ru
Feedback
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

Открыть в Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ +251118124566 0900834565

Больше
2 848
Подписчики
+824 часа
+257 дней
+2430 день

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июнь '26
июнь '26
+68
в 1 каналах
май '26
+104
в 3 каналах
Get PRO
апрель '26
+118
в 3 каналах
Get PRO
март '26
+226
в 3 каналах
Get PRO
февраль '26
+87
в 2 каналах
Get PRO
январь '26
+77
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '25
+104
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+602
в 5 каналах
Get PRO
октябрь '25
+196
в 2 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+104
в 2 каналах
Get PRO
июль '25
+114
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+103
в 2 каналах
Get PRO
май '25
+61
в 2 каналах
Get PRO
апрель '25
+65
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+95
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+130
в 0 каналах
Get PRO
январь '25
+41
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+55
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+32
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+28
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+13
в 0 каналах
Get PRO
июль '24
+7
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+16
в 0 каналах
Get PRO
май '24
+16
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+106
в 0 каналах
Get PRO
март '24
+10
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+12
в 1 каналах
Get PRO
январь '24
+13
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+22
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+46
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '23
+16
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+12
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+18
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+16
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+9
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+15
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+21
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+11
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+19
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+23
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+46
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+10
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+43
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+44
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+35
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+35
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+28
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+36
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+113
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+12
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+14
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+27
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+28
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+85
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+80
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+59
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+688
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
20 июня+1
19 июня+8
18 июня+7
17 июня+7
16 июня+3
15 июня+3
14 июня+3
13 июня+1
12 июня+4
11 июня+7
10 июня+1
09 июня+3
08 июня0
07 июня+1
06 июня+4
05 июня+3
04 июня+5
03 июня+3
02 июня+3
01 июня+1
Посты канала
2
+9
Нет текста...
358
3
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለተገልጋዮች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ተገልጋዮች ገለጹ 🇪🇹አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12፣ 2018 🇪🇹 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለተገልጋዮች የላቀ አገልግሎት ለመስጠት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ቢሮው በከተማ አስተዳደሩ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፣ በየሳምንቱ ረቡዕ እና አርብ ቀናት አመራሮቹ በቢሮ በመገኘት የተገልጋዮችን ጥያቄ በቀጥታ የሚፈቱበትን አሰራር በመዘርጋት አገልግሎት እየሰጠ ነው። ይህንን አሰራር ተከትሎ ዛሬ በተከናወነው የመስተንግዶ ሂደት በርካታ ተገልጋዮች የቢሮውን አገልግሎት ያገኙ ሲሆን፣ ተገልጋዮቹም ስለነበራቸው ቆይታ አዎንታዊ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የተለያዩ የሥራ ተቋራጮች እና የጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተዉ እየሰሩ ያሉ የኢንተርፕራይች ተወካዮች  ለቢሮው አመራሮች የተለያዩ የመልካም አስተዳር ጥያቄያቸውን ማቅረባቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ በተለይም፦ •  ቀልጣፋ አቀባበል እና ክፍት ውይይት: ተገልጋዮች በቢሮው አመራሮች የተደረገላቸው አቀባበል እጅግ በጣም ጥሩ እና ከሽንገላ የጸዳ መሆኑን ገልጸዋል። ውይይቶቹም ፈጽሞ ግልጽ (ኦፕን) በሆነ ሁኔታ እየተከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል። •  የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ድጋፍ: የሥራ ተቋራጮች በቢሮው በኩል እየተደረገላቸው ያለውን የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ትስስር አበረታች እንደሆነ አረጋግጠዋል። በተለይም ለተመራቂ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገው ድጋፍ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ተገልጋዮች ተናግረዋል። •  የአሰራር ለውጥ: አሁን ላይ ያለው አሰራር ቀደም ሲል ከነበሩት የተሻለ እና ለተጠቃሚዎች ምቹ እንደሆነ የገለጹት ተገልጋዮቹ፣ በቢሮው የሚሰጠው ፈጣን ምላሽ የሥራ ዕድገታቸውን ለማፋጠን እየረዳ እንደሆነ  ገልጸዋል። የቢሮው አመራሮች በበኩላቸው፣ ለተገልጋዮች ቅድሚያ በመስጠት ጥያቄዎቻቸውን በመፍታት ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። በቀጣይም በከተማ ደረጃ የተቀመጠውን የአሰራር አቅጣጫ መሰረት በማድረግ፣ የተገልጋዮችን ቅሬታና ጥያቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸዉን አስታውቋል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
309
4
+5
Нет текста...
