es
Feedback
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

Ir al canal en Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ +251118124566 0900834565

Mostrar más
2 827
Suscriptores
+124 horas
+87 días
-430 días
Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+43
en 1 canales
mayo '26
+104
en 3 canales
Get PRO
abril '26
+118
en 3 canales
Get PRO
marzo '26
+226
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+87
en 2 canales
Get PRO
enero '26
+77
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+104
en 1 canales
Get PRO
noviembre '25
+602
en 5 canales
Get PRO
octubre '25
+196
en 2 canales
Get PRO
septiembre '25
+99
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+104
en 2 canales
Get PRO
julio '25
+114
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+103
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+61
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+65
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+95
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+130
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+41
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+55
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+32
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+28
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+15
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+13
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+7
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+16
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+16
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+106
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+10
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+12
en 1 canales
Get PRO
enero '24
+13
en 0 canales
Get PRO
diciembre '23
+22
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+46
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+16
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+12
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+15
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+18
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+16
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+9
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+15
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+21
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+11
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+19
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+23
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+46
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+10
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+43
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+44
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+35
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+35
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+28
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+36
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+113
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+12
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+14
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+27
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+28
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+85
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+64
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+80
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+59
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+688
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
16 junio+1
15 junio+3
14 junio+3
13 junio+1
12 junio+4
11 junio+7
10 junio+1
09 junio+3
08 junio0
07 junio+1
06 junio+4
05 junio+3
04 junio+5
03 junio+3
02 junio+3
01 junio+1
Publicaciones del Canal
2
በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት 70ሺ ለሚሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ እድል እንደሚፈጠር ተገለጸ፡፡ 🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣዮቹ ዘጠና ቀናት  በዋናነት ያለፈውን ዓመት አፈጻጸም በማጠናከርና በዘላቂነት ላይ የተመሠረተ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል። በዚህም መሠረት 175,000 አዳዲስ አማራጭ የሥራ ዕድሎችን በጥናት የመለየት፣ 70,000 የከተማ ነዋሪዎችን በአዳዲስ የስራ ዕድል  ተጠቃሚ የማድረግ፣ እንዲሁም በከተማ ግብርና፣ ኢንዱስትሪ እና አገልግሎት ዘርፎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የማስፋት ሥራዎች በቅድሚያ ይከናወናሉ። ለዚህ ስኬታማነትም 630,000 የከተማ ነዋሪዎችን በማሳተፍ የሚከናወኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎችና መድረኮች በወረዳ፣ በብሎክና በክፍለ ከተማ ደረጃ ተዘጋጅተው ወደ ተግባር ይገባሉ። የኢንተርፕራይዞችን አቅም በማሳደግ ረገድ አዳዲስ 2,000 ኢንተርፕራይዞችን በማደራጀት 14,000 አንቀሳቃሾችን ወደ ሥራ ለማስገባት ታቅዷል። የፋይናንስ አቅርቦትን በተመለከተም 660 ሚሊዮን ብር ብድር፣ የመሳሪያ ሊዝ አገልግሎት፣ እና ለ925 ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታ የማመቻቸት ሥራዎች በዋናነት ይከናወናሉ። በተጨማሪም ከተማዋን ሊቀይሩ በሚችሉ የአካባቢ ልማት ሥራዎች ላይ 208,118 ተጠቃሚዎችን በማሳተፍ የመንግስት ማቺንግ ፈንድ ክፍያዎችን መፈጸምና ተጠቃሚዎች የባንክ ሂሳብ እንዲኖራቸው የማድረግ የኑሮ ደረጃ ማሻሻያ ስራዎች በቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል። የክህሎት ሥልጠናን በተመለከተ የመንግስት ኮሌጆች 8,526 ተመራቂዎችን በብቃት አስመርቆ ለሥራ ገበያው የማስተሳሰር ሥራ ይከናወናል። የሥልጠና ጥራትን ለማረጋገጥም 2,773 አሰልጣኞችን በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና ማብቃት፣ 312 አመራሮችን በስልጠና ማብቃት እና 150 አዳዲስ አሰልጣኞችን በመቅጠርና በመመደብ የሰው ኃይል አቅምን የማጠናከር ስራ ይሰራል። ከኢንዱስትሪዎች ጋር ተጠናከረ ትስስር በመፍጠር 80% የሚሆኑ ተመራቂዎችን ከሥራ ጋር የማገናኘትና አዳዲስ መመሪያዎችን በማጽደቅ የአሰራር ማነቆዎችን የመፍታት ሥራዎች በዘላቂነት ይሰሩበታል። የከተማውን የኢንዱስትሪ ሰላም ለማስጠበቅ በ4,900 ድርጅቶች ላይ የሥራ ሁኔታዎች ቁጥጥር ይካሄዳል። የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ለ800 አመራሮችና ፈጻሚዎች በመስጠት፣ እንዲሁም 150 አዳዲስ የሠራተኛ ማህበራትን በማደራጀት የኢንዱስትሪ ሰላምን የማስጠበቅና የሠራተኛውን ጥቅማ ጥቅም የማስከበር ተግባራት በሦስቱ ወራት ውስጥ በልዩ ትኩረት ይፈጸማሉ። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
101
3
+2
Sin texto...
312
4
+9
Sin texto...
303
5
