ch
Feedback
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ-Addis Ababa Labor and Skill Bureau

前往频道在 Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄዎ +251118124566 0900834565

显示更多
2 824
订阅者
-224 小时
+47
+130
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+36
在0个频道中
五月 '26
+104
在3个频道中
Get PRO
四月 '26
+118
在3个频道中
Get PRO
三月 '26
+226
在3个频道中
Get PRO
二月 '26
+87
在2个频道中
Get PRO
一月 '26
+77
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+104
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+602
在5个频道中
Get PRO
十月 '25
+196
在2个频道中
Get PRO
九月 '25
+99
在1个频道中
Get PRO
八月 '25
+104
在2个频道中
Get PRO
七月 '25
+114
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+103
在2个频道中
Get PRO
五月 '25
+61
在2个频道中
Get PRO
四月 '25
+65
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+95
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+130
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+41
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+55
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+32
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+28
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+13
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+7
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+16
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+16
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+106
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+10
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+12
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+13
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+22
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+16
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+12
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+15
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+18
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+16
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+9
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+15
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+21
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+11
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+19
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+23
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+46
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+10
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+43
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+44
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+35
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+35
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+28
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+36
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+113
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+12
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+14
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+27
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+28
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+85
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+64
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+80
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+59
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+688
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
13 六月+1
12 六月+4
11 六月+7
10 六月+1
09 六月+3
08 六月0
07 六月+1
06 六月+4
05 六月+3
04 六月+5
03 六月+3
02 六月+3
01 六月+1
频道帖子
2