514
5
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከፍትሕ ቢሮ የትብብር ጥምረት ጽሕፈት ቤት ጋር በመሆን፤ ባለፉት 11 ወራት 807 ሺህ ዜጎችን በግንዛቤ ፈጠራ ተደራሽ የማድረግ፣ ለ740 ስደት ተመላሾች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችለዋል ፡፡ 🇪🇹ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ|አበባ🇪🇹 📊 የሥራና ክህሎት ቢሮ ዓበይት ስኬቶች በቁጥር፡- 📢 የ127% የግንዛቤ ፈጠራ ስኬት፡- ሕገ-ወጥ ስደትንና የሰዎች ዝውውርን አስከፊነት ለሕብረተሰቡ ለማስገንዘብ 635,379 ሰዎችን ተደራሽ ለማድረግ አቅደን፣ ዕቅዱን በከፍተኛ ደረጃ በማሳለጥ 807,384 ዜጎችን በተለያዩ መድረኮችና የሚዲያ አማራጮች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል። 💼 የሥራ ዕድል ፈጠራ፡- ለ716 ስደት ተመላሾች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ፣ ለ740 ተመላሾች (235 ወንዶችና 505 ሴቶች) የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ለ68 ዜጎች ደግሞ የመሥሪያ ቦታ (የገበያ ሼድ) ተሰጥቷቸዋል። 🤝 አጋርነትና ቅንጅት፡- ከዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት (ILO)፣ UN Habitat እና ሳፋሪኮም (Safaricom) ጋር በመተባበር የ200 (60  ፕርሰንት ስደት ተመለሽ 㙀ENA 40 host community )ስደት ተመላሾችን ሕይወት የሚቀይሩ 100 ዘመናዊ ሱቆች ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል። በተጨማሪም ከባለድርሻ አጋር ድርጅቶች (እንደ Good Samaritan, TaYA, DEC, CARITAS እና ሌሎች) ጋር የመግባቢያ ሰነድ (MOU) ተፈርሟል። ⚖️ የአጠቃላይ የትብብር ጥምረቱ ስትራቴጂካዊ ስራዎች (በፍትሕ ቢሮ የሚመራ)፦ በፍትሕ ቢሮ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ዮሐንስ ብርሃኑ አስተባባሪነት፣ ጥምረቱ በ5 ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ግቦች ላይ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። እነዚህም፡- የግንዛቤ ሥራዎችን በአደባባይ፣ በሚዲያና በመድረክ በስፋት መስጠት፣ ወንጀል መከላከልና ሕግ ማስከበር ሥራዎች፣ የፍልሰት ጉዳዮች ምክር ቤትና የትብብር ጥምረት አደረጃጀትን ማጠናከር፣ የወንጀል ጥቆማዎችን በነፃ ስልክ ጥሪ 6073 መቀበልና መረጃ መስጠት፣ የወንጀል ተጋላጭነት ቦታዎችን የመለየት ጥናትና የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች ናቸው። 🗣 የዕውቅና አስተያየት፦ ከትብብር ጥምረት ጽ/ቤት  ጋር መድረኩን ያመቻቹት የሆፕ ፎር ጀስቲስ ካንትሪ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሶስና ይርጋ እንደገለጹት፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀልን ለመቅረፍ ባለድርሻ አካላትን አቀናጅቶ መሥራት የሚጠይቅ ሲሆን፣ ጥምረቱ ከሌሎች አቻ ክልሎች ጋር ጭምር የጀመራቸው የቅንጅት ሥራዎችና የሥራና ክህሎት ቢሮ ያሳያቸው ተጨባጭ አፈጻጸሞች ለሌሎችም እንደ መልካም ተሞክሮ ሊወሰዱ የሚችሉ ናቸው። ቢሮአችን በቀጣይም ከተመዘገቡት ጠንካራ ስኬቶች በመነሳትና ክፍተቶችን በመሙላት፣ ከፍትሕ ቢሮና ከሁሉም የትብብር ጥምረት አባላት ጋር በመሆን የዜጎችን ደህንነትና ዘላቂ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል። https://aabols.gov.et/qr.html
494
6
+9
Нет текста...
