የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau
Открыть в Telegram
3 087
Подписчики
+624 часа
+157 дней
+8030 дней
Архив постов
አዲስ ልሳን ጋዜጣ በመስከረም 1፤2019 ዕትሟ።
የሥራ ዕድል ፈጠራ መረጃ አያያዝ ስርአቱን ከማንዋል ወደ ዲጂታል የቀየረው የተቀናጀ የሥራ ዕድል ፈጠራ አስተዳደር ሲስተም።ሰፊ ትንታኔ ይዛ ወጥታለች ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ።
ከተጠሪ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ጋር በመስቀል ደመራ እና በኢሬቻ ክብረ በዓላት ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
🌼 መስከረም 4፤ ቀን 2019 ዓ.ም 🌼
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ከተጠሪ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ጋር በመስቀል ደመራ እና በኢሬቻ ክብረ በዓላት ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በውይይቱ በመስከረም ወር የሚከበሩ የመስቀል ደመራ እና የኢሬቼ ክብረ በዓላት ኃይማኖታዊና ባህላዊ እሴቶቻቸውን ጠብቀው እንዲከበሩ መደረግ ስለሚገባቸው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
የመስቀል ደመራ እና የኢሬቼ ክብረ በዓላት በባህሪያቸው የአደባባይ ላይ በዓላት በመሆናቸውና ሰፊ ህዝብ የሚታደምባቸው በመሆኑ ፍፁም ሰላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቁ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባ ተጠቁሞል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - መስከረም 2፣ 2019ዓ.ም
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የነገው ቀን
"ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር
ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው።
ንግድና አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ መረጃዎችን ተደራሽ ያደርጋል፣ ዘርፎችንም ያዘምናል! የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ ወደ 7 ሚሊዮን ግባችን እያመራ ሲሆን የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን አረጋግጧል።
በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን ደግሞ የማንቆጣጠራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጥገኝነት አላቆ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆም አዲሷ ኢትዮጵያ በታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን በኩራት ያበስራል!"