‹‹የዓለም ባንክን ተሞክሮ በኢትየጵ መንግስት  በጀት መተግበራችን ከተረጂነት የተላቀቀ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው›› — አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ቀደም ሲል ከዓለም ባንክ ጋር ይተገበር የነበረውን አሰራር ወደ መንግስት አሰራር በመቀየር ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በከፍተኛ ስኬት እየገበረ ይገኛል። የቢሮው የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ የሥራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን እንደገለጹት ይህ ፕሮጀክት ዜጎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት የሚያሸጋግር ቢሮው የያዘው ዋነኛ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ ነው። በዚህም መሠረት ቢሮው 145 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ በ20 ወረዳዎች የሚገኙ 3 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ቤት ውስጥ የተቀመጡ ሴቶች ወደ ገበያ እንዲገቡ ለማድረግም 60 በመቶ የሚሆነው የዕድል ኮታ ለሴቶች እንዲሰጥ ተደርጓል። ወጣቶቹ ወደ ድርጅቶች ከመሰማራታቸው በፊት በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የ12 ቀን የሕይወት ክህሎት ሥልጠና እንዲወስዱ የተደረገ ሲሆን በዚህም የመጀመሪያ ምዕራፍ 3 ሺህ 751 ወጣቶች ሥልጠናውን አጠናቀዋል። ከዚያም በጥብቅ ምልመላ ያለፉ 3 ሺህ ወጣቶች በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽንና በአገልግሎት ዘርፍ ለሥራ ባህል ምቹ በሆኑ 758 ድርጅቶች ውስጥ የ6 ወር ተግባራዊ ልምምዳቸውን አድርገዋል። መንግስት በየወሩ የ3 ሺህ ብር የትራንስፖርት አበል የከፈለ ሲሆን በርካታ ድርጅቶችም የወጣቶቹን ትጋትና አፈፃፀም በማየት ከቢሮው ክፍያ በተጨማሪ ከ4 እስከ 5 ሺህ ብር ተጨማሪ የፓርት ታይም ክፍያና ጥቅማጥቅሞችን አበርክተውላቸዋል። የፕሮግራሙን አካታችነት ይበልጥ ያረጋገጠው ሌላው ስኬት በሀገሪቱ የመኖር ፈቃድ ያላቸውን 2 ሺህ የሚጠጉ የየመን፣ ሶማሊ፣ ሱዳንና ኤርትራ የውጭ ሀገር ስደተኞችን በ338 ድርጅቶች ውስጥ ማካተቱ ነው። ይህ አካሄድ የዓለም ባንክን ሞዳሊቲ መንግስት በራሱ አቅምና በጀት ወስዶ በመተግበር ያሳየው ትልቅ ስኬት መሆኑን አቶ ሰብሃዲን ጠቁመዋል። አሁን ላይ የልምምድ ጊዜያቸውን አጠናቀው ሰኔ 10 ሙሉ በሙሉ ከድርጅቶች የሚወጡትን ወጣቶች በቋሚነት ለመቅጠር ሰፊ ሥራ እየተሠራ ሲሆን ካለው ኮታ ውስጥ እስካሁን በቋሚነት ያልተሳሰሩ  ወጣቶች ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ የማስተሳሰር ሥራው እንደሚጠናቀቅ ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። ይህ የብቃት የወጣቶች የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ወጣቶች የ6 ወር የሥራ ልምድ ማረጋገጫ ይዘው የተሻለ ተወዳዳሪና ከፍተኛ ክፍያ የሚያገኙበትን ዕድል የፈጠረ ሲሆን ሰልጣኞቹ አሁን ላይ ራሳቸውን ችለው ድርጅት ለመክፈት የሚያስችሉ የኢንተርፕረነርሺፕ ሐሳቦችን እያነሱ ይገኛል። ቢሮው ይህንን ስኬት መሠረት በማድረግ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም በየዓመቱ 3 ሺህ ወጣቶችን በማቀፍ፣ በአጠቃላይ በቀሪዎቹ 119 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 15 ሺህ ወጣቶችን የዚህ  ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለማድረግ የስትራቴጂክ ዕቅዱን አጽድቆ ወደ ተግባር መሸጋገሩን አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን አስታውቀዋል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
373
3
+3
没有文字...
438
4
በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው እየተስተናገዱ ይገኛሉ። 🇪🇹 ሰኔ  5/2018 ዓ.ም 🇪🇹 የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የባለጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ በቢሮው አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የተሳለጠ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። የባለጉዳይ ቀንን አስመልክቶ የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በቢሮው አገልግሎት ፈልገው የመጡ ባለጉዳዮችን ባነጋገረው መሠረት፤ በቢሮው እየሰጠ ያለውን አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አድርጓል።  በዚህም አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ የውስጥና የውጭ ተገልጋዮች የጉዳዮቻቸውን ፍሰት ተከትለው በአግባቡና በፈጣን ሁኔታ እየተስተናገዱ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል። በዕለቱ በቢሮው ተገኝተው አገልግሎት ያገኙ ልዩ ልዩ ተገልጋዮችም በተሰጣቸው መስተንግዶ መደሰታቸውንና ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከሰንሻይን ኮንስትራክሽን ድርጅት ሰራተኛ ለማዋዋል ወደ ቢሮው የመጡት አቶ ንዋይ ተፈራ በሰጡት አስተያየት ወደ ቢሮው እንደመጡ ከአንድ ሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ፈጽመው ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። አቶ ንዋይ አክለውም «በቢሮው ውስጥ በጣም ቅን የሆኑ ባለሙያዎችን አግኝተናል። በዚህ መልክ የሚስተናገድ ከሆነ በየቀኑ እንኳን ብንመጣ ደስ ይለናል ማንም ሰው ሳይከፋ በአገልግሎቱ ተደስቶ ነው የሚሄደው» ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተመሳሳይ ከመስኮን ኮንስትራክሽን አገልግሎት ለመጠየቅ የመጡት ኢንጂነር ብሩክታይት ገብሬ በበኩላቸው ከቢሮው የበር መግቢያ ጀምሮ የተደረገላቸው አቀባበልና መስተንግዶ እጅግ የሰለጠነና በስርዓት የሚመራ መሆኑን ገልጸዋል። የቢሮው የውስጥ አቀማመጥ እንዲሁም በፋይናንስና በመዝገብ ቤት በኩል የነበረው የሥራ ፍሰት ቀልጣፋ መሆኑን ያነሱት ኢንጂነር ብሩክታይት ለአገልግሎት አሰጣጡ ይበልጥ መሻሻል የሚረዳ ገንቢ አስተያየታቸውንም አካፍለዋል። ኢንጂነሯ በአስተያየታቸው «መስተንግዶው በጣም ጥሩ ቢሆንም፤ ተገልጋዮች ዶክመንት ኮፒ ለማድረግ ከቢሮው ወጥተው ሩቅ መንገድ ለመጓዝ እየተገደዱ ነው። ስለዚህ ይህንን እንግልት ለማስቀረት በቢሮው ቅጥር ግቢ ውስጥ ወይም በቅርበት የኮፒ አገልግሎት የሚሰጥበት ቢዝነስ ሴንተር ቢከፈት መልካም ነው» የሚል ጥቆማ ሰጥተዋል። ቢሮው የተገልጋዮችን እርካታ ይበልጥ ለማሳደግ መሰል የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተመላክቷል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
429
5
没有文字...