1 158
7
በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት 70ሺ ለሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ እድል እንደሚፈጠር ተገለጸ፡፡ 🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት  በዋናነት ያለፈውን ዓመት አፈጻጸም በማጠናከርና በዘላቂነት ላይ የተመሠረተ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል። በዚህም መሠረት 175,000 አዳዲስ አማራጭ የሥራ ዕድሎችን በጥናት የመለየት፣ 70,000 የከተማ ነዋሪዎችን በአዳዲስ የስራ ዕድል  ተጠቃሚ የማድረግ፣ እንዲሁም በከተማ ግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና አገልግሎት ዘርፎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የማስፋት ሥራዎች በቅድሚያ ይከናወናሉ። ለዚህ ስኬታማነትም 630,000 የከተማ ነዋሪዎችን በማሳተፍ የሚከናወኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎችና መድረኮች በወረዳ፣ በብሎክና በክፍለ ከተማ ደረጃ ተዘጋጅተው ወደ ተግባር ይገባሉ። የኢንተርፕራይዞችን አቅም በማሳደግ ረገድ አዳዲስ 2,000 ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት 14,000 አንቀሳቃሾችን ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል። የፋይናንስ አቅርቦትን በተመለከተም 660 ሚሊዮን ብር ብድር፣ የመሳሪያ ሊዝ አገልግሎት፣ እና ለ925 ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ የማመቻቸት ሥራዎች በዋናነት ይከናወናሉ። በተጨማሪም ከተማዋን ሊቀይሩ በሚችሉ የአካባቢ ልማት ሥራዎች ላይ 208,118 ተጠቃሚዎችን በማሳተፍ የመንግስት ማቺንግ ፈንድ ክፍያዎችን መፈጸምና ተጠቃሚዎች የባንክ ሂሳብ እንዲኖራቸው የማድረግ የኑሮ ደረጃ ማሻሻያ ስራዎች በቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። የክህሎት ሥልጠናን በተመለከተ የመንግስት ኮሌጆች 8,526 ተመራቂዎችን በብቃት አስመርቆ ለሥራ ገበያው የማስተሳሰር ሥራ ይከናወናል። የሥልጠና ጥራትን ለማረጋገጥም 2,773 አሰልጣኞችን በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና ማብቃት፣ 312 አመራሮችን በስልጠና ማብቃት እና 150 አዳዲስ አሰልጣኞችን በመቅጠርና በመመደብ የሰው ኃይል አቅምን የማጠናከር ስራ ይሰራል። ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተጠናከረ ትስስር በመፍጠር 80% የሚሆኑ ተመራቂዎችን ከሥራ ጋር የማገናኘትና አዳዲስ መመሪያዎችን በማጽደቅ የአሰራር ማነቆዎችን የመፍታት ሥራዎች በዘላቂነት ይሰሩበታል። የከተማውን የኢንዱስትሪ ሰላም ለማስጠበቅ በ4,900 ድርጅቶች ላይ የሥራ ሁኔታዎች ቁጥጥር ይካሄዳል። የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ለ800 አመራሮችና ፈጻሚዎች በመስጠት፣ እንዲሁም 150 አዳዲስ የሠራተኛ ማህበራትን በማደራጀት የኢንዱስትሪ ሰላምን የማስጠበቅና የሠራተኛውን ጥቅማ ጥቅም የማስከበር ተግባራት በሦስቱ ወራት ውስጥ በልዩ ትኩረት ይፈጸማሉ። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
1 051
8
+2
Нет текста...
655
9
+9
Нет текста...
