋናው ቁም ነገር ግን፥ ዋናው ያልተግባባንበት ጉዳይ፥ አንጓው ነገር፥ በተሰረቀ ምድር ላይ ህገወጥ የሚባል ማንም የለም።
There are no illegals on a stolen land!
ከ አማራ ጋ ታግሎ አብይን ለመገርሰስ መጀመሪያ የ አማራ የሆነውን በማክበር መጀመር፣ የአምሓራን የአምሓራ ማለት ቅድመ ሁኔታ ብቻ አይዶለም። ይህንን ለመረዳት ደሞ አማሪካ የተጎለቱ የካድሬ ልጆች እናና ያጎት ልጆች የፖለቲካ ሃሁ ሊያስተምሩን አይችሉም። በከባድ ኩራት የምናገረው፥ አይደለም እኔ ዘመዶቼም ካድሬ ሆነው ኖረው እንደማያውቁ ነው። የቀወት ሰው ሲታገል ንጂ ሲከድር ዐይታወቅም። የመሐል ሜዳ አርበኞች ልጅ መሆኔን መናገር ያለብኝ አይመስለኝም። ደብረ ሲና ላይ ወያኔን በመትረየስ ሲታገሉ የተሰውት ሰዎች በስም ሳይሆን በደም ነው የማውቃቸው። እንደ አንበጣ የጎጣቸውን ክብር ለማስጠበቅና አንድን ጎጥ ስልጣን ላይ ለማውጣት የሚውተረተሩ ጀብራሮች ግን ፥ ጮኸው ዝም ያሚያደርጉኝ መስሏቸው ሰነበቱ አሉ። ልናይ ደርሶ!!
Bottom line
You don’t need to go to school to learn stupidity! Because you are born with it!
በሬህን ከሰረቀው ሰው ጋር ፍለጋ ከሄድክ በሬህን መቼም አታገኘውም::
@Henok Yeshitila | 377 |
| 11 | ሶማሊያ ለቱርክ 3 የነዳጅ እና ጋዝ ፍለጋ ቀጠናዎችን ፈቀደች፤ ተጨማሪ ለመስጠትም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ሀገራቸው ካሏት 12 የባህር ላይ የሃይድሮካርቦን (የነዳጅ እና ጋዝ) ፍለጋ ቀጠናዎች መካከል ሶስቱን ለቱርክ መስጠታቸውን አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህ አጋርነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ተጨባጭ እና ቀጣይነት ያለው የደህንነትና የልማት ድጋፍ የሚያንጸባርቅ ነው ብለዋል።
ቀሪዎቹ ዘጠኝ ብሎኮች ለምዕራባውያን ኩባንያዎች የተሰጡ ቢሆንም፣ አንደኛው ኩባንያ የኢንቨስትመንት አቅም ማነስን በመጥቀስ ሰባቱን ብሎኮች በቅርቡ መልሶ ማስረከቡ ተገልጿል። ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በሀገሪቱ ከሚገኝ መገናኛ ብዙሃን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ቱርክ ካስፈለጋት በቀጣይም ከተሰጧት ሶስት ቀጠናዎችን በተጨማሪ ሌሎችንም ለመስጠት ሀገራቸው ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።
ከበርካታ አስርት ዓመታት ግጭት በኋላ ወደ መረጋጋት በተወሰነ ደረጃ እየተመለሰች የምትገኘው ሶማሊያ፣ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ መርሃ ግብሯ ለኢኮኖሚ እድገቷ ስትራቴጂካዊ ፋይዳ እንዳለው አምናበታለች። የሀገሪቱ የባህር ክልል ከፍተኛ ያልተነካ የነዳጅና ጋዝ ክምችት እንዳለው ቢገመትም፣ በንግድ ደረጃ ማውጣት ግን የረጅም ጊዜ እቅድ መሆኑ ተመልክቷል። | 400 |
| 12 | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ውል ላይ ደረሰ
*
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል። | 1 |
| 13 | بدون متن... | 798 |
| 14 | ሔዝቦላህ 10 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን የእስራኤል ድሮን መትቶ ጣለ
ታጣቂ ቡድኑ ‘ሄሮን 1’ የስለላ ድሮንን በሊባኖስ ቤቃ ሸለቆ ላይ ተኩሶ እንደጣለ አስታውቋል። | 721 |