505
6
የነጻ ግራፊክ ዲዛይን ስልጠና ጥሪ በፊን ቸርች ኤይድ (FCA) የተዘጋጀ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂ ነዎት? በግራፊክ ዲዛይን ሙያ ተግባራዊ ክህሎቶችን ለማግኘት ይህን ነጻ ስልጠና ይቀላቀሉ። በስልጠናው የሚማሩት፦ • የግራፊክ ዲዛይን መሰረታዊ እውቀቶች • ብራንዲንግ እና ሎጎ ዲዛይን • የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ዲዛይን • የዲዛይን ሶፍትዌሮች እና የፈጠራ መሳሪያዎች • የስራ ፖርትፎሊዮ ዝግጅት የስልጠና ዝርዝር፦ • ቆይታ፡ 6 ሳምንት • መርሃ ግብር፡ በሳምንት 2 ቀን (ከጠዋቱ 3:00 እስከ 11:00 ሰዓት) • ቦታ፡ FCA Creators Hub, ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ አዲስ አበባ ማመልከት የሚችሉ፦ • ስራ ፈላጊ የዩኒቨርሲቲ፣ ኮሌጅ ወይም TVET ተመራቂዎች • ከ18–34 ዓመት ዕድሜ ያላቸው • ስደተኞች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ በተለይ ይበረታታሉ • ሙሉ የስልጠና ጊዜውን መከታተል የሚችሉ ያመልክቱ፡ https://forms.gle/7wfyjGeYT2Gx9dXs6 የማመልከቻ መጨረሻ ቀን፡ ሰኔ 10፣ 2018 ዓ.ም. (June 17, 2026) ⚠️ የተወሰነ ቦታ ስላለ በፍጥነት ያመልክቱ!
637
7
没有文字...
584
8
+2
没有文字...
655
9
+9
没有文字...
719
10
የወርቃማ ሰኞ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ። 🇪🇹ሰኔ 2/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ  አበባ  ሥራና ክህሎት ቢሮ  ሳምንታዊውን  የወርቃማ ሰኞ የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር  ትኩረቱን ራስን መስራት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ አድርጎ  አካሂዷል። በመድረኩ  የአዲስ አበባ ከተማ ሥራና ክህሎት ቢሮ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ  ወ/ሮ  ዘለቃሽ ባህሩን ጨምሮ ዳይሬክተሮች እና የቢሮው ጠቅላላ ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡ በመድረኩ ሀሳባቸውን ያካፈሉት በማህበረሰብ ልማት በማተኮር ሰፋፊ ስራዎችን በመስራት የሚታወቁት በመቐለ ዩኒቨርስቲ እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፓርት ታይም መምህር ፣የከፍታ ትምህርት ድርጅት ስራ አስፈፃሚ ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጣ "የመጋቢ አዕምሮ" መደብ አዘጋጅ ፣መናኸሪያ ሬዲዮ አዘጋጅና አቅራቢ የሆኑት አቶ ዘላለም ይትባረክ ናቸው። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1 👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https://t.me/AABOLS 👉YouTube https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf 👉website https://aabols.gov.et 👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ https://complain.aabols.gov.et 👉ለነፃ የስልክ ጥሪ 6524
530
11
+6
没有文字...
