es
Feedback
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

Ir al canal en Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ +251118124566 0900834565

Mostrar más
2 960
Suscriptores
+724 horas
+887 días
+13530 días
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+92
en 2 canales
junio '26
+113
en 1 canales
Get PRO
mayo '26
+104
en 3 canales
Get PRO
abril '26
+118
en 3 canales
Get PRO
marzo '26
+226
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+87
en 2 canales
Get PRO
enero '26
+77
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+104
en 1 canales
Get PRO
noviembre '25
+602
en 5 canales
Get PRO
octubre '25
+196
en 2 canales
Get PRO
septiembre '25
+99
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+104
en 2 canales
Get PRO
julio '25
+114
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+103
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+61
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+65
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+95
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+130
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+41
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+55
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+32
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+28
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+15
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+13
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+7
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+16
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+16
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+106
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+10
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+12
en 1 canales
Get PRO
enero '24
+13
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+22
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+46
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+16
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+12
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+15
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+18
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+16
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+9
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+15
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+21
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+19
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+23
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+46
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+10
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+43
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+44
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+35
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+35
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+28
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+36
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+113
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+12
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+14
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+27
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+28
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+85
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+64
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+80
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+59
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+688
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
07 julio+7
06 julio+7
05 julio+8
04 julio+7
03 julio+37
02 julio+24
01 julio+2
Publicaciones del Canal
2
+9
Sin texto...
546
3
የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም በዕውቀትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ አሠራር ለመዘርጋት እንደሚያስችል ተገለፀ። 🇪🇹 ሰኔ 30/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር የመጀመሪያ ምዕራፍ ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ፣ ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ሠራተኞች ጋር በንፋስ ስልክ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በተግባረ ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር የውይይት መድረክ አካሂዷል። በንፋስ ስልክ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ክላስተር በተካሄደው መድረክ ላይ የተገኙት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ የሪፎርሙ ዋና ዓላማ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ አሠራር በመገንባት ሠራተኛው በብቃት ላይ የተመሠረተ ፍትሐዊ የሥራ ዕድገት የሚያመጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከሠራተኞች የደረጃ ዕድገት ጋር የተያያዙ መዋቅራዊ ጥያቄዎችን አንስተዋል። ሠራተኞች በራሳቸው ጥረት ትምህርታቸውን አሻሽለው ቢመጡም ምደባ እያገኙ እንዳልሆነና ይህም በሠራተኛው ሞራል ላይ ጫና ስላለው፣ በትግበራው ወቅት አድልዎ እንዳይኖር ግልጽ የቅሬታ ማስተናገጃ ሥርዓት አብሮ ሊዘረጋ እንደሚገባ አሳስበዋል። ከተሳታፊዎቹ ለተነሱት ለእነዚህ መዋቅራዊ ጥያቄዎችና ስጋቶች ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡት በአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ የአደረጃጀትና አሠራር ሪፎርም ዳይሬክተር አቶ ጌቱ ቱፋ ሪፎርሙ ካለፉት የለውጥ መሣሪያዎች በተለየ መንገድ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ እስከ ታችኛው እርከን ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ተናግረዋል ። ዳይሬክተሩ ስለ የብቃት ምዘና ፈተና ሲያስረዱ አዲሱ ምዘና ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እና በገለልተኛ ተቋም የሚመራ በመሆኑ ከሰው ጣልቃ ገብነት ነፃ መሆኑን ገልጸዋል። ሠራተኛው ፈተናውን ኦንላይን እንደጨረሰ ውጤቱን እዚያው ማወቅ የሚችልበት አሠራር በመዘርጋቱ፣ አድልዎ ወይም ያለአግባብ መጠቀም የሚደረግበት ዕድል እንደሌለ አብራርተዋል። በተመሳሳይ ሁኔታ በተግረዕድ ክላስተር በተካሄደው ውይይት የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ አማካሪ አቶ ዩሐንስ ምትኩን ጨምሮ የአዲስ አበባ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዳይሬክተሮች የተገኙ ሲሆን ለዘርፉ አመራርና ሰራተኛ ግልፅነት መፍጠር መቻሉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ለዘርፉ አመራርና ሰራተኛ ግንዛቤ የመፍጠር ስራው በቀጣይም በተለያዩ ክላስተሮች ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። ታዲያ በእርስዎ አስተያየት፣ ይህ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኦንላይን ፈተና እና አዲሱ አገራዊ ሪፎርም በሠራተኛው የሥራ ተነሳሽነት ላይ ምን ዓይነት ዘላቂ ለውጥ ያመጣል ብለው ያስባሉ? የራስዎን ምልከታ በኮሜንት መስጫው ላይ ያጋሩን! <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
503
4
OPEN CALL: Free Digital Marketing and E-Commerce Training Program Powered by FCA (Finn Church Aid) Are you an unemployed graduate from a university, college, or TVET institution ready to kickstart your career in digital marketing? This is your opportunity. About the Program This 3-month program includes: • 2 months of hands-on training (theory and practical) • 1 month internship and possible job linkage opportunities What You will Gain • Practical and theoretical skills in digital marketing and E-Commerce • Soft skills training • Real-world experience to boost your employability • Mentorship and networking opportunities Schedule & Commitment • Duration: 3 months • 2 days per week | 9:00 AM – 5:00 PM • Location: FCA Creators Hub at Teferi Mekonnen Polytechnic College, Addis Ababa Who Can Apply • Unemployed graduates (university, college, or TVET) • Ages 18–34 • Refugees • People with disabilities How to Apply Apply here: https://forms.gle/mkqrc3TTg2fVatuR7 Deadline: July 19, 2026 Spots are limited. Apply now!