605
10
በበጀት ዓመቱ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተሸጋገሩ፤ በቦሌ ሰሚት በሳይንስና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ አዲስ የልማት ተአምር ያስመዘገበው የ“ፍሬህይወት ዘሮባቤል” ማህበር አርአያነት ተበሰረ 🇪🇹ሰኔ 9 ቀን 2018  አዲስ አበባ (የቢሮ ጋዜጠኛ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ  በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከጥቃቅን ጀምሮ እስከ መካከለኛ ደረጃ የሚገኙ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር ማድረጋቸውንና ይህም ከባለፉት ዓመታት እጅግ የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበበት ስኬት መሆኑን የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ አስታወቀ። ዘርፉ የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና የአሠራር ሥርዓታቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማጥለቅ ታላቅ ሳይንሳዊ የምክክርና የተሞክሮ ማስፋፊያ መድረክ አካሂዷል። ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ፣ በከተማ ግብርና (በእንስሳት እርባታ) ዘርፍ እጅግ የላቀና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲስ ተስፋ የፈነጠቀውን የ«ፍሬህይወት ዘሮባቤል እና ጓደኞቻቸው የወተት ከብት እርባታ ህብረት ሽርክና ማህበር»ን ምርጥ ተሞክሮ ሳይንሳዊ በሆነ ዘዴ በተግባር እንዲሰፋ ተደርጓል።   የፖሊሲ ሪፎርም እና የኢንተርፕራይዞች ታሪካዊ ሽግግር የቢሮ የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ላይ የተሞክሮ ቅመራና የእድገት ደረጃ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኑሩ ሁሴን መሐመድ አሊ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ የመድረኩ ዋና ዓላማ የፖሊሲ ሪፎርሞችን ማውረድና የተመረጡ ምርጥ ተሞክሮዎችን በሳይንሳዊ መንገድ ወደ ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ማስፋት ነው። በበጀት ዓመቱ እስከ 11 ወራት ባለው ሪፖርት ብቻ 162 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ሞዴል ኢንተርፕራይዞች መፍራት መቻላቸውን የጠቆሙት አቶ ኑሩ፣ መንግስት ለዚህ ስኬት በርካታ የፋይናንስ ድጋፍ፣ የመሳሪያ ሊዝ አቅርቦት፣ የምርታማነት ልኬት እገዛና የገበያ ትስስር ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን ከመንግስት ድጋፍ ውስንነት፣ ከራሳቸው ከኢንተርፕራይዞቹ የግንዛቤ ክፍተት እና ሰነዶችን ለጥቅም ማግኛ ብቻ ከመጠቀም ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጽናት መታገል እንደሚገባ አቶ ኑሩ አሳስበዋል። “የመድረኩ ዋና ዓላማ 'መስራት ይቻላል' የሚለውን እሳቤ በተግባር ማሳየት ነው” ያሉት ዳይሬክተሩ፣ በቀጣይም ይህ ምርጥ ተሞክሮ መሬት ላይ መውረዱን ባለሙያዎች በቅርብ ክትትል እንደሚያረጋግጡ በቁርጠኝነት ገልጸዋል።   ከቀውስ ወደ ስኬት ማማ፦ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር የልማት ተአምር በመድረኩ ማጠቃለያ ቀን 125 በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችና ባለሙያዎች በተገኙበት፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሰሚት ኮንዶሚኒየም አካባቢ የሚገኘውና በጠንካራዋ ሴት ወይዘሮ ፍሬህይወት ዘሮባቤል የሚመራው ማህበር ተሞክሮ በቪዲዮና በፕረዘንቴሽን ቀርቦ ተተንትኗል። በአንድ ወቅት ፈታኝ በነበረው የስራ አጥነት እና የወደፊት ተስፋ ማጣት ውስጥ የነበረችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ዛሬ የወተት ከብት እርባታን ሙሉ በሙሉ በሳይንስና በጥናት ላይ የተመሰረተ ማራኪ የኢንቨስትመንት መስመር አድርጋዋለች።   የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂ ድል ማህበሩ ስራ ሲጀምር የወንዶች ጥጃዎች ብቻ መወለድ እና የዝርያ እጥረት ለከፍተኛ ኪሳራ ዳርጎት እንደነበር ያስታወሰችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ላሞችን ከውጭ ሀገር በአውሮፕላን ለማስገባት የሚጠይቀው ከፍተኛ ወጪ (ከ1,000 እስከ 6,000 የአሜሪካ ዶላር) ትልቅ ማነቆ ሆኖባቸው እንደነበር ገልጻለች። ይህንን ፈተና ለመስበር ማህበሩ የጥጃውን ጾታ አስቀድሞ መወሰን የሚያስችለውን የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂን በድፍረት ስራ ላይ አውሏል። ቀደም ሲል ያልተለየው መደበኛ ዘር እስከ 500 ብር ይሸጥ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ጾታው የተለየው ምርጥ ዘር ከ1,500 እስከ 2,000 ብር በሚደርስ ተመጣጣኝ ዋጋ ለመንግስት በመክፈል ማህበሩ በስፋት እየተጠቀመበት ይገኛል። በዚህም ተአምራዊ በሆነ መንገድ በአንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 13 ምርጥ የሴት ጊደር ጥጃዎችን ማፍራት ችለዋል።   "ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም" — አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ለእርባታ የማህበሩን የእድገት አቅጣጫና ስልታዊ የቢዝነስ ፕላን የሚያዘጋጀው ወጣቱ ባለሙያ ቢኒያም፣ ቅዱስ መጽሐፍ ላይ የሚገኘውን “ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም” የሚለውን የወርቃማ  ቃል በመጥቀስ ስራቸውን ሙሉ በሙሉ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ላይ መመስረታቸውን በስሜት አብራርቷል። ማህበሩ እንደ ጎግልና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ያሉ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጮችን ለመረጃ ምንጭነት ይጠቀማል። መረጃዎቹን በቀጥታ ከመተግበራቸው በፊት፣ በዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታተሙ የሪሰርች ወረቀቶች (Research Papers) ጋር በማጣራት (Cross-check) ያረጋግጣሉ። ባለሙያው ቢኒያም እንደገለጸው፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እጅግ ሰፊ የሆኑ የኮርማዎችን ታሪክ በጥልቀት በማንበብና በዘርፉ የላቀ እውቀት ለሌላቸው ሰዎች ጭምር በቀላሉ በሚረዳ ቋንቋ (Layman's terms) በመተንተን ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ይህ የቴክኖሎጂ እገዛ ማህበሩ የሚከተሉትን ስራዎች በስኬት እንዲወጣ አስችሎታል፦ 1/የላሞቹን ወተት ምርት፣ ቁመትና የደረት ስፋት ለማሻሻል ትክክለኛውን የኮርማ ዝርያ መምረጥ። 2/ የተመጣጠነ የከብት ምግብ (Balanced feed) በሳይንሳዊ መንገድ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዓለም አቀፍ ሰነዶችን ማሰባሰብ።   የምርት ዘመን ዑደት እና የአሁኑ አቅም በውጭ ሀገራት ተሞክሮ አንዲት ላም ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የምትሰጠው ከተወለደችበት ጊዜ ጀምሮ ቢበዛ እስከ 5 ዓመት ብቻ መሆኑን የጠቀሰው ቢኒያም፣ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ግን በጥንቃቄ በመያዝ ላሞች እስከ 6 እና 7 ዓመታት ድረስ ምርት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል። በአሁኑ ወቅት ማህበሩ በአጠቃላይ ጥጃዎችን፣ ጊደሮችን እና የሚታለቡ ላሞችን ጨምሮ 35 የከብቶች ክምችት ላይ ደርሷል። ከእነዚህም ውስጥ 10 የሚሆኑት ላሞች በአሁኑ ወቅት እርጉዝ ሲሆኑ፣ በቅርቡ ወደ ምርት ምዕራፍ ሲገቡ የማህበሩን የወተት አቅርቦት በአስደናቂ ሁኔታ በእጥፍ ያሳድጉታል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር ስኬት፣ ጠንክሮ ለሚሰራ እና ቴክኖሎጂን ለሚጠቀም ማናቸውም ኢንተርፕራይዝ “መስራት እና መለወጥ ይቻላል!” የሚል ትልቅ የተስፋ ስንቅና ህያው ምስክር ሆኖ አልፏል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
534
11
Нет текста...
544
12
#ዜና ሹመት አቶ ሙሉቀን ዮናስ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስትዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ   ሆነው ተሹመዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ  የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት  መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንልዎ ይመኛል። 🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹 <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
534
13
Нет текста...