1 887
12
ከአፍሪካ ጋር የሚወዳደረው የኢትዮጵያ አውቶሞቲቭ ማዕከል፡ የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ስኬት! 🇪🇹2018 ዓ.ም ግንቦት 28 አዲስ አበባ🇪🇹 ብዙዎቻችን "ዘመናዊ የኤሌክትሪክ እና የሃይብሪድ መኪናዎች ሲበላሹ በሀገራችን እነማን ይጠግኗቸዋል?" ብለን እንጠይቃለን። መልሱ እጅግ አስደሳች ነው! የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአፍሪካ ጋር ሊወዳደሩ የሚችሉ ዘመኑን የዋጁ ማሰልጠኛዎችን በመታጠቅ የነገዋን ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች እያፈራ ይገኛል። በኮሌጁ የአውቶሞቲቭ መምህር የሆኑት ኢንስትራክተር ተሻለ አዳነ እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል በኤሌክትሪካል እና ሜካኒካል ዘርፍ የነበሩ የቁሳቁስ እጥረቶች ሙሉ በሙሉ አሁን  ተቀርፈዋል። አሁን ላይ ተቋሙ  በአዉቶሞቲቭ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 (Level\ 1\ to\ 5) በቀን 500 እና በማታዉ መርሃ ግብር 500 ሰልጣኞችን  ተቀብለዉ  ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ይህ ተቋም በአሁኑ ወቅት የዓለም ገበያን የመራቸውን የኤሌክትሪክ መኪና ቴክኖሎጂ በሚከተሉት 3 ዋና መሰረቶች ላይ ጥሎታል፦ •  💻 ዘመናዊ የሲሙሌሽን ሲስተም፦ ሰልጣኞች እውነተኛ መኪና ላይ ከመቀመጣቸው በፊት የፍሬን (Brake)፣ የኤቢኤስ (ABS)፣ የስቲሪንግ እና የተሽከርካሪ መረጋጋትን (Stability\ Control) በኮምፒውተር ሲሙሌሽን ፈትነው እንዲያዩ ያስችላል። •  🔋 የሃይብሪድ እና ቻርጅ ስቴሽኖች፦ በነዳጅና በኤሌክትሪክ በጥምረት የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን (Hybrid\ Cars) ማስተማሪያ መሳሪያዎችና የቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ ተሟልተዋል። •  🌊 እንደ ጎርፍ የሚጎርፍ ፍላጎት፦ በአሁኑ ወቅት በመደበኛ (Regular) 500 እና በማታ (Extension) 500 በአጠቃላይ 1,000 ገደማ ሰልጣኞች እያሰለጠነ ይገኛል። "ለአሰልጣኞች የሚሰጠውን ስልጠና አጠናቀናል፤ አሁን ወደ ገበያው በመግባት በኢንዱስትሪው ውስጥ የክህሎት ክፍተት (Skill\ Gap) ላለባቸው ተቋማት ስልጠና ለመስጠት በሙሉ ዝግጅት ላይ ነን" — ኢንስትራክተር ተሻለ አዳነ 💬 ለእርስዎ፦ የሀገራችን የቴክኒክና ሙያ ተቋማት እንዲህ ዘመናዊ ሲሙሌተሮችን መታጠቃቸው የኢንዱስትሪውን የሰው ኃይል እጥረት በምን ያህል ፍጥነት ይቀርፈዋል ይላሉ? እንዲሁም ወደፊት እውነተኛ የኤሌክትሪክ መኪናዎች (Full\ EV) ቀጥታ እንዲገቡ የሚሰጠውን ሀሳብ እንዴት ያዩታል? የራስዎን እይታ በኮሜንት ያጋሩን! <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ  መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ  https://aabols.gov.et/qr.html
1 475
13
+4
没有文字...
1 564
14
+9
没有文字...
1 422
15
+9
没有文字...