396
5
ነጻ የዲጂታል ማርኬቲንግ እና የኢ-ኮሜርስ ሥልጠና ፕሮግራም በኤፍ.ሲ.ኤ (FCA) የቀረበ ከዩኒቨርሲቲ፣ ከኮሌጅ ወይም ከቴክኒክና ሙያ (TVET) ተቋማት የተመረቁ እና በዲጂታል ማርኬቲንግ ሙያ ሥራ ለመጀመር የተዘጋጁ ሥራ አጥ ተመራቂ ነዎት? ይህ ለእርስዎ የተዘጋጀ ዕድል ነው። ስለ ፕሮግራሙ  ይህ የ3 ወር ፕሮግራም የሚከተሉትን ያካትታል፦ የ2 ወር የተግባር ሥልጠና (ንድፈ ሃሳብ እና ተግባራዊ) የ1 ወር የኢንተርንሺፕ እና የሥራ ትስስር ዕድሎች የሚያገኙት ጥቅም በዲጂታል ማርኬቲንግ እና በኢ-ኮሜርስ ዘርፍ ተግባራዊ እና ቲዮሪቲካል ክህሎቶች የልል ክህሎቶች (Soft skills) ሥልጠና የሥራ ዕድልን ለማሳደግ የሚረዳ እውነተኛ ልምድ የአማካሪነት እና የኔትወርክ ግንባታ ዕድሎች የሥልጠና መርሃ ግብር እና ግዴታ የቆይታ ጊዜ፦ 3 ወራት በሳምንት 2 ቀናት | ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ማታ 11፡00 ቦታ፦ አዲስ አበባ፣ ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሚገኘው የኤፍ.ሲ.ኤ ፈጠራ ማዕከል (FCA Creators Hub) ማን ማመልከት ይችላል? ሥራ አጥ ተመራቂዎች (ዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም ቴክኒክና ሙያ) ዕድሜያቸው ከ18–34 የሆኑ ስደተኞች አካል ጉዳተኞች እንዴት ማመልከት ይቻላል? በዚህ ሊንክ ያመልክቱ፡ https://forms.gle/mkqrc3TTg2fVatuR7 የመጨረሻ ቀን፡ ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም የሥልጠና ቦታዎች ውስን ስለሆኑ አሁኑኑ ያመልክቱ!
295
6
Sin texto...
258
7
ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 30/2018 ዓ.ም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት፥ በበጀት ዓመቱ በተከናወኑ የተቀናጁ ሥራዎች በአጠቃላይ ከ5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን አስታውቀዋል። የሥራ ዕድል ስምሪት፡- • በሀገር ውስጥ፦ 4.9 ሚሊዮን ዜጎች • በውጭ ሀገር፦ 600 ሺህ ዜጎች • በሪሞት ጆብ (የርቀት ሥራ)፦ 40 ሺህ ዜጎች ሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን ዋና ዋና የሥራ ዕድል የተፈጠረባቸው ዘርፎች፦ • ግብርና፦ 2 ሚሊዮን የሥራ ዕድል • አገልግሎት፦ 1.8 ሚሊዮን የሥራ ዕድል • ኢንዱስትሪ፦ 900 ሺህ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ የ13 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ደግሞ የ27 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ማብራራታቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስፍሯል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
317
8
Sin texto...