በበጀት ዓመቱ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች ተሸጋገሩ፤ በቦሌ ሰሚት በሳይንስና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ አዲስ የልማት ተአምር ያስመዘገበው የ“ፍሬህይወት ዘሮባቤል” ማህበር አርአያነት ተበሰረ 🇪🇹ሰኔ 9 ቀን 2018  አዲስ አበባ (የቢሮ ጋዜጠኛ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ  በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከጥቃቅን ጀምሮ እስከ መካከለኛ ደረጃ የሚገኙ ከ10 ሺህ በላይ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር ማድረጋቸውንና ይህም ከባለፉት ዓመታት እጅግ የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበበት ስኬት መሆኑን የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ አስታወቀ። ዘርፉ የኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና የአሠራር ሥርዓታቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማጥለቅ ታላቅ ሳይንሳዊ የምክክርና የተሞክሮ ማስፋፊያ መድረክ አካሂዷል። ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ፣ በከተማ ግብርና (በእንስሳት እርባታ) ዘርፍ እጅግ የላቀና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲስ ተስፋ የፈነጠቀውን የ«ፍሬህይወት ዘሮባቤል እና ጓደኞቻቸው የወተት ከብት እርባታ ህብረት ሽርክና ማህበር»ን ምርጥ ተሞክሮ ሳይንሳዊ በሆነ ዘዴ በተግባር እንዲሰፋ ተደርጓል።   የፖሊሲ ሪፎርም እና የኢንተርፕራይዞች ታሪካዊ ሽግግር የቢሮ የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ላይ የተሞክሮ ቅመራና የእድገት ደረጃ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኑሩ ሁሴን መሐመድ አሊ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ የመድረኩ ዋና ዓላማ የፖሊሲ ሪፎርሞችን ማውረድና የተመረጡ ምርጥ ተሞክሮዎችን በሳይንሳዊ መንገድ ወደ ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ማስፋት ነው። በበጀት ዓመቱ እስከ 11 ወራት ባለው ሪፖርት ብቻ 162 ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ሞዴል ኢንተርፕራይዞች መፍራት መቻላቸውን የጠቆሙት አቶ ኑሩ፣ መንግስት ለዚህ ስኬት በርካታ የፋይናንስ ድጋፍ፣ የመሳሪያ ሊዝ አቅርቦት፣ የምርታማነት ልኬት እገዛና የገበያ ትስስር ማመቻቸቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን ከመንግስት ድጋፍ ውስንነት፣ ከራሳቸው ከኢንተርፕራይዞቹ የግንዛቤ ክፍተት እና ሰነዶችን ለጥቅም ማግኛ ብቻ ከመጠቀም ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በጽናት መታገል እንደሚገባ አቶ ኑሩ አሳስበዋል። “የመድረኩ ዋና ዓላማ 'መስራት ይቻላል' የሚለውን እሳቤ በተግባር ማሳየት ነው” ያሉት ዳይሬክተሩ፣ በቀጣይም ይህ ምርጥ ተሞክሮ መሬት ላይ መውረዱን ባለሙያዎች በቅርብ ክትትል እንደሚያረጋግጡ በቁርጠኝነት ገልጸዋል።   ከቀውስ ወደ ስኬት ማማ፦ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር የልማት ተአምር በመድረኩ ማጠቃለያ ቀን 125 በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችና ባለሙያዎች በተገኙበት፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ሰሚት ኮንዶሚኒየም አካባቢ የሚገኘውና በጠንካራዋ ሴት ወይዘሮ ፍሬህይወት ዘሮባቤል የሚመራው ማህበር ተሞክሮ በቪዲዮና በፕረዘንቴሽን ቀርቦ ተተንትኗል። በአንድ ወቅት ፈታኝ በነበረው የስራ አጥነት እና የወደፊት ተስፋ ማጣት ውስጥ የነበረችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ዛሬ የወተት ከብት እርባታን ሙሉ በሙሉ በሳይንስና በጥናት ላይ የተመሰረተ ማራኪ የኢንቨስትመንት መስመር አድርጋዋለች።   የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂ ድል ማህበሩ ስራ ሲጀምር የወንዶች ጥጃዎች ብቻ መወለድ እና የዝርያ እጥረት ለከፍተኛ ኪሳራ ዳርጎት እንደነበር ያስታወሰችው ወይዘሮ ፍሬህይወት፣ ላሞችን ከውጭ ሀገር በአውሮፕላን ለማስገባት የሚጠይቀው ከፍተኛ ወጪ (ከ1,000 እስከ 6,000 የአሜሪካ ዶላር) ትልቅ ማነቆ ሆኖባቸው እንደነበር ገልጻለች። ይህንን ፈተና ለመስበር ማህበሩ የጥጃውን ጾታ አስቀድሞ መወሰን የሚያስችለውን የሳይንሳዊ ዘር (Sexed Semen) ቴክኖሎጂን በድፍረት ስራ ላይ አውሏል። ቀደም ሲል ያልተለየው መደበኛ ዘር እስከ 500 ብር ይሸጥ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ጾታው የተለየው ምርጥ ዘር ከ1,500 እስከ 2,000 ብር በሚደርስ ተመጣጣኝ ዋጋ ለመንግስት በመክፈል ማህበሩ በስፋት እየተጠቀመበት ይገኛል። በዚህም ተአምራዊ በሆነ መንገድ በአንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 13 ምርጥ የሴት ጊደር ጥጃዎችን ማፍራት ችለዋል።   "ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም" — አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ለእርባታ የማህበሩን የእድገት አቅጣጫና ስልታዊ የቢዝነስ ፕላን የሚያዘጋጀው ወጣቱ ባለሙያ ቢኒያም፣ ቅዱስ መጽሐፍ ላይ የሚገኘውን “ነፍስ እውቀት የሌለባት ትሆን ዘንድ መልካም አይደለም” የሚለውን የወርቃማ  ቃል በመጥቀስ ስራቸውን ሙሉ በሙሉ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ላይ መመስረታቸውን በስሜት አብራርቷል። ማህበሩ እንደ ጎግልና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ያሉ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጮችን ለመረጃ ምንጭነት ይጠቀማል። መረጃዎቹን በቀጥታ ከመተግበራቸው በፊት፣ በዘርፉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከታተሙ የሪሰርች ወረቀቶች (Research Papers) ጋር በማጣራት (Cross-check) ያረጋግጣሉ። ባለሙያው ቢኒያም እንደገለጸው፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እጅግ ሰፊ የሆኑ የኮርማዎችን ታሪክ በጥልቀት በማንበብና በዘርፉ የላቀ እውቀት ለሌላቸው ሰዎች ጭምር በቀላሉ በሚረዳ ቋንቋ (Layman's terms) በመተንተን ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ይህ የቴክኖሎጂ እገዛ ማህበሩ የሚከተሉትን ስራዎች በስኬት እንዲወጣ አስችሎታል፦ 1/የላሞቹን ወተት ምርት፣ ቁመትና የደረት ስፋት ለማሻሻል ትክክለኛውን የኮርማ ዝርያ መምረጥ። 2/ የተመጣጠነ የከብት ምግብ (Balanced feed) በሳይንሳዊ መንገድ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዓለም አቀፍ ሰነዶችን ማሰባሰብ።   የምርት ዘመን ዑደት እና የአሁኑ አቅም በውጭ ሀገራት ተሞክሮ አንዲት ላም ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የምትሰጠው ከተወለደችበት ጊዜ ጀምሮ ቢበዛ እስከ 5 ዓመት ብቻ መሆኑን የጠቀሰው ቢኒያም፣ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ግን በጥንቃቄ በመያዝ ላሞች እስከ 6 እና 7 ዓመታት ድረስ ምርት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል። በአሁኑ ወቅት ማህበሩ በአጠቃላይ ጥጃዎችን፣ ጊደሮችን እና የሚታለቡ ላሞችን ጨምሮ 35 የከብቶች ክምችት ላይ ደርሷል። ከእነዚህም ውስጥ 10 የሚሆኑት ላሞች በአሁኑ ወቅት እርጉዝ ሲሆኑ፣ በቅርቡ ወደ ምርት ምዕራፍ ሲገቡ የማህበሩን የወተት አቅርቦት በአስደናቂ ሁኔታ በእጥፍ ያሳድጉታል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ የፍሬህይወት ዘሮባቤል ማህበር ስኬት፣ ጠንክሮ ለሚሰራ እና ቴክኖሎጂን ለሚጠቀም ማናቸውም ኢንተርፕራይዝ “መስራት እና መለወጥ ይቻላል!” የሚል ትልቅ የተስፋ ስንቅና ህያው ምስክር ሆኖ አልፏል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
276
6
Sin texto...
415
7
#ዜና ሹመት አቶ ሙሉቀን ዮናስ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስትዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ   ሆነው ተሹመዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ  የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት  መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንልዎ ይመኛል። 🇪🇹ሰኔ 9/2018 ዓ.ም🇪🇹 <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
403
8
Sin texto...
778
9
‹‹የዓለም ባንክን ተሞክሮ በኢትየጵ መንግስት  በጀት መተግበራችን ከተረጂነት የተላቀቀ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው›› — አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ቀደም ሲል ከዓለም ባንክ ጋር ይተገበር የነበረውን አሰራር ወደ መንግስት አሰራር በመቀየር ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በከፍተኛ ስኬት እየገበረ ይገኛል። የቢሮው የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን እንደገለጹት ይህ ፕሮጀክት ዜጎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚያሸጋግር ቢሮው የያዘው ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ ነው። በዚህም መሠረት ቢሮው 145 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ በ20 ወረዳዎች የሚገኙ 3 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ቤት ውስጥ የተቀመጡ ሴቶች ወደ ገበያ እንዲገቡ ለማድረግም 60 በመቶ የሚሆነው የዕድል ኮታ ለሴቶች እንዲሰጥ ተደርጓል። ወጣቶቹ ወደ ድርጅቶች ከመሰማራታቸው በፊት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የ12 ቀን የሕይወት ክህሎት ሥልጠና እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ 3 ሺህ 751 ወጣቶች ሥልጠናውን አጠናቀዋል። ከዚያም በጥብቅ ምልመላ ያለፉ 3 ሺህ ወጣቶች በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽንና በአገልግሎት ዘርፍ ለሥራ ባህል ምቹ በሆኑ 758 ድርጅቶች ውስጥ የ6 ወር ተግባራዊ ልምምዳቸውን አድርገዋል። መንግስት በየወሩ የ3 ሺህ ብር የትራንስፖርት አበል የከፈለ ሲሆን በርካታ ድርጅቶችም የወጣቶቹን ትጋትና አፈፃፀም በማየት ከቢሮው ክፍያ በተጨማሪ ከ4 እስከ 5 ሺህ ብር ተጨማሪ የፓርት ታይም ክፍያና ጥቅማጥቅሞችን አበርክተውላቸዋል። የፕሮግራሙን አካታችነት ይበልጥ ያረጋገጠው ሌላው ስኬት በሀገሪቱ የመኖር ፈቃድ ያላቸውን 2 ሺህ የሚጠጉ የየመን፣ ሶማሊ፣ ሱዳንና ኤርትራ የውጭ ሀገር ስደተኞችን በ338 ድርጅቶች ውስጥ ማካተቱ ነው። ይህ አካሄድ የዓለም ባንክን ሞዳሊቲ መንግስት በራሱ አቅምና በጀት ወስዶ በመተግበር ያሳየው ትልቅ ስኬት መሆኑን አቶ ሰብሃዲን ጠቁመዋል። አሁን ላይ የልምምድ ጊዜያቸውን አጠናቀው ሰኔ 10 ሙሉ በሙሉ ከድርጅቶች የሚወጡትን ወጣቶች በቋሚነት ለመቅጠር ሰፊ ሥራ እየተሠራ ሲሆን ካለው ኮታ ውስጥ እስካሁን በቋሚነት ያልተሳሰሩ  ወጣቶች ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ የማስተሳሰር ሥራው እንደሚጠናቀቅ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። ይህ የብቃት የወጣቶች የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ወጣቶች የ6 ወር የሥራ ልምድ ማረጋገጫ ይዘው የተሻለ ተወዳዳሪና ከፍተኛ ክፍያ የሚያገኙበትን ዕድል የፈጠረ ሲሆን ሰልጣኞቹ አሁን ላይ ራሳቸውን ችለው ድርጅት ለመክፈት የሚያስችሉ የኢንተርፕረነርሺፕ ሐሳቦችን እያነሱ ይገኛል። ቢሮው ይህንን ስኬት መሠረት በማድረግ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም በየዓመቱ 3 ሺህ ወጣቶችን በማቀፍ፣ በአጠቃላይ በቀሪዎቹ 119 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 15 ሺህ ወጣቶችን የዚህ  ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለማድረግ የስትራቴጂክ ዕቅዱን አጽድቆ ወደ ተግባር መሸጋገሩን አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን አስታውቀዋል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
707
10
+3
Sin texto...
567
11
በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው እየተስተናገዱ ይገኛሉ። 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የባለጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ በቢሮው አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የተሳለጠ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። የባለጉዳይ ቀንን አስመልክቶ የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የመጡ ባለጉዳዮችን ባነጋገረው መሠረት፤ በቢሮው እየሰጠ ያለውን አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አድርጓል።  በዚህም አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው በአግባቡና በፈጣን ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል። በዕለቱ በቢሮው ተገኝተው አገልግሎት ያገኙ ልዩ ልዩ ተገልጋዮችም በተሰጣቸው መስተንግዶ መደሰታቸውንና ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከሰንሻይን ኮንስትራክሽን ድርጅት ሰራተኛ ለማዋዋል ወደ ቢሮው የመጡት አቶ ንዋይ ተፈራ በሰጡት አስተያየት ወደ ቢሮው እንደመጡ ከአንድ ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ፈጽመው ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። አቶ ንዋይ አክለውም «በቢሮው ውስጥ በጣም ቅን የሆኑ ባለሙያዎችን