1 042
16
"የዞኒንግ" ስትራቴጂ የመጣ ተቋማዊ ስኬት፣ የዲጂታላይዜሽን ምዕራፍ እና ዘመናዊው የማህበረሰብ ተጠቃሚነት በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 🇪🇹ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም 🇪🇹 ከ3,000 በላይ ሰልጣኞች፣ ዘመናዊ የ"ስማርት" ክፍሎች እና ለሰራተኞች የሚቀርብ የ40 ብር ወተት! የንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአዲሱ ስትራቴጂ እያስመዘገባቸው ያሉ አስደናቂ ተቋማዊ ስኬቶች የኮሌጁ የተቋማት ልማትና አስተዳደራዊ ዘርፍ ምክትል ዲን አቶ ጎሳይ አለሙ እና የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ወ/ሮ መስከረም አስፋው በሰጡት ልዩ መግለጫ፤ ኮሌጁ በአዲሱ የ"ዞኒንግ እና ዲፍረንሺየሽን" መመሪያ መሰረት 10 ዲፓርትመንቶችን አደራጅቶ ስራ ላይ ውሏል። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ 1,543 ነባር እና 1,528 አዳዲስ (በአጠቃላይ 3,071) ሰልጣኞችን በብቃት እያሰለጠነ ሲሆን፣ 761 የዘንድሮ ተመራቂዎችን ለሀገር አቀፍ የብቃት ምዘና ለማዘጋጀት ሰፊ የቲቶሪያልና የሞዴል ፈተናዎች ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል። - የላቁ ስኬቶች • 💻 ስማርት ክፍሎች እና አይሶ ሰርቲፊኬሽን (ISO)፦ ተቋሙ ከባህላዊ የጥቁር ሰሌዳ አጠቃቀም ሙሉ በሙሉ በመውጣት መማር ማስተማሩን ዲጂታላይዝ አድርጓል። በ"ስማርት ክፍል" (Smart\ Classroom) የተደራጁትና በካይዘን ፍልስፍና ስታንዳርዳቸውን የጠበቁት ወርክሾፖች ተቋሙን $ISO$ ሰርቲፋይድ ሊያደርጉት ችለዋል። • ♿️ አካቶ ትግበራ እና የ10 ሚሊየን ብር ማዕከል፦ የስልጠና አካባቢው ለአካል ጉዳተኞች እና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ዜጎች ምቹ የተደረገ ሲሆን፣ ከተለያዩ ድርጅቶች በተገኘ የ10 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማሽነሪዎች የተሟሉለትና በአካል ጉዳተኛ አሰልጣኝ የሚመራ የኢንኩቤሽን ማዕከል (Incubation\ Center) ተቋቁሟል። • 🤝 የተሳካ የኢንዱስትሪ ትስስርና የ226 ካምፓኒዎች ውል፦ ኮሌጁ በውል ከተፈራረማቸው 226 እና በቅንጅት ከሚሰሩ 171 (በአጠቃላይ 337) ኢንዱስትሪዎች ጋር በመሆን 1,556 ሰልጣኞችን በተግባር ስልጠና (Apprenticeship) ውጤታማ አድርጓል። እንደ በላይነህ ክንዴ (በኢ-ቪክል/E-vehicle ዘርፍ) ያሉ ተቋማት ሰልጣኞችን ገና ሳይመረቁ በቋሚነት እየቀጠሯቸው ሲሆን፣ ኮሌጁም ሰልጣኞች ስራና ትምህርታቸውን ጎን ለጎን እንዲያስኬዱ የትምህርት ፕሮግራሙን ወደ ማታ ፕሮግራም ቀይሮላቸዋል። • 💰 የውስጥ ገቢና አረንጓዴ ቲቪት (Green\ TVET)፦ ከከተማው ስፖርት ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ የለማው የስፖርት ሜዳ ለኮሌጁ በወር 300 ሺህ ብር የውስጥ ገቢ እያስገኘ ሲሆን፣ ከኤንጂኦዎች ጋር በተደረገ ትብብር የ92 ሚሊየን ብር የማቴሪያል ድጋፍ ተገኝቷል። ኮሌጁን ሙሉ በሙሉ ወደ ሶላር ሲስተም ለመቀየርና ዘመናዊ የቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል (Recycling) ስራዎች ተጀምረዋል። • 🥛 ለሰራተኛው የደረሰው "የሌማት ትሩፋት"፦ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል በከተማ ግብርና የወተት ላሞችን በማስገባት አንድ ሊትር ወተት በ40 ብር ብቻ ለሰራተኛው እያቀረበ ይገኛል። የዴይ ኬር (Daycare) አገልግሎት፣ የማዕድ ማጋራት እና በየሳምንቱ አርብ የከተማ ግብርና ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ የማቅረብ ስራዎች ተከናውነዋል። "በአጫጭር ስልጠና ከተሰጠን እቅድ ውስጥ በቴክኒካል ዘርፍ ከተመዘኑት ሰልጣኞች 95.7% ብቁ መሆን ችለዋል። በቀጣይም