879
14
‹‹የዓለም ባንክን ተሞክሮ በኢትየጵ መንግስት  በጀት መተግበራችን ከተረጂነት የተላቀቀ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው›› — አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ቀደም ሲል ከዓለም ባንክ ጋር ይተገበር የነበረውን አሰራር ወደ መንግስት አሰራር በመቀየር ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በከፍተኛ ስኬት እየገበረ ይገኛል። የቢሮው የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን እንደገለጹት ይህ ፕሮጀክት ዜጎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚያሸጋግር ቢሮው የያዘው ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ ነው። በዚህም መሠረት ቢሮው 145 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ በ20 ወረዳዎች የሚገኙ 3 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ቤት ውስጥ የተቀመጡ ሴቶች ወደ ገበያ እንዲገቡ ለማድረግም 60 በመቶ የሚሆነው የዕድል ኮታ ለሴቶች እንዲሰጥ ተደርጓል። ወጣቶቹ ወደ ድርጅቶች ከመሰማራታቸው በፊት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የ12 ቀን የሕይወት ክህሎት ሥልጠና እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ 3 ሺህ 751 ወጣቶች ሥልጠናውን አጠናቀዋል። ከዚያም በጥብቅ ምልመላ ያለፉ 3 ሺህ ወጣቶች በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽንና በአገልግሎት ዘርፍ ለሥራ ባህል ምቹ በሆኑ 758 ድርጅቶች ውስጥ የ6 ወር ተግባራዊ ልምምዳቸውን አድርገዋል። መንግስት በየወሩ የ3 ሺህ ብር የትራንስፖርት አበል የከፈለ ሲሆን በርካታ ድርጅቶችም የወጣቶቹን ትጋትና አፈፃፀም በማየት ከቢሮው ክፍያ በተጨማሪ ከ4 እስከ 5 ሺህ ብር ተጨማሪ የፓርት ታይም ክፍያና ጥቅማጥቅሞችን አበርክተውላቸዋል። የፕሮግራሙን አካታችነት ይበልጥ ያረጋገጠው ሌላው ስኬት በሀገሪቱ የመኖር ፈቃድ ያላቸውን 2 ሺህ የሚጠጉ የየመን፣ ሶማሊ፣ ሱዳንና ኤርትራ የውጭ ሀገር ስደተኞችን በ338 ድርጅቶች ውስጥ ማካተቱ ነው። ይህ አካሄድ የዓለም ባንክን ሞዳሊቲ መንግስት በራሱ አቅምና በጀት ወስዶ በመተግበር ያሳየው ትልቅ ስኬት መሆኑን አቶ ሰብሃዲን ጠቁመዋል። አሁን ላይ የልምምድ ጊዜያቸውን አጠናቀው ሰኔ 10 ሙሉ በሙሉ ከድርጅቶች የሚወጡትን ወጣቶች በቋሚነት ለመቅጠር ሰፊ ሥራ እየተሠራ ሲሆን ካለው ኮታ ውስጥ እስካሁን በቋሚነት ያልተሳሰሩ  ወጣቶች ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ የማስተሳሰር ሥራው እንደሚጠናቀቅ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። ይህ የብቃት የወጣቶች የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ወጣቶች የ6 ወር የሥራ ልምድ ማረጋገጫ ይዘው የተሻለ ተወዳዳሪና ከፍተኛ ክፍያ የሚያገኙበትን ዕድል የፈጠረ ሲሆን ሰልጣኞቹ አሁን ላይ ራሳቸውን ችለው ድርጅት ለመክፈት የሚያስችሉ የኢንተርፕረነርሺፕ ሐሳቦችን እያነሱ ይገኛል። ቢሮው ይህንን ስኬት መሠረት በማድረግ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም በየዓመቱ 3 ሺህ ወጣቶችን በማቀፍ፣ በአጠቃላይ በቀሪዎቹ 119 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 15 ሺህ ወጣቶችን የዚህ  ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለማድረግ የስትራቴጂክ ዕቅዱን አጽድቆ ወደ ተግባር መሸጋገሩን አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን አስታውቀዋል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
795
15
+3
Нет текста...