256
9
+3
Sin texto...
249
10
የ2018 በጀት ዓመት የመጨረሻው ሳምንታዊ የወርቃማ ሰኞ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ። ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሥራና ከህሎት ቢሮ  የ2018 በጀት ዓመት የመጨረሻው ሳምንታዊው የወርቃማ ሰኞ  ማለዳ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሂዷል። በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ባለሙያ የሆኑት አቶ አሸናፊ ደበላ በኢንኩቤሽን ዙሪያ ገለፃ አድረዋል። ሳምንታዊው የሰኞ ማለዳ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር  በአመራሩና ሰራተኛው መካከል የልምድ ልውውጥ እና አብሮነትን በማጠናከር ዕውቀቶችን በማጋራት ለተቋማዊ ዕቅድ ስኬት ሚና እየተወጣ ይገኛል ያሉት ደግሞ የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ አበራ ናቸው። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
257
11
የሰላም ጥሪ ለትግራይ ‎ ‎በመጀመሪያ ደረጃ የሚያስፈልገን ሰላም፣ ትብብር እና አብሮ መስራት ነው። በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት ቢኖሩም፤ ጦርነት አውዳሚና ትርፍ የለሽ በመሆኑ እምቢ ብለናል። አሁንም ቢሆን ለሰላም፣ ለንግግርና ለውይይት በራችን ምንጊዜም ክፍት ነው። የራሳችንን ጥቅም መስዋዕት አድርገንና ተጎድተን እንኳ በትግራይ ዘላቂ ሰላም የሚመጣ ከሆነ ዋነኛ ፍላጎታችን እርሱ ብቻ ነው። እርስ በርስ መጠላለፍና መውደቅ ማንንም አይጠቅምም። ‎ይሁን እንጂ ለትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚመጣው የሕወሓት አመራሮች በወጣቶቻቸው ላይ እምነት ጥለው ለተተኪው ትውልድ ዕድል መስጠት ሲችሉ ብቻ ነው። የመደመር መንግሥት ዋነኛ መሻትና ግብ በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ላይ የሚታየው ልማትና ዕድገት በትግራይም ተደራሽ ሆኖ ማየት ነው። ‎ ‎#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
331
12
Sin texto...
328
13
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በተመለከተ፦ ‎ ‎ጠላቶቻችን ‘3መ’ን መርህ አድርገው ይከተላሉ፤ አንደኛው ‘መ’ መካድ ነው፤ ኢትዮጵያ ድልብ ሀብት ያላት መሆኗን፣ አልገዛም ያለ ህዝብ ያላት መሆኗን፣ ኢትዮጵያን ማንበረከክ ቀላል አለመሆኑን ቢያውቁም ግን ይክዳሉ። ሁለተኛው ‘መ’ መርሳት ነው፤ ስልታዊ ጥልቀት ያላት ሀገር መሆኗን፣ የወጣት ሀገር መሆኗንና ከከፋም እራሱንና ሀገሩን መከላከል እንደሚችል እንዲሁም የሀገሪቷ አቀማመጥም ሆነ ተቋማዊ ልምምድ ቀላል አለመሆኑን መርሳት፤ ስለእኛ ሲያስቡ እምቢ ባይነታችንን ይዘነጋሉ። ሶስተኛው ምኞት ነው፤ ያለፈበት ስልት እስረኛ የመሆን ምኞት፤ ሀገር ውስጥ ያሉ ጽንፈኞች ከውጪ ጠላቶች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን አሸንፋለው ብሎ መመኘት። እውነታው ግን ማንም ቢመጣ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ ቅንጣት ታክል ስጋት የለብንም፤ ያንንም ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅም እየገነባን ነው! ‎ ‎#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
339
14
Sin texto...