በሀገር አቀፍ የብቃት ምዘና (COC) ሂደት ላይ የሚታዩትን የመዛኞች እና የፈተና መሣሪያዎች ክፍተቶች ይበልጥ ለማቃለል፣ የኮሌጁን አንጋፋ አሰልጣኞች ፍላጎት መሰረት ባደረገ መልኩ በምዘና ሂደቶች ላይ በስፋት ማሳተፍ እና የአሰራር ማሻሻያዎችን ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በቅንጅት መፍታት ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል" — አመራሮቹ ለእርስዎ፦ ሰልጣኞች ገና ትምህርታቸውን ሳይጨርሱ በትልልቅ ግንባር ቀደም ኢንዱስትሪዎች በቋሚነት ተፈላጊ መሆናቸውና መቀጠራቸው፣ የኮሌጁን የላቀ የክህሎት ጥራት አያሳይምን? የእርስዎን አጭር አስተያየት በኮሜንት ያጋሩን! <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ 👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@bols20116?_t=ZM-8y9L28EOubG&_r=1 👉Facebook https://www.facebook.com/addisababatvetbureau 👉Telegram https://t.me/AABOLS 👉YouTube https://youtube.com/@bureauoflaborandskill?si=t9ZklwKzGx9rRyXf 👉website https://aabols.gov.et 👉ለቅሬታ፣ አስተያየትና ጥቆማ https://complain.aabols.gov.et 👉ለነፃ የስልክ ጥሪ 6524
892
17
+1
没有文字...
638
18
የመንግስት ቀዳሚ ትኩረት ዜጎች በአገራቸው ሰርተው እንዲለወጡ ማስቻል ነው። 🇪🇹 ግንቦት 26/2018 ዓ.ም 🇪🇹 በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታዩ የኢኮኖሚ ለውጦች የሥራ ዕድል ፍላጎቶች እና የሕዝብ ቁጥር ዕድገቶች ምክንያት የሰዎች ከአገር ወደ አገር የመንቀሳቀስና የተሻለ የሥራ ዕድል የመፈለግ ዝንባሌ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል። ይህ ዓለም አቀፋዊ እውነታ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ የጎላ ሲሆን በርካታ ዜጎች የተሻለ ሕይወትን ፍለጋ ወደ ተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለመጓዝ ይነሳሳሉ። ይሁን እንጂ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ፍላጎት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ የሚያጓጉዙ፣ ሰብአዊ መብታቸውን የሚገፉና ለከፍተኛ እንግልትና ማጭበርበር የሚያጋልጡ ድንበር ተሻጋሪ የወንጀል መረቦች ቁጥር በዓለም ዙሪያ እየሰፋ መምጣቱ ትልቅ ሥጋት ሆኗል። ይህንን ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮትና እውነታ መነሻ በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ የውጭ አገር የሥራ ስምሪት ፍላጎት መጨመሩን ተከትሎ መንግስት ዜጎች ሕጋዊውን መስመር ብቻ ተከትለው እንዲጓዙና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ይሁን እንጂ ይፋዊ አሰራሮችን በመተላለፍ ዜጎችን ለአደጋ የሚያጋልጡ ሕገ-ወጥ ደላላዎችና አጭበርባሪዎች ቁጥር ቀላል አለመሆኑ አሳሳቢነቱን ጨምሮታል። በአዲስ አበባ ሥራ እና ክህሎት ቢሮ የውጭ አገር ሥራ ስምሪት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ሳሙኤል ግርማ እንዳሉት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ከ765 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሕገ-ወጥ ዝውውርን አስከፊነት የተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተሰርተዋል። ቡድን መሪው አክለው እንደገለጹት ይህ ትልቅ ቁጥር የሚያሳየው ችግሩ ምን ያህል ስር የሰደደ መሆኑን እና የጥንቃቄ መልዕክቶች ለሕብረተሰቡ መድረስ እንዳለባቸው ነው። ሕገ-ወጥ አሸጋጋሪዎችና