አግኝተናል። በዚህ መልክ የሚስተናገድ ከሆነ በየቀኑ እንኳን ብንመጣ ደስ ይለናል ማንም ሰው ሳይከፋ በአገልግሎቱ ተደስቶ ነው የሚሄደው» ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተመሳሳይ ከመስኮን ኮንስትራክሽን አገልግሎት ለመጠየቅ የመጡት ኢንጂነር ብሩክታይት ገብሬ በበኩላቸው ከቢሮው የበር መግቢያ ጀምሮ የተደረገላቸው አቀባበልና መስተንግዶ እጅግ የሰለጠነና በስርዓት የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። የቢሮው የውስጥ አቀማመጥ እንዲሁም በፋይናንስና በመዝገብ ቤት በኩል የነበረው የሥራ ፍሰት ቀልጣፋ መሆኑን ያነሱት ኢንጂነር ብሩክታይት ለአገልግሎት አሰጣጡ ይበልጥ መሻሻል የሚረዳ ገንቢ አስተያየታቸውንም አካፍለዋል። ኢንጂነሯ በአስተያየታቸው «መስተንግዶው በጣም ጥሩ ቢሆንም፤ ተገልጋዮች ዶክመንት ኮፒ ለማድረግ ከቢሮው ወጥተው ሩቅ መንገድ ለመጓዝ እየተገደዱ ነው። ስለዚህ ይህንን እንግልት ለማስቀረት በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ወይም በቅርበት የኮፒ አገልግሎት የሚሰጥበት ቢዝነስ ሴንተር ቢከፈት መልካም ነው» የሚል ጥቆማ ሰጥተዋል። ቢሮው የተገልጋዮችን እርካታ ይበልጥ ለማሳደግ መሰል የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተመላክቷል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
617
12
Sin texto...
622
13
የነጻ ግራፊክ ዲዛይን ስልጠና ጥሪ በፊን ቸርች ኤይድ (FCA) የተዘጋጀ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂ ነዎት? በግራፊክ ዲዛይን ሙያ ተግባራዊ ክህሎቶችን ለማግኘት ይህን ነጻ ስልጠና ይቀላቀሉ። በስልጠናው የሚማሩት፦ • የግራፊክ ዲዛይን መሰረታዊ እውቀቶች • ብራንዲንግ እና ሎጎ ዲዛይን • የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ዲዛይን • የዲዛይን ሶፍትዌሮች እና የፈጠራ መሳሪያዎች • የስራ ፖርትፎሊዮ ዝግጅት የስልጠና ዝርዝር፦ • ቆይታ፡ 6 ሳምንት • መርሃ ግብር፡ በሳምንት 2 ቀን (ከጠዋቱ 3:00 እስከ 11:00 ሰዓት) • ቦታ፡ FCA Creators Hub, ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ አዲስ አበባ ማመልከት የሚችሉ፦ • ስራ ፈላጊ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂዎች • ከ18–34 ዓመት ዕድሜ ያላቸው • ስደተኞች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ በተለይ ይበረታታሉ • ሙሉ የስልጠና ጊዜውን መከታተል የሚችሉ ያመልክቱ፡ https://forms.gle/7wfyjGeYT2Gx9dXs6 የማመልከቻ መጨረሻ ቀን፡ ሰኔ 10፣ 2018 ዓ.ም. (June 17, 2026) ⚠️ የተወሰነ ቦታ ስላለ በፍጥነት ያመልክቱ!
755
14
Sin texto...
657
15
+2
Sin texto...
691
16
+9
Sin texto...
783
17
የወርቃማ ሰኞ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ። 🇪🇹ሰኔ 2/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ  አበባ  ሥራና ክህሎት ቢሮ  ሳምንታዊውን  የወርቃማ ሰኞ የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር  ትኩረቱን ራስን መስራት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ አድርጎ  አካሂዷል። በመድረኩ  የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ  ወ/ሮ  ዘለቃሽ ባህሩን ጨምሮ ዳይሬክተሮች እና የቢሮው ጠቅላላ ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡ በመድረኩ ሀሳባቸውን ያካፈሉት በማህበረሰብ ልማት በማተኮር ሰፋፊ ስራዎችን በመስራት የሚታወቁት በመቐለ ዩኒቨርስቲ እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፓርት ታይም መምህር ፣የከፍታ ትምህርት ድርጅት ስራ አስፈፃሚ ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጣ "የመጋቢ አዕምሮ" መደብ አዘጋጅ ፣መናኸሪያ ሬዲዮ አዘጋጅና አቅራቢ የሆኑት አቶ ዘላለም ይትባረክ ናቸው። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1 👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https://t.me/AABOLS 👉YouTube https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf 👉website https://aabols.gov.et 👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ https://complain.aabols.gov.et 👉ለነፃ የስልክ ጥሪ 6524
559
18
+6
Sin texto...