| 15 | የኦህዴድ ብልፅግና የተሳሳተ ኢኮኖሚ ፖሊሲ መር ውጤት የምግብ ዋጋ 14.6 በመቶ ጨመረ
በግንቦት ወር 2018 ዓ.ም ብቻ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ደግሞ 13.4 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 14.6 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው የተመዘገበ ነው። በቀጣይ ግሽበቱ ሊቀጥል እንደሚችልም ጥናቶ ያሳያሉ።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 11.1 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንሰፖርት (12.1 በመቶ)፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ (14.6 በመቶ)፣ በኮሙዩኒኬሽን (9.1 በመቶ) ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች (10.5 በመቶ) እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች (17.9 በመቶ) ሆነው ተመዝግቧል። | 679 |
| 16 | بدون متن... | 662 |
| 17 | ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።
የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ።
ከሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አዲሱ ህግ ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ጀምሮ ገቢራዊ ተደርጓል።
ስራ ላይ የዋለው አዲሱ ህግ ግብረ-ሰዶማዊነትን ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ እስራት እና በገንዘብ ይቀጣል።
ቅጣቱ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸውን ሰዎች ጋብቻ ያስፈጸሙ ሰዎችን፣ ምስክሮችን፣ ጋብቻው እንዲፈጸም ፍቃድ የሰጡትን እንዲሁም የሰርጉን አዘጋጆች በሙሉ ያጠቃልላል ነው የተባለው።
ከዚህ ቀደም በኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነት በህግ የተከለከለ ባይሆንም፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ማግለል ይደርስበት ነበር።
ኒጀር ይህንን እርምጃ በመውሰድ ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች።
ግብረሰዶማዊነት በሴኔጋል፣ ኬንያ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ እስከ 10 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆነ እስራት ያስቀጣል።
በሶማሊያ፣ ዩጋንዳ እና ሞሪታኒያ ደግሞ የወንጀሉ ቅጣት እስከ ሞት ፍርድ ሊደርስ እንደሚችል ዘገባው አመልክቷል። | 750 |
| 18 | ዋናው ጥርሰ ሹል አውዳዊ ፋሽስት ጠላትን ተዘንግቶ ሰሜናዊ የቀጠና ግንኙነት ስጋቶች ላይ ተቸክሎ መቅረት በራሱ አስጠርጣሪ ነው።
ሚዲያዎችም ሆኑ መላው አምሓራ እና የትግሉ ባለ ድርሻ አካላት በአፋብን የቀጠናዊ ትስስር አካሔዶች ላይ ጥያቄ እና ጥርጣሬ ቢያድርባቸው፣ መጠየቅ ጥርጣሬው እንዲገፈፍ፣ መተማመን እና የውስጥ አንድነት እንዲጠናከር መስራት ባለበት ሆኖ ዋና የትግል ኢላማችን የሆነውን አገዛዝ የዘነጋ መሆን የለበትም።
አንዳንድ ሚዲያዎች፦ በአካሔድ ማስተካከል እና የቀጠና ትስስር ስህተቶች ሰበብ ለጠላት ግብዐት የሚሆኑለት ፕሮፖጋንዳዎችን አብዝተው እየሰሩ እያየን ነው።