827
16
በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው እየተስተናገዱ ይገኛሉ። 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የባለጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ በቢሮው አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የተሳለጠ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። የባለጉዳይ ቀንን አስመልክቶ የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የመጡ ባለጉዳዮችን ባነጋገረው መሠረት፤ በቢሮው እየሰጠ ያለውን አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አድርጓል።  በዚህም አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው በአግባቡና በፈጣን ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል። በዕለቱ በቢሮው ተገኝተው አገልግሎት ያገኙ ልዩ ልዩ ተገልጋዮችም በተሰጣቸው መስተንግዶ መደሰታቸውንና ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከሰንሻይን ኮንስትራክሽን ድርጅት ሰራተኛ ለማዋዋል ወደ ቢሮው የመጡት አቶ ንዋይ ተፈራ በሰጡት አስተያየት ወደ ቢሮው እንደመጡ ከአንድ ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ፈጽመው ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። አቶ ንዋይ አክለውም «በቢሮው ውስጥ በጣም ቅን የሆኑ ባለሙያዎችን አግኝተናል። በዚህ መልክ የሚስተናገድ ከሆነ በየቀኑ እንኳን ብንመጣ ደስ ይለናል ማንም ሰው ሳይከፋ በአገልግሎቱ ተደስቶ ነው የሚሄደው» ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተመሳሳይ ከመስኮን ኮንስትራክሽን አገልግሎት ለመጠየቅ የመጡት ኢንጂነር ብሩክታይት ገብሬ በበኩላቸው ከቢሮው የበር መግቢያ ጀምሮ የተደረገላቸው አቀባበልና መስተንግዶ እጅግ የሰለጠነና በስርዓት የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። የቢሮው የውስጥ አቀማመጥ እንዲሁም በፋይናንስና በመዝገብ ቤት በኩል የነበረው የሥራ ፍሰት ቀልጣፋ መሆኑን ያነሱት ኢንጂነር ብሩክታይት ለአገልግሎት አሰጣጡ ይበልጥ መሻሻል የሚረዳ ገንቢ አስተያየታቸውንም አካፍለዋል። ኢንጂነሯ በአስተያየታቸው «መስተንግዶው በጣም ጥሩ ቢሆንም፤ ተገልጋዮች ዶክመንት ኮፒ ለማድረግ ከቢሮው ወጥተው ሩቅ መንገድ ለመጓዝ እየተገደዱ ነው። ስለዚህ ይህንን እንግልት ለማስቀረት በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ወይም በቅርበት የኮፒ አገልግሎት የሚሰጥበት ቢዝነስ ሴንተር ቢከፈት መልካም ነው» የሚል ጥቆማ ሰጥተዋል። ቢሮው የተገልጋዮችን እርካታ ይበልጥ ለማሳደግ መሰል የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተመላክቷል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
778
17
Нет текста...
693
18
የነጻ ግራፊክ ዲዛይን ስልጠና ጥሪ በፊን ቸርች ኤይድ (FCA) የተዘጋጀ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂ ነዎት? በግራፊክ ዲዛይን ሙያ ተግባራዊ ክህሎቶችን ለማግኘት ይህን ነጻ ስልጠና ይቀላቀሉ። በስልጠናው የሚማሩት፦ • የግራፊክ ዲዛይን መሰረታዊ እውቀቶች • ብራንዲንግ እና ሎጎ ዲዛይን • የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ዲዛይን • የዲዛይን ሶፍትዌሮች እና የፈጠራ መሳሪያዎች • የስራ ፖርትፎሊዮ ዝግጅት የስልጠና ዝርዝር፦ • ቆይታ፡ 6 ሳምንት • መርሃ ግብር፡ በሳምንት 2 ቀን (ከጠዋቱ 3:00 እስከ 11:00 ሰዓት) • ቦታ፡ FCA Creators Hub, ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ አዲስ አበባ ማመልከት የሚችሉ፦ • ስራ ፈላጊ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂዎች • ከ18–34 ዓመት ዕድሜ ያላቸው • ስደተኞች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ በተለይ ይበረታታሉ • ሙሉ የስልጠና ጊዜውን መከታተል የሚችሉ ያመልክቱ፡ https://forms.gle/7wfyjGeYT2Gx9dXs6 የማመልከቻ መጨረሻ ቀን፡ ሰኔ 10፣ 2018 ዓ.ም. (June 17, 2026) ⚠️ የተወሰነ ቦታ ስላለ በፍጥነት ያመልክቱ!
891
19
Нет текста...
847
20
+2
Нет текста...
1 011