342
15
የትግራይን አሁናዊ ሁኔታ በሚመለከት፦ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በርካታ ጥቅሞችን ያስገኘ ቢሆንም፣ ለምን ተስማማችሁ በሚል ያኮረፉ በርካታ ኃይሎች ተፈጥረዋል። ከሕወሓት ባሻገር፤ በትግራይ ላይ ጥፋት ሊቀጥል ይገባ ነበር ብለው የሚያስቡ አካላት በማኩረፍ ከእኛ የራቁ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ እርስ በእርስ ለመተባበር የሞከሩበት ሁኔታ አለ። አሁን ላይ በትግራይ ባሉ ኃይሎች በየቀኑ አዳዲስ ግጭቶችንና ጦርነትን ሊቀሰቅሱ የሚችሉ ትንኮሳዎች እየተፈጸሙ ይገኛሉ። ከሁሉ በላይ የሚያሳዝነውና የከፋው ጉዳይ ግን በአሁኑ ወቅት በርካታ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍሰው በሱዳን እየተካሄደ ላለው ጦርነት እንዲሰለፉ መደረጉ ነው። እነዚህ ወጣቶች በማያውቁትና በማይመለከታቸው ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ሕይወታቸውን እያጡ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሳይበቃ፣ ጉዳዩ ወደ ሱዳንም ተሻግሯል። በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ የችግሩ ፈጣሪ ሳይሆን፣ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ነው። የትግራይን ሕዝብ ይበልጥ የጎዳውና ጉዳቱን ያባባሰው የማይታይ የውስጥ ቁስል መኖሩ ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ የውስጥ ቁስል ደግሞ በቀላሉ የማይሽር ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ዛሬ በትግራይ ውስጥ ከሚኖረው ይልቅ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ እና በአዳማ በሰላም እየኖረና ያለምንም ስጋት ወጥቶ የሚገባው የትግራይ ተወላጅ ቁጥር ይበልጣል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
365
16
Sin texto...
271
17
ኢንዱስትሪን በሚመለከት፦ የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እያሳየ ይገኛል። አጠቃላይ የማኑፋክቸሪንግ አቅም ከነበረበት 47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ እንዲል ሰፊ ጥናቶች እና የድጋፍ ስራዎች ተከናውነዋል። ይህ እድገት ከነባሮቹ የኮምቦልቻ፣ የመቐለ እና የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተጨማሪ አስር አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ከ80 በመቶ በላይ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን መሳብ ተችሏል። በተጨማሪም የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት የመተካት ስትራቴጂ ተግባራዊ ተደርጓል። በዚህም ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ብርጭቆ እና ሴራሚክስን የመሳሰሉ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ብቻ ወደ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ መቆጠብ ተችሏል። ዘርፉ እያስመዘገበ ባለው ፈጣን እድገትም በማዕድን ዘርፍ 24 በመቶ፣ በማኑፋክቸሪንግ 20.3 በመቶ እና በኢነርጂ ዘርፍ ደግሞ 23 በመቶ ጭማሪ ታይቷል። ለወደፊቱም ይህን ስኬት ዘላቂ ለማድረግ ትኩረት የተደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ብቻ የ12.7 በመቶ እድገት እና ከኢንዱስትሪ ምርቶች ኤክስፖርት የ1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
274
18
Sin texto...
238
19
ግብርና እና የምግብ ሉዓላዊነትን በተመለከተ፦ በዘንድሮው የምርት ዘመን 29 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1.3 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉ እንዲሁም ዘርፉ የ7.7 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡ፤ የኢትዮጵያ ግብርና እያሳየ ላለው መዋቅራዊ ሽግግር ግልጽ ማሳያ ነው። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተተገበረው የ‘ሌማት ትሩፋት’ መርሃ-ግብር አስደናቂ ውጤቶችን ያስመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም አቮካዶን ወደ ውጭ በመላክ ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃን መያዝ መቻሉ ለሀገሪቱ ተጨማሪ ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት አስደናቂ ድል እንዲመዘገብ አስችሏል። ከዚህም በላይ ለረጅም ጊዜ በከባድ ድርቅ ይጎዳ የነበረው የቦረና ቀጣና ዛሬ በሰፊ የስንዴ ልማት ተሸፍኖ ማየት መቻሉ የስትራቴጂያዊ ግብርና ስራችንን ስኬታማነት ያረጋግጣል። ምንም እንኳ የዓለም አቀፍ ጫናዎች ቢበዙም፣ የማዳበሪያ እና የነዳጅ ዋጋ ቢንርም፣ በቁርጠኝነትና በጠንካራ ስራ በምግብ ራሳችንን ለመቻልና በአፍሪካ ላይ የተለጠፈውን የረሃብ ታሪክ ለመቀየር በተግባር እየሰራን እንገኛለን፤ ምክንያቱም ምርጫችን ለምኖ መኖር ሳይሆን ሰርቶ ማደር ነው! #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
250
20
Sin texto...
250