2 019
19
ከአፍሪካ ጋር የሚወዳደረው የኢትዮጵያ አውቶሞቲቭ ማዕከል፡ የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ስኬት! 🇪🇹2018 ዓ.ም ግንቦት 28 አዲስ አበባ🇪🇹 ብዙዎቻችን "ዘመናዊ የኤሌክትሪክ እና የሃይብሪድ መኪናዎች ሲበላሹ በሀገራችን እነማን ይጠግኗቸዋል?" ብለን እንጠይቃለን። መልሱ እጅግ አስደሳች ነው! የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአፍሪካ ጋር ሊወዳደሩ የሚችሉ ዘመኑን የዋጁ ማሰልጠኛዎችን በመታጠቅ የነገዋን ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች እያፈራ ይገኛል። በኮሌጁ የአውቶሞቲቭ መምህር የሆኑት ኢንስትራክተር ተሻለ አዳነ እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል በኤሌክትሪካል እና ሜካኒካል ዘርፍ የነበሩ የቁሳቁስ እጥረቶች ሙሉ በሙሉ አሁን  ተቀርፈዋል። አሁን ላይ ተቋሙ  በአዉቶሞቲቭ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 (Level\ 1\ to\ 5) በቀን 500 እና በማታዉ መርሃ ግብር 500 ሰልጣኞችን  ተቀብለዉ  ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ይህ ተቋም በአሁኑ ወቅት የዓለም ገበያን የመራቸውን የኤሌክትሪክ መኪና ቴክኖሎጂ በሚከተሉት 3 ዋና መሰረቶች ላይ ጥሎታል፦ •  💻 ዘመናዊ የሲሙሌሽን ሲስተም፦ ሰልጣኞች እውነተኛ መኪና ላይ ከመቀመጣቸው በፊት የፍሬን (Brake)፣ የኤቢኤስ (ABS)፣ የስቲሪንግ እና የተሽከርካሪ መረጋጋትን (Stability\ Control) በኮምፒውተር ሲሙሌሽን ፈትነው እንዲያዩ ያስችላል። •  🔋 የሃይብሪድ እና ቻርጅ ስቴሽኖች፦ በነዳጅና በኤሌክትሪክ በጥምረት የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን (Hybrid\ Cars) ማስተማሪያ መሳሪያዎችና የቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ ተሟልተዋል። •  🌊 እንደ ጎርፍ የሚጎርፍ ፍላጎት፦ በአሁኑ ወቅት በመደበኛ (Regular) 500 እና በማታ (Extension) 500 በአጠቃላይ 1,000 ገደማ ሰልጣኞች እያሰለጠነ ይገኛል። "ለአሰልጣኞች የሚሰጠውን ስልጠና አጠናቀናል፤ አሁን ወደ ገበያው በመግባት በኢንዱስትሪው ውስጥ የክህሎት ክፍተት (Skill\ Gap) ላለባቸው ተቋማት ስልጠና ለመስጠት በሙሉ ዝግጅት ላይ ነን" — ኢንስትራክተር ተሻለ አዳነ 💬 ለእርስዎ፦ የሀገራችን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት እንዲህ ዘመናዊ ሲሙሌተሮችን መታጠቃቸው የኢንዱስትሪውን የሰው ኃይል እጥረት በምን ያህል ፍጥነት ይቀርፈዋል ይላሉ? እንዲሁም ወደፊት እውነተኛ የኤሌክትሪክ መኪናዎች (Full\ EV) ቀጥታ እንዲገቡ የሚሰጠውን ሀሳብ እንዴት ያዩታል? የራስዎን እይታ በኮሜንት ያጋሩን! <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
1 561
20
+4
Sin texto...
1 641