ደላላዎች ዜጎችን የሚያታልሉባቸውን ስልቶች መለየት የመጀመሪያውና ዋናው የጥንቃቄ እርምጃ መሆኑን አቶ ሳሙኤል ግርማ ያስረዳሉ። እነዚህ አጭበርባሪ አካላት ፈጣን፣ ቀላል እና እጅግ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኝ ስራ እንደሚያገኙ በመግለጽ የሐሰት ተስፋዎችን በመስጠት ዜጎችን እንደሚያታልሉ ገልጸዋል። በአንጻሩ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚጓዙ ዜጎች መብታቸው የማይከበርበት፣ በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ የሚያልፉበት እና ሕይወታቸውን ጭምር ሊያጡ የሚችሉበት አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ከተሳሳቱ መረጃዎች ራስን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ አቶ ሳሙኤል በጥንቃቄ መልዕክታቸው አሳስበዋል። በመሆኑም ዜጎች ወደ ውጭ አገር ሄደው ለመስራት ሲያስቡ ፈቃድ ካላቸው የቅጥር ኤጀንሲዎች እና ከመንግስት ተቋማት ውጪ ያሉ አካላትን በፍጹም ማነጋገር እንደሌለባቸው አብራርተዋል። መንግስት በአሁኑ ወቅት በግልጽ የሁለትዮሽ ስምምነት ያደረገባቸውን የአምስት የመካከለኛው ምስራቅ አገራትን መዳረሻዎች ለይቶ እያሰራ መሆኑን የቡድን መሪው ጠቅሰዋል። እነዚህም አገራት ዱባይ፣ ኳታር፣ ጆርዳን፣ ሳውዲ አረቢያ እና ኩዌት መሆናቸውን የገለጹት አቶ ሳሙኤል ግርማ ወደ እነዚህ ስፍራዎች ለመሄድ የሚፈልጉ ዜጎች በአዲስ አበባ ከተማ ስር በሚገኙ የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ወይም ፈቃድ ባላቸው የግል ኮሌጆች አስፈላጊውን ስልጠና ወስደው በሕጋዊ መንገድ ብቻ መጓዝ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በዚህም መሰረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ከ15 ሺህ በላይ ዜጎች ይህንን ሕጋዊ መስመር ተከትለው ወደ ውጭ አገር መጓዝ መቻላቸውንና ይህም የስራው ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን በዝርዝር አስረድተዋል። የዜጎችን ደህንነት አስተማማኝ ለማድረግ ቢሮው የውጭ አገር ኤጀንሲዎችን የስራ እንቅስቃሴ በቅርበት የመከታተል፣ የመደገፍና የመቆጣጠር ስራ እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሳሙኤል በክትትል ወቅት የሚታዩ ክፍተቶችና ግኝቶችም በቀጥታ ለፌደራል አካላት ሪፖርት እንደሚደረጉ አስታውቀዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ማጭበርበርን በቁርጠኝነት ለመከላከል የፍትህ አካላት በተለይም የፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በደላላዎች የተታለሉ ወይም ማጭበርበር የደረሰባቸው ዜጎች መረጃዎችን የሚያቀርቡበት በፍትህ ቢሮ በኩል የተዘጋጀ የነጻ ስልክ መስመር መኖሩን እና ጥቆማ መስጠታቸው ራሳቸውንና ሌሎችን ከመጠበቅ አንጻር ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ቡድን መሪው አብራርተዋል። በማጠቃለያውም አቶ ሳሙኤል ግርማ እንደገለጹት የመንግስት ቀዳሚ እና ዋነኛ ትኩረት ዜጎች በገዛ አገራቸው ሰርተው፣ ጥረውና ግረው እንዲለወጡ ማስቻል ሲሆን የውጭ አገር የስራ ስምሪት ደግሞ እንደ ተጨማሪ አማራጭ የሚወሰድ ነው። በመሆኑም ዜጎች የተሻለ ሕይወትን ፍለጋ በሚያደርጉት ጉዞ የደላላዎች ሰለባ እንዳይሆኑ ሁልጊዜም ሕጋዊውን መስመር ብቻ መምረጥ እና ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል። ከአጠራጣሪ አካላት ስራ ጀርባ ትልቅ አደጋና የሕይወት ክስረት ሊኖር ስለሚችል ማንኛውንም ውሳኔ ከመወሰንዎ በፊት ወደ ሥራ እና ክህሎት ቢሮ ወይም በአቅራቢያዎ ወደሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች በመጠጋት መረጃዎችን ማጣራት ተገቢ ነው። ዜጎች ራሳቸውን ከማታለል ጠብቀው በሕጋዊ መንገድ ሲጓዙ የአገራቸውን ገጽታ ከመገንባት ባለፈ የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ከጉዳት ይታደጋሉ ተብሏል። <<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>> ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://aabols.gov.et/qr.html