አፋብን በማዕከላዊ ፖሊት ቢሮ ወስኖ የሚያደርጋቸው ከየትኛውም ኃይል ጋር ግንኙነቶች ለአምሓራ ህዝብ ጥቅሞች እየተመዘኑ በውስጥ ትግል ይደረግባቸዋል እንጅ… ለፕሮፖጋንዳ እና የውስጥ አንድነትን በሚሸረሽር መልኩ መሆን የለበትም።
አንዳንድ ሚዲያዎች፣ ፋኖ የሚያደርጋቸውን ግንኙነቶች ሁሉ፣ ገና በእንጭጩ በፍረጃ አቋም በትችት ስለት መወጋጋቱ፣ የውስጥ አንድነትን ከፋፋይ አቅጣጫን መከተሉ ለትግሉ የሚጨምረው የለም።
ጥያቄዎች የሚጠሩበት የራሳቸው ጊዜ አላቸው።
በውስብስብ ፍጎቶች እና አደገኛ ሴራ በሚሳለጥበት የምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ ሜዳ… ለጋው፣ ነገር ግን ባለፍርጡም ጡንቻ የሆነው የፋኖ ኃይል በጥንቃቄ በተቼት በግዙፍ ክንድ መደገፍ አለበት።
የፋኖን ትግል፣ የግለሰቦች የስልጣን እና ግልብ የስሜት ፍላጎት ማስፈፀሚያ አስመስሎ ሚዲያ ላይ በመንዛት፣ ክፍፍሎችን በማጋነን በህዝብ አደባባይ ማውሳት የወዳጅ ግብር አይደለም። ትግሉ ከምንጊዜውም በላይ፣ የውስጥም የውጭም ጥንቃቄ ይሻል። የተከበብነው በጠላት እንደመሆኑ፣ ከባቢ ሰርጎገብ ትግላችንን ተጨንብሎ ከውስጥም አለብንና…!!! | 785 |
| 19 | "የትግራይ ወታደራዊ አቅምን ማዳከም አልተቻለም፣ ጥረቱም አልተሳካም"
ጀነራል ምግበይ
የሰሜን ምዕራብ ትግራይ ወታደራዊ ዕዝ አዛዥ ጀነራል ምግበይ ከሰሞኑ በድንበር አካባቢዎች የተፈጸሙት የድሮን ጥቃቶች የትግራይን የመከላከል አቅም ለማዳከም የታለሙ ቢሆንም ዓላማቸው ግን ሳይሳካ ቀርቷል ሲሉ ተናገሩ።
ጀነራል ምግበይ በሽራሮ ከተማ ባደረጉት ንግግር፣ በቅርቡ በተሰነዘሩት የድሮን ጥቃቶች ሳቢያ የሰራዊት አባላት መስዋዕትነት መክፈላቸውን አረጋግጠዋል።
"መስዋዕትነት እየከፈልን ያለነው ለታላቅ ዓላማ ነው" ያሉት ጀነራሉ፣ ጥቃቱ በትግራይ ህዝብና ሰራዊት መካከል ያለውን አንድነት ይበልጥ ያጠናክረዋል ሲሉ ተናግረዋል።
ጀነራል ምግበይ በንግግራቸው በአሁኑ ወቅት ወሳኝ በሆነ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ሲሉ ጠቁመው "ያለን ምርጫ ገመዱን በጥሰን መውጣት አልያም በዚያው ገመድ ታንቀን በድንግርግር ውስጥ መኖር ነው። ይሄ ደግሞ ምርጫችን አይደለም።” ብለዋል።
ይህ ንግግራቸውም አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመለወጥ እስከ መጨረሻው መስዋዕትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውን የሚያመላክት እንደሆነ ተተርጉሟል።
የመከላከል አቅም አለን ጠላቶቻችንም እናሸንፋለን ሲሉ የገለጹት ጀነራሉ ሰራዊቱ ግንባር ላይ እየተዋደቀ፣ አመራሩ እየመራ፣ ህዝቡ ደግሞ ደጀን ሆኖ በጋራ በመቆም ድልን እንቀናጃለን ሲሉም ተናግረዋል።
ይህ ንግግራቸውም አካባቢው ወደ ወታደራዊ ግጭት እያመራ መሆኑን የሚያመላክት ጠንካራ መልዕክት አዘል እንደሆነ ተመልክቷል።
ይህ የጀነራል ምግበይ ወታደራዊ ዝግጁነትን የሚያንፀባርቅ ንግግር የተሰማው፣ በፌደራል መንግስቱና በህወሃት መካከል እየታየ ያለውን ውጥረት ለማርገብ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ መቀሌ ደርሰው ከተመለሱ በኋላ መሆኑ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል። የፌደራል መንግስቱ እስካሁን በትግራይ ስላለው የጸጥታ ሁኔታም ሆነ ስለ ድሮን ጥቃቱ የሰጠው ይፋዊ መግለጫ የለም
Via : times mereja | 790 |
| 20 | https://www.youtube.com/live/YfTjg6YBzvY?si=O3ZQPy3C8ZW5ZnIT | 733 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