710
19
没有文字...
1 156
20
ካናዳ፤ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም! 🛑 🇪🇹ግንቦት 19/2018 ዓ.ም🇪🇹 የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በውጭ ሀገራት በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ላይ በህጋዊ መንገድ እንዲሰማሩ ለማስቻል በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ዜጎች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብና ህጋዊ ሂደቶችን በመከተል፣ ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት ወደተፈራረመችባቸው የሚከተሉት ሀገራት በህጋዊ መንገድ በመሰማራት ላይ ይገኛሉ፦ 👉ሳውዲ አረቢያ 👉የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ 👉ጆርዳን 👉ኳታር 👉ሊባኖስ 📍ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪት አለ? የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" (FUTURE FIT INTERNATIONAL INC.) ጋር ስምምነት የፈጸመው በዋነኛነት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው። ስምምነቱ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ብቻ ያተኩራል፦ • ከካናዳ ኮሌጆች ጋር በመተባበር ተማሪዎችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ በሚፈለጉ ክህሎቶች ማሰልጠን፤ • ብቁ የሆኑ ተማሪዎች በካናዳ በሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የነፃ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማመቻቸት። ⚠️ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ! ከዚህ ስምምነት ውጪ፦ ✅"ሚኒስቴሩ ወደ ካናዳ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ጀምሯል" በማለት የተሳሳተ መረጃ ከሚሰጡ፤ ✅"ወደ ካናዳ እንልክዎታለን" በማለት ከፍተኛ ገንዘብ ከሚጠይቁ፤ ✅"ከሚኒስቴሩ ህጋዊ ውክልና ተሰጥቶናል" ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሳችሁን ጠብቁ! 📍ምን ማወቅ ይኖርብዎታል? ✍️ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር የተደረገው ስምምነት ወደ ተግባር ሲገባ፣ ዝርዝር መረጃው በሚኒስቴሩ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና በብሔራዊ ሚዲያዎች ብቻ ይፋ ይደረጋል። ✍️ለዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ለመሆን ምንም ዓይነት ክፍያ መፈጸም አይጠበቅብዎትም! ክፍያ የሚጠይቁ አካላት ሁሉ አጭበርባሪዎች መሆናቸውን ይወቁ። ✍️አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ( 9138 በነፃ የስልክ መስመር ወይም info@mols.gov.et ) እና በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የህግ አስከባሪ አካላት ይጠቁሙ። 🚨ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ይፋዊ አድራሻዎቻችንን ብቻ ይጠቀሙ፦ ምንጭ፦የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Facebook
1 289